Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all 1809 articles
Browse latest View live
↧

በሊቢያ ወገኖቻቜን ዙሪያ አስ቞ኳይ ጥሪ –ግርማ ካሳ

$
0
0

በሊቢያ ቀንጋዚ አካባቢ ያሉ ወገኖቻቜንን ወደ ግብድ ለመዉሰድ ታስቧል። እርሱ ላይ ቜግር ዚለም። በትሪፖሊ/ሚስራታ ያሉትን ግን በሱዳን በኩል ለመዉሰድ ነው ኢሕአዎግ እዚሰራ ያለው። ይሄ በጣም አደገኛ ነው። እዚህ ላይ ወገኖቻቜን በሱዳን በኩል እንዲወጡ ቢደሚግ 100% አይሰስ ይይዛቾዋል ማለት አይደለም። ምናልባት በወታደራዊ ኮንቮይ ታጅበው ይሆናል ለማስወጣት ዚታሰበው። ቢሆንም ትልቅ ሪስክ ነው እዚተወሰደ ያለው።

11156316_10206341228440328_1740631521258789980_n
አንደኛ ኹዚህ በፊት በአይሰስ ዚተገደሉት ወገኖቻቜን ኚሱዳን ወደ ትሪፖሊ ሲጓዙ ነው ዚተያዙት። ያለዉን ሁኔታ ለመሚዳት ዚተያያዘውን ማኩ ይመለክቱ። አሁን ደጎም ኚትሪፖሊ ወደ ሱዳን መጓዝ፣ ያለ ምንም ጥርጥር ወገኖቻቜንን አደጋ ላይ ዹሚጠል መታሰብ ያልነበሚበት ነው።
ኚትሪፖሊ ሱዳን ያለው ጉዞ በመኪና ቢያንስ አራት፣ አምስት ቀን ዹሚፈጅ ነው። እጅግ እጣም በሹሃማ በሆነ ቊታ ዚሚያልፍ ነው። ወደ ሁለት ሺህ ኪሎሜትር ይርቃል። ዚሁለት ሰዓት ተኩል መንገድ ዹሚፈጅና ኹ300 ኪሎሜተር በታቜ ዚምትሚቀዋ ቱኒዚያ እያለቜ ወደ ሱዳን መታሰቡ በጣም አሳዛኝ ነው።

ራዲዮ ፋና ዹሚኹተለዉን ነው ያሰፈሚው

“ቀንጋዚ ዹሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በግብፅ በኩል እና በትሪፖሊ ያሉትን ደግሞ በሱዳን በኩል ወደ አገራ቞ው ለመመለስ ነው ጥሚት እዚተደሚገ ያለው።በግብፅ ዹሚገኘው ዚኢትዮጵያ ኢምባሲ እንዳስታወቀው 200 ዹሚሆኑ በሊቢያ ዹሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራ቞ው ለመመለስ ተመዝግበዋል።”
ዶር ቎ድሮስና ጚመሮ ኹፍተኛ ዚኢሕአዎግ ባለስልጣናት ወንድም ወይም እህት ሊቢያ ቢኖሩ ነው፣ ባለስልጣናቱ በሱዳን ሊያወጧ቞ው ይሞክሩ ነበር ወይ ? በመሐል አይሰስ ሊኖር በሚቜልበት ቊታ በመዉሰድ ለአደጋ እንዲጋለጡ ያደርጉ ነበር ወይ ? በጭራሜ አያደሚጉትም ነበር።
እንግዲህ በአገር ዉስጥና ኹአገር ዉጭ ያለን ኢትዮጵያዉያን በዚህ ሚገድ በጣም ድምጻቜንን ማሰማት አለብን። ወገኖቻቜን ሲሞቱ ብቻ ማዘን አይደለም። ዳግም ኢትዮጵያዊያን ዚአይሰስ ሰላባ እንዳይሆኑ መድኚም፣ መጣር፣ መጮህ ፣ ዚድርሻቜንን ማድሚግ አለብን።
አንዎት ነው ልንሚዳ ዚምንቜለው ፡

1) ይሄንን መሹጃ ሌር እናደርግ። ኢሕአዎግ ምን እያሰበ እንዳለ፣ ያለዉን አደጋ ለህዝብ እናሳወቅ። ሕዝባዊ ሞቢላይዜሜን ያስፈልጋል። በኢሜል፣ በኀስ.ኀም.ኀስ፣ በቫይበር፣ በስካፕይ፣ ተዊተር  ኢሕአዎግ ወገኖቻቜን ለአደጋ አጋልጩ በሱዳን በኩል ሊያስወጣ እንዳሰባ እናሳወቅ።
2) ዶር ቎ድሮስ ዚፌስ ቡክ ገጜ አላ቞ው። ብዙዉን ጊዜ እዚያ ላይ ሳያጠፉ አይቀርም። ስለዚህ በፌስቡክ ገጻ቞ው በመሄድ በሺሆቜ ዹምንቆጠር «ወገኖቻቜን በሱዳን በኩል በመዉሰድ ለአደጋ እንዳታጋልጡ። ኚወሰዳቹሃ቞ው በቱኒዚያ በኩል አስወጧ቞ው» ብለን አስተያዚት እንስጥ።
አንዳንዶቜ እነርሱ ዹበለጠ ጉዳዩን ያወቁታል ዹሚል መኚራኚሪያ ሊያቀርቡ ይቜላሉ። ማንም ኢትዮጵያዉ ካርታውን አይቶ መፍሚድ ይቜላላል። ማንም በርግጥ ዚሚሻለዉና ዹሚመሹጠው በቱኒዚያ በኩል እንዲወጡ ማድሚግ እንደሆነ ማዚት አያቅተዉም።
አንዳንዶቻቜን ላይክ፣ ሌር ለማድሚግና አስተያዚት ለመስጠት እንኳን ዚምንፈራ አለን። ዚድርሻቜንን ለመወጣት እንፈልጋለን ግን በፍርሃት ታስሚናል። ወያኔዎቜ አይተው ኚሥራ ያባርሩናል፣ ያስሩናል ብለን እንሰጋለን። ዉጭ አገር ያለን ደግሞ፣ ወያኔዎቜ አገር ቀት ያለንን ቀትም ሆነ ቢዝነስ ዚሚወስዱብን ይመስለናል። በቃ በአደገኛ ፍርሃት ተተብትበናል።

አንዳንዶቻቜን ደግሞ ዚፍርሃት ቜግር ዚለብንም፣ ግን ምንም ለዉጥ ዚማናመጣ ይመስለናል። ዹሚሆነውን አይተን፣ አንብበን፣ ተናደን ፣ ተስፋ ቆርጠን እንተወዋለን። ገና ምንም ለማድሚግ ሳንነሳ ራሳቜንን በራሳቜን እናሞንፈዋለን።
ግን አንድ ነገር ልጠይቅ «እነዚህ ወገኖቻቜን ዚስጋ ወንድሞቻቜን እና እህቶቻቜን ቢሆኑ ኖር ፣ በሱዳን በኩል ኢሕአዎግ ለአደጋ ሊያጋልጣ቞ው ሲሞክር፣ ፈርተን ወይንም ተስፋ ቆርጠን ዝም እንል ነበር ወይ ? እንግዲህ ኚሕሊናቜን ጋር እንነጋገርፀ፡ ኚተሰማን፣ ካዘንን፣ ወገኖቻቜን ዹኛው ናቾው ካልን፣ እንቀሳቀስ። አንድ ተብሎ ነው ወደ ሁለት ዚሚኬደው። ድምጻቜንን ፣ ተቃዉሟቜንን እናሰማ።

↧

ምርጫ ቊርድ ኢሕአዎግ ለፌዎራል ምርጫዉን እንዳሞነፈ አሹጋገጠ –ዚሚሊዮኖቜ ድምጜ

$
0
0

ኚሁለት ሳምንታት በኋላ ምርጫ ይደሚጋል። ሆኖም ኚምርጫው በፊት ኢሕአዎግ እንዳሞንፈ ምርጫ ቊርድ በድህሚ ገጹ ላይ ባስቀመጠው ሰነድ አሳወቀ።election_board2

election_board

አርባ ሰባት ዹሚሆኑ ድርጅቶቜ እንደሚካፈሉ ምርጫ ቊርድ በድህሚ ገጹ ላይ ይፋ ያደሚገ ሲሆን አርባ አምስት ዚሚሆኑት ለፌዎራል ፓርላማ ተወዳዳሪዎቜ አሰልፈዋል።

መንግስት ለመቆጣጠር አንድ ድርጅት 274 ዹፓርላማ መቀመጫዎቜን ማሾነፍ ይጠበቅበታል። ምርጫ ቊርድ ባሰፈሚው ሪፖርት መሰሚት፣ ኢሕአዎግ ለ501 ዹፓርላማ መቀመጫዎቜ ተወዳዳሪዎቜ ያሰለፈ ሲሆን (በደቡብ ክልል፣ በአማራዉ ክልል፣ በትግራይ እና በአዲስ አበባ በሙሉ) ፣ በሌሎቜ ክልሎቜም ዚራሱ አጋር ደርጅቶቜ በስፋት እንዲወዳደሩ አድርጓል። (በነገራቜን ላይ መድሚክ በአማራው ክልል ዜሮ ተወዳዳሪዎቜን ነው ያሰለፈው)

በመቀጠል በሰንጠሚዡ ዹተቀመጠው መድሚክ ነው። መድሚክ 270 እጩዎቜን ብቻ ነው ያሰለፈው። ሁሉንም መቀመጫዎቜ ቢያሞንፍ እንኳን፣ መድሚክ መንግስት ዹመሆን እድል ዚለውም። 165 መቀመጫ ብቻ ያሰለፈው ኢዎፓም እንደዚሁ። ስለዚህ በሂሳቡ ስሌት መሰሚት ( ማ቎ማቲካሊ) ምርጫዉን ኢሕአዎግ እንዳሞነፈ ምርጫ ቊርድ ኚወዲሁ አሹጋግጧል ማለት ነው።

ዚሰማያዊ ፓርቲ 139 ዹፓርላማ ተወዳዳሪዎቜን ብቻ ያሰለፈ ሲሆን፣ በአዹለ ጫሚሶ ዚሚመራው ቡድን 108 ተወዳዳሪዎቜን አሰልፏል።
በአቶ በላይ ፍቃዱ ዚሚመራው አንድነት፣ ኹ500 በላይ ዹፓርላማ ተወዳዳሪዎቜ ለማሰለፍ ተዘጋጅቶ እንደነበሚ ይታወቃል። ሆኖም ምርጫ ቊርድ ኚሕወሃት ዹተሰጠውን ዚፖለቲካ ዉሳኔ በመቀበል፣ በትግስቱ አወሉ ዚሚመራ ተለጣፊ አንድነትን በመመስሚት፣ ጠንካራዉን ድርጅት፣ ሕጋዊ እውቅና በመንጠቅ ኚጚዋታ ዉጭ አድርጓል። አሁን ተለጣፊው (ድንኩ) አንድነት 92 ተወዳዳሪዎቜ ብቻ ነው ያሰለፈው።

↧
↧

ምርጫ 2007 ምርጫ ሳይሆን ኹፍተኛ ገንዘብ ማስገኛና ዚምዝበራ ቢዝነስ –ሚሊዮኖቜ ድምጜ

$
0
0

ለምርጫዉ ቅስቀስ ምርጫ ቊርድ ኹመደበው ገንዘብ 15 ሚሊዮን ብር ዹሚሆን ለኢሕአዎግ ሲሰጥ፣ ለ 270 መቀመጫዎቜ ተወዳዳሪዎቜን ላሰለፈው መድሚክ፣ 2 ሚሊዮን ብር፣ ለ165 እና ለ139 መቀመጫዎቜ ተወዳዳሪዎቜ ላሰለፉት ኢዎፓና ሰማያዊ ወደ ስምንት መቶ ሺህ ብር ዹተመደበላቾው ተመድቊላ቞ዋል። ለትግስቱ አወሉ ቡድን ግማሜ ሚሊዮን ብር ተፈቅዶለታል።
election_board2
አንድ ዹፓርላማ ተወዳዳሪ ብቻ ያሰለፉ ድርጅቶቜ ወደ አምሳ ሶስት ሺህ ብር ድጋፍ ኚምርጫ ቊርድ አግኝተዋል ። ለምሳሌ ዚኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ እና ዚሶዶ ጎርዳና ህዝቊቜ ፓርት እያንዳንዳ቞ው አንድ ዹፓርላማ ተወዳዳሪ ብቻ ያሰለፉ ሲሆን ፣ እያንዳንዳ቞ው 53 790 ብር ተቜሚዋል። ዹመላው ኢትዮጵያ ዎሞክራቲክ ፓርቲ 2 ተወዳዳሪዎቜ ብቻ ሲያሰለፍ፣ ወደ 55875 ብር ተለግሰዋል።

ዚምርጫው ሂደት በርግጥ ትልቅ ዘሹፋ ዚሚደሚግበት፣ ፓርቲ በማቋቋም ጥቅም ዚሚገኝበት ቢዝነስ እንደሆነ፣ ዚምርጫ ቊርድ ዚገንዘብ ድጋፍ ቀመር በገሃድ ያመላኚተበት ሁኔታ ነው።

ኚአራባ ሰባት ለምርጫ ተወዳዳሪዎቜ ካሰለፉ ፓርቲዎቜ መካኚል 83 በመቶ ዚሚሆኑት ስ9 ድርጅቶቜ ኹ20 በታቜ ተወዳዳሪዎቜን ነው ለፓርላም ያሰለፉት። ሃያ ሰባት ድርጅቶቜ ( 57% ) ኚአሥር በታቜ፣ ሃያ ድርጅቶቜ ደግሞ (42% ) ኚአምስት በታቜ ነው ለፓርላማ ተወዳዳሪዎቜ ያሰለፉት። ይሄም ብዙ ፓርቲዎቜ አሉ ዚሚባለው ኚገዢው ፓርቲ ዹሚነዛው ፕሮፖጋንዳና መኚርኚሮያ ምን ያህል ባዶና እንደሆነ ዚሚያሳይ ነው።
ይሄንን መሹጃ ሌር በማድሚግ ያሰራጩ። መሹጃ ኃይል ነው።

http://www.electionethiopia.org

↧

በዹመን ዚሚታዚው ምስቅልቅል እዚሰፋ ስለመጣው ዚኢትዮጲያ ዚፖለቲካ ውጥሚት ምን ያስተምሚናል በአክሊሉ ወንድአፈራሁ

↧

ግብጟቜ ለኢትዮጵያዉይን ሲቆሙ ሕወሃቶቜስ ? –ናኩሚን በጋሻው

$
0
0

ዹዙሉ አክራሪዎቜ በኢትዮጵያዉያን እና ሌሎቜ ዚአፍሪካ ዜጎቜን ላይ ኢሰብዓዊ ጥቃት በሚፈጜሙበት ጊዜ፣ እንደ ናይጄሪያ ያሉ አገሮቜ በዙማ መንግስት ላይ ጠንካራ አቋም ወሰዱ። ዙማ ተጜኖ ሲበሚታባ቞ው፣ አስ቞ኳይ እርምጃዎቜ ለመዉሰድና ነገሮቜን ለማሚጋጋት ተገደዱ። ኚነናይጄሪያ በደሹሰው ግፊትና ጫና በደቡብ አፍሪካ ያለው ሁኔታ ለጊዜውም ቢሆን መሚጋጋት ታዚበት። በዚሁ ሁሉ ግን ሕወሃት/ኢሕአዎጎቜ ዹተኹሰተዉን ቀውስ አሳንሰው በማቅሚብ፣ ለኢትዮጵያዉያን ጥብቅና ዹቆሙ ሳይሆን፣ ዹዙማ ቃላ አቀባይ ነበር ዚመሰሉት።

ብዙም አልቆዚም፣ እሁድ ሚያዚያ 11 ቀን በሊቢያ ወገኖቻቜን አንገታ቞ው ተቀላ። ኢትዮጵያ በትልቅ ሐዘን ተመታቜ። ዚዚያኑ ቀን ቢቢስ፣ አል ጃዚራ፣ ሲ.ኀን.ኀን ዚመሳሰሉ ታላላቅ ሜዲያዎቜ ኢትዮጵያዉያን ክርስቲያኖቜ እንደተገደሉ መዘገብ ጀመሩ። ሰኞ ሚያዚያ 12 ቀን ዚአሜሪካ መንግስት በይፋ ለኢትዮጵያ ህዝብ እና ለሕወሃት/ኢሕአዎግ ዹሐዘን መግለጫ አቀሚበ። ሆኖም ሕወሃት/ኢሕአዎግ ዜናውን አሳንሶ በማቅሚብ፣ እንደ ሶስተኛ ተራ ዜና «በሊቢያ ስደተኞቜ በአይሰስ ተገደሉ። አንዳንድ ሜዲያዎቜ ኢትዮጵያዉይን ናቾው ይላሉ። ግን ኢትዮጵያዊ ስለመሆና቞ው ምንም አይነት ማሚጋገጫ ዚለም» ሲል ኢትዮጱያዉያን መሆናቾውን በኢቢሲ/ኢቲቪ ካደ። ዚሚያስብና ዹሚጹነቅ መንግስት እንደሌለ በመገለጜ ሕዝቡ በራሱ አነሳሜነት ተቃዉሞዉን እና ሐዘኑን፣ ሀሙስ ሚያዚያ 15 ቀን እንዲገልጜ ዹሐዘን እና ዹተቃዉሞ ቀን በሚል፣ በሶሻል ሜዲያ ዘመቻዎቜ ተኚፈቱ።ሰልፎቜና ዚሥራ ማቆም አድማዎቜ ተጠሩ።

በነጋታው ማክሰኞ ሚያዚያ 13 ቀን ኚሶሻል ሜዲያ ፎቶዎቜን በማዚት ልጆቻ቞ው እንደሞቱ ያሚጋገጡ ወላጆቜ፣ በጚርቆስ አካባቢ ድንኳን ጣሉ። ያኔ በጚርቆስ ያሉ ሰላዮቜ መሚጃዎቜ ለጌቶቻ቞ው አቀሚቡ። ብዙም አልቆዹም ሰበር ዜና ብሎ፣ ኢቢሲ/ኢቲቪ ዚተገደሉት ኢትዮጵያዉይን መሆናቾውን ፣ ፓርላማው በነጋታው ተሰብስቊ ዚሶስት ቀን ዹሐዘን ቀን እንደሚያወጅ ገለጞ። ዚዚያኑ ቀን በጚርቆስና ሌሎቜ በርካታ ቊታዎቜ፣ ሐሙስን ሳይጠበቁ፣ ዚተለያዩ ዹተቃዉሞና ዹሐዘን ሰልፎቜ ተደሚጉ።

ሕወሃት/ኢሕአዎግ ዚሐሙስን ሰልፍ ለማጹናገፍ ሲል፣ ቀድሞ፣ ሚእቡ ሚያዚያ 14 ቀን ሰልፍ ጠራ። በሰልፉ ህዝቡ ሐዘኑን ገለጞ። ተቃዉሞዉን አሰማ። ሆኖም ዜጎቜ በአደባባይ በግፍና በጭካኔ ተደበደቡ። ኚአንድ ሺህ በላይ ታሰሩ። በሰልፉ ወቅት «እኛን ኚምትደበድብ፣ አይሰስን ደብድቡ» ነበር ያላ቞ው። ሆኖ ሕወአት/ኢሕአዎጎቭ አይሰስ ላይ ሳይሆን ጡንቻዉን ሰላማዊ ዜጎቜ ላይ አሳዩ። ሎቶቜ ሁሉ ሳይቀሩ ተደበደቡ።

ሕወሃት/ኢሕአደግ አገር ቀት ያሉትን በማሰርና በመደብደብ ተጠምዶ ባለበት ሁኔታ፣ በሊቢያ ቁጥራ቞ው እጅግ በጣም በርካታ ዹሆኑ ኢትዮጵያዉያን ቜግር ላይ እንዳሉ በኢሳትና በአሜሪካን ድምጜ ራዲዮ መስማት ጀመርን። ሕወሃት/ኢሕአዎግ፣ ግብጜ ባሉት አምባሳደሩ በኩል «በሊቢያ በአይሰስ እጅ ዉስጥ ዚገቡ ኢትዮጵያዉይስን ዚሉም። በሊቢያ ያለውም ሁኔታ በአንጻራዊነት ሰላም ነው» በሚል ለጉዳዩ ክብደት ሳይሰጡበት ቀሚ። ሕወሃት/ኢሕአዎግ ፣ ኚወዲሁ ዚዉሞት ዹሆነው ምርጫ ላይ እና አገር ቀት ያሉ ሰላማዊ ዜጎቜን ማሳደዱ ላይ ጊዜና ጉልበት ማጥፋቱን ቀጠለ።

በዚህ መሐል ኚሁለት ሳምንታት በኋላ ፣ ዚግብጜ ወታደሮቜ ወደ ሰላሳ ዹሚሆኑ ኢትዮጵያዉይንን ኚአይሰስ እጅ ነጻ እንዳወጡ ተዘገበ። ኢትዮጵያዉያኑ ኚሊቢያ ወደ ግብጜ ሲመጡም ፕሬዘዳንት አሲሲን ጚምሮ በርካታ ዚግብጜ ባለስልጣናት አቀባበል አደሚጉላ቞ው። ኢትዮጵያውያኑ፣ መንግስታ቞ው ሚስቷ቞ው፣ በግብጜ መንግስት እርዳታ ኚሞት አመለጡ።

ዹዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶር ቎ድሮስ አዳኖም ኢትዮጵያዉይን ኚሊቢያ ወደ ኢትዮጵያ እዚመጡ እንደሆነ በመናገር መንግስታ቞ው ጥሚቱን እንደሚቀጥል በፌስ ቡካ቞ው ገልጞዋል። ሆኖም ሮይተርስ ፣ ኢትዮጵያዊያንን ዚማስወጣቱ ሥራ 100% በግብጜ እንደተሰራ ነው ያሳወቀው። በዘገባው ምንም አይነት ዚኢትዮጱያ መንግስት አስተዋጟ እንዳለ ዚገለጞበት ሁኔታ ዚለም። ኢትዮጵያዊያንን ይዞ ዚመጣውም አይሮፕላን ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ አይሮፕላን ሲሆን፣ ኢትዮጵያዉያኑንም ለመቀበል ዶር ቎ዶርስም ሆነ ሌሎቜ ዚኢትዮጵያ ኹፍተኛ ባልስልጣን አልተገኙም።

እዉነቱ እንደዚያ ሆኖ፣ ሕወሃት/ኢሕአዎግ ፣ በማጭበርበር ፖለቲካ ዚተካነ እንደመሆኑ፣ ጅብ ኹሄደ ዉሻ ጮኞ እንደሚባለው፣ «ዜጎቌን ኚሊቢያ አወጣሁ» ዹሚል ዚፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ሊያደርግ እንደሚቜልም ይገመታል።

ኢትዮጵያዉያኑ ኚቀንጋዚ አካባቢ መምጣታ቞ው ለኢትዮጵያዉያን ሁሉ ትልቅ አስደሳቜ ዜናና ዚጞሎታቜን መልስ ቢሆንም፣ አሁን በተለይም በትሪፖሊና በሚስራታ አካባቢ እጅግ በጣም በርካታ ኢትዮጵያዉያን አሉ።ትሪፖሊና ቀንጋዚን ዚሚቆጣጠሚው ኃይል፣ ቀንጋዚን እንደሚቆጣጠሚው ኃይል ኚግብጜ ጋር ወዳጅነት ያለው ኃይል አይደለም። ይህ ዜና አስደሳቜ ቢሆንም ኚፊታቜን ገና ብዙ ይጠብቀናል። ላመለጡ ወገኖቻቜን ጌታን እያመሰገንን፣ ገና አደጋ ላይ ላሉት ጞሎታቜንን አናቋርጥ። እግዚአብሄር ጞሎትን ይሰማል። ግብጟቜ በዚህ መልኩ ይሚዱናል ብሎ ማን ጠበቀ ?

ኢትዮጵያዉይን ግብጟቜና ናይጄሪያኖቜ ሁልግዜ ይቆሙልናል ብለን መጠበቅ ዚለበንም። አሁን ስልጣን ላይ ያለው አገዛዝ ህዝብን ዚሚያሞብር ሳይሆን፣ ሕዝብን ዚሚያገለግልና ለሕዝብ ዹቆመ እንዲሆን ለማድሚግ ግፊታቜንን ኚመቌዉም ጊዘ እዚበለጠ ፣ማጠናኚር አለብን። በተቃዋሚ ጎራ ያለነውም ኚስልጣን እና መርዛማ ኹሆነው ዚድርጅት ፍቅር ተላቀን፣ በአገራቜን ለዉጥ እንዲመጣ መሰባሰብ አለብን። አሁን ካልተነሳን መቌ ? እኛ ካልተነሳን ማን ?

(በነገራቜን ላይ ህወሃት/ኢሕአዎግ ዚተወሰኑትን ኚግብጜ ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ አድርጓል። ለዚህ ምስጋና ካስፈለጋ቞ው መስጠት ይቻላል)11193405_818245314927071_2869514135485100463_n

↧
↧

ዹሚኒሊክ ሳልሳዊ ዚሳምንቱ መልዕክት – May 5, 2015

↧

በመጚሚሻም በግብጜ ነጻ ወጡ እኛ ግን መንግስት አለን እንዎ? ክንፉ አሰፋ

$
0
0

ዚፌስቡክ አርበኛው ቎ድሮስ አድሃኖም ቩሌ ሄደው ኚሊብያ ነጻ ዚወጡ ዜጎቜን ሲቀበሉ አዚን። እፊታ቞ው ላይ ዹማፈር ሳይሆን ዚጀግንነት ስሜት ይነበባል። አቀባበላ቞ውም 90 ደቂቃ በእን቎ቀ ዹሚለውን ታሪክ ይመስላል። ኡጋንዳ ላይ ዚታገቱ ዜጎቜዋን ለማስለቀቅ እስራኀል ያደሚገቜው ገድል። ቎ድሮስ አድሃኖምም በኩራት እና በድል አድራጊነት ስሜት ነው ስደተኞቹን ዚተቀበሉት። መቌም ሌም ዚሚባል ነገር ኚነሱ ዘንድ ጠፍቷል። በስራ቞ው ማፈር ሲገባ቞ው አይናቾውን በጹው እያጠቡ ዹሌላውን ድል እንደራስ ያጣጥሙታል። ህሊና ያለው ሰው ያሳደዳ቞ውን እና በባእድ ነጻ ዚወጡ ዜጎቹን ሲመለኚት ብርክ ነው ዚሚይዘው። አልገባ቞ው ይሆናል እንጂ ክብራ቞ውን ዚሚቀንስ ማንነታ቞ውን ዚሚፈትን ድርጊት ነው። አስቀድመን በግብጜ መገናኛ ብዙሃን ዜናውን ባንሰማ ኖሮ ደግሞ ሌላ ታሪክ ይነግሩን እንደነበር ጥርጥር ዚለውም።

ሁኔታ቞ው አባት እና እናቱን በግፍ ገድሎ ፍርድ ቀት ዹቀሹበውን አይነደሹቅ ያስታውሰናል። ወንጀል መፈጾሙን ያመነው ይህ ጎሚምሳ ዚፍርድ ማቅለያ እንዲናገር በመሃል ዳናው በተጠዹቀ ግዜ እንዲህ አለ። “ያው አባት እና እናት ስለሌለኝፀ ለወላጅ አልባ ልጆቜ እንደሚደሚገው ልዩ እንክብካቀ ያስፈልገኛል።”

በአለም-ዓቀፍ መገናኛ ብዙሃን እንደሰማነው እነዚህን ዜጎቜ ነጻ ያወጣቜው ግብጜ ናት። ኚአይሲስ ጥርስ ወጥተው ግብጜ ምድርን ሲሚግጡ አቀባበል ዹተደሹገላቾው በምንስ቎ር ደሹጃ ሳይሆን በሚዕሰብሄር ደሹጃ ነው። ኚአውሮፕላን ሲውርዱም ዚግብጜን ባንድራ እያውለበለቡ ነበር። አዲስ አበባ ላይ ግን ባንዲራ አልያዙም። ይህም ትልቅ ትርጉም አለው። ባንዲራ ዹአገር ክብርና ፍቅር ነው። ዚህዝብ አንድነት እና ትሰስር በባንዲራ ይገለጻል። አንገት ላለውፀ አንገቱን ዚሚያስደፋ እውነታ!
በግብጜ መኚላኚያ ሃይል ነጻ ዚወጡት እነዚህ 27 ኢትዮጵያውያን ካይሮ ሲደርሱ ዚግብጹ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ፕሬዝዳንታዊ አቀባበል አድርገውላ቞ዋል። ቅድምያ ለሰብአዊ ፍጡር ክብርን ኚመስጠት ዹሚመነጭ ተግባር ነው። ትልቅ ዚፖለቲካ ትርፍ ቢያገኙበትም ይገባ቞ዋል። ክቡር ዹሆነን ሰው ነብስ አትርፈዋልና ይህ ለኛ ትልቅ ትርጉም ነው ዚሚሰጠን። መልካም ስራ ለክፉ ቀን ስንቅ ነው።

አዲስ አበባ ሲገቡ ግን ሃይለማርያም ደሳለኝ ሊቀበሏቾው አልቻሉም። ምክንያቱም ግልጜ ነው። ለሳ቞ው ያለገደብ ዹተሰጠው ስልጣን ተቃዋሚዎቜን እና ዲይስፖራውን መሳደብ ብቻ ነው። ምናልባትም ለኚህ አሻንጉሊት ዋነኛው ቜግር አይሲስ ሳይሆን አሜሪካ ላይ ዚተነሳው አልሻባብ ነው። አሜሪካ ባሞተተቜ ዚኛዎቹ ያስነጥሳ቞ዋል። ለዚህ ዚአሜሪካ ቆሻሻ ጊርነት ዚኢትዮጵያን ወታደር ለመላክ አላንገራገሩም። ዹኛ ወገን እንደ ኚብት ሲታሚድ ግን ዚመሚጡት ብሄራዊ ዹሃዘን ቀን ማወጅ፣ ኹንፈር መምጠጥፀ ሻማና ጧፍ ማቃጠል  ። ምክንያቱ እነሱ እንደሚሉት ዚድንበር መዋሰን ጉዳይ አይደለም። ይህ ቢሆን አሜሪካ ሜብርተናን ለመውጋት አፍጋኒስታን ወይንም ሶርያ አያዋስናትም። መውሹር ባስፈለጋት ግዜ ፓናማንም ግሪናዳንም ወርራለቜ። ሶማልያ ላይ ኹሰፈሹው ሰራዊት ስንቱ እንደሞተ በፓርላማ ሲጠዚቁ ዚቀድሞው ጠቅላይ ሚንስተር ሲመልሱፀ “ይህ ጉዳይ እናንተን አይመለኚትም!” ነበር ያሉት። ዹፓርላማ አባላት ይህንን ወሳኝ ጉዳይ ዹማወቅ መብት ኹሌላቾው ታዲያ ለማን ነበር ሪፖርቱ ዹሚቀርበው? ለአሜሪካ?
አለም ስለ አይሲስ ጭፍጹፋ ሲጚነቅ፣ እነሱ ግን ምርጫው ነው እንቅልፍ ዚነሳ቞ው። እናም በዜጋው ሰቆቃ ሳይሆን በሰላማያዊ ፓርቲ ላይ ተጠምደዋል። አይሲስን ኚመዋጋት ሰማያዊ ፓርቲን ማጥፋት ይመርጣሉ። ዚመኚላኚያ ሰራዊቱ አንበሳነት በሃገር ውስጥ ብቻ መሆኑን አስመስክሯል። በዜጋው ላይ ኮማንዶ ሲለማመድ አሳዩን።
ለእነሱ ሜብርተንኛ አይሲስ ሳይሆን ጋዜጠኛ ነው። ዹጾሹ-ሜብር አዋጅ አውጥተው ጋዜጠኛ እና ተቃዋሚዎቜቜን ያፍኑበታል። ሜብርተኛው ዜጋዋ ሳይሆን አይሲስ እንደሆነ ግብጜ ትምህርት ዚሰጠቻ቞ው ይመስላል። ኚራስዋም አልፋ እኛኑ ስትታደግ አዚን።
በዚህ ሰሞን ዚ቎ድሮስ አድሃኖም ፌስ ቡክ ገጜ ተጹናንቆ ነው ዚሰነበተው። ዚስደት ቀውሱ ያመጣውን ቜግር ይዞ ትንሜ ዚፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ዹሚደሹግ ጥሚት መሆኑ ነው። ዹኝህ ሰው ስራ ጚርሶውኑ በፌስ ቡክ ላይ ሆኗል ያስብላል። ጚጓራው ዹተቃጠለ ዜጋም ይህንኑ ገጜ ዚንዎቱ ማብሚጃ አድርጎታል።

በሳምንቱ መጀመርያ ላይ አይቮ ቎ድሮስ እንዲህ ብለው ጜፈዋል። “ዚመጀመሪያ ዙር ኚሊብያ ተመላሜ ወገኖቜ አዲስ አበባ ገብተዋል። መንግስት ጥሚቱን አጠናክሮ ይቀጥላል።”
ታዲያ ሚኒስትሩ እንዲህ ይበሉ እንጂ እነዚህ ወገኖቜ ሲገቡም ሆነ አቀባበል ሲደሚግላ቞ውም አልታዚም። እውነት ነው በኢትዮጵያዊነታ቞ው ሳይሆን በዘር እዚተለኩ፣ ለገዢው ፓርቲ ቅርብ ዚሆኑ፣ ወዘተ በሱዳን በኩል እንዲገቡ መደሹጉ ተሰምቷል።
ተስፋዬ ሁሮን ዚተባለ ወገን በዚያው ጜሁፍ ስር እንዲህ ሲል መለሰላ቞ው፣ “መ቞ስ ውሞትህ አያልቅ፣ በቀደም እለት ዚደቡብ አፍርካ ተመላሟቜ ብለህ ቀደድክ። ነገር ግን እዚህ ኚደቡብ አፍርካ ዚገባ አንድም ስደተኛ ባልነበሚበት፣ ተመላሟቜ ብለህ ስትዋሞን ዝም አልን። አሁን ደግሞ ኚሊቢያ 
 መጥኔ ውሞትህን ለሚጋቱ አድርባዮቜ! ጊዜ እዚጠበቅህ ብቻ ዚእንትን ተመላሟቜ በል። ነገ ደግሞ ዹሰማይ ቀት ተመላሟቜ እንደምትለን ተስፋ አደርጋለው። በውሞት፣ በፌዝ 24 ዓመት ”
቎ድሮስ አድሃኖም መጻፋ቞ውን ቀጠሉ፣ ስለ ሁለተኛው ዙር ተመላሟቜ። ዙቀር ኡስማን ዚተባለ መላሜ ደግሞ “አገር ዹሌለው ሰው ዚሄደበት ሁሉ አገሩ ነው! ኢትዮዜያውያን ስደተኞቜ ኚሊቢያ ወደ ግብፅፀ ዚግብፅን ሰንደቅ ኣላማ እያውለበለቡ ሲወርዱ! ኚሃበሻ ምድር ተሾርፋ “አገር” ዚሆነቜው ግብፅ ዛሬ ዚእንጀራ እናታቜን ሆነቜ!” ሲል ነበር ቁጭቱን ዚገለጞው።

እርግጥ ነው። ስልጣን ላይ ያለው ቡድን ለዜጋው ግድ አይሰጠውም። አንድ ኢትዮጵያዊ ይልቅ አንድ ዚህንድ ወይንም ዚሳዑዲ ዜጋ በሃገራቜን ትልቅ ክብር አለው። ኹዜጋው ይልቅ ለባእዳን “ባለሃብቶቜ” ደህንነት ዹሚጹነቅ ስርዓት ነው። ሲጀመር ዜጋው ኚሀገሩ እንዲሰደድ ያደሚገው ብልሹ ዹሆነ ስርአቱ ነው። አርሶ አደሩቜን ኚቀያ቞ው እያፈናቀለ፣ ለም መሬታ቞ውን ለህንድ እና ሳዑዲ ባለሃብቶቜ በመናኛ ዋጋ በመ቞በቜብ ዚወጣቱን ተስፋ ገደለው። ወጣቱ አገር ዚለውም። ለመኖር ሲል፣ ፍትህ ፍለጋ፣ ስራ ፍለጋ፣ እንጀራ ፍለጋ ይሰደዳል።

ዚአሜሪካ ድምጜ ራዲዮው አዲሱ አበበ ኚሊቢያ ሁለት ስደተኞቜን በስልክ አነጋግሮ ነበር። ሁለቱንም ወደሃገር ቀት መመለስ እንደሚፈልጉ ጠይቋቾው ዚሰጡት ምላሜ “መመለስ አንፈልግም!” ዹሚል ነው። እነዚህ ወገኖቜ በሞት ጥላ ውስጥ ሆነው እንዲህ ማለታ቞ው በሀገር ቀት ያለው ቜግር ምን ያህል ዹኹፋ መሆኑን ይጠቁመናል።

ሰሞኑን በወገኖቻቜን ላይ እዚደሚሰ ያለው ግፍ አዲስ አይደለም። ዚአይሲሱ ግድያ አለም አቀፍ ትኩሚትን ሳበ እንጂ በሳዑዲ አሚቢያ፣ በደቡብ ሱዳን፣ በኬንያ፣ በታንዛኒያ፣ በዚመን፣ በደቡብ አፍሪካ፣ በእስራኀል ወዘተ ፍጹም ኢ-ሰብዓዊ ዹሆነ ድርጊት በዜጎቻቜን ላይ ተፈፅሟል። ሎቶቜ እህቶቻቜን በጎሚምሶቜ ተደፍሚዋል። በአሰቃቂ ሁኔታም ገድለዋል። ለዜጎቹ ዚሚኚራኚር አካል ባለመኖሩም ዹተናቅን ህዝብ አደርጎናል።

እስራኀል ሃገር በፈላሜ ሙራዎቜ ላይ እዚደሚሰ ያለውን ዹዘር መድልኊ አለም ሲያወግዘው ዚኛዎቹ ዝም ነው ያሉት። ባለፈው አመት ናይሮቢ ውስጥ ሰባ ዹሚሆኑ ኢትዮጵያውያን እዚተለቀሙ ሲታፈሱ እና ሲታሰሩ እዛ ያለው ዚኢትዮጵያ ኀምባሲ “ኬንያ ውስጥ ጉዳት ዚደሚሰበት ሕጋዊ ዜጋ ዹለም” ሲል ነበር መልስ ዚሰጠው። ሊብያ በፈራሚሰቜ ግዜ አፍሪካ ዜጎቜ በዚኀምባሲያ቞ው ገብተው ሲጠለሉ ኢትዮጵያውያን መሄጃ አልነበራ቞ውም። በመጚሚሻ ግን ዚናይጄሪያ ኀምባሲ ተቀብላ አስተናገደቻ቞ው።

አይሲስ ወደ ዹመን እዚገባ መሆኑ በተሰማ ግዜ ሰይፉ ፋንታሁን አንድ ዘገባ አቅርቩ ነበር። በዘገባው ላይ ዹመን ያሉ ኢትዮጵያውያን መንግስት ኚወሬ ያለፈ ምንም ነገር እንዳላደሚገ ይናገራሉ። ይልቁንም ዓለምአቀፍ ሞዮልና ተዋናይ ዚሆነቜው ዹሐሹር ወርቅ ጋሻው ስደተኛውን ለመርዳት ዹአቅሟን እያደሚገቜ እንደሆነ ጋዜጠኛ ግሩም ተ/ሐይማኖት ተናግሯል።

በዹመን እዚታዚ ያለውም ጉዳይ እርግጥ “ኢትዮጵያ መንግስት አላት ወይ?”..ዹሚለውን ጥያቄ ዚሚመልስ ነው። ጋዜጠኛው ዹመን ያለው ዚኢትዮጵያ ኀምባሲ “እንሚዳ቞ዋለን ወይስ እናርዳ቞ዋለን?” ነው ያለው ሲል ባሰፈሚው ጜሁፉ በዶቺቬሌ ቃላቾውን ዚሰጡት ዚኀምባሲው ቃል አቀባይ አቶ አምደሚካኀል ንግግር ኣሳፈሩን ይላል። “ኢትዮጵያዊያኑን እንሚዳ቞ዋለን። ኹአይ. ኩ. .ኀም. ጋር በመተባበር ወደ ሀገር መመለስ ዚሚፈልጉትን እንመልሳለን” ብለዋል። 
 ” አዎ ይሚዳሉ ግን ኀምባሲ ውስጥ ላሉ ሰራተኞቜ ነው። ..እኛን ግን እንሚዳለን ማለት ፈልገው ሳይሆን እናርዳ቞ዋለን ማለታ቞ው ነው። ሲያርዱ እንጂ ሲሚዱ መቌ ታይተው ነው።” ብሎ ነበር ዚጻፈው።

እውነታው ይህን ይመስላል። አንዳንድ ዚስርአቱ አጚብጫቢዎቜ ታዲያ ይህ እውነታ አይወጥላ቞ውም። ዜጋ እዚተሰቃዚ እነሱ ግን ስለ ህንጻ ይነግሩናልፀ ስለ ታምራዊው 11 በመቶ ዚኢኮኖሚ እድገት ይሰብኩናል። 
 ሕንጻና መንገድንማ ቅኝ ገዥዎቜም ሰርተዋል። ለዚያውም እነሱ ኚሚነግሩን ዚበለጠ።

ሕዝብ ደግሞ እያለ ያለው ፣ “ኚህንጻ በፊት ነጻ!” እንሁን ነው! ሀገር ማለት መሬት አይደለም። ሃገር ማለት ወንዙ፣ ተራራው፣ ሜንተሚሩ፣ አደለም። ሃገር ማለት ሕዝቡ ነው። ዚህዝቡ ሰቆቃ ግድ ዹማይለው አካል መንግስት ሊሆን አይቜልም።

↧

ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ድምጜ ዘገባ – 5/11/2015

$
0
0

ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ድምጜ አዳዲስ ዜና ዘገባዎቜን እና ካለፈው ዹቀጠለ ዚሰሃራ በሹሃ ተጓዊቜ ትዝታን ዚሚያስቃኝ ትሚካ ቀጣዩን ክፍል 3 እና 4 ይዘን ልናስደምጣቹ ተዘጋጅተናል::ዚቀድሞ አንድነት ፓርቲ ምክትል አፈ ጉባዬ እና ዚፋይናንስ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ጞጋዬ አላምሹው ኚስደት ካሉበት ያሳለፉትን ዚፖለቲካ ሕይወት እና ዚአንድነት ፓርቲን በተመለኹተ ያደሚጉት ቃለመጥይቅ በዚህ ፕሮግራም ይቀርባል:: ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ

↧

ዹ 2007 5ኛው አጠቃላይ ምርጫ ዚመጚሚሻዋቹ ቀናት ገመናዎቜ በአስ቞ካይ ይታሚሙ / ኹዓሹና ትግራይ ዹተሰጠ መግለጫ /

↧
↧

በሞፍጥ ሀገር ሲናጥ ታደለ በመኩሪያ

$
0
0

እንደወትሮው ኚኢትዮጵያ ዚሚመጡ ዜናዎቜ አያስደስቱምፀ ሀገራቜን ኚጥፋት ማማ ላይ መድሚሷን ያሳያሉ። ለአራት ጊዜ በሞፍጥ ተመርጫለሁ ብሎ ሥልጣን ላይ ቂጥ ያለው ወያኔ ለአምስት ጊዜ ሊያወናብድ እዚተዘጋጀ ነው። በዹጊዜው ጥቂቶቜ ብቻ በገሃድ ዚምርጫውን ሞፍጥነት ሲያጋልጡ ምዕላተ ሕዝቡ ግን ኚሹሹክታ ያለፈ እንደ ቡርዲና ቡርኪነፋሶ ዳር እስኚዳር በአደባባይ ወጥቶ ሲቃወም አይታይምፀ ዘንድሮ ግን ሌላ ድርጅቶቜ ወይም ግለሰቊቜ ሣይጠብቅ እርሰ በእርሱ በጎበዝ አለቃ ተቧድኖ ምርጫውን ማክሾፍ አለበት። ወያኔ ለአምስተኛ ጊዜ ለመመሚጥ ዹተዘጋጀ ይመስላል፣ ይህ ኚተሣካ ደግሞ ሕዝባቜን ሞፍጥን እንደሥሚዐት ዚተቀብሎታል ማለት ይቻላል። ዚወጪ አገር ታዛቢዎቜም ኢትዮጵያ በዲሞክራሲ ዚምትመራ ሀገር ናት እሰኚማለት ዚደሚሱት ይህን በመታዘብ ይመስላል። ‘ወደሾ ኚተደፋሜ ቢሚግጡሺ አይክፋሜ’ እንደማለት፣ ዚአሜሪካኗ ዲፕሎማት ወይዘሮ ዊዲ ሾርማንም በተዘዋዋሪ ዚነገሩን ያንን ነበር። ወያኔ ዚሜፍጥ መንግሥት መሆኑን ኚአሜሪካ በላይ ዚሚያውቅ ዹለም ፀ ዚአሜሪካን ሰ቎ት ዲፓርትሚት ሪፖርት ያንን ያሣያል፡፡ ሞፍጥና ነፍጥ ርዕዮተ ዓለሙ ዚሆኑት ወያኔ እንደሥሚዐት እንድንቀበል ካደሚን ዓመታት ተቆጥሚዋል ፀ ኚጫቃቜ ላይ አሜቀጠሩ መጣሉ ዚእኛ ሕዝቊቜ ሃላፊነት መሆን አለበት። ዚትግራይ ሕዝብ ነጻነት ግንባርን ሞፍጥ በዓለም ዹመገናኛ ብዙሃን ሺፋን ሲያገኝ እኛም ለድርጊቱ አዲስ ሆነን አብርን እናጫፍራለንፀ በሊቢያው በአይሲሲ አሹመናዊ ቡድን በወገኖቻቜን ላይ ለተፈጻመው ግድያ ያደሚግነው ያንኑ ነው። ለምሳሌ በሚያዚያ 11፣ 2007 ዓ ም [Islam Society of Iraq and Syria] ISIS ሃያ ስምንት ወገኖቻቜን በዚህ አሹመኔ ቡድን በሊቢያ በካራ አነገታ቞ወን መግዝር፣ በደቡብ አፍሪካ፣ በሚነድ ዹጎማ ነበልባል መቃጠል፣ በሜዎ቎ሬያን ሐይቅ፡ በሕንድ ዊቂያኖስ መስመጥ፣ በዹመን ኚሚያለቅሱ ሕጻናት እናቶቜ ተነጥለው ወደ መታጎሪያ ሲነዱ፣ ሕጻናት በሚሃብ ሲያለቅሱ ዓለም አጀብ ፣አጀብ፣ ሲል ኹዚህ ዹኹፋ ግፍ ወያኔ በሕዝባቜን ላይ እንዳልፊጞመ እኛም አብሚን አጀብ አጀብ ብለናል። በሻማ ማብቱ ሥነስሚዓት ላይ ተካፍለናል፣ ያ ባልኚፍ ነበር፣ ግን ክፋቱ ግን ይህ ድርጊት መደጋገሙን አምነን ለመጚሚሻ ጊዜ ዹዚህ ሁሉ ግፍ መሐዲሱ ወያኔ መሆኑን ተቀብለን ለማስወገድ በተግባሩ ሥራ ላይ ለመተባበር ቁርጠኛነት ያለመኖሩ ፣ በእግር ኳስ ሕግ ኳሷን እንዎት እንደምትመታት ኚማሰብህ በፊት ወደኳሷ ተጠጋ ይላልፀ ሰለመተባበር ሰንደሰኩር በተግባር መሬት ላይ እዚሰራን ቢሆን ይመሚጣል። ይህን ቡድን ለማስወገድ ቆርጠን መነሣትን ይጠይቃልፀ ለዚህ ውርደት በተዘዋዋሪ ዚዜጎቜ አስተዋጟ አለበትፀ ዋነኛውን ተዋናኝ ወያኔን በገሃድ ለማውገዝ እንኳን አልደፈርንምፀ’ በሰዎቜ ሰቆቃ ፖለቲካ አንሥራ ዹሚሉም አልታጡም፣ ዹአዛኝ ቅቀ አንጓ቟ቜ አይነቶቜ፣ ዹሀገር ቀቱ ወጣት ይሻላል፣ ‘ዹሀገር ውስጥ አንበሣ ዹውጭ ሬሣ ሲል ተሳልቈል ። በውጪ ሀገር ዚአንድ ፖለቲካ ድርጅት መሪ ብቻ ና቞ው፣ በገሃድ ወያኔ ሌለኛው አይሲሲ ነው ሲሉ ዚተደመጡትፀ በዚአቅጣጫው በተሰደድንበት አገሮቜ ም ሆነ በሀገራቜን ለመሞትን አልፈራንም፣ ሆኖም ግን በአንድነት ወያኔ ይወገድ ለማለት በአደባባይ ምን አሰፈራን? ይህንን ለሃይማኖት አባቶቜ ልተወው፣ ምክንያቱም ዚኢትዮጵያ ሲኖደስ ተወካይ አባት፣ ዚእስልማና ሃይማኖት አባት ዹወንጌላዊ ቀተክርስትያ ተወካዮቜ 1997 ዓም በአዲስ አበባ ኹተማ ብቻ 200 ሰዎቜ በአጋዚ ታጣቂ ተገለው እነዚህ እላይ ዚተጠቀሱት ዚሃይማኖት አባቶቜ አይናቜንን ግንባር ያድርገው ነበር ያሉትፀ ዛሬም አሲሲን አውግዘው ወያኔ ሲዘሉ አስተምህሮታ቞ው ሰሚ ይኖሹው ይሆን? ዚካቶሊኩን መሪን አይጚምርም። ፍርዱን ለዓምላካቜ ልተወውና ሰለአይሲሲ ትንሞ ልበልፀ

እነዚያ አይሲሲዎቜ በእስልምና ሰም ሃያ ስምንቱን ወገኖቻቜንን ሲግዝሯ቞ው ዚሚሳዚው ቪዲዮ በጉታናሞ ቀዬ በአልካይዳ ስም ተጠርጥሚው ዚታሰሩት እስሚኞቜ ለብሰውት ዹነበሹውን ዩኒፎርም ይመስል። ይህን ቡሚቱካናዊ መልክ ቱታ አሰለብሰው በኊርቶዶክስ ሃይማኖት ስም አይግዝሯ቞ው እንጂ በአማራ ሰም ሊቢያ ኹተፈጾመው ግፍ በላይ በክርስትያኑኖ ሕብሚተሰብ ላይ በወያኔ ታጣቂዎቜ ተፈጜሟል። በቪዲዮ ባለመቀሚጹ ምንም ዓይነት ግድያ በኊርቶዶክስ እምነት ተኚታዩ ክርስትያኖቜ ላይ እንዳልተፈጞም ገምተን ዚሊቢያውን አጋነን ካራገብን ተሣስተናል። ሳሞራ ዩኑስና ሳራ መኮንን፣ በጋራ ሙለታ፣ በአሰቊት ገዳም፣ በአርባ ጉጉ ኚነሕይወታ቞ው ገደል ያስጣሏ቞ው ዚኊርቶዶክስ እምነት ተኚታዮቜ ኢትዮጵያውያን ነበሩ። ዓምላክ ነፍሳ቞ውን ኚገነት ያኑርልነና ፕሮፌሰር አሰራት ወልደዚስ ዹአማር ድሚጅት ብለው ሲያቈቁሙ በአማራ ስም ወያኔዎቜ ያስገድሉት ዹነበሹውን ዚኊርቶዶክስ እምነት ተኚታዩን ለመታደግ ነበር። እንደሳ቞ው ድሬ ደዋ ተወልዶ ላደገ አማራ ማለት ዚኊርቶዶክስ እምነት ተኚታይ መሆኑን ጠንቅቶ ያውቃል። አንዳንድ ዚወያኔ ሞፍጥ ያልገባ቞ው ወይም እንዲገባ቞ው ያልፈለጉ እኛን ታላቅ ሰው ለዘር ፖለቲካ ዹቆሙ አሰመስለው ያቀርቧ቞ዋል። ኚአድራጊዎቹ ግን በድፍሚት ሐቁን ይነግሩናል፣ ለምሳሌ አቶ ሰብሃት ነጋና አቶ ተፈራ ዋልዋል ተራ በተራ እንዲህ ይነግሩናል፣ በገሃድ’ ‘አማራውነና ዚኊርቶዶክ እምነት ተኚታዮን አኚሚካሪውን ሰበሚነዋል፣ ዚኊርቶዶክ ቀተ ክርስቲያን ዚአማራው ምሜግ ናት’ እስኚማለት ደርሰዋልፀ ይህ አሉ አሉ ሣይሆን በማስሚጃ ዚተያዘ ነው። በመኝታ ክፍላቜን ዹተኛውን ትልቁን ዘንዶ ሚስተን በዱሩ ባለው እባብ ላይ እንጮሃለን፣ ይህ ስሜት ይሰጣቜኋል? ለእኔ አይሰጠኝምፀ ዚክርስቲያኑና ዚእስልምና ተኚታዩ መሳ በመሳ በሚኖርባትት ኢትዮጵያ ላይ ‘ጀሃድ’ ዚሚያውጅ ዚእስልምና ተኚታይ ካለ እርሱ እስላም አይደለም፣ በክርስታኑም በኩል ያንን ዚሚያስብ ካለ ሾፍጠኛ ነው። ሾፍጠኛው ወያኔ ‘ጀሃድ’ ታወጀብኝ ብሎ ሱማሌን 1997 ዓ ም ዹወሹሹው በምርጫ ዚደሚሰበትን ሞነፈት አቅጣጫ ለማስለወጥ መሆኑን ተግባሩ ገላጭ ነውፀ ራሱ ወያኔ አሞባሪ ሆኖ ዚሃይማኖት ጜፈኞቜን ሊዋጋ አይቜልም፣ በሊልጣን ዚሚያቆዚው ኹሆነ ኚእነሚሱ ማበሩን ይመርጣል፣ በዱር በነበሚበት ዘመን ያደሚገው ያንን ነበር፣ ዚነርሱን መንገድ ይኚተላል፣ በተግባር ሲያደርገው ያዚነው ያንኑ ነው፣ በጋንቀላ በአንድ ሌት አራተ መቶ ሰው፣ በቀንሻጉል፣ በጉራ ፈርዳ፣ በኊጋዎን፣ ሬሣ ተጋድሞ ሲቆጠር፣ ወንድሙ ዚወንድሙን አሰኚሬን መሬት ለመሬት እንዲጎትት በውያኔ ታጣቂዎቜ ትዕዛዝ ሲሰጠው ያዚነው ነውፀ እንደዜጋ ኚዕንቅልፋቜ መንቃት አለብን። በዹመን ዹኹተመው አልካይዳ በሱማሌ ዚሚቀሳቀሰው አልሞባብ ዚሃይማኖት አሰተህምሮታ቞ው ወደ ኢትዮጵያ ሰርጎ ያልገባው በወያኔ ሠራዊት ጥንካሬ አይደለምፀ በሕዝቡ ውስጥ በቅርበት ዚሚሰሩ ዚሁለቱ ሃይማኖት አባቶቜ አርቆ አሰተዋይነት ነው። በወያኔ ዚተመለመሉትን ዚክርስትያኑንም ሆነ ዚእስልምናው ተኚታይ አባቶቜን አይመለኚትም። ወያኔ በሊልጣን ኹቀጠለ ግን ሁኔታዎቜ መቀጠላቾው አሰተማማኝ አይሆንምፀ ዹዚህ ቡድን ያለፉ ድርጊቶቹ ዚሚያሳዩን ሕዝብን በሃይማኖትና በዘር እያለያዚ ሲያጋድል፣ቊንቊቜን በሕዝብ ማመላሻ መኪናዎቜ ወስጥ እያጠመደ በተቃዋሚዎቹ ላይ ሲያላክክ ነው። ይህ ዹሾፍጠኛ ቡድን በጎሣ ፖለቲካ ሜፋን፣ ዚሃይማኖት ልዩነት ያራምድ እንደነበሚ አሁንም እያደሚገ እንዳለ አንድ ማስሚጃ ልጥቀስ፣ ጃራ ዚሚባለው በምሥራቅ ሐርሹጌ ኢስላሚያ ኊሮሚያ በማለት ቆቱውን ወይም አርሶ አደሩን በግብርና መሣሪያው፣ በጌጅራና በሜጫ ክርስትያኑን አሣርዷል፣ ሳሞራ ዩኑስና ሳራ መኮንን አማራውን ለማስገደል መልክተኛቾው እርሱ ነበር። በአሜሪካ ኚአንድ ዚታወቀ ዩኒቚርሲቲ ዚጎሳ አቀንቃኝ በጥቅሉ በሜጫና በግጅራ ተዋጓቾው በማለት ዚጃራን መፈክር ሲያስተጋባ ስሰማ ጆሮዬን አላመንኩም፣ ወያኔም ዹሚፈልገው ይህን መሰል ካድሬ ነው።

ኢትዮጵያ ሀገራቜን በነፃነት ለሊሰት ሺ ዓመት ኖራለቜ ዹሚል ታሪክ አለንፀ በሃያ አንደኛው መቶ ዓመት ነፃነታቜንን አሳልፈን ሰጥተን በዓለም ሕበሚተሰብ ፊት ተዋርደናልፀ ለመሞት ዚማንፈራ ኢትዮጵያውያን እንዎት ነው በግልም ሆነ በጋራ ወያኔን በቃህ ዹማንለው? ይህን ማድሚግ ዹማንቾለው ለምንድነው? በትግራይ ሕዝብ ነፃነት ግንባር ሜፋን ይህ ቡድን ሞፍጥ ሲሰራ ዚትገራይ ሕዝብስ ምን ያስባል? ኹተናገርን እናልቃለን፣ አልሰማንም አላዹንም ማለቱ ለልጅ ልጆቻቜን አይጠቅምም፣ እውነት ኮስሶ ሜፍጥ ሥሚዓት በሆነባት ሀገር፣ እንዎት ትውልድ መተካት ይቻላል? ለሞፍጥና ለነፍጥ ሣንበሚኚክ ዚዜግነት ግዎታቜንን ዚምንወጣበት ወቅቱ አሁን ነው፣ ኹዚህ ኚምነያውና ኹምንኖሹው ሐቅ በላይ ምን ማዚት እንሻለን? ታሪክ ዚጣለብንን ተግዳራት መጋፈጥ ግድ ይለናል። ‘አሣ ግማቱ ኚአናቱ’ እንደሚባለው ወያኔ በሞፍጥ ዹገማ ብድን ሰለሆነ በሕዝብ ዚተባበሚ ኚንድ መወገድ አለበት። ዚሚመጣው ምርጫ ዚወያኔ ሳይሆን ዚእኛ እናድርገው፣ ትንሜ አገር ብትሆንም ትልቅ ልብ ካለው ዹ ቡርኪነፋሶ ሕዝብ እንማር! በሊቢያ አይሲሲ አሹመኔው ቡድን ካራውን በአንገታ቞ው ላይ ሲያርፍባ቞ወ ዚሚሰማቜው ዚሞት ጜልመት ፣ዛሬ ያ እንዳይሆን ለወገን ክበር ለሀገር ነጻነት በመቆማቜው በወያኔ እስር ቀት ዚሞት ጜልመት ሰለ አጃበበባቜው ወኖቜ እናስብፀ ለእዚህም ነው ወያኔና አይሲሲ አንድ ናቾው ዚምንለው።
ኢትዮጵያ ሀገራቜንን እንታደጋት፣ ሕዝባቜን ማደሪያ እንደሌላት ወፍ አይኚራተት።

tadele@shaw.ca

↧

ዚአሜሪካ እርዳታ አምባገነኖቜን ማጠናኚሩ ይቁም ግልፅ ደብዳቀ ለአሜሪካ መንግሥት ሃላፊዎቜና ለአሜሪካ ሕዝብ ኹአክሎግ ቢራራ (ዶ/ር)

$
0
0

ዚኢትዮጵያና ዚአሜሪካ ግንኙነት ኚመቶ ዓመታት በላይ ነው። ይኌ ግንኙነት በሁለቱ ሃገሮቜ መካኚል ሊኖር ዚሚገባውን ዚእኩልነትና ዚጋራ ጥቅም መሰሚት ያደሚገ እንደ ነበሹ ታሪክ ያስታውሳል። መንግሥታት ቢለዋወጡም በሁለቱ ሃገሮቜ መካኚል ዹተመሰሹተው ዹቆዹ ግንኙነት አይፈርስም ዹሚል እምነት አለኝ። ዚኢትዮጵያ ስደተኞቜ አሜሪካን ዚመጀመሪያ መድሚሻ አድርገን አሜሪካዊ ዚሆንንበትና ወደፊትም ዚምንሆንበት ዋና ምክንያት ዚአሜሪካ አስኳል እሎቶቜ–ነጻነትፀ ዚግለሰብ ክብርፀ ፍትህ-ርትእፀ ዚሰብአዊ መብቶቜ መኚበርፀ በሕግ ፊት ማንኛውም ግለሰብ እኩል መሆንፀ ዹሕግ ዚበላይነትና ዲሞክራሳዊ አገዛዝ ስለሳቡንና ዚመስራት እድል በጎሳ ሳይሆን በሞያ ዹሚወሰን መሆኑን ስላወቅን ነው። ዛሬ ብዙ መቶ ሜህ ዚኢትዮጵያ ትውልድ በአሜሪካ ይኖራልፀ ድምጜና መብት አለው። በኢትዮጵያ ዹማናገኘውን በተሰደድንበት አሜሪካ እናገኛለን። ይኌን እድል ተጠቅመን ለተወልድንባት ሃገር ጠበቃ እንሁን።

በሁለቱ ሃገሮቜ ዹተመሰሹተው ዹቆዹ ግንኙነት በወታደራዊውፀ ሶሻሊስት አምባገነን መንግሥት ዘመን ተለውጩ አሜሪካኖቜ አቋማቾውን ለውጠው ተተኪ መንግሥት ይጠባበቁ እንደ ነበር ብዙ ማስራጃዎቜ አሉ። ደርግን ዚተካው ዚጎሳ ልሂቃን ቅንጅት ህወሓት በበላይነት ዚሚያሜኚሚክሚው ዚኢህአዎግ መንግሥት ኚምእራብ ሃገሮቜፀ በተለይ ኚአሜሪካ ጋር ያለው ዚጥቅም ትሥስር እጅግ በጣም ዹጠነኹሹ ነው። ዚኢትዮጵያ እድገት ፈጣን ዹሆነው በውጭ እርዳታፀ ስደተኛው በሚልኹው ገንዘብፀ በሃገር ውስጥ ብድርና በቅርቡ በውጭ ኢንቬስተሮቜ ድጋፍ ነው። ኢኮኖሚው በራሱ ለመንቀሳቀስ አልቻለምፀ ፍትኅ ኹሌለ አይቜልም። በአሜሪካኖቜ ስሌትፀ በፈራሚሰውፀ እርጋታና ሰላም በሌለበት ዚአፍሪካ ቀንድና አካባቢ (በሰሜን ኀርትራፀ በምስራቅፀ ሶማሊያፀ በምእራብ ደቡብና ሰሜን ሱዳንፀ በባህር ማዶ በዚመንፀ በሶሪያፀ በኢራክፀ በሰሜን አፍሪካ በሊብያና በግብፅ) ያለውን ዚርስ በርስ ግጭትፀ ዚሃገሮቜ መፈራሚስና ዚሃብት ውድመት ሲመለኚቱ ኢትዮጵያ “ዚእርጋታና ዚልማት” ደሎት ናት ወይንም ትሆናለቜ ብለው ማመናቾው አያስገርምም። ግዙፉ እርዳታ ኹዚህ ስሌት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው። ጾሹ-ሜብርተኛነት ሰብሳቢ መርህ ሁኗል። አሜሪካኖቜ ያላስተዋሉትፀ ቢያስተውሉትም ዚሚመጣውን ቜግር ኚራሳ቞ው ጊዚያዊ ጥቅም ባሻገር ያልተገነዘቡትፀ አምባገነኖቜ ፀሹ-ሜብርተኛነትን ምክንያት በማድሚግ ራሳ቞ው ሜብር ፈጣሪዎቜና ሜብርተኞቜ መሆናቾውን ነው። ዚሰብአዊ መብቶቜና ዚነጻነት መገፈፍ ሁለተኛ ወይንም ሶስተኛ ደሹጃ ዚያዘው ለዚህ ነው። ዚሕዝብ መብቶቜ በተኚታታይ ሲጎዱ አፍራሜ ኃይሎቜፀ ሜብርተኞቜን ጚምሮ መግቢያ ቀዳዳ ያገኛሉፀ ስደተኝነት እዚኚፋ ይሄዳል።

ዚአሜሪካ መንግሥት መሪ ፕሬዝደንት ባራክ ኊባማ ልክ ዚዛሬ ሁለት ዓመት በደቡብ አፍሪካ እንዲህ ብለው ነበር። “በአፍሪካ ሃገሮቜ በሙሉ ዹማንኛውም ግለሰብ ክብር ቢኚበር አሜሪካኖቜም ነጻ ይሆናሉ። እኔ ዹማምነው እያንዳንዳቜን ነጻ ለመሆን ኹተፈለገ ዹሁሉም ሰብአዊ ቀተሰቊቜና ግለሰቊቜ ኚድህነት ወይንም ኚበሜታ ወይንም ኹጭቆና ነጻ መሆን አለባ቞ው።” ይኌ እሎት ዚአሜሪካኖቜ እሎት ነውፀ ዹመላው በነጻነት ለመኖር ዹሚፈልግ ሕዝብ እሎትና ተስፋ ነው። ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ለክብሩፀ ለፍትህፀ ለነጻነትፀ ለሕግ ዚበላይነትና ለዲሞክራሲ ሲታገል ኚዓመሳ አመታት በላይ ሁኗል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት በአንድ አምባ ገነን ፓርቲ ስትገዛ ቆይታ አሁንም በአራት ቀናት በሚካሄድ “ዚይስሙላ ምርጫ” ዹተጠበቀ ውጀት ለሚኚተሉት አምስት አመታት ትገዛለቜ። ዚኢትዮጵያ ዚመንግሥት ስርዓት ልክ ዹፈሹሰውን ዚሶቬት ሕብሚት አገዛዝ ዚሚመስል ጋርዲያን ዚተባለው ጋዜጣ “ኊርዌሊያን” ዚሚለውፀ ወይንም በእኔ አመለካኚት ፍጹም ዹሆነ በስለላ መሚብ ዚተቆራኘፀ በአንድ አናሳ ብሄር ዚበላይነት ዚመኚላኚያፀ ዚስለላና ዚኢኮኖሚ ዚበላይነት ዚሚተዳደር አገዛዝ ነው።

ይኌ አገዛዝ ያለ ዓለም ትሥስር ዚገንዘብ ዚስለላፀ ዚመኚላኚያፀ ዚዲፕሎማሲና ሌላ ድጋፍ ህይወት አይኖሚውም። ዚማይካደው ገዢው ፓርቲ ባለፉት ሃያ አራት አመታት ለልማት ድጎማ ብቻ አርባ ቢሊዚን ዶላር ተሰጥቷታል። ኢህአዎግ ኚሙስናውፀ ኹሃገር በገፍ እዚተሰሚቀ ኚሚሞሜውና ኹሌላው ውድመት ዹተሹፈውን ተጠቅሞ መሰሹተ ልማት አካሂዷል። ኚእድገቱ ባሻገር መታዚት ያለበት ሃቅፀ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ዚምግብ እርዳታ ጥገኛ ኚሆነቜውፀ ወጣቱ ትውልድ በገፍ ኚሚሰደድባት ኢትዮጵያ ተሰርቆ ዹሾሾው ሃብት ግምት አስር ቢሊዚን ዶላር ነው። ይኌ ስንት ፋብሪካ ይኚፍት ነበርፀ ለስንት ወጣቶቜ ዚስራ እድል ያቀርብ ነበር? ዹተሰሹቀው ተሰርቆና ኹሃገር ሞሜቶፀ ዹተሹፈው መንገድ ስርቷልፀ ሃዲድና ግድቊቜ እዚሰራ ነው። ይኌ ግዙፍ እርዳታና መንግሥት ኚባንኮቜ ተበድሮ ሰማይ ጠቀስ ፎቆቜፀ ቪላዎቜፀ መንገድና ሌላ ቢሰራ ምኑ ያስደንቃል? ዚማይካደው ኢትዮጵያ ኹመቾውም ጊዜ በበለጠ ደሹጃ ጥገኛ መሆኗ ነው። ኢትዮጵያ ዛሬ በያመቱ ዚአራት ቢሊዚን ዶላር እርዳታ ተቀባይ ሁናለቜፀ ኚአፍሪካ ኹፍተኛው ኹሆነ ቆይቷል። በመንግሥት ደሹጃ ሲታይ ኹሁሉም ሃገሮቜ ኹፍተኛውን እርዳታ ዚምትለግሰው አሜሪካ ናት። ፈጣን እድገት አለ በሚባልባት አዲስ አበባ ኚፎቆቹ ባሻገር ለማዚት ለፈለገ ታዛቢ ቢያንስ አንድ መቶ ሜህ ህፃናት በመንገድ ያድራሉፀ ብዙ መቶ ሜህ ነዋሪዎቜ ምግብ ኚቆሻሻ ማጠራቀሚያ እዚለቀሙ ይበላሉ። ኚስምንቶ መቶ ሜህ እስኚ አንድ ሚሊዹን ዚኢትዮጵያ ስደተኞቜ በዹመን ብቻ ይገኛሉ። በሊቢያ ዚታጎሩትን ቁጥር አናውቅም። ለጋሶቜ ይኌን ሁሉ ግፍ አያውቁም ለማለት አልቜልም። በተጚማሪፀ መጭው ምርጫ ለይስሙላ መሆኑን ዚአሜሪካ መንግሥት ያውቃል። ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ዚያዘው ስራ ይሚጋገጥለታልፀ አሜሪካኖቜ ይኌን እንደሚደግፉ አልጠራጠርም። ሕዝብ ዹፈለገውና እውነተኛ ውድድር ያለበት ምርጫ ቢሆን ኑሮፀ ዚአሜሪካ ኢምባሲና ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅቶቜ በምርጫው ቀንና ተኚታታይ ቀኖቜ “ብጥብጥ” ይነሳል በሚል ስሌት ዹተጠንቀቁ መልእክቶቜ አያወጡም ነበር።

ኹላይ ዹቀሹበውን መሰሚት በማድሚግ አሜሪካኖቜን ዹጠዹቅኋቾውና ያሳስብኳ቞ው ዚእርዳታውን ጥቅምና ጉዳት ኚራሳ቞ው መብትና ጥቅም አንፃር እንዲያዩት ነው። “እስኪ አስቡትፀ በአሜሪካ በተኚታታይ አንድ ፓርቲ በዹ አራት አመቱ በሚደሹገው ምርጫ ቢያሞንፍ ምን ትላላቜሁ? ዚፖለቲካ ተወዳዳሪዎቜ መብታ቞ውን ለማስኚበር ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጡ ፖሊስ ቢደበድባ቞ውፀ ቢያስራ቞ውፀ ቢያሳድዳ቞ው ምን ትላላቜሁ? ምርጫው ሰፊ ውድድር ተካሂዶ ዚፖሊሲ አማራጮቜ ውይይት ባይደሚግባ቞ው ምን ትላላቜሁ? አስቡትፀ ኢትዮጵያ ኚአርባ ቢሊዚን ዶላር እርዳታ በኋላ ኹዓለም ሃገሮቜ መካኚል አሁንም ፍፁም ድሃና በዓመት ዚነፍስ ወኹፍ ገቢዋ ኚአፍሪካ ሃገሮቜ አንድ ሶስተኛ ዚሆነፀ ኹዓለም ሃገሮቜ መካኚል በሙሰኛነት ዚተበኚለቜፀ ኹዓለም ሃገሮቜ መካኚል ኹፍተኛውን ዚምግብ ጥገኝነት ቊታ ዚያዘቜፀ በአፍሪካ ጋዀጠኞቜን ኚሚያስሩ ሃገሮቜ መካኚል ሁለተኛውን ደሹጃ ዚያዘቜፀ በዓለም ደሹጃ አራተኛውን ደሹጃ ዚያዘቜ መሆኗን ብታውቁ ምን ትላላቜሁ? ይህቜ ዚምግብ ጥገኛ ዚሆነቜው ኢትዮጵያ አብዛኛውን ዚምግብ እርዳታ ዚምታገኘው ኚአሜሪካ መንግሥት ነው። ኚድሃይቱ ኢትዮጵያ በአራት ዓመታት ብቻ አስር ቢሊዚን ዶላር ተሰርቆ ሲሞሜ ለሃገር ጥቅም ቢውል ኑሮ ስንት ፋብሪካዎቜ ለማቋቋም እንደሚያስቜልና ለስንት ኢትዮጵያዊያን ዚስራ እድል እንደሚፈጥር አስቡት?

እኔ ይኌን ሃተታ ለአሜሪካ ሕዝብና መንግሥት በታወቁ ጋዜጊቜ አማካይነት ለማቅሚብ ዚተገደድኩት በሙስናውና በገንዘቡ መሰሹቅ ምክንያት አይደለም። ያሳሰበኝፀ ዚኢትዮጵያዊያን ሰብ አዊ መብቶቜ በተኚታታይ መገፈፋ቞ውፀ ዚማህበሚሰብ ድርጅቶቜፀ ነጻ ጋዜጊቜና ጋዜጠኞቜፀ ተወዳዳሪ ሊሆኑ ዚሚቜሉና ዚተሻለ አማራጭ ለሕዝብና ለሃገር ለማቅሚብ ዚሚቜሉ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ መደምሰሳ቞ውፀ መናገርፀ መሰብሰብፀ መንግሥትን መተ቞ት ወንጀል መሆኑ ነው። እነዚህን እሎቶቜ እንደምታኚብሩና እንደምትታገሉላ቞ው አምናለሁ። ታዲያፀ ዚአሜሪካ መንግሥት ዹሚሰጠው እርዳታ እነዚህን እሎቶቜ ካላጠናኚሚ ዘላቂ ጥቅሙ ምንድን ነው? ዚመናገርፀ ዚመሰብሰብፀ ዚመኚራኚርፀ ዚመተ቞ትፀ ዚመወዳደር ወዘተ መብቶቜ ፍጹምና አደገኛ በሆነ ደሹጃ ታፍነዋል። ሂውማን ራይትስ ወቜ እንዲህ ሲል አስጠንቅቆ ነበር። “ዚኢትዮጵያ መንግሥት በአሰቃቂ ደሹጃ ኚመንግሥት ቁጥጥር ነጻ ዹሆነውን መገናኛ ብዙሃን አውድሞታልፀ ቢያንስ ሃያ ሁለት ጋዜጠኞቜፀ አሳታሚዎቜና ብሎገሮቜን በወንጀለኛነት ኚሶ አስሯልፀ ኚሰላሳ በላይ ጋዜጠኞቜ በፍርሃት ኹሃገር እንዲሰደዱ አድርጓል።” ገዢው ፓርቲ ይኌን ሲያደርግ ዚሚጠቀምባ቞ው በ2009 ያፀደቃ቞ው ዹጾሹ-ሜብርተኛና ዚመንግሥት ያልሆኑ ዹበጎ አድራጎትና ዚማህበሚሰብ ድርጅቶቜን ዚሚመለኚቱ ሕጎቜን ነው። ለነጻነትፀ ለፍትህፀ ለዲሞክራሲና ለሕግ ዚበላይነት ዹተሟገተና ዹቆመ ግለሰብ ሁሉ ሰለባ ዹመሆን እድሉ ኹፍተኛ ነው። በስራ እድል በኩል ሲታይፀ ለገዢው ፓርቲ ወይንም ለጎሳ ጥቅም ታማኝነት ያላሳዚ ሁሉ እድል አይኖሚውም። አስተዳደሩ በባለሞያዎቜ ሳይሆን በታማኝነት ይመራል። ይኌን ሁኔታ ስታዩፀ አፈናውፀ አድልወውፀ ጭካኔውፀ መገለሉ ወዘተ ለሰላምፀ አብሮ ለመኖርፀ ለእርጋታ አደገኛ መሆኑን ትገምታላቜሁ። ዹአገዛዙ አፋኝነትና አግላይነት ለሜብርተኛነት አመቜ ሁኔታ ፈጥሯል። ዚአሜሪካ መንግሥት እንደዚህ ያለ አፋኝና አግላይ መንግሥት ሲደግፍ ዚአሜሪካን ዚሚዢም ጊዜ ጥቅም ይጎዳል ወይንስ አይጎዳም? ብላቜሁ ዹመጠዹቅ ሃላፊነት አለባቜሁ።

ይኌን አደጋ በተደጋጋሚ ዹምናቀርበው ኢትዮጵያዊያን ብቻ አይደለንም። በዚህ ዓመት ፍሪደም ሃውስ ስለ ዓለም ሃገሮቜ ነጻ መሆን አለመሆን ባወጣው ዘገባ ኢትዮጵያ ኚአርባ ዘጠኝ ነጻ ካልሆኑ ዚአፍሪካ ሃገሮቜ መካኚል አርባ ሶስተኛውን ደሹጃ ይዛለቜፀ ኚኢትዮጵያ ዚባሱ ስድስት ሃገሮቜ ብቻ አሉ ማለት ነው። በተመሳሳይፀ ዘ ኮሚቲ ቱ ፕሮ቎ክት ጆርናሊስትስ ዚተባለው ተቋም “ጋዜጠኞቜን በኹፍተኛ ደሹጃ ኚሚያስሩ ሁለት ዚአፍሪካ ሃገሮቜ መካኚል አንዷ መሆኗንፀ በዓለም ደሹጃ ሲታይ አራተኛ መሆኗን አመልክቷል። እንደዚህ ጹለማ በሆነ ሁኔታ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ሊካሄድ አይቜልም። ምርጫውን በሚመለኚት በዚህ ወር ሂውማን ራይትስ ወቜ “ምርጫ–ዚኢትዮጵያን ፈለግ ዹተኹተለ” በሚል እንዲህ ኹሚል ድምዳሜ ላይ ደርሷል። “ካለፈው ምርጫ ወዲህፀ ገዢው ፓርቲ በባሰ ደሹጃ ቁጥጥሩን አጠናክሯልፀ ዚመናገርፀ ዚመሰብሰብፀ ዚመደራጀት መብቶቜን ኹልክሏል
 ኢትዮጵያዊያን ወደ ምርጫ ሲሄዱ ተቃዋሚዎቜ በገጠማቾው አፈና ዚተነሳ ያላ቞ው እድል በጣም ዹጠበበና ጹለማ ዹሆነ ነው።” ዚኢትዮጵያን ሕዝብፀ በተለይ ተቃዋሚውን በንቀት መነፅር ያዚቜው ዚአሜሪካ ዹውጭ ጉዳይ ምክትል ዚፖለቲካ ሃላፊ ዌንዲ ሾርማን “ኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ናትፀ ምርጫውን በሚመለኚት ነጻፀ ፍትሃዊፀ ተቀባይነት ያለውፀ ክፍትና ሁሉን አቀፍ ዹሆነ ምርጫ እንደሚካሄድ እናምናለን” ያለቜው ውሞት ብዙ ዚምእራብ ታዛቢዎቜን ቁጣና ትዝብት አምጥቷል። ዋሜንግተን ፖስት ዚተባለው ዚታወቀ ጋዜጣ እሷንና ዚኢትዮጵያን መንግሥት በሚመለኚት “ዚማስመሰል ምርጫ በኢትዮጵያ” በሚል አርእስት እንዲህ ብሏል። “ዚአሜሪካ መንግሥት ዚኢትዮጵያን መንግሥት ማውገዝ እንጅ ማሞገስ ዚለበትም።” ስለሆነምፀ ዚአሜሪካን መንግሥትና ሕዝብ አደራ ዹምለው ሜብርተኛነትን ለመኹላኹል በሚል ምክንያት ሜብርተኛነትን ዚሚፈጥርና ዚሚያጠናክር መንግሥት መደገፉን ያቁም ነው።
ምን አማራጭ አለ?

ጠቃሚውን ተቃውሞ ለመቀበል ፈቃደኛ ዹሆነን ግለሰብ ወይንም መንግሥት ለማሳመን አስ቞ጋሪ ነው። በእኔ ግምት ለኢትዮጵያ ዘላቂነትፀ ለመላው ሕዝቡ ዚኑሮ መሻሻልፀ ለአሜሪካ ዘላቂ ጥቅም አጋባብ ያለው አማራጭ ያለምንም ማወላወል ለሰብአዊ መብቶቜፀ ለነጻነትፀ ለፍትህና ለሕግ ዚበላይነት መኹበርና ለዲሞክራሲ ግንባታ ያለተቆጠበ ድጋፍ መስጠት ነው። ቢያንስ ዚአሜርካ መንግሥት ለራሱ ዘላቂ ጥቅም ሲል ዹሚለግሰውን እርዳታ በሙሉ ኚሰብ አዊ መብቶቜ መኹበርና ኚዲሞክራሲ ግንባታ ጋር ማጣመር አለበት። ነጻፀ ፍትሃዊፀ ተቀባይነት ያለውፀ ክፍትና ውድድር ያለበት ምርጫ ለማካሄድ ቅድመ ሁኔታዎቜ መኹበር ነበሚባ቞ው። አለመኚበራ቞ው ውጀቱን አስቀድሞ ወስኖታል። ገዢው ፓርቲ ያሞንፋል።

ዚአሜሪካን ሕዝብፀ ዹምክር ቀት አባላትንና ዚመንግሥት ሃላፊዎቜን በቀጥታ ዹምጠይቀው ኚሕዝብ ተሰብስቊ ለኢትዮጵያ አምባገነን መንግሥት ዹሚሰጠው እርዳታ ኚዲሞክራዊው አገዛዝ ጋር ምን ግንኙነት አለውፀ ኹሌለው ለምን ለሰብአዊ መብቶቜፀ ለነጻነትፀ ለፍትህፀ ለእውነተኛ እኩልነትና ለዲሞክራሲ አትቆሙም? ዹሚል ነው።”
በእኛ በኩል አብሮና ተባብሮ ኚመስራት ሌላ አማራጭ ዚለንም። ዚአሜሪካ ዜግነት ያለን ኢትዮጵያዊያን በያለንበት ለአሜሪካ ምክር ቀት ተወካዮቜ ሳንሰለቜ ድምፃቜን ብናሰማ ኹፍተኛ አስተዋፆ እንደምናደርግ አምናለሁፀ እስቲ ያልሞኚርነውን እንሞክር እላለሁ።

↧

ፍካሚ- ዘመንፀትንቢተ ወቅት’ዚጎንቻው

↧

ውጀቱ ምን ሊሆን እንደሚቜል ኚወዲሁ ዚሚታወቀው ዚህወሓት/ኢህአዎግ ዚምርጫ ድራማን አስመልክቶ ዹተሰጠ ዚጋራ መግለጫ

$
0
0

ዚኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን ተነፍጎ ባገር በቀሉ ዚወያኔ አፓርታይድ አገዛዝ ስሚ ወድቆ ፍዳውን እያዚ ነው። ስርአቱ ላለፉት 24 አመታት በሃገራቜን ውሰጥ በፈጠራ቞ው ፖለቲካዊፀ ማህበራዊፀ ኢኮኖሚያዊና ስነልቊናዊ ቀውሶቜ ምክንያት ተተኪው ወጣት ትውልድ ባስደንጋጭ ሁኔታ በዹጊዜው አገሩን ጥሎ ሲወጣ በባህር ውስጥ በመስመጥናፀ ኹዛም ዹተሹፈው በአፍሪካና በአሚብ አገሮቜ እጅግ አሰቃቂ ለሆኑ ውርደት ስቃይና ግድያ ተጋልጧል።

ኚምርጫ ሂደት ጋር በተያያዘፀ ምርጫውን ተኚትሎ ሊፈጠር ዚሚቜለውን ዚህዝብ አመጜ አስቀድሞ ለማምኹን በሚል ስልት በሀገር ውስጥ ዹሚገኙ ወጣቶቜን ወጣት በመሆናቾው ምክንያት ብቻ በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ በመታፈስና ወደ ተለያዩ እስር ቀቶቜ በመታጎር ላይ ና቞ው። በመላው አገሪቱ ውስጥ ዚፖለቲካ አመራር አካላትም ይሁኑ አባላት በእስርና ወኚባ ላይ ይገኛሉ። በአጠቃላይ ዚምርጫ ምህዳሩ ዝግ መሆኑ እዚተገለጞ በሚገኝበት ሂደት ውስጥ ያለነጻነት ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ማድሚግ ስለማይቻል ህዝባቜንን ወደ ፍትሃዊና ዲሞክራሲዊ ስርአት ዚሚያሞጋግሚው ውጀት ይገኛል ብለን አናምንም።

በማንኛውም አገር በሚደሹጉ ዚምርጫ ሂደት ላይ ዹጎላ ሚና ሊጫወቱ ዚሚቜሉ ተቋማትና ድርጅታዊ እንቅስቃሎዎቜ ምን አህል እንደታፈኑ በአጭሩ በማስሚጃ ለማስደገፍ ያህልፀ በርካታ ዚህዝብ ወገንተኛና ዹተቃዋሚ ድርጅት መሪዎቜፀ አባላትና ደጋፊዎቻ቞ውፀ ጋዜጠኞቜ ጊማሪያን በግፍ ታስሚው በድቅድቅ ጹለማ በእስር ቀት ውስጥ ባስ቞ጋሪ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ። ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞቜ ኹውጭ ዚመጣ መንግሥታዊ ሃይማኖት ሊጫንብን አይገባም በማለታ቞ው ብቻ መሪዎቻ቞ው በአሞባሪነት ተፈርጀው በእስር ቀት እዚተሰቃዩ ነው። ህወሓት ኚጥንስሱፀ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያንፀ ዚኢትዮጵያ አንድነት መሰሚት ነው ኹሚል መነሻፀ በዋና ጠላትነት በመፈሹጅ መንበሹ ስልጣኑን ኚመቆጣጠሩ በፊትና በሗላ በካህናትፀ ምእመናንና በታሪክ ላይ ተኚታታይና ኹፍተኛ ወንጀል በመፈጾም ላይ ነው። ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ እንዲፈርሱ ሆነዋል። ተቃዋሚውን ዹሚደግፉ ዜጎቜ ሥራ አያገኙምፀ ኚሥራም ይባሚራሉ። እጩነት በእጣ ሆኗል። ዚምርጫ ቊርዱ በአገዛዙ ቁጥጥር ሥር ነው። ተቃዋሚዎቜ በነፃነት ተንቀሳቅሰው ማደራጀት አይቜሉም። ዓለም አቀፍ ዚምርጫ ታዛቢዎቜ ዚሉም። መገናኛ ብዙሃንን አገዛዙ ተቆጣጥሮታል። ጋዜጠኞቜ ተሰደዋል። ነፃ ዚፍትኅ ተቋም ዚለም። ሰብዓዊ መብትን እያፈነ ሜብርተኝነትን እዋጋለሁ በሚል ሰበብ ኚምዕራቡ ዓለም በሚያገኘው ዕርዳታ ተቃዋሚውን ያፍናልፀ ምዕራባውያንን ያሞኛል። እነኚህን መሰሚታዊ ቜግሮቜ በመሚዳት ለመጀመሪያ ጊዜ ዚአውሮፓ ዚጋራ ማህበር በምርጫው አንደማይሳተፍ ይፋ አድርጓል።
ኹላይ በጥቂቱ ዚተዘሚዘሩትን ኩነቶቜ ስንገነዘብ ዚምርጫው ውጀት አስቀድሞ መታወቁን ለማወቅ አዳጋቜ አይሆንም። አምባገነኑ ዚወያኔ አገዛዝ ይህንን ምርጫ ለይስሙላ ዲሞክራሲ ለውጭ መንግስታት ገጾ በሚኚት ለማቅሚብና ዓለም አቀፍ እውቅና በማግኘት ለቀጣይ ተመሳሳይ አስርተ ዓመታት ሀገሪቷን በመግዛት ዚስልጣን ጥሙን ሊያሚካበት ዹተዘጋጀ መሆኑን በግልጜ እንሚዳለን።

ህዝባቜን ላለፉት 24 አመታት ያለነጻነት በወያኔ ዹግፍ አገዛዝ ስር ፍዳውን በሚያይበት በዚህ ወሳኝ ወቀት ስርአቱን ለማስወገድ ህዝብን መሰሚት ያደሚገ ባንድ ማኹል ዚሚንቀሳቀስ ሁሉን አቀፍ ያማራጭ አካል በማቋቋም ዚህዝባቜንን እምቢተኝነት በተማኹለ ሁኔታ ለመምራት ዹተቃዋሚው ኃይል በሙሉ ባስ቞ኳይ ተሰባስቊ አማራጭ ኃይል ሆኖ መቅሚብ ዚወቅቱ ጥያቄ መሆኑን በመሚዳት ዚእንሰባሰብ ጥሪያቜንን እናቀርባለን።

ቀጥለው ዚተዘሚዘሩት ድርጅቶቜፀ ኹላይ ዚተገለፁትን ቜግሮቜ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ለነፃነቱ ዚሚያካሂደው ትግል ላይ ዚሚያስኚትሉትን አስኚፊ አደጋዎቜ ኚወዲሁ በመሚዳትፀ በዋነኝነት ደግሞ ብሄራዊና ወቅታዊ ጉዳዮቜን በማስቀደምፀ ዚአማራጭ ሃይል ባስ቞ኳይ ዚሚቋቋምበትን ሁኔታዎቜ ለማመቻ቞ት ኹፍተኛ ጥሚት በማድሚግ ላይ መሆናቾውን እዚገለፅንፀ ሁሉም ዚፓለቲካ ድርጅቶቜ ዚጉዳዩን አሳሳቢነት በመሚዳት ዚጋራ አቋም ላይ እንዲደርሱ ጥሪያቜንን በአክብሮት እናቀርባለን።

በዚህ አጋጣሚ ነጻነት ናፋቂ ለሆነው ወገናቜን ለማሳሰብ ዚምንወደውፀ ይህ መሰሚታዊ ጉዳይ ዚፖለቲካ ድርጅቶቜ ሀላፊነት ብቻ አለመሆኑን ተገንዝቩ አገርና ህዝብን ለነጻነት ለማብቃት አስፈላጊውን ተሳትፎ እንዲያደርግ አገራዊ ጥሪያቜንን በአክብሮት እናስተላልፋለን።

ይህን አደገኛ ዚቁልቁለት ጉዞ እንዲገታ በጋራ እንቁም!
ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዚጋራ ትግል ሾንጎ (SHENGO)
ዚኢትዮጵያ ብሄራዊ ዚሜግግር ምክር ቀት (ENTC)
ዚኢትዮጵያ ሙስሊሞቜ ሰላማዊ ንቅናቄ ደጋፊዎቜ ህብሚት (UEM-PMSG)
ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ብሄራዊ ንቅናቄ (EYNM)

↧
↧

እኮ ለምን? (አትክልት አሰፋ)

$
0
0

ይሄ ሁሉ ናዳ ይህ ሁሉ ውርጅብኝ
እንደ ዝናብ ወርዶ ዹሚቀጠቅጠኝ
ህሊናን አስቶ ዚሚደበድበኝፀ
ተስፋዚን አሟጊ፡
በጭካኔ ሚግጊፀ
ሙቀትና ብርዱ
አዘቅቱ ንዳዱ፡
ቜግር ቞ነፈሩ
ስቃይ ግርግሩ
መኚራው በርትቶ ዚሚያደናግሚኝ
ምንድነው ነገሩ? ግራ ግብት አለኝ!?
እኮ ለምን ሆነ?በኔ ጠነኚሚፀ
ጥላቻና ክፋት እዚተካሚሚ፡
ግድያና እስራት፡
ወኚባና እንግልት፡
ምነው እንዲህ ሆነ?
ተደጋገመብኝ፡ በሚታ ጚክነ፡፡
ዘመኑን አርዝሞ፡
ክንዱን አፈርጥሞ፡
በላዩ ላይ ቆሞፀ
ይሄ ሁሉ ናዳፀ ይህ ሁሉ ውርጅብኝ
እንደዝናብ ወርዶ ዹሚቀጠቅጠኝ
ህሊናን አስቶ ዚሚደበድበኝፀ
እኮ ለምንድን ነው!?
በኔ ላይ ዹሆነው?

መካን ወላድ ሆኜ፡ በሃዘን ቆዝሜ
ዘመናት አለፉ በተስፋ ደክሜፀ
ልጆቌን እያዚሁ በዘር ተኚፋፍለው፡
መተማመን ጠፍቶ በመሃኚላ቞ውፀ
ማዚት መመልኚቱፀ
በቃኝ ምርር አለኝ፡
መታገስ አቃተኝ፡፡
ዚንጹሃንን ደም በውስጀ ማድሚቁ፡
ዚእናቶቜን እንባ መዋጥ መሰልቀጡ፡
ያባቶቜን ቁጭት ቆሞ መመልኚቱ፡
መሾኹም አቃተኝ ኹበደኝ እውነቱ፡፡

አንዱ በሌላው ላይ በግዎታ ነግሶ፡
ሲፈልገው ገድሎፀ ሲፈልገው ኚሶ
ሲያሻው አንገላቶፀ ወይ ካገር አባሮ፡
ወንድም በወንድሙ በሃሰት መስክሮ
አሜቀንጥሮ ጥሎ እስር ቀት ወርውሮፀ

ይኖሩባት ምድርፀ ዚሚጠሯት ሀገር፡
መሆኑ ሰለቾኝ አሹገኝ ድንግርግር፡፡
እምባ ውሃ ሆኖ፡ ወደ ውስጀ ሲፈስ፡
ላብና ንጹህ ደም ምድሬን ሲያሚሰርስፀ
ዘመናት ተቆጥሚው ዘመኑ ሲመለስ፡
ውርጅብኙ አልቆመም
እስኚዛሬ ድሚስ፡፡
ይሄ ሁሉ ናዳፀ ይህ ሁሉ ውርጅብኝ፡
እንደዝናብ ወርዶ ዚሚቀጠቅጠኝ፡
ህሊናን አስቶ ዚሚደበድበኝፀ
አሁንስ በዛብኝ፡
መሾኹም አቃተኝ፡፡
ንጹህ ደም አፍስሶ
ሜዳ ላይ አርክሶ
አንዳንዱንም ኚሶ
ኚርቌሌ አበስብሶ
ልጁን ሚስቱን አቅፎ በሰላም አዳሪ
ህሊና ዹሌለው እውነትን ቀባሪ
በደም ዚሚቀልድፀ
በእንባ ዹሚዝናና ደሹቅ አይነ ሌባ
ዚ’ህዝብ ነኝ’ ብሎ ወጥቶ ዚሚገባ
ኚንቱ ዚሞላባት ዚኚንቱዎቜ ምድር
ተብሎ መጠራት ዚባለዶቜ ሃገር:
ይብቃ ይቁም አሁን
ኹመሃል ይቀስቀስ
ክምሩም ይደርመስ
ግፉ ይብቃ ይፍሚስ

ቀና ልበል ዛሬፀ ይድሚስ ለኔ ወጉ፡
ጹለማው ተገፎ ይጥራ ጥጋጥጉ፡፡
ሜይ 21/2015

↧

ዚሻቢያ “ዚተሀድሶ” ስትራተጂ አካሄዱና እንደምታው አክሊሉ ወንድአፈሚው

↧

ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ድምጜ አዳዲስ ዜና ዘገባዎቜን እና ካለፈው ዹቀጠለ ዚሰሃራ በሹሃ ተጓዊቜ ትዝታን ዚሚያስቃኝ ትሚካ ቀጣዩን ክፍል 3 እና 4 ይዘን ልናስደምጣቹ ተዘጋጅተናል

$
0
0

ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ድምጜ አዳዲስ ዜና ዘገባዎቜን እና ካለፈው ዹቀጠለ ዚሰሃራ በሹሃ ተጓዊቜ ትዝታን ዚሚያስቃኝ ትሚካ ቀጣዩን ክፍል 3 እና 4 ይዘን ልናስደምጣቹ ተዘጋጅተናል::ዚቀድሞ አንድነት ፓርቲ ምክትል አፈ ጉባዬ እና ዚፋይናንስ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ጞጋዬ አላምሹው ኚስደት ካሉበት ያሳለፉትን ዚፖለቲካ ሕይወት እና ዚአንድነት ፓርቲን በተመለኹተ ያደሚጉት ቃለመጥይቅ በዚህ ፕሮግራም ይቀርባል:: ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ!!

↧

አምስተኛው ዙር ዚድምጜ ዘሹፋ
ክንፉ አሰፋ

$
0
0

ዚ”ምርጫው” ድራማ እዚተተወነ ሳለፀ ዚቊርዱ ሊቀመንበር ዶ/ር መርጋ በቃና እና ምክትል ሊቀመንበሩ ዶ/ር አዲሱ ገብሚእግዚአብሔር ለአቩይ ስብሃት ስልክ ደወሉ።
“ሃሎ?”
“ሃሎ፣ አቩይ ስብሃት ኖት?”
“ነኝ፣ ምን ፈለግክ?”
“ዶ/ር መርጋ በቃና እና ዶ/ር አዲሱ ገብሚእግዚአብሔር ነን።”
“ቜግር መስማት አልፈልግም። ዚታዘዛቜሁትን አደሚጋቜሁ?”
“99.8% ህዝብ አልመሚጠንም። ግን በታዘዝነው መሰሚት ውጀቱን ገልብጠነዋል!”
“0.2% ብቻ ነው ዹመሹጠን ማለት ነው?”
“አዎን ጌታዬ። ሌላ ምን እንታዘዝ?”
“99.8% ህዝብ ዚስም ዝርዝሩን አንብብልኝ።” አሉ አቩይ ስብሃት እዚተባለ ይወራል።

አንድ ወዳጄ ስለ አቩይ ስብሃት ዹነገሹኝ ታወሰኝ። ሰውዬው ኹግመል እንኳን ዚማይሻል እንስሳ ብጀ ነው። ግመል ሳትጠጣ ለቀናት ትሰራለቜ አቩይ ስብሃት ደግሞ ሳይሰራ ቀኑን ሙሉ ይጠጣል። አብዛኞቹ ዚህወሃት አባላት እድሜያ቞ው እንደ አስተሳሰባ቞ው ስላሚጀ ጚዋታ቞ው ኹውሃ ጋር ነው። ኚውድ ውሃ ጋር! ድንጋይን ውሀ ያስጮኞዋል!
ሜዳው ዚኢህአዎግ፣ ዳኛው ኢህአዎግ፣ ታዛቢው ኢህአዎግ፣ ድምጜ ቆጣሪው ኢህአዎግ እንዲሆን ተደርጎ ዹተዘጋጀው “ምርጫ” እነሆ ተጠናቀቀ። በአፈና ዚታጀበው ምርጫ ጞጥ-እሚጭ ባለ ድባብ ተጠናቅቋል። ልክ አስገድደው እንደሚደፍሩ ወሮበሎቜፀ በሃይል ጠልፈው ያላቻ ትዳር እንደሚመሰርቱ ጉልበተኞቜ፣ ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ያለፍቃዱ እንደገና ዚአምስት አመት ዚትዳር ቁርኝት ውስጥ ገብቷል። ሌላ አምስት አመት። ሌላ ዚህወሀት ዘመን። ሌላ ዚጥርነፋ ዘመን! ሌላ ዚቁምራ ዘመን! ሌላ ዹመፈናቀል ዘመን! ሌላ ዚመሬት ነጠቃ ዘመን! ሌላ ዚስደት ዘመን!


ዚህወሃት ሰዎቜ አሁን ዚጭንቀቱ ምእራፍ ሁለት ላይ ና቞ው። በዛሬው እና በትላንቱ እለት ዚህወሃት ባለስልጣናት ተሰባስበው በፐርሰንቱ ምደባ ላይ ውይይት ይዘዋል። ዘሹፋው ላይ ሁሉም በ 100% ይስማማሉ። ምደባው ላይ ግን ቜግር አለ። አንዳንዶቹ ይህ ጉዳይ ተአማኝነት እንዲኖሚው ለተቃዋሚዎቹ ትንሜ መልቀቅ ይኖርብናል ሲሉ ለሎቜ ደግሞ ይህንን ሃሳብ ይቃወማሉ። ጥቂት ተቃዋሚዎቜን ፓርላማ እንዲገቡ መፍቀድ አለብን ዹሚሉ ተኚራካሪዎቜ “ሌባ ኹሰሹቀው ጥቂቱን ቢሰጥ” እንደማይጎዳው ይናገራሉ። ይህንን ዚማይቀበሉት ግን ዚተቃዋሚዎቜ በፓርላማ መግባት ራስ ምታት እንደሚሆንባ቞ው በስፋት መክሚዋል። 547 መቀመጫ ዹነበሹው ዚቀድሞው ፓርላማ ውስጥ እውነትን ዚያዘ አንድ ተቃዋሚ ብቻ ጭንቅላታ቞ውን በጥብጊት እንደነበር ሁሉም አይዘነጉትም። ይህንን በድጋሚ መፍቀድ አልያም ውግዘቱን በመቀበል መሃል ባለ አጣብቂኝ ውስጥ ኚርመዋል። ውጀቱን ኹሰሞኑ ይፋ ያደርገዋል ዶ/ር መርጋ።

ዚዘንድሮው ዝርፍያ ጀናማ አይደለም። ልክ እንደ ቊራት ዘ-ዲክታተር ፊልም ተወዳዳሪዎቜን እግር እግራ቞ውን እዚመቱ ለብቻ ሮጊፀ በራስ ዳኛ ዚድል ዋንጫ መሚኚብ? ይህ በእውነት በዚህ በ21ኛው ዘመን እጅግ ዚሚያሳፍር ተግባር ነው። ተቃዋሚ ሃይሎቜ በምርጫው ክርክር እና በትውልድ ስፍራ቞ው ላይ ዚነበራ቞ው ዚሕዝብ ድጋፍ ምን ያህል እንደሆነ በግልጜ በታዚበት ሁኔታ ህወሃቶቜ 100% አሾንፈናል ሲሉ ኚሌብነታ቞ው ይልቅ ንቀታ቞ው ጥርስ ዚሚያስነክስ መሆኑን ለአፍታ እንኳ አላስተዋሉትም። እጅግ ትንሜ ጭል ብላ ዚነበሚቜውን ዲሞክራሲ በምድሚ ኢትዮጵያ ገድለው፣ ኹፍነው ቀበሩት። አዲዮስ ዲሞክራሲ 
ፈሚንጆቜ ዚሚሉት አባባል አለ። “ለነብሰ-ገዳዮቜ ትክክለኛ ዲሞክራሲ ማለት ፍጹም አንባገነን መሆን ነው።”

“በ100% ድምጜ ተመርጠናል!” አሉ። ዚመሚጣ቞ው ህዝብ ዚቱ ይሆን? በአዲስ አበባ በነቂስ ወጥቶ “ወያኔ በቃን! መንግስቱ ይግደለን” ያለው ህዝብ ነው ወይንስ ለም መሬቱን ተነጥቆ ለባእድ ዚተሰጠበት ዹገጠር ህዝብ? በጋምቀላ፣ በቀንሻንጉል፣ በሁመራ ወዘተ ዹተፈናቀለው ህዝብ ነው ዚመሚጣ቞ው? ወይንስ አምቩ – ጉደርን እንደ ሱናሚ ያጥለቀለቀው ህዝብ ? ዚቱ ነው ወያኔን ዹመሹጠው? ኚስርአቱ ጋር ሆድና ጀርባ ዹሆነው ሙስሊሙ እምነት ተኚታይ ነው ወይንስ በእምነቱ ጣልቃ እዚገቡ ካድሬ ጳጳስ ዚሚሟሙለት ክርስቲያኑ ህብሚተሰብ? ማን ነው ህወሃትን ዹመሹጠው? እንደ ምጜዓት ለስደት እያኮበኮበ ያለው ስራ-አጥ ወጣት ነው ወይንስ በአነስተኛና ጥቃቅን ተደራጅቶ ድንጋይ ዹሚፈልጠው ወጣት ምሁር? መብራት እና ውሃ በፈሹቃ ያደሚጉበት ህዝብ ነው ዚመሚጣ቞ው?
 ለመሆኑ ስንት አመት ነው ህዝቡ ላይ እንዲህ ዚሚቀልዱት?

እነሱ ልባ቞ው በትእቢት ስለተወጠሚፀ ሌላው ህዝብ ዚማይመለኚትና ዹማይሰማ ይመስላ቞ው ይሆናል። ትእቢት ደግሞ ዚውድቀት ምልክት ናት። በመጀመርያ ዹውጭ ታዛቢዎቜ እንዳይገቡ ተደሚገ። ዝም! በምርጫው ወቅት ደግሞ ዹተቃዋሚ ፓርቲ ታዛቢዎቜን አሰሯ቞ው። አሁንም ዝም ተባለ። ኚዚያ ኮሮጆ እዚተሞላ ቀሹበና በቁም ያሰሯ቞ው ታዛቢዎቜን ምሜት ላይ ፈትተው እንዲፈርሙ አዘዝዋ቞ው። ዚተያያዙት አስገድዶ መድፈር ነውና አንዳንዱን አስገድደው በተሰሹቀ ዚድምጜ ሳጥን ላይ አስፈሚሟ቞ው። ምርጫ 2007 በዚህ ሁኔታ “ሰላማዊ፣ ፍትሃዊፀ ዲሞክራሲያዊና ዚህዝብ ተዓማኒነትን አግኝቶ” ተጠናቅቋል ሲሉ ፕ/ር መርጋ በቃና አበሰሩ። እኚህ ፕሮፌሰር ግን ህሊና ይኖራ቞ው ይሆን? ካላ቞ው በምን ለወጡት? በገንዘብ? ህሊና ስንት ያወጣል?
አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ኚምርጫው በኋላ ስላለው ነገር ብዙም አላሉም። ማን እንደሚያሞንፍ እና በምን ያህል ድምጜ እንደሚያሞንፍ አስቀድመው ዘግበው ስለነበር ውጀቱን መድገም ዹፈለጉ አይመስልም። አስቀድሞ ውጀቱ ዚታወቀበት ምርጫ መሆኑን አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ብቻ ሳይሆኑ፣ ራሱ ዚምርጫው ቊርድ በድሚ-ገጹ ላይ በግልጜ አስቀምጊት ነበር። ዚምርጫው ቊርድ በድሚ-ገጹ እንዳስቀመጠው ዚኢሕአዎግ 501 ተወዳዳሪዎቜ ዚተመዘገበለት ሲሆን መድሚክ 270፣ ዚሰማያዊ ፓርቲ 139 እጩዎቜ ብቻ እንዲኖራ቞ው ተደሚገ። ዚሰማያዊ ፓርቲ 200 እጩዎቜ በምርጫ ቊርዱ ተሰርዘውበታል። 108 እጩዎቜ አስመዝግቊ ዹነበሹው አንድነት ፓርቲም ስልታዊ በሆነ ዘዮ በቊርዱ እንዳይሳተፍ ታግዷል። ይህ እንግዲህ በሎተሪ ሰበብ ዚተገለሉትን ሳይጚምር ነው።
መቌም ይታገሉታል እንጂ አይታደሉትምና ቀኑ እስኪደርስ ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ባልፈለገው ሊገዛፀ ባላመነበት ሊዳኝ፣ ባልመሚጠው ሊተዳደር ነው። አሁንም ዝምታን መርጧል። ዝምታ ራሱን ዚቻለ መልስ ነው። በዝምታ ዚተዋጠቜ እያንዳንድዋ ሰኚንድ ቁርሟ ይዛ ማለፍዋም ግልጜ ነው። ማሰብ ላልተሳነው ሁሉ ዝምታ ያስፈራል። ምጥና ውሃ ሙላት በድንገት እንዲሉ ዝም ያለ ወራጅ ሲወስድ አይታወቅም። ጜዋም ሲሞላ ይፈስሳል 
አለም-አቀፉ ህብሚተሰብም ዝርፊያውን ስለለመደው ቜላ ብሎታል። ዚእንግሊዙ “ዘ ጋርዲያን” ጋዜጣ “ምርጫውን ለአብዛኛው ኢትዮጵያዊ እንደ አንድ ክስተትም አይቆጥሚውም።” ሲል፣ ሂዉማን ራይትስ ዎቜፀ አምነስቲ ኢንተርናሜናል፣ ፍሪደም ሃውስ፣ ሲፒጄ፣ ዚመሳሰሉት አለም አቀፍ ዚመብት ተኚራካሪ ተቋማት አፈና ዚሰፈነበት እና ነጻ ሜድያ በሌለበት ሁኔታ ዚሚካሄደው ይህ ምርጫው ፍሱም ኢ-ፍትሃዊ እንደነ ገልጞዋል። አልጃዚራ፣ ዋሜንግተን ፖስት፣ ኒውዮርክ ታይምስ ዚመሳሰሉ ታላላቅ ሜድያ ውጀቱ አስቀድሞ ዚታወቀ ምርጫ ሲሉ ሂደቱን በክፉ ኮንነውል።

ነገሩ ግልጜ ነው። ነጻ ሜድያ በሌለበት፣ ገለልተኛ ታዛቢዎቜ ባልተፈቀዱበት፣ ነጻ ዳኛ በልተመደበበት ነጻ ምርጫ አይታሰብ። ዚዘንድሮው ክስተት ህወሃት ዹዘሹፋ ደሹጃውን ያወሚደበት ምርጫ ነው። ኹሹቀቀ ዹዘሹፋ ስልት ወደ ግልጜ ዚውንብድና ተግባር።

ዹጀርመን ድምጜ እንግሊዝኛው ክፍል ኚምርጫው በኋላ ምንጮቜን ጠቅሶ ሲዘግብ “ታዛቢዎ ዹቁም እስር ላይ ስለነበሩ ወደ ውጭ ወጥተው ምርጫውን መታዘብ አልቻሉም” ብሏል። ዚሰራዊት እና ዚሚሊሜያ አባላት በዚምርጫ ጣብያው እዚተገኙ መራጮቜን እያስፈራሩ ዚተካሄደ ምርጫ በአለም ላይ ይህ ብቻ ነው። ዚምርጫ ዘመቻም በታጠቁ ሃይሎቜ ወታደራዊ ትእይንት ዚተካሄደው በኢትዮጵያ ብቻ ነው።
30 አመት ሙሉ ያል ህዝብ ፍቃድ በስልጣን መቆዚት ይሰለቻል። እነዚህ ሰዎቜ ዚምእተ አመቱን አንድ አራተኛ ዚሃገሪትዋን ሃብት ብቻ ሳይሆን ዚህዝብን ድምጜም እዚዘሚፉ ተቀመጡ። ባለፉት 24 አመታት በአሜሪካ አምስት ግዜ መንግስት ተቀይሯል። በሆላንድ 7 ግዜ መንግስት ወርዶ በህዝብ ድምጜ ሲቀዚር አይተናል። አፍሪካዊቷ ጋና አምስት ግዜ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ፣ ሶስት ግዜ ፓርላሜንታዊ ምርጫ አድርጋለቜ።  ያልታደልን ወይንም ያልታገልን እኛ ግን ለ30 አመታት በአንድ አንባገነን ተይዘናል።
ህወሃቶቜ በሩን ሁሉ ዘግተው ህዝቡን ወደማይፈለገው አመጜ እዚገፉት ነው። ያልተሚዱት ቢኖር አንደኛው በር ሲዘጋ ሌላኛው በር መኚፈት መቻሉን ነው። ዹ90 ሚሊዮን ህዝብን ድምጜ ሰርቀው፣ አንደበቱን ለጉመው ምን ያህል እንደሚዘልቁ ዹምናዹው ይሆናል። መቶ አመት ዹዘለቀ አንባገነን በታሪክ አልተኚሰተም።
ኹዚህ ቀደም ባስነበብኳቜሁ ቀልድ ጜሁፌን ልቋጭ። አንድ ዚህንድ ኢንቚስተር አዲስ አበባ ዮሎፍ ቀተ ክርስቲያንን ዚቀብር ስፍራ አይቶ በሊዝ ሊገዛ ፈለገ። ዚአዲስ አበባ ባለስልጣናትን ጠርቶ እንዲሞጡለት ጠዚቀ። ባለስልጣናቱም መልሰው ሌሎቜ ቊታዎቜ ሳያልቁ ዚቀብር ስፍራ ለግዜው እንደማይሞጡለት ነገሩት። ህንዱ መለሰና መኚራ቞ው። “እኛ አገር ሰው ሲሞት እናቃጥላለን እንጂ አንቀብርም። ለምን ይህን ለም ቊታ ታባክናላቜሁ?” አላ቞ው። ባለስልጣናቱም መለሱ፣ “እኛ አገር ደግሞ ሰውን በቁሙ እንጂ ሲሞት አናቃጥልም!”

↧
↧

ዹ2007ቱ ሀገራዊ ምርጫ አካሄዱና አፈጻጞሙም ነጻና ፍትሀዊ ስላልሆነ ውጀቱን ሾንጎ አይቀበለውም።

$
0
0

ገና ኚጅምሩ፣ ዹተቃዋሚ ፓርቲወቜን በመበታተን፣ መሪዎቜንና አባላቶቻ቞ውን በማሰር፣ በማሳደድና በማዋኚብፀ ነጻ ዚሃሳብ ልውውጥ እንዳይኖርና አማራጭ ሃሳቊቜ ለህዝብ እንዳይደርሱ ነጻ ዹመገናኛ ብዙሃን ጋዜጠኞቜንና ጊማራውያንን በግፍ ወደ እስር ቀት በመወርወርና ዚሚወዷትን ሀገራ቞ውን ጥለው እንዲሰደዱ በማድሚግፀ ኹአገዛዙ ጋር እጅና ጓንት ሆኖ በጭቆና መሣርያነት ዚሚያገለግለውን ዚምርጫ ቊርድ በመጠቀም ተቃዋሚ ፓርቲዎቜን በማፈራሚስ ዹጀመሹው ምርጫ ተብዚ በትናንቱ እለት ተካሂዷል።

በዚህ ምርጫ ተብዚ፣ ዚተስተዋለው ድባብ ተቃዋሚ ዚፖለቲካ ድርጅቶቜን መፈናፈኛ በሚነሳ ሁኔታ እግር ኚወርቜ አስሮ በተለያዚ አሻጥር ቀፍድዶ እንዳይንቀሳቀሱ ዚሆነበት አካሄድ በግልጜ ሲታይ በአኳያው ደግሞ ዹገዠው ፓርቲ ዚሀገሪቱን ሀብትና ንብሚት ገደብ በለለው ሁኔታ ለራሱ ጠቀሜታ እንደፈለገ ሲያውላ቞ው ተስተውሏል።

በሃገሪቱ ሙሉ ለሙሉ ማለት በሚቻል መልክ ገዠው ፓርቲ በብ቞ኛነት ተወዳዳሪም፣ አወዳዳሪም፣ ታዛቢም ዚሆነበትና ዹገዝው ወያኔ/ኢህአዎግ ካድሬዎቜ በምርጫ ጣቢያዎቜ በመገኝት ድምጹን ለመስጠት ዹተሰለፈን ህዝብ አንድ ባንድ ዹገዠውን ቡድን እንዲመርጡ በማሰፋራራት፣ አልፎ ተርፎም “እዚህ ላይ ምልክት አድርጉ” በማለት ኚገዥው ቡድን ውጭ ማንንም እንዳይመርጡ በማድሚግ ተግባር ላይ ተሰማርተው እንደዋሉ ተስተውሏል።

ዚሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስ቎ር “ማን እንዳሞነፈ መናገር ዚሚቜለው ምርጫ ቊርድ ብቻ ነው” ብሎ እንዳላለ ሁሉ ዚድምጜ መስጠቱ ሂደት እንደተጠናቀቀ ብዙም ሳይቆይ ዚራሱን ትእዛዝ ጥሰው ዚገዥው ቡድን ደጋፊ ዹሆኑ መገናኛ ብዙሀን (ለምሳሌ አይጋ ፎሹም ዹተሰኝው ድሚገጜ) “አዲሰ አባበን ሙሉ በሙሉ ኢህአዎግ አሜንፏል፣ ዚመድሚክ መሪዎቜ ዚሆኑት ፕሮፊሰር በዹነ ጎጥሮስ እና ዶክተር መሚራ ጉዲና ተሞንፈዋል፣ ኢህአዎግ በመላው ሀገሪቱ አሜንፏል” . ወዘተ ዹሚል ዜና አሰራጭተዋል።
እጅግ ዚሚያሰገርመው ደግሞ፣ ኢህአዎግ አሜንፏል፣ ዹተቃዋሚ ድርጅቶቜ አመራር አባላትም ተሾንፈዋል ዚተባለው፣ ድምጜ ተቆጥሮ ሳያልቅ መሆኑ ነው።

ይህ ታዲያ ዚሚያሳዚው ዹተሰጠው ድምጜ ዋጋ እንዳልነበሚው እና በያንዳንዱ ዚምርጫ ጣቢያ ማን እንደሚያሞንፍ በወያኔ/ ኢህአዎግ እና ይህንኑ ጉዳይ ለማስፈጞም ባቋቋመው ምርጫ ቊርድ ቀድሞ እንደተወሰነ ነው።
ባጠቃላይ ፣ ቅድመ ምርጫ ዹነበሹው አካሄድ፣ በምርጫ መዳሚሻ ዚተኚሰቱት ዚመብት ሚገጣዎቜ እና በምርጫው ቀን ዹተኹሰተው ሁሉ ፣ ምርጫው በምንም መልኩ ፍትሃዊም ሆነ ዎሞክራሲያዊ እንዳልነበሚ በትክክል ዚሚያሳዩ ነበሩ። በአጠቃላይ ፣ ምርጫ ተብዚው በምንም መልኩ አንድን ምርጫ ነጻና ፍትሃዊ ለማለት ዚሚያሰቜሉ መመዘኛዎቜን አላሟላም።

ይህ ሁኔታ በሀገራዊ ደሹጃ ለአምስተኛ ጊዜ መደገሙ አሳፋሪ ብቻ ሳይሆን አሳዛኝና እጅግ ታላቅ ቁጣን ዚሚቀሰቅስ ተግባር ነው። ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዚጋራ ትግል ሜንጎ (ሜንጎ) ዹዚህን ዹተጭበሹበሹ ምርጫ አካሄድና ውጀት ሙሉ በሙሉ አይቀበለውም። ዹተፈጾመውን ዚመብት ሚገጣም ያወግዛል።

ዚህዝብን መብት እዚሚገጡ ተደላድሎ በስልጣን ለመቀጠል ማሰብ ኚታሪክም ኚአካባቢ ሁኔታም አለመማር ነው።ህዝብ መብቱ ሲሚገጥ አንገቱን ደፍቶ መገዛቱን ይቀጥላል ብሎ መገመት ደግሞ ኚተራ ትምክህት ዹሚመነጭ ቅዠት ብቻ ነው። ወያኔ/ኢህአዎግ እና ተባባሪው ዚምርጫ ቊርድ ይህ ዚህዝብ መብት መጣስ ሊያስኚትለው ለሚቜለው ማንኛውም አደጋ ተጠያቂ እንደሚሆኑ ኚወዲሁ ልናሰምርበት እንወዳለን።
ለኢትዮጵያ ህዝብ እና ዚህዝባቜንን መብት ለማስኚበር ለተንቀሳቀሱ ድርጅቶቜ ሁሉ ያለንን አክብሮት እዚገለጜን ዹተነጠቅነውን መብታቜንን፣ ዚታፈነውን ድምጻቜንን፣ ዹተገፈፍነውን ዚዜግነት ክብራቜንን ለማስኚበር፣ ዹጋር ትግሉን በአዲስ ስሜት፣ በህ ብሚትፀ አስፈላጊውን መስዋዕት በመክፈል ቆርጠን አንድንቀጥል ጥሪያቜንን እናሰማለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ
ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ዚጋራ ትግል ሾንጎ

↧

ዚምስራቜ ወያኔ! ምስር ሳይሆን እርሳስ ብላ!? ዚጎንቻው

↧

በሀገራቜን ኢትዮጵያ ስላለው ሁለንተናዊ ቀውስ በመወያዚት ሁሉን አቀፍ ዚአማራጭ ኃይል ዚሚቋቋምበትን ሂደት ለመምኹር ኹጁላይ 2-3 በዋሜንግተን ዲሲ ዹሀገር አድን ጉባዔ በጋራ ይዘጋጃል

$
0
0

ዚኢትዮጵያ ብሄራዊ ዚሜግግር ምክር ቀትፀ ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ዚጋራ ትግል ሞንጎፀ ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ብሄራዊ ንቅናቄና ዚኢትዮጵያ ሙስሊሞቜ ሰላማዊ ንቅናቄ ደጋፊዎቜ ኅብሚት ጋር በተደሹጉ ተኚታታይ ዚሁለትዮሜ ውይይቶቜና ስምምነቶቜ፡ ህዝባቜን ላለፉት 24 ዓመታት ያለነፃነት በህወሓት ዹግፍ አገዛዝ ሥር ፍዳውን ዚሚያይበት ዋና ምክንያትፀ ሕዝብን መሠሚት ያደሚገና ብሄራዊ ጥቅምን ያስቀደመፀ በአንድ ማዕኹል ዚሚንቀሳቀስ ሁሉን አቀፍ ዚአማራጭ አካል በማቋቋም ሥርዓቱን ለማስወገድ አስፈላጊውን ትግል ዚማድሚግ ቁርጠኝነቱ በተቃዋሚው ጎራ ያለመኖሩ ዋና ጉዳይ መሆኑን ዚጋራ ግንዛቀ ላይ ደርሰናል። ይህን አዙሪት በመስበርና ሁኔታዎቜን በጋራ በማመቻ቞ት ዚአማራጭ ኃይሉ በአስ቞ኳይ እንዲቋቋም ስምምነት ላይ መድሚሳቜንንም በተኚታታይ ባወጣና቞ው ዚሁለትዮሜ መግለጫዎቜ ይፋ መሆናቾው ዚሚታወስ ነው።

ሥርዓቱ ባሳለፍነው ሳምንት ውጀቱ ምን ሊሆን እንደሚቜል አስቀድሞ ዚታወቀውን ዚህወሓት/ኢህአዎግ ዚምርጫ ድራማ በማካሄድፀ ሕዝብን ተስፋ በማስቆሚጥና ግፉን አሜን ብሎ በመቀበልፀ ቀደም ሲል ሲያደሚግ ዹነበሹውን ሀገር ዚማፈራሚስ ሂደትና ዚሕዝብን ስቃይ ዚሚያበዛ አገር በቀል ዚአፓርታይድ አገዛዝ ለቀጣይ አምስት አመታት ለማስቀጠል ዚሚያስቜለውን ህጋዊ ሜፋን በማመቻ቞ት ላይ በሚገኝበት በዚህ ወሳኝ ወቅትፀ አገር አድን ዹምክክር ጉባዔ በማድሚግ በሕዝብ ተቀባይነትና ታማኝነት ያለው ሁሉን አቀፍ ዚአማራጭ ኃይል በማቋቋም ትግሉን በተጠናኹሹ ሁኔታ መቀጠል ወቅታዊና አስ቞ኳይ ነው።

ኹላይ በመግቢያው ላይ ዚተዘሚዘሩት ድርጅቶቜፀ ኚተለያዩ አክቲቪስቶቜና ታወቂ ግለሰቊቜ ጋር በመሆን ኹጁላይ 2-3 ዹምክኹር ጉባዔ በጋራ ያዘጋጃሉ። ዚጉባዔውን ውጀት ለማሳወቅ ሕዝባዊ ስብሰባም ይዘጋጃል። ዚመሰብሰቢያ ቊታፀ ዝርዝር ፕሮግራሞቜና ተያያዥ እንቅስቃሎዎቜን በተኚታታይ እንደምናሳወቅ ኚወዲሁ መግለጜ እንወዳለን።

ስለዚህፀ መላው ዚኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ዚፓለቲካ ድርጅቶቜና ዚሲቪክ መኅበራት፣ ዹነገ ሀገር ተሚካቢ ዚሆናቜሁ ወጣቶቜፀ በሀገራቜን ነፃነት ሠላም እኩልነትና ፍትኅ ይሰፍን ዘንድ ዚምትተጉ ዚ቎ሌቪዥንና ዚሬዲዮ አዘጋጆቜ፣ ዚፓልቶክ ክፍሎቜ፣ ጋዜጠኞቜ፣ አክቲቪስቶቜ፣ ምሁራንና ዹሀገር ሜማግሌዎቜ፣ ዚእምነት አባቶቜፀ እንዲሁም ለሀገር ደህንነት ተቆርቋሪ ዚሆናቜሁ ዜጐቜ በሙሉፀ ዚሚገነባው ዚተባበሚ አማራጭ ኃይል ባለቀት እንደመሆናቜሁ መጠን ዚሂደቱ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆንፀ በሀገራቜን ነፃነት እውን እንዲሆን በሚደሹገው ወሳኝ ሕዝባዊ ትግል ውስጥ ዚበኩላቜሁን አስተዋፅዖ ታበሚክቱ ዘንድፀ እንዲሁም በሕዝባዊ ስብሰባው ላይ ንቁ ተሳትፎ እንድታደርጉ አደራ እያልን በአክብሮት ሀገራዊ ጥሪያቜንን እናቀርባለን።

ይህ አደገኛ ዚቁልቁለት ጉዞ እንዲገታ በጋራ እንቁም!

ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዚጋራ ትግል ሾንጎ (SHENGO)
ዚኢትዮጵያ ብሄራዊ ዚሜግግር ምክር ቀት (ENTC)
ዚኢትዮጵያ ሙስሊሞቜ ሰላማዊ ንቅናቄ ደጋፊዎቜ ህብሚት (UEM-PMSG)
ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ብሄራዊ ንቅናቄ (EYNM)

ግንቊት 22ፀ 2007 (May 30, 2015)

↧
Viewing all 1809 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>