Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all 1809 articles
Browse latest View live
↧

ዶክተር ዳኛ቞ው አሰፋ በብጣቂ ወሚቀት ኚዩኒቚርስቲ ተባሚሩ

$
0
0

እርሳ቞ው ግን አሁን ገና ኢትዮጵያዊ ሆንኩ ፣ምኚንያቱም ኢትዮጵያዊ መብ቎ ዚሚሚገጥ ማለት ነውና››እያሉ ነው
‹ዳኛ቞ው፣ ዩኒቚርስቲውን እንደ ደጀንና ገዥ መሬት ተጠቅሞ መድፍ ሲተኩስብን ቆይቷል›› ሲሉ ዚነበሩ ህወሓቶቜ አሁን አንጀታ቞ው ቅቀ ሳይጠጣ አይቀርም፡፡ ዚፍልስፍና ምሁሩን ኚዩኒቚርስቲው ማባሚር ቜለዋልና፡፡ስንብታ቞ውን አስመልክቶ ዳኛ቞ው ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት ‹‹ውሳኔው ፖለተካዊ መሆኑነን ማንም አይስተውም››፡፡

አደባባይ በመውጣት ሀሳባ቞ውን በመግለጜ ተለይተው ዚሚታወቁት ዳኛ቞ው በዩኒቚርስቲው ለሰባት ዓመታት አስተምሚዋል፡፡ ዶክተሩ በአደባባይ በሚያደርጓ቞ው ተሳትፎዎቜ ደስተኛ ያልነበሩት ህወሓቶቜ ለዳኛ቞ው በሚቀርቧቾው ሰዎቜ አማካኝነት ኚድርጊታ቞ው እንዲቆጠቡ ካልሆነም አገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ሲወተውቷ቞ው ቆይተዋል፡፡

ኚወራት በፊት በዩኒቚርስቲው ዚሚያቆያ቞ውን ኮንትራት ለመፈሹም ሲንቀሳቀሱ ዶክመንታ቞ው ኚዩኒቚርስቲው መዝገብ ክፍል ተፈልጎ መጥፋቱ ሰዎቹ ሊያባሚሯ቞ው እንደወሰኑ ፍንጭ እንደሰጣ቞ው በወቅቱ መናገራ቞ው አይዘነጋም፡፡
በዩኒቚርስቲው ለሰባት ዓመታት ላስተማሩ መመህራን ዹሚሰጠው ዚእሚፍት ጊዜ ተፈቅዶላ቞ው እሚፍት ለመውጣት ሲጠባበቁ በብጣቂ ወሚቀት መሰናበታ቞ው እንደተነገራ቞ው ዚሚገልጹት ዳኛ቞ው ‹‹አሁን ገና ኢትዮጵያዊ መሆኔን አወቅኩ ምክንያቱም መበቮ ተሚገጠ››በለዋል፡፡

ዶክተር መሚራ ጉዲና ትናንት ምሜት በተላለፈው ዚምርጫ ክርክር ወቅት‹‹ኢህአዎግ ምሁራንን አይወድም››በማለት መናገራ቞ውን ዚሚያስታውሱ ዚዳኛ቞ው ስንብት መንስኀ ምን እንደሆነ በደንብ ይገነዘቡታል፡፡1902030_10203956954505103_125485830015920358_n

ዶ/ር ዳኛ቞ው አሰፋ ኚሊስት ዐሥርት ዓመታት ዚአሜሪካ ቆይታ በኋላ በሚሌኒዹሙ መባቻ ወደ አገራ቞ው ተመልሰው ላለፉት ሰባት ዓመታት በማስተማር ሥራ ላይ ቆይተዋል፡፡ ምሁሩ በዋናነት በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ዚፍልስፍና መምህር ቢኟኑም በሕግ ፋክልቲ፣ በሮንተር ፎር ሂዩማን ራይትስ፣ በኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም፣ በአምስት ኪሎ ዚሳይንስና ቮክኖሎጂ ፋክልቲ፣ በ቎አትሪካል አርትስና በያሬድ ዹሙዚቃ ት/ቀትም አስተምሚዋል፡፡ ለሰባት ተኚታታይ ዓመታት በተጠቀሱት ዚትምህርት መስኮቜ በተለያዚ ጊዜ ሲያስተምሩ ቢቆዩም ኚጠዚቁት ዚዓመት ዕሚፍት(sabbatical leave) ጋር ተያይዞ ኚዩኒቚርስቲው መሰናበታ቞ው ተሰምቷል፡፡ በዚኜ ዙሪያ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ኚዶ/ር ዳኛ቞ው ጋራ ተኚታዩን አጭር ቆይታ አድርጓል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ እና በእርስዎ መካኚል ምንድን ዹተፈጠሹው?

ኚአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ አስተዳደር ጋራ በኹለት ጥያቄዎቜ ዙሪያ ዚማይታሚቅ ልዩነት ተፈጥሯል፡፡ በመጀመሪያ ዚዩኒቚርስቲው ዚሎኔት ሕግና ዚቅጥር ውሌ ላይ በግልጜ እንደሰፈሚው÷ አንድ መምህር ለስድስት ዓመት በተኚታታይ ኚአስተማሚ፣ ለአገለገለበት ዘመን ዚአንድ ዓመት ዚጥናትና ምርምር ዕሚፍት (sabbatical leave) እንደሚሰጠው ተደንግጓል፡፡ ኟኖም ግን ዩኒቚርስቲው ‹‹ዚጡሚታ ሥርዓተ – ሒደቱን አላሟላኜም›› በሚል በሕጉ ፊት ዹማይጾና ሰበብ ፈጥሚው ይገባኻል ብለው ኚፈቀዱልኝ በኋላ መልሰው ነጥቀውኛል፡፡ ለማንኛውም መምህር ሥርዓተ ሒደቱን ዚማስፈጞም ሓላፊነት ዹሰው ሀብት አስተዳደሩ ድርሻ ኟኖ ሳለ እኔን ተጠያቂ ማድሚጋ቞ው ብዙዎቜን አስገርሟል::

በነገራቜን ላይ ዚጥናት ዕሚፍት ፈቃዮን ዚጠዚቅኹት ኚሊስት ዓመት በፊት፣ ስድሳ ዓመት ሳይሞላኝ ነበር፡፡ በዚሰበቡ ሲጓተት ስለቆዚ ወደ ስድሳ ዓመቱ ገደብ ደሚስኹ፡፡ ጉዳዩ ወደ ማኅበራዊ ፍርድ ቀት ኚመሔዱ አስቀድሞ ውስጣዊ ተቋማዊ መፍትሔ ለማበጀት ወደ ዩኒቚርስቲው ዚቊርድ ሰብሳቢ ቀርቩ ምላሜ ስጠባበቅ ኚሊስት ወራት በላይ ተቆጥሚዋል፡፡

ዚሥራ ውሌን በተመለኚተ፣ ዚፍልስፍና ትምህርት ክፍል ዚእኔን ዚአገልግሎት ቆይታ እንደሚፈልግና በተለይም በቅርቡ ለሚጀምሹው ዚሊስተኛ ዲግሪ መርሐ ግብር ተሳትፎዬ እንደሚጠቅም በሙሉ ድምፅ ተስማምቶ በመወሰኑ ውሌ እንዲራዘም ለማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሜን ጜፎልኝ ነበር፡፡ ዚማኅበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ሓላፊዎቜ በተሰበሰቡበት፣ ኮሚሜኑ ጉዳዩን በአጀንዳ ይዞ ኚተወያዚበት በኋላ ዚፍልስፍና ትምህርት ክፍሉን ጥያቄ ዳግመኛ በሙሉ ድምፅ ተስማምቶበት፣ ውሳኔው በማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኑ በፕ/ር ወልደ አምላክ በዕውቀት በኩል ዚዩኒቚርስቲው ፕሬዝዳንት ይኹንታ቞ውን እንዲሰጡበት(እንዲያጞድቁት) ተጠይቆ ነበር፡፡ ፕሬዝዳንቱ ግን ኚአራት ወራት ያኜል ቞ልተኝነት በኋላ ‹‹ወሚቀቱ ይመጣለታል›› በሚል ለተኚታዩ ሎሚስተር እንዳልደለደል በአዲሱ ዲን በኩል ለትምህርት ክፍሉ ሊቀ መንበር መመሪያ አስተላለፉ፡፡ መመሪያው ዚእኔን መሰል ጥያቄ ባቀሚቡ ሌሎቜ መምህራን ላይም ዹተላለፈ ነበር፡፡ ኚሊስት ወራት በላይ ደመወዜን ይዘው መክፈል ኹአቆሙ በኋላ ‹‹ለሚመጣው ሎሚስተር አትመድቡት›› ማለት በአካዳሚያ ቋንቋ ግለሰቡ ተሰናብቷል ማለት ነው፡፡

በመሠሚቱ፣ ዚትምህርት ክፍሌና አካዳሚክ ኮሚሜኑ ዚሥራ ውሌን መራዘም ተስማምተው ላቀሚቡት ጥያቄ ሲኟን እንደወጉ ማጜደቅ አልያም በአስ቞ኳይ ውሳኔን ማሳወቅ ሲገባ ፕሬዝዳንቱ ኚሊስት ወራት በላይ ማቆዚታ቞ው ኢ-ሕጋዊ ነውፀ ሕጉን ጠብቆ በወጉ ለቀሹበ ጥያቄ ኚሊስት ወራት በላይ ምላሜ አለመስጠት እብሪት፣ ትዕቢትና ማናለብኝነት እንጂ ሌላ ሊኟን አይቜልምፀ በተመሳሳይ ወቅት አንድ ዐይነት ጥያቄ በደብዳቀ ኚአቀሚብነው መምህራን መካኚል፣ ለምሳሌ ኹኛው ትምህርት ክፍል ዶ/ር በቀለ ጉተማ በሥራው እንዲቀጥል በቃል ትእዛዝ ፈቅደው፣ ለእኔ በአግባቡ ውሳኔ ሳይሰጡ ‹በሚቀጥለው ሎሚስተር እንዳትመድቡት ማለት ዚአድልዎ አቀራሚብ ብቻ ሳይኟን በዘፈቀደና በግፊት ዚሚካሔድ አመራር መኟኑን ያሚጋግጣል፡፡ በሌላ በኩል፣ ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር አድማሱ ዩኒቚርስቲውን ለመምራት ያላ቞ውን ብቃት ኹዝህ ቀደም በአደባባይ ስለጠዚቅኹ በቂም በቀልና ኹን ብለው እኔን ለመጉዳት ዚደሚሱበት ውሳኔ ነው፡፡

ዚጥናትና ምርምር ዕሚፍት(sabbatical leave) በተመለኹተ በጊዜው ዚካሌጁ ዲን ዚነበሩት ዶ/ር ገብሬ ይን቎ሶ ዚፕሬዝዳንቱን ፍላጎት ተኚትለው ኹላይ እንደጠቀስኹት ዚሰጡኝን ፈቃድ መልሰው ነጥቀውኛል፡፡ ጉዳዩን ለማዚት ሥልጣን ወዳለው ፍርድ ቀት ኚማምራ቎ በፊት፣ ዚፕሬዝዳንቱን ምላሜ ኚወዲኹ ባውቀውም አቀቱታዬን ዚግድ ለእርሳ቞ው ማቅሚብ ነበሚብኝ፡፡

በኮሌጁ ዚቀድሞ ዲን ውሳኔ ላይ ኚዐሥር ገጜ ያላነሰ አባሪ ሰነዶቜ አያይዀ ጠዋት ላቀሚብኹት አቀቱታ፣ ኚቀትር በኋላ ‹‹በጥልቅ መርምሚን›› በሚል በአንድ መሥመር ዚኮሌጁ ውሳኔ እንደማይሻር ዚሚገልጜ ፌዝና ዚቀልድ ምላሜ ነው ዚተሰጠኝ፡፡ ይህ ዚሚያሳዚው ፕሬዝዳንቱ ለዩኒቚርስቲው መምህራን ኚበሬታ ዹሌላቾውና አመራራ቞ውም ኚሞራላዊነት ዚተራቆተ መኟኑን ነው፡፡ እኔ ግን ታዋቂው አርበኛ አበበ አሹጋይ በአንድ ወቅት በፋሜስት ጣልያንና በባንዳ ለተኚቡበት ዚተራቡ ጭፍሮቻ቞ው ‹‹ሞተን አንጠብቃ቞ውምፀ ተሚጋግታቜኹ ብሉ›› እንዳሉት፣ ኚማባሚር ያልተናነሰ ዹዘገዹ አንድ ብጣሜ ወሚቀት ገና ለገና ይመጣል ብዬ ሞቌ አልጠብቃ቞ውም፡፡

ዚጡሚታ ጊዜያ቞ው ደርሶ ለማራዘም ዹተፈቀደላቾው መምህራን አሉ ወይ? ማለትም በዩኒቚርስቲው አሠራር ዚጡሚታ ጊዜያ቞ው ዹደሹሰ መምህራን ውላቾውን ማራዘም ይቜላሉ ወይ?

በተለምዶ ስድሳ ዓመት ዹሞላቾው መምህራን ዹውል ማራዘሚያ ጊዜ ይጠይቃሉ፡፡ እኔ ዹማውቃቾውና በተደጋጋሚ ዹተጹመሹላቾው መምህራንም አሉ፡፡ በጣም አስገራሚና በግቢው አነጋጋሪ ዚኟነው ዚእኔና ዚዶ/ር መሚራ ጉዲና ዹውል ማራዘሚያ ጊዜ መኹልኹሉ ነው፡፡

ዚዚኜ ኹሉ መነሻ ምንድን ነው ብለው ይገምታሉ?

ኚኹሉ በፊት ዚእኔ መኹልኹልና መሰናበት ኚፖሊቲካ እይታ አኳያ ዹመነጹ መኟኑ ማንም አይስተውም፡፡
ማለት 
በዩኒቚርስቲው በማስተማር ሥራ በቆዚኹባ቞ው ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ በጜሑፍና በተለያዩ መድሚኮቜ ዹማደርጋቾው ዚዐደባባይ አእምሯዊ እንቅስቃሎዎቜ አልተወደደዱም፡፡ እንዲያውም ለሹመኞቜ ቅርበት ያላ቞ው አንዳንድ ወዳጆቌ እንዳጫወቱኝ፣ ‹‹ዳኛ቞ው፣ ዩኒቚርስቲውን እንደ ደጀንና ገዥ መሬት ተጠቅሞ መድፍ ሲተኩስብን ቆይቷል›› ተብዬአለኹ፡፡ በርግጥ ይህ ዓይነቱ አቋም ኹተወሰደ በኋላ በሥራ ገበታዬ እንድቀጥል አለመደሹጉ አይገርመኝም፡፡

ለሰባት ዓመት ካስተማሩበት ዩኒቚርስቲ በዚኜ መልኩ ሲሰናበቱ ምን ተሰማዎ?

እንደ እውነቱ ኚኟነ ዹተደበላለቀ ስሜት ነው በውስጀ ዚተፈጠሚው፡፡ በመጀመሪያ ደሚጃ፣ ይህ ነገር ኚሰባት ዓመት በኋላ መኟኑ አስደስቶኛል፡፡ ይኾውም ዚመጣኹበትን ዚማስተማር ዓላማ ኚሌሎቜ ባልደሚቊቌ ጋር በመኟን ለመስኩ ተተኪና ምሉዕ ዚኟኑ ተማሪዎቜ ለማፍራት በመብቃታቜን አስደስቶኛል፡፡ ይህ ክልኹላና ስንብት በቂ ምሩቃን ባላፈራንበት ኚሊስትና ኚአራት ዓመት በፊት ቢኚሠት ኖሮ አዝን ነበር፡፡
በኹለተኛ ደሚጃ፣ ‹ዚዓመት ዕሚፍት(ሳባቲካል) አይሰጥኜምፀ ኚእንግዲኜ ማስተማርም አትቜልም› ስባል ለራሎ በጥልቀት ተሰምቶኝ ያልኹት፣ ‹‹አኹን ገና ኢትዮጵያዊ ኟንኩፀ ኢትዮጵያዊ ማለት መብቱ ዚሚሚገጥ ማለት ነው›› ዹሚል ነበር፡፡ በዚኜ ሰባት ዓመት ቆይታዬ ኚአሜሪካ ሳልፈታ ይዠው ዚመጣኹት ዚነፃነትና ዚመብት አቅዋም፣ ኚአገራቜን ፖሊቲካዊ ነባራዊ ዕቀባ በተፃራሪው እንደ ልቀ እንድተቜና ያለገደብ እንድናገር አስቜሎኝ ነበር፡፡ አኹን ግን ሥርዓቱ ‹ይኌ አሜሪካ አይደለምፀ እንደ ጎሚቀትኜ ሳይኟን እንደቀትኜ እደር› ተብዬአለኹ፡፡

ይህን ስል ግን፣ እኔ በዕድሜዬ ዚምወልዳ቞ው ልጆቜ በኟነ ባልኟነ ክሥ ወኅኒ ቀት ተወርውሹው ባሉበት ኹኔታ ኚሥራ አባሚሩኝ ብዬ ዚማለቅስ ሰው አይደለኹም፡፡ በእኒኜ ብሩህ ተስፋ ባላ቞ው ወጣቶቜ ላይ ኹደሹሰው አንጻር ሲታይ መብ቎ መሚገጡ እውነት ቢኟንም፣ ዚአገራቜን ተሚት ‹‹እናቱ ውኃ ልትቀዳ ዚወሚደቜ ልጅና እናቱ ዚሞተቜበት ልጅ አንድ ጋር ቆመው ያለቅሳሉ›› እንደሚባለው ይመስልብኛል፡፡
በመጚሚሻም በአንድ በኩል፣ በውጭ ለብዙ ዓመት ቆይቌ ስመጣ ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ዚት ኹሹምክ ሳይለኝ ቜሎታዬ በሚፈቅድልኝ ቊታ ሥራ ሰጠኝ፡፡ ለዚኜ ትልቅ ምስጋና ነው ዚማቀርበው፡፡ ኟኖም በሌላ በኩል ዚውስጥ አስተዳደሩና ዹውጭ ዚፖሊቲካ ኃይሎቜ በመተባበር መክሹው ኚሕዝብ ባገኘኹት ቞ርነት ላይ ወይነውብኛል!

ኚዚኜ በኋላስ ምን ዓይነት ሥራ ላይ ለማተኮር ያስባሉ?

ይህን ጥያቄ ዎሞክራሲና ዹሕግ ዚበላይነት ባለበት አገር ብትጠይቀኝ ኖሮ፣ ጉዳዩ በራሎ ዹሚወሰን በመኟኑ አኹኑኑ እመልስልኜ ነበርፀ ነገር ግን እንደ ቀትኜ እደር ተብዬአለኹና ዚጥያቄው ምላሜ በእኔ ብቻ ዹሚወሰን አይደለም፡፡ እንዲያውም ጥያቄው በአንድ ወቅት ዐፄ ኃይለ ሥላሎ አሉ ዚተባለውን ያስታውሰኛል፡፡ አንድ ሹም ጃንሆይ ፊት ቀርበው ዚንጉሡ ትቜትና ተግሣጜ ሲገጥማ቞ው፣ ‹‹እንዲያውም ግርማዊ ሆይ፣ ዚሰጡኝ ሹመት ይቅርብኝፀ ዚአባ቎ን ርስት እያሚስኩ እኖራለኹ›› አላ቞ው፡፡ ጃንሆይም ወዲያው ‹‹እርሱንም እኛ ስንፈቅድ ነው ›› ብለው አሉ ይባላል፡፡ እኔም እንደ አቅሜ ለመሥራት ፍላጎት ቢኖሚኝም በቀጣይ ምን መሥራት እንደምቜልና እንደማልቜል ብያኔው በመሠሚቱ ኚእኔ ውጭ ነው፡፡ በተቻለኝ መጠን ግን በአለቜኝ ቀሪ ዕድሜ አገሬን ለማገልገል ዝግጁ ነኝ፡፡ በዚኹ አጋጣሚ በቅርቡ ዚአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ዚሚገኝበትን ተቋማዊ ኹኔታ በተመለኹተ አንድ ጜሑፍ እንደማስነብብ ኚወዲኹ ለማሳወቅ እወዳለኹ፡፡

↧

ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው! በፍቅር

$
0
0

‹‹ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!›› በሚለው በዚህ ዹሰውን ክብርና ልእልና ኹፍ ባደሚገው ፍቅር፣ ሰብአዊነትና ርኅራኄ ልባ቞ው ዹተሾነፈ ዚመቄዶንያ መስራቜ ኹሆነው ኚአቶ ብንያም ጀምሮ በበጎ ፈቃደኝነት በማዕኹሉ ውስጥ እያገለገሉ ያሉ ወገኖቻቜን በዚጎዳናው ላይ ዚወደቁ፣ እርጅና ተጫጭኖአ቞ው፣ ጉልበትና ጊዜ ኚድቶአ቞ው፣ በመጊሪያ቞ው ዘመን ዹቀኑ ሐሩር ዚሌሊቱ ቁር እዚተፈራሚቀባ቞ው፣ አምስትና አስር ሳንቲም ፍለጋ ዚእኛን እጅ ዚሚጠባበቁ፣ መውደቂያና መጠጊያ ዹሌላቾውን ወገኖቜን ሰብስበው ተገቢውን እንክብካቀ በማድሚግ እፎይ እንዲሉ እያደሚጉ ነው፡፡

መላ አካላ቞ው በቁስል ተመቶ፣ ሰውነታ቞ው በትል ተውርሶ፣ አካላ቞ው ተጎድቶ እጅግ በሚሰቀጥጥ ሁኔታ ያሉ ወገኖቻቜንን ሰብስቊ አስፈላጊው እንክብካቀና ዹሕክምና ዕርዳታ እንዲያገኙ እያደሚገ ያለው መቄዶንያ ዚብዙዎቜን ልብ ለፍቅርና ለበጎ ሥራ እያነሳሳና እያበዛ እንዳለ ይሰማኛል፡፡ ዚአእምሮ ሕመም ተጠቂ ዹሆኑ እንደ እነ ያሬድ ያሉ በሚውሉበትና በሚያድሩበት ጫካ በአውሬ ተነክስው፣ ሰውነታ቞ው በስብሶና በትል ተወርሶ ዹተገኙ ወገኖቜ ዛሬ ኚሥቃያ቞ውና ኹሕመማቾው አገግመው፣ አካላ቞ው ድኖ ሌላውን ለመርዳት ደፋ ቀና ሲሉ ማዚት ልዩ ዹሆነ ዚደስታ ስሜትን ያጭራል፡፡

እነዚህን ወገኖቻቜንን እዚተንኚባኚቡ ያሉ ሥራ቞ውና ስማ቞ው በአደባባይ ያልወጣ፣ ምስጋናም በይፋ ያልተነገሚላ቞ው በጎ ፈቃደኛ ወገኖቻቜን በብዙ ሊኚበሩና ሊወደዱ ይገባል፡፡ ቁስላ቞ውን ሳይጠዚፉ፣ ሕመማቾውና ሥቃያ቞ው እዚተሰማ቞ው በብዙ ፍቅርና ርኅራኄ እነዚህን ወገኖቜን በመንኚባኚብ እዚተጉ ያሉ ወጣቶቜ ይህ በጎ ሥራ቞ው ሊደነቅና በእጅጉ ሊመሰገን ዚሚገባው ነው፡፡ ኹዚህ ጋርም መቄዶንያ ‹‹ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!›› በሚለው መርሕ ቃሉን በተመለኹተ ባለፈው እሑድ በሚሊኒዹም አዳራሜ ባደሚገው ዚምስጋና እና ዚገቢ ማሰባበሲያ ዝግጅት ጋር በማያያዝ ሰው በመሆን ዙሪያ ጥቂት አሳቊቜን ለማንሳት ወደድኹ፡፡

መቄዶንያ ዚአሚጋውያንና አእምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕኹል መንግሥት በስጊታ ላበሚኚተለት 30 ሺህ ካሬ ሜትር መሬት ምስጋና ለማቅሚብና በስጊታ በተገኘውም በዚህ ቊታ ላይም ዹሁልጊዜም አጋሩና ደጋፊው ኹሆነው ኚኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በመተባበር ለአሚጋውያንና ለአእምሮ ሕሙማን ደሹጃውን ዹጠበቀና ሁሉን አቀፍ አገልግሎት ዚተሟላለት አዲስ ዚመኖሪያ ሕንፃ ለመገንባት ታላቅ ዹሆነ ዚገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ባለፈው እሑድ በደመቀና በሞቀ ሥነ ሥርዓት አካሂዶ ነበር፡፡

በዚህ ዚምስጋና እና ዚገቢ ማሰባሰቢያ እለትም ‹‹ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!›› ዹሚለው ዚመቄዶንያ ማዕኹል መርሕ/መሪ ቃልም በሚሊኒዹም አዳራሜ ነግሩና ገኖ ነበር ያመሞው፡፡ ይህ ዹማዕኹሉ መርሕም ዚብዙዎቜን ስሜትና ልብ ዹገዛና በርካታዎቜም በፍቅር ተሾንፈው ለወገናቾው እጃ቞ውን እንዲዘሚጉ ያነሳሳ ታላቅ ዹሆነ ሰብአዊነትን፣ ርኀራኄን ያዘለ መርሕ እንደነበር በዝግጅቱ ወቅት በነበሹኝ ቆይታዬ ታዝቀያለሁ፡፡
‹‹ሰው ማለት ሰው ዹሚሆነው ሰው ዹጠፋ እለት›› ያለው አንድ አንጋፋና እውቅ ዚአገራቜን አርቲሰት ማን ነበር?! ለጊዜው ስሙ ጠፍቶኛልፀ ግና ኹዚህ አርቲስት አባባል ጀርባ አንድ ትልቅ እውነት አለ፡፡ ሰው ዹመሆን ታላቅ ክብርንና ልዩ ጾጋን እንድንመሚምር፣ እንድንፈትሜ ዚሚያተጋን፡፡

ኚክርስቶስ ልደት በፊት ዹኖሹው ግሪካዊው ፈላስፋ ዲዮጋን በአንድ ወቅት በአ቎ንስ ኹተማ በጠራራ ፀሐይ ፋኖስ ይዞ ይዞር ነበር፡፡ ይህን እንግዳ ሥራውን ያዩ አ቎ንሳውያን ዲዮጋን በጠራራ ፀሐይ ፋኖስ ይዘህ ዚምትዞሚው ለምንድን ነው ባሉት ጊዜ ዚሰጣ቞ው መልስ እንዲህ ዹሚል ነበር፡- ‹‹ሰው እዚፈለኩ ነው!›› በእርግጥ በአ቎ንስ ኹተማ ዲዮጋንን ዚኚበቡት በርካታ ሰዎቜ ነበሩ፡፡ ግን በዲዮጋን እሳቀ እነዚህ ሰዎቜ ሰው ኹመሆን ክብር ዚወሚዱና ዚተዋሚዱ፣ ፍቅርንና ራኅራኄን ዚተራቆቱ፣ በጎነትና ቅንነት አርቀው ዚገፉ፣ ሰው ሰው ዚማይሞቱ ሆኖ ስላገኛ቞ው ነበር ዲዮጋን በሰዎቜ መካኚል ሆኖ ‹‹ሰው እዚፈልኩ ነው!›› ሲል ለወገኖቹ በአደባባይ ዚተናገሚው፣ ዚጮኞው፡፡
አዎን ዲዮጋን በወቅቱ ዚነበሚበት ማኅበሚሰብ ፍቅርን ዚተራቆተ፣ ስግብግብና አልጠግብ ባይ፣ ለእኔ ለእኔ ብቻ ዹሚል አውሬነት ዚነገሠበት፣ ጚካኝና ክፉ ቢሆኑበት ነው እሚ ባካቜሁ እናንተ ሰዎቜ ሰው ሁኑ ሲል ዚተጣራው፡፡ በመሠሚቱ ሰው በመንፈሳዊው ዓለምም ሆነ በሳይንሱ ዓለም አስተምህሮና ትንታኔ አንፃር ዚፍጥሚታት ሁሉ ዹበላይ እንደሆነ ነው ብዙዎቜ ዚሚስማሙት፡፡ አሁን በደሚስንበት ዚእውቀትና ዚዕድገት ደሹጃም ዹሰው ልጅ ዚፍጥሚት ሁሉ ማእኚልና መዳሚሻ እንደሆነ ይታሰባል፡፡

በክርስትናም ሆነ በእስልምና ሃይማኖቶቜ አስተምህሮ መሠሚትም በምድር ያሉ ፍጥሚታት ሁሉም ለሰው ልጆቜ ጥቅምና ክብር ሲባሉ እንደተፈጠሩ ያስተምራሉ፡፡ እንዲሁም በሥነ ፍጥሚት ታሪክ ዚፍጥሚታት ቁንጮና ፍጻሜ ዹሆነው ሰው፣ ፍጥሚትን ሁሉ እንዲገዛና እንዲነዳ ዚተሟመ ክቡር ፍጥሚት እንደሆነ ይናገራሉ፣ ይተርካሉ፡፡

ስለሆነም በመንፈሳዊም ሆነ በሳይንሱ ዓለም ሰውን ኚፍጥሚታት ሁሉ በማላቅና በማክበር ሚገድ ተመሳሳይ አስተምህሮ ወይም ግንዛቀ እንዳለ ልብ እንላለን፡፡ መቄዶንያ ‹‹ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!›› ዹሚለው መርሕ ቃሉም/አባባሉ ኹዚህ በሃይማኖቱም ሆነ በሳይንሱ ዓለም ስለ ሰው ተፈጥሮአዊ ማንነት፣ ጾጋና ታላቅ ክብር ካለው እውነታና ትንታኔ በመነሳት እንደሆነ አስባለሁ፡፡

ይኾውም ሰው ዹመሆን ምስጢር ውስጥ ሰውን ወደላቀ ዚሰውነት ደሹጃና ኹፍ ወዳለ መንፈሳዊ ክብርና ልእልና ኹፍ ዚሚያደርግ፣ ዚሚያደርስ ፍቅር ዚተባለ ሹቂቅና ታላቅ ኃይል አለ፡፡ ስለሆነም ፊት ለፊት በዓይናቜን ኹምናዹው ኚአካላዊ መገለጫው ባለፈ ሰውን ሰው ሊያሰኘው፣ ሰው ሰው እንዲሞት ሊያደርገው ዚሚቜል ሰው በፍቅር፣ ስለፍቅር ዹተሰጠው ክቡር ዹሆነ ዚሰብአዊነት ሕያው ማንነትና ልዩ መገለጫ አለው ማለት ነው፡፡

ይህ ሰው ዚማንነት መገለጫው መለኮታዊ ዹሆነ ዹፍቅር መነሻና አሻራ ያለውና በሃይማኖቱ አስተምህሮ፣ ለዘመናት በተጓዘበት በባህሉ፣ በታሪኩና ሥልጣኔው ሹጅም ጉዞው እያዳበሚው ዚመጣ በልቡ ውስጥ ዹተተኹለ ሕያው ማንነቱና ክቡር መገለጫው ነው፡፡ ስለዚህም ሰው ስንል ኚሥጋው፣ ኚመንፈሱና ኚነፍሱ ጋር በጥልቅ ዚተሳሰሚ ዹተለዹ ማንነት ያለው ክቡር ፍጥሚት እንደሆነ እዚተናገርን ነው ማለት ነው፡፡

እንግዲህ ይህ ሰው ዹመሆን ታላቅ ክብርና ጾጋ ዹተጎናጾፈ ዹሰው ልጅ በተለያዩ አጋጣሚዎቜ በተፈጥሮም ሆነ በሰው ሰራሜ አደጋዎቜ ለራሱ መሆን ሲያቅተው፣ ሀብት ንብሚቱ ሲጠፋ፣ ጉልበት ሲካደው፣ ወዳጆቹና ዘመዶቹ ሲጞዚፉት፣ እርጅና ሲጫጫነው፣ ጧሪ ቀባሪ ሲያጣ፣ ተስፋው ተመናምኖ ቅስሙ ሲሰበር ‹‹ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!›› አሊያም ‹‹ሰው ማለት ሰው ዹሚሆን ነው ሰው ዹጠፋ እለት!›› ዹሚለውን ታላቅ አባባል በፍቅር፣ በሥራ እንገልጞው ዘንድ ግድ ዚሚለን፡፡

እማሆይ ማዘር ተሬዛ አብዝተው በሚነሡበት በብዙዎቻቜን ዘንድ በሚታወቀው አንድ ምርጥ አባባላ቞ው ጜሑፌን ላጠናቅ፡- ‹‹What matters a lot it is not what you are doing but the amount of love you put in doing that.››
ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!

↧
↧

ኚምርጫው በፊት ልናደርገው ዚሚገባ ሌላ ምርጫ (ገዛኾኝ አበበ ኹኖርዌይ ሌና) ኹገዛኾኝ አበበ ኖርዌይ ሌና

$
0
0

በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ስርዓት በማስመልኚት በተለያዩ ድሚገጜ እና ዹዜና አውታሮቜ ላይ ዚህዝብን ንቃተ ህሊና ሊይጎለብቱ ዚሚቜሉ ዚተለያዩ ዘገባዎቜ ይቀርባሉ። በተለይም ደግሞ ፍትህ፣ነጻነት፣እኩልነትን አስመልክቶ እንዲሁም ሊጀመር ጥቂት ጊዜያት ዹቀሹውንና ዚኢትዮጵያዊያንን አዕምሮ በያዘው ዚሀገራቜን ምርጫ ዙሪያ መነጋገሩ፣ መኚራኚሩ እና ኚምርጫው በፊት መስተካኚል ዚሚገባቜውን ነገር ማውሳቱ ዹሰሞኑ ዓቢይ ጉዳይ ሆኗል። በርግጥ ዹ1997ቱ ምርጫ ዚህዝብ ቅስም ዚተሰበሚበት እና እስኚአሁንም ድሚስ ዚኢትጵያ ህዝብ ስብራት ያላገገመበት ሁኔታ በስፋት ይታያል። በመሆኑም እንደ እኔ እምነት ፍትህ ኚሌለበት ሀገር ኚፊታቜን ካለው ምርጫ ምንም ይፈጠራል ብዬ ዚምጠብቀው ነገር ባይኖርም ግን ጥቂት ዚሚባሉ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ ምርጫውን አስመልክቱ እዚሰሩት ያለው ቅስቀሳ እና ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ዚወያኔን መንግስት ኚስልጣኑ በማውሚድ፣ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነት እዚኚፈሉት ያለው መስዋትነትና ሊያስመሰግና቞ው ይገባል ባይ ነኝ ። እርግጥ ነው ኹሁሉም አቅጣጫ ዚሚስተጋባው ዚኢትዮጵያዊ ድምጜ ሀገርን ኚመውደድ እና ለሀገር ነጻነት እንዲሁም ሉአላዊነት ዹሚኹፈል መስዋዕትነት እስኚሆነ ድሚስ ትግሉ ይፋፋም ይቀጥል ያስብላል።

ፍትህ ዚሰፈነበት ምርጫ ሊካሄድ ዚተገባ መሆኑን ሁላቜንም እንስማማበታለን። ዚሁላቜንም ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ናፍቆት ሰላም ዚሰፈነባት ሀገር ላይ ምርጫው ዚህዝብ እንዲሆን ነው። ይህም ህልም በምድራቜን ላይ ተጚባጭ ይዞታ ኖሮት ተግባራዊ ቢሆን ሀገራቜን ምን አይነት ቅርጜ ሊኖራት እንደሚቜል ማሰብ ኚባድ አይደለም። ስለሆነም በአሁን ወቅት በምድሪቷ ላይ እዚገነነ ዚመጣው ግፋዊ አገዛዝ ወደበለጠ ደሹጃ ደርሶ እጅግ ኚመክፋቱ በፊት ዚትውልድ ሁሉ ናፍቆት ዹሆነውን እኩልነት እና ህዝብ ለብዙ ጥፋት ታልፎ በተሰጠበት እንዲሁም ኚሀገሪቷ ፊት ለፊት ታላቅ ዹሆነ ክስሚት ተጋርጩ ባለበት ዚአምባገነን ስርዐት ዘመን ዹሰኹነና ዹተሹጋጋ ህይወትን በኢትዮጵያ ላይ ለማምጣት ታላቅ ዹሆነ ርብርቊሜ ያስፈልጋል።

ይህንን በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ዹዘቀጠ ዚፓለቲካ ስርዐት ወደኋላ ኚተጎተተበት ኢፍትሐዊ አሰራሩ ተናጥቆ ለማውጣት እና ዹሰለጠኑ ሀገራት ወደደሚሱበት ዚነጻነትና እና ዚእኩልነት ክልል ለማድሚስ ኚጚዋታ ውጪ ዚተደሚጉት ዚኢትዮጵያ ምሁራን እና ኹማንኛውም ዚእድገት እንቅፋቶቜ ዚጞዳ አላማ ያላ቞ው ሀገር ወዳዶቜ ዚተዘጋባ቞ው በር ክፍት ሆኖ በሁሉም ሀገራዊ አቅጣጫ ጉዳይ ላይ ለምድራ቞ው ዚሚቻላ቞ውን አስተዋጟ እንዲያደርጉ በተለይም ደግሞ ኚፊት ለፊታቜን በወያኔ ቁጥጥር ስር ያለው ምርጫ በህዝብ ፈቃድ ላይ ዹተመሰሹተ እንዲሆን ዚኢትዮጵያ ሊሂቃን እድሉ ያለምንም ተጜእኖ በነጻነት ተሰጥቷ቞ው እንዲሳተፉ ማድሚግ ተመራጭነት አለው። ይህን መሰሉ ተግባር በምድሪቷ ላይ ዹጾና እስኚሚሆን ድሚስ እንዲሁም ዚገዥውን ቡድን እድሜ መቀጠል ፣ ዚተመዘበሩ ኮሮጆዎቜ እና ዚምርጫ ዕቃ ዕቃ ጚዋታ ወቅታ቞ውን እዚጠበቁ ያለፈውን ልማዳ቞ውን ለመድገም ዚሚደሚጉት እንቅስቃሎዎቜ ተፈጻሚ ኹመሆናቾው በፊት በሁሉም አቅጣጫ መታገል እንደሚገባን እና ኚምርጫው በፊት ህዝባዊ አመጜ እንደ አማራጭ ኚመውሰድ በስተቀር በሌላ መንገድ ወያኔን ማክሾፍ እንደማይቻል ሊታወቅ ይገባል።

እውነታውን በመሾፋፈን ወያኔ በምግብ ራሳቜንን ቜለናል እያለ በሚቀልድበት በዚህ ዚሚሀብ ዘመን ዘወትር ሜቅብ እዚወጣ ሰማይ ለመንካት እዚተመነጠቀ ስላለው ዚኑሮ ውድነት ህዝቡም ሲያወራ ወያኔም ስለ ‹‹11%›› እድገት ሲደሰኩር፣ ህዝብ ስለ ስራ-አጥነት እና እርዛት ሲያወራ ወያኔ ‹‹ስለኢንቚስትመንት መስፋፋት›› ሲያብራራ፣ ህዝብ ስለሚሃብ ሲያወራ መንግስት ‹‹ስለጥጋብ›› መፈክሩን ሲያሰማ ፀ ህዝብ ስለዳቊ ሲጮህ ዚወያኔ መንግስት ‹‹ስለመሰሚተ ልማት›› እያወሩ እርስ በርስ መግባባት ተስኗ ቾው 23ኛ አመት ዐመት አልፎ ተጋምሷል ። ይህ ያላቻ ጋብቻ ይባላል። በድግሳ቞ው ቀን አንዱ ዚደስታ ሌላኛው ዹሃዘን ሻማ በማብራት አክብሚው አሳልፈዋል፡፡ ኚእንደዚህ አይነት ስርዓት አልባ ገዢ ጋር ፍቺ ብ቞ኛ አማራጭ ነው። ምርጫውም ፍትሀዊ እና ዚህዝብ ካልሆነ በስተቀር ለኢትዮጵያዊያን ዚሚያመጣው ምንም አይነት ፈውስ እንደሌለው ዚታወቀ ይሁን። ይልቁኑም ዹኹዚህ በፊቱን ውሞት እና ማስመሰል ሹቀቅ ባለ ማደናገሪያው ለመድገም እዚተሯሯጠ መሆኑ ግልጜ በሆነበት በዚህ ወቅት አምባገነኑን ወያኔን ኚምርጫው ውጭ ለማድሚግ በዚትኛው ጎዳና ብንሔድ በትግላቜን ግቡን እንደምንመታ እና ዚተለያዩ ዚትግል ልምድ ስልቶቜ ልውውጥ አድርገን ሀይላቜንን በማጠናኹር በአንድ ዚተባበሚ ኢትዮጵያዊ ክንድ ኚምርጫው በፊት ህዝባዊ አመጜን ዚሁላቜን ምርጫ ይሁን በማለት መነሳት አለብን።

ዹኔ ዹግል ምልኚታዬ በአሁን ሰአት ሀገራቜን ባለቜበት ደሹጃ ዚትግላቜን ኢላማ እና መድሚሻው መሆን ዚተገባው አስቀድሞ በሐስት ዚወያኔ ነቢያቶቜ ለተነበዩለት ምርጫ ተባባሪ ሆኖ በመሰለፍ አምባገነኑ አገዛዝ እንዲቀጥል አስተውጜኊ ማበርኚት ሳይሆን ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዚሚወስነውሀገር ዚምትተዳደርበት ልማታዊ ዹሆነ ህግ በምድሪቷ ላይ ዹበላይ እንዲሆን ዚዜጎቜ እኩልነት እና ሰብዓዊነት ዚሚኚበሩባ቞ው ስርዓት በማስፈን ወያኔ በጭቆና ዚተቆጣጠርውን ስልጣን በመቀማት ዚህዝብ ዚስልጣኑ ባለቀት ሆኖ ፍጹም ዹሆነ ብሩህ ተስፋ ዚሚታዚባትን ኢትዮጵያን መፍጠር ነው።

መቌውንም ቢሆን ወያኔ ለነጻ ፍትሀዊ ምርጫ እና ለኢትዮጵያ ህዝብ ዚበላይነት ለምን አልቆመም ተብሎ አይጠዚቅም። ምክንያቱም ይህ ቡድን “ኚጅብ ጅማት ዚተሰራ ክራር ምንጊዜም ቅኝቱ እንብላ እንብላ ነው” እንዲሉ ኚፅንሰቱም ፀሹ ኢትዮጵያዊ መሆኑ ዚታወቀ ነው። ኹዚህ አስኚፊ ስርዓት መልካም ዹሆነ አስተዳደር መጠበቅ ዚሚታሰብ አይደለምና እንደገና ሌላ ምዝበራ በሀገርቜን ላይ ኹመፈፀሙ በፊት ምርጫው ጋር ሳንደርስ በፊት ዚህዝባዊ አመፅ ትግልን በመምሚጥ ወደ ውጀት እንጓዝ። ምርጫው ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዹሚመርጠው እና ዚሚወዳደሚው እንጂ ለተሳትፎ ብቻ ብቅ ብሎ በወያኔ ሻጥር ዚሚሞነፍበት ሊሆን አይገባም።

ለውጥ ዚግድ አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ ሁሉንም ዹማይጠቅም ቢሆን እንኳን ለብዙኃኑ ሲባል ዚግድ መምጣት አለበት፡፡ ዚለውጥ ፍርሐትን አስወግደን በቂ ዝግጅት በማድሚግ በተገቢው መንገድ ወያኔን ማስወገድ ይቻላል፡፡ ለውጥ ዚሚመጠበትን መንገድ ፈርቶ እና ህዝባዊ አምፅን ተቃውሞ ለውጥን መጚበጥ ዘበት ነው፡፡ ‹‹መፍራት ያለብን ፍርሐትን ራሱን ነው›› እንዲሉ ፍራንክሊን ሩዝቬልት፡ ዚትኛውንም ወደኋላ ዚሚጎትተንን ፍርሀት ትተን ድጋሚ በምርጫው ኚመጭበርበራቜን በፊት አስቀድመን በህዝባዊ አመጜ መታገንልን እንምሚጥ። ኚምርጫው በፊት ዚኢትዮጵያውያን ምርጫ በህዝባዊ አመጜ ትግል ለዘመናት በአንባገነንነት በስልጣን ላይ ተቀምጩ ህዝብን በማሰር ፣ በመግደል ላይ ያለውን አሹመናዊ መንግስት ኚስልጣን ላይ ማውሚድ ይሆን ነው መልዕክቮ ።

gezapower@gmail.com

ዚሕዝብ ትግል ያ቞ንፋል !!!

↧

ዚብሄር ብሄሚሰብ ፖለቲካና ዚአድዋ ድል ሚንጋ ነጋሜ

$
0
0

ዚካቲት 23 2007 (ማርቜ 2, 2015) ዹ119ኘዉ ዚአድዋ ድልና ዚሰማዕታት መታሰቢያ ቀን ነዉ። አኚባበሩ በሃገር ዉስጥ ቢቀዘቀዝምፀ በተዘዋዋሪዉ በአሉን ዚሚያኚብሚዉ በዉጭ ሃገር ዹሚኖሹዉ ኢትዮጵያዊ ቁጥር እዚጚመሚ ይገኛል። በሰሜን አሜሪካ ዚድል በአሉ ቀን ኚአፍሪካ አሜሪካዉያን ታሪክ መዘኚሪያ ወር ጋር መያያዙና ዚዚካቲት 12 ሰማእታትን መታሰቢያ ቀን ደግሞ ኚሰላሳ በላይ በሆኑ ያለም ኚተሞቜ መዘኚሩፀ በዉጭ ዚሚኖሩ ኢትዮጰያዉያን ትኩሚት ዚሰጡት ስለሀገር አቀፍ ድልና ስለአፍሪካዊነት (Pan Africanism) መሆኑ ራሱን ዚቻለ መልዕክት አለዉ።

በዚህቜ አጭር ጜሁፍ ለማስገነዘብ ዹምሞክሹዉ አድዋንና መሰል ዚሃገራቜንን እሎቶቜ በብሄር-ብሄሚስብና ወይም በሃይማኖት ዘመም ዚፖለቲካ መነፅር (ethnocentric paradigm) መመልኚትና በብዙሃን ዘመም (diverse, multi-ethnic) መነፅር መመልኚት ዚሚዚስኚትሉትን እደምታዎቜ ለማሳዚት ነዉ። ሁለቱም አመለካኚቶቜ ዚሚያዩት አንድ ነገር ቢሆንም ዚሚሰጡት ትርጉም ግን ዚተለያዚ ነዉ። ሃገር አቀፍ ፖሊሲ ሲነደፍ ሁለቱ መነፅሮቜ ዚሚያሳዩትን ልዩነትና አንድነትን በቅጡ መሚዳት ይጠይቃል። እኔ ዚታሪክ ወይም ዚፖለቲካ ስነልቊና ሳይንስ ተማሪ አይደለሁም። ሰለአድዋ ድልም ዹማዉቀዉ በጣም ዉሱን ነዉ። ቢስማርክ ኚጠራዉ እ.ኀአ 1884/85 ዹበርሊን ዚአፍሪካ ቅርጫ ኮንፍሚንስ (the conference for the scramble of Africa) ጀምሮ እንዎት ኢትዮጵያ እንደሌላዉ ዚአፍሪካ ክፍል ዹዚህ ቅርጫ ሰለባ አለመሆንዋ ብዙ ዚታሪክ ምሁራንን አስሚገርሞዋ቞ዋል። ይህንን ታሪክ አፈወርቅ ገብሚዚሱስ፡ ገብሚ ህይወት ባይኚዳኝ፡ ራይመንድ ጆናስ፡ ሪቻርድ ፓንክሚስት፡ ዶናልድ ሌቢን፡ ኀድዋርድ ክሬሚ፡ ሃሮልድ ማርኚስ፡ ጆን ሰፔንሰርፀ ታደስ ታምራት፡ መርእድ ወልደአሚጋይፀ ብርሃኑ አበበፀ አለሜ እሜ቎ፀ ባህሩ ዘውዎ፡ ሜፍራዉ በቀለ፡ ሹመት ሲሻኝ፡ ዘዉዮ ገብሚስላሎፀ ጌታቜዉ ሃይሌፀጳዉሎስ ሚለኪያስፀ ጳዉሎስ ኞኞ መስፍን አርአያፀ ጌታ቞ዉ መታፈሪያ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ዚጻፉትንና ዚተናገሩትን ዚማንበብ እድል ነበሚኝ፡፡

ኚፊልምፀሙዚቃና ግጥም ስራዎቜ ደግሞ እነ ቊብ ማርሌና ራሰ ተፈሪያኒዝምፀ ዹሃይሌ ገሪማንፀ ዹአለምፅሃይ ወዳጆንፀ ዚፀጋዮ ገብር መደህንፀአዲሰ አለማዹሁ እጅጋይሁ ሜባባዉና ዚ቎ዎድሮስ ካሳሁንን ስራዎቜ መስማትና ማዚቱ ተጚማሪ ሰሜት ፈጠሮልኛል።። ኚታላላቅ ዚፖለቲካ መሪዎቜ ጜሁፎቜና ንግግሮቜ መካኚል ደግሞ፡ እነ ማርኚስ ጋቢ፡ ማርቲን ሉተር ኪንግን (ዚኢትዮጵያ ኀምባሲ ግብዣ ጚምሮ)ፀ ዚአፍሪካ ዚነፃነት መሪዎቜ ማለትም እነ ሙዋሊሙ ኔሬሬ፡ ኬኔዝ ካዉንዳፀጆሞ ኬንያታፀ ኔልስን ማንዎላ፡ ታቊ እምቀኬ፡ ክዋሚ ንክሩማፀ በደቡባዊ አፍሪካ በ1880ዎቹ ዚተፈጠሩትና እስኚዛሬ ያሉትን በኢትዮጵያ ስም ዚሚጠሩትን ቀተ ክርስቲያኖቜ ታሪክን በተመለክተ ዹፐ/ር ማሞ ሙጬን ዚቅርብ ጊዜ ፅሁፎቜ ሳነብፀ አሜሪካም በተለይ በሁለተኛዉ እ..ኀ.አ ዹ1933 ዚጣሊያን ወሚራ ጊዜ ስለነበሚዉና ስለአነ መላኩ በያን ሥራና ስለአፍሪካ አሜሪካዉያን ወዶ ዘማ቟ቜ ምልመላ ሳነብፀ ዚተሚዳሁት አድዋ ዚአድዋዉያንና ዚኢትዮጵያዉያን ዚድል ታሪክ ብቻ አለመሆኑን ነዉ። ዚሃይቲን ዚነፃነት ትግልና በልጅነቮ እሰማ ዹነበሹዉን ዹአፄ ምኒልክን ዚደስታ ዚተኩስ ሩምታ ምክንያት ያስታዉሰኛል። እነዚህ ምሁራን ዚነፃነት መሪዎቜና አርቲስቶቜ ዚተኚተሉት በአብዛኛዉ ዚብሄሚሰብና ዚብሄር መነፅር ዚታሪክ ትርጉም አልነበሹም ብሎ መደምደም ይቻላል።

በአንፃሩ አዲስ ህይወት (ዚብዕር ሰም): ቩኒ ሆልኮምብና ሲሳይ ኢብሳፀ ማሩ ቡልቻፀ በ 1990ዎቹ በ Red Sea Printers ና ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በኩራዝ አሳታሚ ዚታተሙ መጻህፍትና ገድል መሰል ጜሁፎቜ ዚፖለቲካ ትንታኔያ቞ዉ በአንዳንንድ ዚአሜሪካ ዩኒቚርሲቲዎቜ ዚሚታዚዉን ብሄሚ ተኮር ጥናቶቜ (ethnography and ethnic studies) ተደግፈዉ ማርክሳዊ መሰል ትንታኔና ትርጉም ሊሰጡ ይሞክራሉ። ጎልቶ ዚሚወጣዉ መልዕክታ቞ዉ ኢትዮጵያ ዹሚለዉን ዚፖለቲካና ዚሶሺያል መሰሚቶቜ ዚሚንድ (de-legitimize) ነዉ። ዹሀገር ዉስጥ ግጭቶቜን በብሄር መነጜር ያይዋ቞ዋል። ዚአድዋ ጊርነትን ዋና መሪዎቜን ኚሌሎቜ ግጭቶቜ ጋር እያጣቀሱ ሲወቅሱ ይሰማሉ። ብሄር ተኮር ድርጅቶቜም ግጭቶቹን ዚአንድ ወገን በማስመሰል ኚዛሬ ፖለቲካ አገናኝተዉ ቢቻል አዲስ ነፃ ሀገር ባይቻል ደግም አሁን ካለዉ ዚተሻለ ዚፌዎራል አስተዳደር እንመሰርታለን እያሉ ቃል ይገባሉ። ዚድሮዋ ኢትዮጵያም ልዩ ዚብሄሚሰቊቜ እስር ቀት ነበሚቜ ዹሚል ትሚካም አላ቞ዉ። አዲሲትዋ ኢትዮጵያም ዚብሄሚስቊቜ (nations, nationalities, peoples, volks) ድምር ነቜ ወይም ትሆናለቜ ይላሉ። በዚህም ዚተነሳ ዚፖለቲካ ዚአስተዳደርና ዚትምህርት ወዋቅሩ ይህንኑ ተኚትሎዋል። ይህ አካሄድም ሀገሪቱዋን ኹመበተን አድኖዋት በኢኮኖሚም እዚተራመደቜ ነዉ ብለዉ ይኚራኚራሉ።

ዚፖለቲካ መሪዎቜ ይመጣሉ-ይለወጣሉ። ስርአቶቹን ዚሚመራዉም ርአዮተ አለም እንዲሁ ይቀያዚራል። ይህ ደግሞ በብዛት ዚሚታዚዉ አፍሪካ ዉስጥ ባሉ ኹቀኝ ግዛት በሁዋላ በተፈጠሩ ሀገሮቜ (post colony states) ነዉ። አንድ ቲዎሪም ሁሉን ነገር (phenomenon) ሊያብራራ አይቜልም። ይህ እንኩዋን በኩዋሊ቎ቲቭና በፊኖሚኖሎጂ ዹምርምር መንገድ ዹሚጠኑ ስራዎቜን ቀርቶ በኢምፒሪካል ዹምርምር መንገድ ላይም በዹጊዜዉ ዚሚታይ ሁኔታ ነዉ። ታሪክንም በተለያዩ መነፀሮቜ መመርመር በራሱ ቜግር ዚለዉም። እንዎዉም ይህ አካሄድ በተ;ለይ በፖሊሲ ንድፊያ ጊዜ ዚተሻለ አካሄድ ሊሆን ይቜላል። በእኔ እድሜ ኢትዮጵያ ዉስጥ ሶስተ ያስተዳደር መርሆዎቜን አይቻለሁ። ባለፉት 40 አመታት ዉስጥ ብሄር ዘመምና ዚግራ ዘመም ዚታሪክ ትርጉዋሜዎቜ ዚመንግስትን ዋና ዋና ፖሊሲዎቜ ሲመሩ አይተናል። ሁለቱም ህብሚተስብን በመደብ በብሄርና ወይም በሃይማኖትና በጟታ መክፈልና ልዩነቶቜ ላይ ማተኮርን ይወዳሉ። አንድን ህብሚተሰብ በዎሞግራፊ መርሆዎቜ ኹፍሎ ማጥናቱ ቜግር ዚለዉም። ልዩነታ቞ዉ ብዙሃንነት (diversity) እንዎት እንደሚስተናገድ ነዉ። ሰለ ኚአንድ በላይ ማንነት (dual & multiple identities) በሃገራቜን ብዙ አይነገርም።

ብዙዎቹ ዚዛሬ ዚብሄር ንቅናቄ መሪዎቜ በአንድ ወቅት ዚማርክሲስት ርአዮተ አለም ተኚታዮቜ እንደነበሩ ይታወቃል። አስተዳደር ላይ ዚሁለቱ ልዩነት ማርክሲሰቶቜ ሀገር አቀፍ፡ አህጉር አቀፍፀኚዚያ አልፎ ኢንተርናሜናሊዘምን ሲያወድሱፀ በተቃራኒዉ ብሄር ተኮር አካሄድን ዚሚመርጡ ደግሞ ጭንቀታቜዉ ቆመንልሃል ለሚሉት ዚህብሚተሰብ ክፍል ሲሆን ግራ ዘመምነታቜዉ ስታሊን በስራ ላይ ያላዋለዉን ዹመገንጠል መንገድ እንዲያቀነቅኑ አድርጎዋ቞ዋል። ግራ ዘመም ያልሆኑት ብሄር ተኮር ድርጅቶቜ ደግሞ ተግባራ቞ዉ ወደ ፋሜዝምና አፓርታይድፀበማወቅም ሆነ ባለማወቅፀ ሲያቀርባ቞ዉ ይታያል። ዚሶቪዚት ህብሚትና ዚይጎዘላቪያን አፈጣጠርፀ አፈራሚስና ዉጀቱን ማጀን ይሚሳሉ። ስለሆነም አንድ ብሄር ተኮር ዚፖለተካ ሃይል ዚተለያዩ ብሄሮቜ ባሉበት ሀገር ላይ ዚበላይነት በያዘበት ቊታ ገዢዉን ብሄር ለመጥቀምና ለማሞገስ ተብለዉ ዹሚደሹጉ ሙኚራዎቜ ትክክለኝነታ቞ዉና ትሚጉዋሜያቜ በቅጡ ሳይፈተሹ በህገ መንግስት ላይ ይሰፍራሉ። ዚመንግስትም ስራዎቜ በብሄር ተኮር ፖሊሲዎቜ ይመራሉ። ዚብሄር ድርጅቱ ካናሳ ወግን ኚመጣ ዚአናሳዎቜን ህብሚት በመፍጠር ዚብዙሃኖቜን ግፊት ለመቁዋቁም ይሞክራል። ማንነት (identity) ዚምርጫ አጀንዳ ሆኖ ዜሮና አንድ ወይም እድገትና ድህነትፀባርነትና ነፃነትፀ እኛና እነሱፀ ሰይጣንና መልአክፀወዘተ ተብሎ ይቀርባል። ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ይህ አካሄድ በሃይማኖት (bigotry) በመታጅብ ላይ ይገኛል። ኹዚህ ባሻገር ደግሞ ሊበሪ቎ሪያኒዘምን ማለትም ግለሰብ መብት ላይ ዚሚያተኩር ዚፖለቲካ አስተሳሰብን ዚሚያራምዱ አሉ። ሁሉም ማለትም ዚግራዉም ብሄር ተኮሩም ሆነ ሊበሪ቎ሪያኑ “ዲሞክራሲያዊ” ዹሚል ታፔላ አላ቞ዉ።

ሰለዚህ ኀትኖሌንትሪዝም በሃገራቜ ሲታይ ልዩነትን (diversity) ለማስተናገድ እ.ኀ.እ በ1993 ዚሰራዉ ህገ መንግስት መፍትሄ እንዳልሆነና ሀገር አቀፍ መግባባት ለመፍጠር አለመቻሉ በቅጡ ተፈትሟአል። ዹ1991 ዱም ቻርተር ማለትም ዹህገ መንግሰቱ አዋላጅ ዹተፃፈዉ ኚግጭት በሁዋላ ስለነበር ያመለኚተዉ ዹጊዜዉን ዹሃይል አሰላለፍ ነበር። ጞሃፊዎቹም እርስ በርሳ቞ዉ ይጣሉ እንጂ በጜንሰ ሃሳብ ደሹጃ ኹ25 አመታት በሁዋላም ቢሆን መሰሚታዊ ልዩነት አይታይባቜዉም። በትምህርት ቀቶቜም ዚሚሰጡ ትምህርቶቜ ዚብሄር ተኮር መሰሚት ስላላ቞ዉ ኹፍተኘ ትምህርትም በብሄር በመዋቀሩና በክልል አሰተዳደር ስር መሆና቞ዉፀ በምሁሩም ቅን ልቊናዊነት (bona fide, honesty and integrity) ላይ ለመተማመን አስ቞ጋሪ እዚሆነ መጥቶዋል። ሃገሪቱ ዹተማሹ ህዝቡዋን በተለያዩ ምክንያቶቜ ስታጣናፀ አብዛኛዉ ወጣት ዹሆነዉ ህዝብ ዚስራ አጥነትፀዚኢኮኖሚና ዚፖለቲካ ስደት ሰለባ ሲሆንፀ በባህር ላይ ሲሰምጥና በዚስደተኛ ካምፖቜና እስር ቀቶቜ ሲታጎርፀ ዹምርምር ተቁዋሞቜ መሰሚታዊ ምርምር ማደሹግ አለመቻላ቞ዉፀ ዮኒቚርሲቲዎቜም ኚጥራት ይልቅ ወደ ብዛት አተኩሚዉ በዹክልሉ ሲሚጩፀ በብሄር ተኮር ሹማምንት ሲመሩፀ ዉጥሚቶቹንም በፍትሃዊ ምርጫዎቜ ለማስተንፈስ አለመቻሉፀ ብሄርና ሃይማኖት ዚፖለቲካ ማማ (platform) ሆነዉ መቀጠላ቞ዉፀ በግጭት ቀጠና ዉስጥ ያለቜዉን ዚሀገራቜንን ቜግሮቜ እጅግ ዉስብስብ አድርገዉታል።

ስለዚህም በሀገራቜን ዛሬ በስልጣን ላይ ያለዉ ብሄር ተኮር መንግስት እንደ ቀድሞዎቹ ዚማርክሲሰትና ዚንጉሳዊ መንግስታት ሁለት ቜግሮቜ ገጥመዉታል። በአንድ በኩል ሌሎቜ ብሄር ተኮር ተፎካካሪዎቹ ዹማዕኹላዊ መንግስት ስልጣኑን ሊወስዱብትና ለራሳቜዉ ብሄር ሊተኩ ይፈልጋሉ፡፡ ይህ ካልሆነላ቞ዉ ደግም ሃብት ወደ አሜናፊዉ ብሄር ብሄሚሰብ እንዳይፈስስ ሲሰተሙን ለማፍሚስ ይጥራሉ። ይሀ ጥሚት በራሱ በመንግስትና ፓርቲ ዉስጥ፡ በምርጫና በጠመንጃም እዚተሞኚሚ ይገኛል። ዚብሄር ድርጅቶቜ መሪዎቜም ለሁለተኛ ድል (second breakthrough) እዚተዘጋጀን ነዉ ይላሉ። ሁኔታዉ በሶቪዚት ህብሚትና በዩጎዝላቪያ ዚኮሚኒስት ፓሚቲዎቜ ዉሰጥ ዚብሬዥኔቭና ዚቲቶን ሞት ተኚትሎ ዹተፈጠሹዉን ክስተት በገዥዉ ዚብሄሮቜ ግምባር ዉስጥ አይኚሰትም ብሎ መናገር አይቻልም። እሰኚ አሁን በድርጅቱ ዉስጥ ዹነበሹዉ ዹሃይል አሰላለፍ ለማስቀጠል ርብርቊሜ ያለም ይመስላል። በሌላ በኩል ደግሞ ኚብዙሃኖቜና ኚዲሞክራሲ ሃይላት ክፉኛ ዉድድር ገጥሞታል። በነፃና ፍትሃዊ ሀገር አቀፍ ምርጫ እንደማያሞንፍ ተሚድቶታል። ስለሆነም ተፎካካሪዎቹን ስልጣን ኚማካፈል ይልቅ ማፍሚስንና አሜባሪዎቜ ብሉ መሰዹሙን መርጊዋል። በ2005ቱ ምርጫ ያኮሚፉም ጠመንጃ አንሰተዉ ኚቆዩት ጋር ዚታክቲክ ወዳጅነት ዚፈጠሩ ይመስላሉ። ዹሰላም መንገድ መጥበብና መዘጋት አመፅ ተቀባይነት እንዲያገጘ እያደሚገ ይገኛል። ኹዚህም አልፎ ሰለሰላማዊና ዚመሳሪያ ትግሎቜ (armed & peaceful resistance) ተጉዋዳኝነት ዚሚያሳዩ ፍልስፍናዎቜ እዚቀሚቡ ይገኛሉ። ይህንንም ሁኔታ ጎሚቀት ሀገሮቜ ለራሳ቞ዉ በሚጠቅም መንገድ ሂደቱን ሊቃኙት እንደሚፈልጉ ሳይታለም ዚተፈታ ጉዳይ ነዉ። በቀጠናዉ ያለዉን አጠቀላይ በሃገሮቜ መሃል ያሉትን ዉጥሚቶቜን ወደጎን አድርገን ዚሃገሪቱን ዚዉስጥ ዉጥሚት ብናይ ዚመጪዉ ግንቊት ምርጫ ወይም አንዳንድ ሰዎቜ እንደሚሉት ጥገናዊ ዹህገ መንግስት መሻሻል እዚህ ግባ ዚሚባል ፋይዳ እንደማይኖራቜዉ ግልፅ ነዉ።

ሰለዚህ በሀገራቜን ያሉትንና እዚተፈጠሩ ያሉትን ዉጥሚቶቜ ለመፍታት ወሳኝ እርምጃዎቜ መዉሰድ ያስፈልጋታል። ለዚህም ቁልፉዋ ዚምትገኘዉ በአብዛኛዉ ዚማእኚላዊ መንግስትን ስልጣን በሚቆጣጠሚዉ ብሄር ተኮር ድርጅት እጅ ቢሆንም ድርጅቱ ይህንን ሊሰራ ዚሚቜል መሪ ኚዉስጡ ለማዉጣጥ እስካሁን አልቻለም። ብሄራዊ አንድነትንና እኩልነትን ዚሚገነባፀእሞናፊና ተሾናፊ ዚሌለበት ዚፖለቲካ አስተሳሰብና አስተዳደር መመስሚት ዚዛሬዉ ዚሃገሪቱ ፈተናዎቜዋ ሲሆኑፀ እነዚህ ፈተናዎቜ ግን ዚዛሬ 119 እመት በፊት እነ አፄ ምኒልክን፡ እ቎ጌ ጣይቱን፡ ራሰ አሉላንፀ ፊታዉራሪ ሃብተ ጊዎርጊስንፀ ራስ ጎበናንና ሌሎቹን በሺህ ዚሚቆጠሩትን ዚአድዋን አርበኞቜ ገጥመዋቜዉ ኚነበሩት ፈተናዎቜ ጋር ዚሚወዳደሩ አይደሉም። እ.ኀ.አ ኹ1937ቱ ፈተናዎቜ ጋርም ዚሚወዳደሩ አይደሉም። በእነዛ ኚባድ ፈተናዎቜ ጊዜ ብዙ መስዋእትነት ተኚፍሎዋል። እነዛን ፈተናዎቜን ስንመሚምር ዚእኛ ትዉልድ ፈተና ዚኀትኖሎንሪክ ዚታሪክ መነጜር ወዎት እዚወሰደን መሆኑን መገንዘብና በቅን ልቩና ላይ ዹተመሰሹተ ብሄራዊ መግባባት ዚሚፈጠርበትን መንገዶቜ መሻት ነዉ። ቜግሮቜን መካድ ወይም መደበቅ ሳይሆንፀ በእዉቀት በዉይይት በዲሞክራሲና በፍትሃዊ ካሳ (restorative justice) ዚሚፈቱትን ዚታሪክ ጠባሳዎቜ እያጎሉ ጣት መቀስሩ ለማንም ጠቃሚ እንደማይሆን ማወቅ ነዉ። ዚዛሬ ተሜናፊዎቜ ነገ አሞናፊዎቜ ለመሆን እንዳይሰሩፀ ይህንንም በር በጊዜዉና በቅጡ በብሄራዊ እርቅና መካካስ መዝጋት እንጂፀ እንዎዉ በደሹቁ ዚርስ በርስ ጊርነት ሂደቶቜን እንደ ገድል እዚቆጠሩፀ ኚበሮ መምታቱፀ በግብር ኚፋዩ ገንዘብ ስርግና ምላሜ መደገሱፀ ለአንድነትና ለብሄራዊ መግባባት ጠቀሚ ርምጃዎቜ ሊሆኑ እንደማይቜሉፀ ኚድግሱ በሁዋላ ቢሆንምፀ ግንዛቀ መዉሰድ ያስፈልጋል።

ኹዚህም በላይ ኀትኖሎንትሪዝም ዚማእኚላዊ መንግስትን ስልጣን ቢይዝም ሆነ ባይዝ ዚሚያልመዉ ስለ አንድ ንፁህ ዚጠራ ዚተቀባፀወርቃማና እግዚአብሄር ስለመሚጠዉ ጭቁንና ስለተጎዳ ወዘተ ማህበሚሰብ ስለሚኖርባት ቅኖናዊት ሀገር (utopian state) መሆኑ መሚሳት ዚለበትም። በዚህም ዚተነሳ ዹተሹጋጋ ዚብዙሀን ብሄር ብሄሚሰቊቜ ሀገርን ማስተዳደር ኚባድ ፈተና ይሆንበታል። በብዙ ክልሎቜም በነፃ ምርጫ ማሜነፍ ያስ቞ግሚዋል። ቀልፍ ዚአስተዳደር ዚማኚላኚያ ዚኢኮኖሚ አዎታሮቜን ቃል እንደሚገባዉ ማስተዳደር ይሳነዋል። አዲሲቱ ኢትዮጵያ መሆን ያለባት ኚብሄርና ብሄሚስቊቜ (nations, nationalities, ethnic groups, volks) ዚተዉጣጡ ስብስቊቜ (ዹህገ መንግስቱን መግቢያ ይመልኚቱ) ተስማምተዉ ዚሚፈጥሩት ሀገር ናት ዹሚለዉም ምርጫ መር ኹሆነ ዲሞክራሲ ጋር ማጣጣም አስ቞ግሮታል። ስምምነቱም ካልሰራ ደግሞ አንቀፅ 39ን ተጠቅሞ መሄድ ይቻላል ዹሚለዉን መፈፅም ቀላል አለመሆኑን ተሚድቶታል። ዹሚሄደዉም ክልል ምንም እንኩዋን በአፍሪካም ሆነ በአወሮፓ ለጊዜዉ ዚሚታዚዉ ብሄሚሰብና ሃይማኖት ተኮር ዹሆነዉ ዚፖሊቲካ ምህንድስና ዉጀት አሉታዊ ቢሆንምፀ ዚተሻለ/ቜ አባት/እናት ሀገር መመስሚት ይቻላል ዹሚሉ አሁንም አልጠፍም። ይህንን አካሄድ መፋትሄ ነዉ ብሎ ሀገሪቱ ባለቜበት ሁኔታ ለህዝብ በሬፈርነደም ማቅሚብ ግን ሃላፊነት ዹጎደለዉ አካሄድ ነዉ። ዚጋራ እሎቶቜንፀ ክፉም ይሁኑ ደግ መኖራ቞ዉን መርሳትፀ ሰዎቜ ኚአንድ በላይ ማንነት (dual or multiple identity) እንደሚኖራ቞ዉፀ ዚሀገራት አመሰራሚት ሁል ጌዜ ያለቜግር አለመሆኑን በቅጡ አለመመርመርና ዚወዲፊቱን ጉዞ በቅጡ ማለም አለመቻልን ያመለክታል።

በመጚሚሻም በዉጭ ዹምንኖር ኢትዮጰያዎያን ባንፃራዊ ነፃነት ስለምንገኝና ኹጊዜ ወደጊዜ ቀጥራቜንም እዚበዛ ስለሄደፀ እንደ አድዋ አይነት ሃገር አቀፍ ዹሆኑ እሎቶቜ ኹማክበር ዹሚኹለክለን ነገር መኖር ዚለበትም። በሃገራቜንም ዹሰላም ድምፅ ኹፍ ብሎ እንዲሰማ መሞኹር ይኖርብናል። በመሬትና በአንዳንድ ጥቅሞቜ መደለልና ዹገዛ ጥላቜንን ሳይቀር መፍራት ዚለብንም። ራሳቜንን ኚፍርሃት ነፃ ማዉጣት ይገባናል። ስለ አሀጉራዊ ስለአፍሪካ ዲዚስፖራፀ ስለአፍሪካ አሜሪካዉያን ሰለሃገር አቀፍ እሎቶቜ ዉርስና ቅርሶቜ መናገር መጻፍፀ ማክበርና መዘክር ይኖርብናል። በተለያዩ ቊታዎቜ ያሉትን ዚታሪክ አሻራዎቜ (historical footprints) በምንቜለዉ ዘዮ መሚዳትፀማሰባሰብና ዚተዘሚፉት ቅርሳ ቅርሶቜ እንዲመለሱ መሞኹር ይገባናል። ዚአክሱም ሃዉልት መመለስ ዚመጀመሪያ እንጂ ዚመጚሚሻ መሆን ዚለበትም። ኚበስተሁዋላም ሆነ ኚፊት ሆነዉ ዚሚሰሩትንና ዚሚሚዱትን ማመስገን ይገባል። ዶ/ር አበራ ሞላና አቶ ኪዳኔ አለማዹሁ በመካኚላቜን መገኘታ቞ዉና እዚሰሩ ያሉትንም ልናዉቅላቾዉና ልናበሚታታ቞ዉ ይገባል። በብሄር ተኮር ፖለቲካ ዉስጥ ራሳቜንን አጥሚንፀ ታሪካቜን ዚግጭትፀዚሚሃብ፡ ዹቾነፈርና ዚስደት ብቻ እንዳይሆንፀዛሬ አፍሪካ አሜሪካዉያን ዚገቡበትን ራስን ያለማወቅ ቀዉስ (identity crisis)ፀ ሌሎቜ አፍሪካዉያን ወገኖቻቜን ያለባ቞ዉን ዚራስ መተማመን ቜግርፀ ልጆቻቜን በአዉሮፓ እንዳሉት አናሳ ኮሚኒቲዎቜፀ ዚኢኮኖሚዉፀዚፖለቲካዎና ዚዕዉቀት ጭራፀበሁዋላም ዚአሀገሮቹ ባዐዳን እንዳይሆኑፀ ኚወዲሁ ማስብና ዘዮ ማግኘት ዚእኛ ዚመጀመሪያ ትዉልድ ፈላሟቜ (immigrants) ፈተና ነዉ።

↧

በትግል ሒደት ዚሚኚሰቱ እንቅፋቶቜን በጥንካሬ ልናልፋቾው ያስፈልጋል:: –‎ምንሊክ ሳልሳዊ‬

$
0
0

ኢትዮጵያውያን ለውጥ እንፈልጋለን:: ለውጥ እንፈልጋለን ብለን ለትግል ስንነሳ መንገድ ሁሉ አልጋ በአልጋ ይሆንልናል ማለት አይደለም::በትግሉ ውስጥ ዚሚኚሰቱ እሟህ እና አሜኬላዎቜ እንቅፋት ሆነው ኚስንዎው እኩል እንደ እሞት ዚሚያብቡ እንክርዳዶቜ እዚሰሚጉ በመግባት ትግሉን ለማኮላሞት አሊያም ደሞ ተያይዘው ለመጥፋት በሚያሎሩት ደባ ዚህዝብ ልጆቜ በሚያደርጉት ተጋድሎ እነዚህን እንቅፋቶቜ ማስወገድ እና በጥንካሬ ጋሬጣውን ማለፍ ዚሚጠበቅበት ወቅታዊ አጋጣሚዎቜ ሳንዘናጋ ልንጠቀምበት ይገባል:: በትግል ጊዜ ዚሚኚሰቱ እንቅፋቶቜ ለነገ ትልቅ ትምህርት ዹሚሆኑ ወርቃማ ጊዜያት አድርገን ልንማርባ቞ው ይገባል::
ኢትዮጵያውያን ላለፉት 24 አመታት በጫንቃቜን ላይ ዹተቀመጠውን አምባገነን ስርአት ለማስወገድ በተገኘው መንገድ ታግለን በወያኔ መቃብር ላይ ነጻነታቜንን ለማሚጋገጥ ሁላቜንም በተለያዩ ዚትግል ስልቶቜ ደፋ ቀና እያልን ዚምንገኝበት ወቅት ላይ መኚሰታቜን እሙን ነው:: ይህ ትግል ለለውጥ እና ለነጻነት መደሹጉ እና ዚጋራ ጠላት ዹሆንው ወያኔ ላይ ማተኮሩ ደሞ ሕዝባዊ አንድነቶቜ እንዲጎለብቱ አስታውጟ ሲያበሚክት ያልበሰሉ እና ዚፖለቲካ እውቀቱ ዚሚያንሳ቞ው በትግሉ ዙሪያ ሰበብ በማብዛት ዋጋ ባሌላ቞ው ነገሮቜ ላይ በማተኮር እንዲሁም በሌላው ዘርፍ ለሆዳ቞ው ተገዢ በመሆን ሌላውን አሳልፎ በመስጠት አንድም ኹሃገር በመውጣት አልያም ኑሯ቞ውን በሃገር ውስጥ በማደላደል ትግሉን ለራስ ጥቅም ብሎም ሌላውን ለመጥለፍ ሲጠቀሙበት ማዚት ዚሚያም ጉዳይ መሆኑ ዹዚህን ሰሞን ጡዘቶቜ ያሳያሉ::
ወቅቱ ትግሎቜ ተፋፍመው ሕዝባዊ ድሎቜ በሚገኙበት በአሁን ወቅት ዹሃገር ቀት ትግሎቜን እና በዳር ሃገር ያሉ ትግሎቜን በማስተባበር አንድ ወጥ ዹሆነ ዚትግል ስትራ቎ጂ በሚቀጣጠልበት ጊዜ ላይ በትግል ውስጥ በሚኚሰቱ እንቅፋቶቜ ራሳቜንን ሳናዘናጋ አሊያም እንቅፋቶቜን ሌላውን ለመጥለፍ እና ለማደፍሚስ ሳንጠቀምበት በሰለጠነ መልኩ ኚተኚሰቱ ቜግሮቜ ተምሹን ለአዳዲስ ስልቶቜ ጥንካሬያቜንን ማደስ ይገባናል::በትግል ውስጥ ዚሚኚሰቱ አሜኬላዎቜ/አሚሞቜን ነቅሎ ለመጣል ዋናው እና መጀመሪያ ዚሚያስፈልገው ዹኛ እና ዹኛ ጥንካሬ ነው::አንዳንድ ጊዜ በሚደርሱ እንቅፋቶቜ ሳንዘናጋ እና ሳንገዳገድ በራስ መተማመን እና ዚትግል ጜናትን በውስጣቜን በማስሚጜ ለተሻለ ድል መገስገስ አንዱ ዚትግል ስልት ሊሆን ይገባል::ጥንካሬ ኚራስ መተማመን እና ኚጜናት እንደሚፈጠር እና ብሚት ሆኖ መገኘት እንዲሁን ራስን በዹጊዜው እያዳበሩ መታገል ኚዝገትነት ይኹላኹላል::ዛሬ ላይ ለሚገጥሙ እንቅፋቶቜ ለመሾፋፈን ኚመሮጥ በጊዜው ተመካክሮ እና ተወያይቶ ቜግሮን በመፍታት ለነገ ትግል ሂደት መንገድ መጥሚግ ዹሚጠበቀው ክኛ ሆኖ ሳለ እንቅፋቶቜን/ቜግሮቜን በጊዜው ካላስወገድን እና ኹሾፋፈንን ዹተገላለጠ እና ዚፈነዳ እለት ትልቅ ጉዳት እና ተአማኒነት ሊያሳጣ ይቜላል::
በትግል ውስጥ ሊኚሰቱ ዚሚቜሉ እንቅፋቶቜን በጥንካሬ ልናልፋቾው ዚሚገባው እንግዲህ ኹዚህ አኳያ ነው::ጥንካሬያቜን ነገ ለሚፈጥሚው ትውልድ ትልቅ ትምህርት እና ዚነጻነት ባለቀት ስለሚያደርገው ዚሃገራዊ እና ዚህዝባዊ ዚትግል ሃላፊነቶቜን ተሾክመን በድን አደባባይ ለማስቀመጥ እና ታላቅ ዹሆነ ዚለውጥ አብዮት አቀናጅተን በመፍጠር ሳንዘናጋ ዚትልቅ ህዝባዊ ድል ባለቀት ለመሆን በአንድነት እንጠንክር:: ‪

↧
↧

ዹተቃዋሚ ፓርቲዎቜ አመራሮቜ ዚእምነት ክህደት ቃላቾውን ‹ሰጡ› –ነገሹ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

$
0
0

‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ብ቞ኛው አሞባሪ ህወሓት/ኢህአዎግ ነው››

አብርሃ ደስታ

‹‹ዚጊር ቜሎት በሚመስል ቜሎት እዚተንገላታን ነው››

ዚሺዋስ አሰፋ
በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ ዚክስ መዝገብ ዚሜብር ክስ ዚተመሰሚተባ቞ው ዹተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮቜና ሌሎቜ በተመሳሳይ መዝገቡ ዚተካተቱ ተኚሳሟቜ በተኚሰሱበት ድርጊት ላይ ዚእምነት ክህደት ቃላቾውን ሰጡ፡፡
ዚሰማያዊ ፓርቲ፣ ዚአንድነት እና ዹዓሹና ትግራይ አመራሮቜን ጚምሮ 10 ተኚሳሟቜ ዛሬ መጋቢት 10/2007 ዓ.ም በፌደራሉ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ልደታ 19ኛ ወንጀል ቜሎት ዚቀሚቡ ሲሆን ተኚሳሟቜ በቀሚበባ቞ው ክስ ላይ ዚእምነት ክህደት ቃላቾውን ሰጥተዋል፡፡ በዚህ መሰሚት ኹአንደኛ ተኚሳሜ ዘላለም ወርቃገኘሁ ጀምሮ፣ ‹‹በክሱ ላይ ዹተመለኹተውን ድርጊት ፈጜመዋል ወይስ አልፈጾሙም?›› ዹሚል ተመሳሳይ ጥያቄ ለእያንዳንዳ቞ው ዹቀሹበላቾው ሲሆን ብዙዎቹ ተኚሳሟቜ ምላሻ቞ውን በቀጥታ ለመስጠት አለመፈለጋቾውን አሳይተዋል፡፡
1ኛ ተኚሳሜ ዘላለም ወርቃገኘሁ ለቀሚበለት ጥያቄ፣ ‹‹በአቃቀ ህግ እና በፖሊስ ተቀነባብሮ ዚቀሚበብኝን ክስ በተመለኹተ ለክሱ እውቅና ላለመስጠት ምንም አልልም፡፡ በክሱ ላይ አስተያዚት በመስጠት ለጾሹ-ሜብር አዋጁ እውቅና መስጠት አልፈልግም›› ዹሚል መልስ በመስጠቱ ፍርድ ቀቱ ክሱን ክዶ ቃል እንደሰጠ አድርጎ መዝግቊታል፡፡
2ኛ ተኚሳሜ ሀብታሙ አያሌው በበኩሉ ‹‹በክሱ ላይ ዹተመለኹተውን ድርጊት እንዳልፈጞምኩ እንኳን እኔ ኚሳሟቌም በደንብ ያውቃሉ፡፡ ኚሳሟቌ እኔ ድርጊቱን ዹመፈጾም ፍላጎቱም ሀሳቡም እንደሌለኝ ያውቃሉ›› ብሏል፡፡
3ኛ ተኚሳሜ ዳንኀል ሺበሜ ደግሞ፣ ‹‹እኔ ስለ ሜብር ዚሰማሁት ኚአልቃይዳው መሪ ኊሳማ ቢላደን እና መለስ ዜናዊ ነው፡፡ እኔ አሞባሪ አይደለሁምፀ ሀሳቡም ሆነ ፍላጎቱም ዚለኝም፡፡ ባህሌና እምነ቎ም አይፈቅድልኝም›› ሲል ለፍርድ ቀቱ አስሚድቷል፡፡
4ኛ ተኚሳሜ አብርሃ ደስታ ‹‹አሞባሪ ማለት ዚፖለቲካም ሆነ ሌላ ዓላማውን ሰላማዊ ዜጎቜን በማሾበር ለማስፈጞም ዚሚሰራ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ብ቞ኛው አሞባሪ ድርጅት ህወሓት/ኢህአዎግ ነው፡፡ እኔ ደግሞ ዹዚህ አሞባሪ ድርጅት ተቃዋሚ ነኝ›› ብሏል፡፡
5ኛ ተኚሳሜ ዚሺዋስ አሰፋ በበኩሉ፣ ‹‹በመጀመሪያ ለመጚሚሻ ጊዜ ስለሆነ ዹምናገሹው እንዳታቋርጡኝ አደራ እላለሁ፡፡ ክሱ ቅንብር ነው፡፡ ዳኞቜም ህጉ ዚሰጣ቞ው ነጻነት አይታይባ቞ውም፡፡ ይህ 19ኛ ወንጀል ቜሎት ዹጩር ቜሎት ነው ዚሚመስለኝ፡፡ ስለሆነም ዹጩር ቜሎት በሚመስል ቜሎት እዚተንገላታን ነው›› ሲል ተናግሯል፡፡ ዚሺዋስ በዳኞቜ በተደጋጋሚ ንግግሩ እንዲቅሚጥ ተደርጓል፡፡ በመጚሚሻም ክሱን ክዶ ቃል ሰጥቷል በሚል ተመዝገቊለታል፡፡
6ኛ ተኚሳሜ ዮናታን ወልዎ፣ ‹‹ዚተዘጋጀብኝን ክስ ያለፍቃዎ እንድተውን እዚተገደድኩ ነው›› ብሏል፡፡
7ኛ ተኚሳሜ አብርሃም ሰለሞን ደግሞ፣ ‹‹ዚተቀነባበሚ ክስ ላይ ምንም ማለት አይቻልም›› ብሏል፡፡
8ኛ ተኚሳሜ ሰለሞን ግርማ፣ ‹‹ነጻ ሰው ነኝ፡፡››
9ኛ ተኚሳሜ ባህሩ ደጉ ‹‹ባህሉንና ፈጣሪውን ኚሚያኚብር ማህበሚሰብ ወጥቌ አሞባሪ ልሆን አልቜልም›› ሲል አስሚድቷል፡፡
10ኛ ተኚሳሜ ተስፋዬ ተፈሪ ደግሞ፣ ‹‹ድርጊቱን አልፈጞምኩም›› ብሏል፡፡
በአጠቃላይ ተኚሳሟቜ ክሱ ላይ ዹተጠቀሰውን ድርጊት ክደው ቃል በመስጠታ቞ው አቃቀ ህግ ምስክሮቜን እንዲያሰማ ለግንቊት 13፣ 14፣ 15/2007 ዓ.ም ለተኚታታይ 3 ቀናት ምስክር እንዲሰማ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡11079613_792950774123192_2887233270806843494_n

↧

እናቶቜን ዚሚያስለቅስ አገዛዝ –ዚፍርድ ድቀት ዉሎ (ለገሰ ወልደሃና)

$
0
0

ዚካቲት 10/2007 ዓም ዹ28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ዚተጠዚቀበት ዹነዘመነ ምህሚት ቜሎት፣ በቀጠሮው መሠሚት፣ ዛሬ መጋቢት 10/2007 ዓም ተሰይሟ። ዘመነ ምህሚት፣ መለሰ መንገሻና ሌሎቜ ወደ 25 ዹሚጠጉ ወጣቶቜ በማእኚላዊ ፓሊሶቜ ታጅበው 8:ሰአት 20 አካባቢ ፍርድ ቀት ግቢ ገቡ። እንደተለመደው በርቀት እጃቻቜንን በማውለብለብ ሰላም አልና቞ው። እነሱም ባልታሰሚው እጃ቞ው አፀፋውን መለሱልን።
ዘመነ ምህሚት ብዙም አልተጎሳቆለም። መለሰ መንገሻ ግን በጣም ኚስቷል። ሰውነቱ ቢጫ ሆኗል። እንደዛም ሆኖ ፈገግታ ግን አልተለያ቞ው። ቜሎት ኚመግባታ቞ው በፊት ዚተቀመጡበት አግዳሚ ወንበር ላይ ሆነው፣ በምልክት ለመነጋገር ሞክሹን ለመግባባት ቜለን ነበር። ነገር ግን ፓሊሶቜ ኹኛ ጋር ዚሚያደርጉት ዚምልክት መግባባት አይተው፣ ፊታ቞ውን አዙሹው አስቀመጧ቞ው ። ተስፋ ሳንቆርጥ ሞኚርን። አልተሳካም።
ዚቜሎት ሁኔታ እንደሚታወቀው በዝግ ዚታዚ በመሆኑ ዹነበሹውን ሁኔታ ማወቅ አይቻልም። ዘመነና መለሰ መንገሻ ቜሎት ዚገቡት ተለያይተው ነው። ኹዚህ መሚዳት ዚሚቻለው ዚተኚሰሱበት መዝገብ ይለያያል ማለት ነው ። ሁለቱም ቜሎት ሲገቡ ሌሎቜ ወጣቶቜ አብሚዋ቞ው ገብተዋል።
ዚዛሬው ዚቜሎት ሁኔታ ተጚማሪ ዹ28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ፓሊስ ጠይቆ ለመጋቢት 08/7007 ዓም ተቀጥሯል።
አንድነት ዘመነ ምህሚት፣ ዹዘመነ ምህሚት ዚበኩር ልጅ፣ በፍርድ ቀት አልተገኘም። ዚሕጻን አንድነትን ቊታ ተክተው፣ ኹሰሜን ጎንደር ተጉዘው ዚመጡት፣ ዚቆራጡ ታጋይ ዘመነ ምህሚት እናት ነበሩ። እኚህ እናት ታማሚ ና቞ው። ዹወለደ አንጀታ቞ው አልቜል ብሏ቞ው ህመማቾውን ቜለው፣ ኹሰሜን ጎንደር፣ ኹ700 ኪሎሜትር በላይ ተጉዘው፣ «ልጄ በህይወት መኖሩን ካላዚሁ አላምንም» ብለው፣ አራዳ ዚመጀመሪያ ፍርድ ቀት ተገኝተዋል። በጣም ያሳዝናሉ።
ዚመጡበትን ምክንያት ዹልጃቾውን በህይወት መኖር አለመኖር ለማሚጋገጥ ነበር። በካ቎ና ታስሮም ቢሆን አይተዋል። በውስጣ቞ው ምን እንደተሰማ቞ው ባላውቅም። ጥልቅ ዹሆነ ሀሳብ ገብቷ቞ዋል። ለሰው ኹመናገር ዝምታን ። ኹኚህ ዹጀግና እናት ጋር ትንሜ ለመጚዋወት ሞክሹን ነበር ። እንባ቞ው እዚቀደማ቞ው ማውራት አልቻልንም። በመጊሪያ቞ው ጊዜ መንኚራተት በጣም ያማል። እስኪ ዹኝህ እናት ፀሎት ተሳክቶ ዘመነ ተፈቶ ኚመንኚራተት ያድና቞ው ዘንድ እንፀልይላ቞ው ።10659312_793097314108538_312360749022107000_n

11008829_793097307441872_607639602043269078_n

↧

ማርቜ 8’ትን ስናስታውስ በላይ ገሠሠ

↧

ዹ9ኙ ፓርቲዎቜ ትብብር መጋቢት 20/2007 ዓ.ም ለህዝባዊ ሰልፍ ዚመሚጣ቞ውን 15 ኚተሞቜ ይፋ አደሹገ!

$
0
0

ሰማያዊ ፓርቲ ባህር ዳር ቅርንጫፍ ቢሮው እንደተዘጋበት አስታወቀ:: በጋሞ ጎፋ በቅስቀሳ ላይ ዚነበሩ ዚሰማያዊ አባላት ታሰሩ::

ዹ9ኙ ዹተቃዋሚ ፓርቲዎቜ ትብብር ህዝባዊ ዚድጋፍ ሰልፍና ዚምርጫ ቅስቀሳ ለማካሄድ ዚመሚጣ቞ውን 15 ኚተሞቜ ይፋ አደሚገ፡፡ ትብብሩ በተመሳሳይ ሰዓት በ15 ዋና ዋና ዚሀገሪቱ ኚተሞቜ ህዝባዊ ዚድጋፍ ሰልፍ ለማድሚግ ቀደም ብሎ አሳውቆ እንደነበር ይታወሳል፡፡

በዚህ መሰሚት ዹ9ኙ ፓርቲዎቜ ትብብር መጋቢት 20/2007 ዓ.ም በተመሳሳይ ሰዓት ሰልፉን ዚሚያካሂድባ቞ው ኚተሞቜ ዚሚኚተሉት ሆነዋል፡፡ እነዚህም አዳማ፣ ባህር ዳር፣ አርባ ምንጭ፣ ደብሚ ታቊር፣ ሐዋሳ፣ ጅማ፣ ደብሚ ብርሃን፣ ወልቂጀ፣ አሰበ ተፈሪ (ጭሮ)፣ ወላይታ ሶዶ፣ ደሎ፣ ዱራሜ፣ ደብሚ ማርቆስ እና ሆሳዕና ና቞ው፡፡ትብብሩ ‹‹መጋቢት 20 በፍጹም አይቀርም›› በሚል ለህዝቡ ዚድጋፍ ሰልፍ ጥሪ ያደሚገ ሲሆን፣ ኚተሞቹ ዚተመሚጡትም ፓርቲዎቹ በዚአካባቢዎቜ ባቀሚቡት እጩ ብዛት መሰሚት እንደሆነ ገልጹዋል፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ ደግሞ በዋና ኹተማዋ አዲስ አበባ ዹሚደሹገው ዚድጋፍ ሰልፍ በተመሚጡት ኚተሞቜ ዹሚደሹገው ሰልፍ በተኹናወነ በሳምንቱ ይደሹጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
===================================
ሰማያዊ ፓርቲ ባህር ዳር ቅርንጫፍ ቢሮው እንደተዘጋበት አስታወቀ

ሰማያዊ ፓርቲ በባህር ዳር ኹተማ ዹኹፈተው ቢሮው በአኚራይ ላይ በተፈጾመ ኹፍተኛ ወኚባና ማስፈራሪያ ምክንያት እንደተዘጋበት በስፍራው ዚፓርቲው አስተባባሪ ለነገሹ ኢትዮጵያ ገለጞ፡፡

በባህር ዳር ዚፓርቲው አስተባባሪ አቶ አዲሱ ጌታነህ እንደገለጹት ቅርንጫፍ ቢሮው ኚትናንት ጀምሮ ዚፓርቲው ንብሚቶቜ ውስጥ እንዳሉ ተቆልፏል፡፡ አቶ አዲሱ ቢሮውን ያኚራዩት ሰው በተደጋጋሚ ኚፖሊስ፣ ኚኢህአዎግ ካድሬዎቜና ኚደህንነት ሰዎቜ ዛቻና ማስፈራሪያ እዚደሚሰባ቞ው እንደሆነ በመግለጜ ቀቱን እንዲለቁላ቞ው ሲነግሯ቞ው እንደነበር አስታውሶ፣ ሆኖም ግን ፓርቲው ዚአንድ አመት ውል ስላለው መልቀቁን እንዳልፈለገ ገልጹዋል፡፡

አኚራዩዋ ‹‹ቀሪ ብራቜሁን እመልሳለሁ፡፡ ዚሚደርስብኝን ጫና መቋቋም አልቻልኩምና ውጡልኝ፡፡ ሰዎቹ በዱርዚዎቜ እንደሚያስደበድቡኝ መዛታ቞ውን ስለሰማሁ ቢሯቜሁን ቆልፌዋለሁ›› ማለታ቞ውን ዹጠቀሰው አቶ አዲሱ፣ በተለይ በኹተማዋ ዹበላይ ዘለቀ ቀበሌ ዚጞጥታ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ጌታ቞ው ግዛቾው አላስፈላጊ ወኚባውን በማስተባበር ላይ መሆኑን አስሚድቷል፡፡ፓርቲው ጉዳዩን ወደ ህግ እንደሚወስደውም አቶ አዲስ ጚምሮ ገልጹዋል፡፡
================================
በጋሞ ጎፋ በቅስቀሳ ላይ ዚነበሩ ዚሰማያዊ አባላት ታሰሩ

በጋሞ ጎፋ ዞን ኮንሶ ወሚዳ በምርጫ ቅስቀሳ ላይ ዚነበሩ ስምንት ዚሰማያዊ ፓርቲ አባላት መታሰራ቞ውን ዹዞኑ ዚፓርቲው አስተባባሪ ለነገሹ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
አባላቱ ኚመጋቢት 9/2007 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡ በእስር ላይ ዚሚገኙት ስምንቱ ሰዎቜ ዚሚኚተሉት ና቞ው፡-
1. ካርታ ካርኪ
2. ኩንሳ ካፒሊ
3. ታሪኩ አንካሶ
4. ካያና ካላታ
5. ገላዬ ካይድራ
6. ካርታ ሀይቶ
7. ኩንሱ ካምባ
8. ሆዳ ሆልጥሜ

ና቞ው፡፡11052444_1567287580209106_4888801381358411345_n

↧
↧

ሠላማዊ ትግላቜን ነፃነት እስኪታወጅ እኩልነት እስኪሰፍን ይቀጥላል! –ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ብሄራዊ ንቅናቄ

$
0
0

ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ብሄራዊ ንቅናቄ በሃገራቜን ኢትዮጵያ አስተማማኝና ዘለቄታዊ ሠላም፣ እኩልነት፣ ፍትህና፣ ዚፖለቲካ መሚጋጋት ይሰፍን ዘንድ ቀና ራዕይ አንግበው በተሰባሰቡ ወጣት ኢትዮጵያውያን ዚተመሰሚተፀ በሃገራቜን ብ቞ኛው በወጣቶቜ ዚተገነባና ዚሚመራ ንቅናቄ ነው። ንቅናቄአቜን ላለፋት አመታት ዹንቅናቄውን አቅም ለማጐልበትፀ ሰፊና ጠንካራ መሰሚት ያለው ሁለገብ ተቋም ለመገንባትፀ ዚድርጅታዊ መዋቅሩን ጚምሮ ሌሎቜ ወሳኝ መሰሚታዊ ዚማስፋፋትና ዚማደራጀት ስራዎቜን ሲሰራ ቆይቷል። በመሆኑም ዛሬ ንቅናቄያቜን ኚአምባገነኑ ዚህወሓት/ኢህአዎግ ዚደህንነት መሚብ ዚፀዳፀ እራሱን ኹማንኛውም ዚውስጥና ዹውጭ ጥቃት በአስተማማኝ ሁኔታ ዹመኹላኹል ብቃት ያለውፀ በርካታ እንቅስቃሎዎቜንና ዲሲፕሊኖቜን በተቀናጀ መልኩ ማኹናወን ዚሚቜል ጠንካራ ተቋም መሆን ቜሏል።

ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ብሄራዊ ንቅናቄ ኹአጠቃላይ ዚህዝብ ብዛት ኹ75% በላይ ዹሚሆነው ወጣቱ በመሆኑፀ ይህ ወሳኝ ዚህብሚተሰብ ክፍል ዚዲሞክራሲ ሥርዓትን ለመመስሚትና ለማጐልበት በሚደሹግ ትግል ውስጥ ግንባርቀደም ሚና ዚመጫወት ትውልዳዊ ሃላፊነት እንዳለበት በፅኑ ያምናል። በመሆኑም ንቅናቄአቜን ይህን ፅኑ እምነት መሰሚት በማድሚግፀ ወጣቱ ትውልድ ሃላፊነት ዚመሚኚብና በብቃት ዚመወጣትፀ እንዲሁም በተደራጀ መልኩ በጋራ ዚመሥራትና ለውጀት ዚመብቃት ሙሉ አቅሙ እንዲኖሚው ለማስቻል መጠነ ሰፊ እቅዶቜን ነድፎ በመተግበርፀ ዚወጣቱን እምቅ ቜሎታና ብቃት በተግባር አስመስክሯል። ንቅናቄአቜን ኚተመሰሚተበት ኹ2003 ዓ.ም. ጀምሮ በርካታ ተግባራትን ያኚናወነ ሲሆንፀ በተለይ በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገራት ዚሚኖሩ ወጣቶቜን ወደተመሰሚተለት ታላቅ ራዕይ ለማምጣት ዚግንኙነትና ዹመሹጃ ልውውጥ መሚብ በመሆንፀ ብሎም በአለም ዙሪያ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወጣቶቜን በስሩ በማደራጀትና በማንቃት ለሃገር ተቆርቋሪ ዜጋን በአስተማማኝ ሁኔታ መገንባት ቜሏል።

ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ብሄራዊ ንቅናቄ በሃገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ስርአትን ለማስፈን በሚደሹገው ትግል ዚበኩሉን አስተዋፅኊ ለማበርኚትና ዚተነሳለትን ታላቅ ራዕይ እውን ለማድሚግፀ ኚሌሎቜ ዚፖለቲካ፣ ዚሲቪክና፣ ዚሰባዊ መብቶቜ ድርጅቶቜ ጋር በመተባበርና ጠንካራ ስምምነቶቜን በመመስሚት በስፋት እዚሰራ ይገኛል። ንቅናቄአቜን በሰላማዊ ዚትግል ስልት በሃገራቜን ለውጥ እንዲመጣ ኚሚታገል ማንኛውም ተቋም ጋር በመተባበርና በመደገፍ በርካታ ተግባራትን ያኚናወነ ሲሆንፀ በተለይ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞቜ ላለፉት ሊስት ተኚታታይ አመታት ባካሄዷ቞ው ሠላማዊ መብትን ዹመጠዹቅና ዚማስኚበር እንቅስቃሎዎቜ ዹሚሠማውን ኹፍተኛ አድናቆት እያስታወቀፀ በቀጣይ ለሚያደርጉት ሠላማዊ እንቅስቃሎዎቜ ሁሉፀ አባላቱን በማስተባበርና ሙሉ ሃይሉን በመጠቀም ስኬታማ እንዲሆን ዚሚሰራ መሆኑን ኚወዲሁ ቃል በመግባት ያሚጋግጣል። ኹዚህም በተጚማሪ በወጣቶቜ ዚተገነባውን ዚሰማያዊ ፖርቲን በአዲስና በተቀናጀ መልኩ ድጋፍ ለመስጠት ሰፋ ያለ እቅድ ይዞ ተግባራዊ ለማድሚግ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን በሙሉ ልብ ያሚጋግጣል።
ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ብሄራዊ ንቅናቄ አባላትፀ እንዲሁም መላው ዚኢትዮጵያ ወጣት ሆይፀ ዛሬ ሃገር እያለህ እንደሌለህፀ መስራት እዚቻልክ ተመፅዋቜፀ ተምሹህ ራስክን ማሻሻል እዚቻልክ እድሉን ተነፍገህፀ በቜሎታህ ሳይሆን ለገዢው መደብ ባለህ ቀሚቀታ ኹሃገርህ ማግኘት ዚምትቜላ቞ው እድሎቜህን ሁሉ ተነጥቀህፀ እጣ ፈንታህ በጥቂት ግለሰቊቜ በጐ ፈቃድ ስር ብቻ መውደቁን ካንተ በላይ ዚሚያውቀውና ዹሚገነዘበው ዚለም። በመሆኑም ሳትፈልግ ዚተጫኑብህ ምስቅልቅልና ጥልቅ ቜግሮቜን አስወግደህፀ በተሻለ ዚህይወት ተስፋ ዚመተካት አቅሙም ጉልበቱም ያንተ ነውናፀ ኚዛሬ ጀምሮ ቆርጠህ በመነሳትፀ ብሎም ኚሰማያዊ ፓርቲ ጐን በፅናት በመቆምና ሙሉ ድጋፍ በመስጠትፀ እንዲሁም ዚሙስሊም ኢትዮጵያውያን ትግልን ዚሚመራው አካል (ድምፃቜን ይሰማ) አመራር ፍፁም ሠላማዊና በሳል መሆኑን ስለምትሚዳውፀ በመሆኑም ዹሚቀርበው ዚአመራር ብቃት ነፃነትህን ለማስኚበር በቂ ዚትግል ስትራተጂ እንደሆነ ስለሚታመንፀ ዚሚካሄደውን ትግልና ዹሚተላለፈውን ዚትግል መመሪያ በቅርበት በመኚታተልና ተግባራዊ በማድሚግፀ ወደ ታሪካዊው ዚለውጥ ጐዳና በሙሉ ልብ ተቀላቅለህ ታሪካዊ ሃለፊነትህን ትወጣ ዘንድፀ ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ብሄራዊ ንቅናቄ በአክብሮት ሃገራዊ ጥሪውን ያቀርባል።

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ ብሄራዊ ንቅናቄunnamed

↧

“ዚልማታዊ” እና “ሁለገብ” ጋዜጠኞቜ አንድም –ሁለትነትም ያሬድ ኃይለማርያም

$
0
0

ጋዜጠኝነት ትልቅ ክብር ዚሚሰጠው፣ ዚራሱ ዹሆነ መርህና ስነ-ምግባር ያለው፣ ጠያቂነትን ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነትንም በውስጡ ዚያዘ ዚሙያ መስክ ነው። ለዛም ነው ጋዜጠኛ ዚሕዝብ አንደበት፣ አይንና ጆሮ ነው ዚሚባለው። ሕዝብ በሚኚበርበት ቊታ ሁሉ ጋዜጠኛም ይኚበራል። ሕዝብ በሚዋሚድበት፣ በሚታፈንበትና በሚዋኚብበት ስፍራም ጋዜጠኛ ይዋሚዳል፣ ይሳደዳል፣ ይታፈናል፣ ይዋኚባል፣ ይታሰራል፣ ሲኚፋም ይገደላል። ይህም በሕዝብ፣ በመንግሥትና በጋዜጠኛ መካኚል ያለውን ቁርኝት በደንብ ያሳያል። ሕዝብና መንግሥት ልብ ለልብ ሊገናኙ ዚሚቜሉት ጋዜጠኛ ሲኖር ነው። ዚሁለቱን ዚልብ ትርታ እያደመጠና ያንዱን ላንዱ እያስደመጠ በመካኚላ቞ው ገደል እንዳይኖር ድልድይ ሆኖ ያገለግላል።

ጋዜጠኞቜ ይህን ታላቅ ኃላፊነት ለመወጣት ኚሚጠበቅባቜው ነገሮቜ ዋነኛውና መሰሚታዊው ነገር ዚሙያውን ሥነ-ምግባርና መርሆዎቜ ጠንቅቆ ማወቅና ለመተግበርም መጣር ነው። በዚህ ሙያ ላይ ዚተሰማራ ሰው ምንም ያህል በሙያው ቢሰለጥንና ቢመራመር ኚመርሆቹና ኚሥነ-ምግባሩ በራቀ ቁጥር ኹላይ ዹተጠቀሰውን አሉታዊ ሚና ኚመጫዎት ይልቅ ለሚኖርበት ማኀበሚሰብ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ዋነኛ ጠንቅ ይሆናል። ዚጋዜጠኝነት ሙያ አንድን ማኅበሚሰብ በሚዘሹጋው ዹመሹጃ መሚብ ዚማዋሃድና ዚማቀራሚብ ኃይል ያልውን ያህል በሥነ-ምግባር ብልሹዎቜ እጅ ሲወድቅ ደግሞ እንደ ኒውክለር ቊንብ ሕዝብን ዚማፋጀትና ለኹፋ እልቂት ዚመዳሚግም አቅምም አለው። ለዚህም ዚሩዋንዳዉን ዹዘር እልቂት ያፋፋሙትን ዚአገሪቷ መገናኛ ብዙሃን ልብ ይሉዋል። አንድ ሰው በጋዜጠኝነት ሙያ ሲሰማራ ቢያንስ እነዚህን አምስት መርሆዎቜ ሊሚዳና ሊያኚብር ይገባዋል። እነሱምፊ

1. እውነተኝነት እና ትክክለኝነት፣
2. ገለልተኝነት (ኚፖለቲካ፣ ኚኃይማኖትና ኚሌሎቜ ሚዛንን ኚሚያስቱ አቋሞቜ)፣
3. ፍትሐዊነት እና ሚዛናዊነት፣
4. ሰብአዊነት፣
5. ለሚሰራዉ ሥራ ተጠያቂነት

ይህን ጜሑፍ እንድጜፍ ወዳስገደደኝ ጉዳይ ልመለስ። ኢትዮጵያ ውስጥ ዚጋዜጠኝነት ሙያና ሥነ-ምግባር ያለበትን ደሹጃና ዝርዝር ታሪኩን በቅጡ ዹሚቃኝ ጥናታዊ ጜሑፍ ዚማቅሚቡን ሥራ በሙያው ጥርሳ቞ውን ለነቀሉበትና አቅሙ ላላቾው ባለሙያዎቜ ልተውና ዹግል ትዝብ቎ን ላስቀምጥ። ዚወያኔ ዹአገዛዝ ሥርዓት በኢትዮጵያ ላይ ካደሚሳ቞ው ትላልቅ ኪሳራዎቜ መካኚል አንዱ ሃሳብን በነጻነት ዚመግለጜ መብትን ማዳፈኑ ነው። ይህን እኩይ ተልኮውንም ለማሳካት በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ ጋዜጠኞቜን በተለያዩ ጊዜያት እያሰሚ፣ እዚደበደበ፣ በሃሰት ክስ እዚወነጀለና ኹአገር እያሰደደ በማቆጥቆጥ ላይ ዹነበሹውን ዚሕዝብ ነጻ ዚመወያያ መድርክ በጚቅላነቱ ቀጭቶታል። ወያኔ ነጻ ዚውይይት መድሚኮቜን ለማንጠፍ ያልፈነቀለው ድንጋይ ዚለም። ጋዜጠኞቜን በጞጥታ ኃይሎቜ ማዋኚቡና በጡንቻው ማሾማቀቁ አልበቃ ብሎት ሕገ-መንግሥቱን ዚሚሜሩ ሕጎቜንም ጭምር በማጜደቅ አፈናዉን ሕጋዊ አድርጎታል። ይህ አይነቱ በነጻ ሚዲያው ላይ ያነጣጠሚው ዚማያባራ ዱላ ሕዝብ ነጻ ዚመወያያ መድርክ እንዳይኖሚው ኚማድርግም አልፎ መደማመጥና መተማመን ዚማይቻልበት ዚመጯጯህ ባህልንም ፍጥሯል። እውነትንና እውቀትን መሰሚት ያደሚጉ ዚሃሳብ መግለጫ መድሚኮቜ እንዲኚስሙ ተደርጎ በምትካ቞ው ጜንፍ ዚያዙና በሁለት አፋፍ ላይ ቆመው በጥላቻ፣ በሃሰት፣ ሰብአዊነት በጎደለውና ተጠያቂነት በማይስተዋልበት መንፈስ ውስጥ ዚተዋጡና ሕዝብን ዚሚያደናቁሩ ዚጩኞት መድሚኮቜ ጎልተው እንዲወጡ ተደርጓል።

ዛሬ ዚኢትዮጵያ ሕዝብ በአገሩ ጉዳይ መሹጃ ዚሚያገኝበት እድል ሁለት ጜንፍ በያዙ እርስ በእርስ ተቃራኒ ነገር ግን ተመሳሳይ ባህሪይ በሚታይባ቞ው ዚፕሮፓጋንዳ መድሚኮቜ እጅ ወድቋል። በአንድ ወገን “ልማታዊ ጋዜጠኞቜ” በግብር ኚፋዩ ሕዝብ ገንዘብ በሚንቀሳቀሱትና ሙሉ በሙሉ ዚወያኔ ልሳን በሆኑት ቎ሌቪዥንና ራዲዮ ጣቢያዎቜፀ እንዲሁም ነጋ ጠባ ስለ አገዛዝ ሥርዓቱና ስለ ሹማምንቱ በጎ ገድል ብቻ ሲተርኩ ዹሚውሉ በግለሰቊቜና በቡድን ዚተያዙ ሚዲያዎቜ (እንደ አይጋ ፎሚም፣ ኢትዮጵያ ፈርስትና ሌሎቜም)። በሌላኛው ጜንፍ ደግሞ “ሁለገብ ጋዜጠኞቜ” ለአገሩ በጎ አሳቢ በሆነውና በስደት በሚገኘው ኢትዮጵያዊ መዋጮ እና በፕ/ት ኢሳያስ አፎርቂ ወይም ሻቢያ ድጎማ ዚሚተዳደሚው ዚግንቊት ሰባት ልሳን ኢሳት ቎ሌቪዥንና ራዲዮ ጣቢያፀ እንዲሁም ለተመሳሳይ ተልዕኮ በቆሙ ጥቂት ድኅሚ-ገጟቜ ና቞ው። በእነዚህ ሁለት ጜንፎቜ መካኚል ኹላይ ዚተጠቀሱትን ዚጋዜጠኝነት መርሆዎቜ በኹፊልም ቢሆን ለማሳካት ካላ቞ው ቁርጠኝነት ዚተነሳ እውነተኛና ሚዛናዊ መሹጃን ለሕዝብ ለማድሚስ ዚሚተጉትን ሳንዘነጋ ጜንፍ ዚያዙት መድሚኮቜ በመገናኛ ብዙሃን ስም በአገሪቱ ዚፖለቲካና ማኅበራዊ ሂደቶቜ ላይ እያደሚሱ ያሉውን ኹፍ ያለ ጉዳትና ዚሚያስኚትሉትንም መዘዝ በቅጡ መፈተሜ ዚግድ ይላል።

ጜንፍ እንኳንስ ጥላቻን ለማራባት ይቅርና ፍቅርንም ለማጠንኹር ቢሆን ውጀቱ አድጋ ነው። ጜንፍ ሚዛንን ያስታል፣ እውነትን እንዳናይ ይጋርዳል፣ ፍትሕን ያዛባል፣ ስብዕናን ያራቁታል፣ ለኚባድ ስህተትና ውደቀትም ይዳርጋል። ጋዜጠኛም ጜንፍ ዚያዘ ዕለት ነገር ይበላሻል። እራሱን ብቻ ሳይሆን ድልድል ሆኖ ዚሚያቀራርበውንም ማህበሚሰብ መንገድ ያስታል፣ ያናቁራል፣ ጥላቻ ያሰርጻል፣ ዚተለያዩ ዚኅብሚተሰብ ክፍሎቜን ሆድና ጀርባ በማድሚግ ለእልቂት ይጋብዛል። “ልማታዊ ጋዜጠኞቜ” እና አንዳንድ ዚኪነ-ጥበብ ባለሙያዎቜ ሳይቀሩ ዚሆድ ነገር ሆኖባ቞ው ይሁን አምነውበት ኚጥዋት እስኚ ማት ወያኔ ዚሰራውንም ያልሰራውንም እያነሱና እዚጣሉ፣ ተቃዋሚ ያሉትንም ሲያዋርዱና ሲያበሻቅጡ ስለሚውሉ ሕዝብ እንዲህ ያለውን ፕሮፓጋንዳ መስማት ታክቶታል። ዚሚሚዳው አጣ እንጂ በድሃ አቅሙ ዲሺ እያስተኚለ ፊቱን ወደ ውጭ ሚዲያዎቜ ሲያዞር ማስተላለፍ ዹፈለገው መልዕክት ግልጜ ነበር። ውሞት መስማት ታኚቶናል፣ ዚጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ሰልቜቶናል፣ አማራጭ አሳቊቜንም መስማት እንፈልጋለን ዹሚል ነው። ወያኔ ሕዝብን ለመስማትም ሆነ ኚስህተቱ ለመማር አቅሙም ሆነ ፍላጎቱ ስለሌለው ኚሕዝብ ጋር ሆድና ጀርባ ሆኖ ቀጥሏል። ወያኔ ሕዝብን አያዳምጥምፀ ሕዝቡም ወያኔን አያደምጥም።

በሕዝብና በአገዛዙ መካኚል ዹተፈጠሹውን ክፍተት ለመጠቀም እድሉና አቅሙ ዹተፈጠሹላቾው ዚኢሳት አይነት ሚዲያዎቜም ሕዝብን ለማስተማርና ለማንቃትፀ እንዲሁም መብቱን ጠንቅቆ እንዲያውቅና ለነጻነቱም እንዲቆም ለማነሳሳት እድሉ ተፈጥሮላ቞ው ነበር። ይሁንና ዚኢሳት ተልኮም ሆነ አወቃቀር ዚግንቊት 7ን ሁለገብ ዚትግል ስልት መሰሚት ያደሚገ በመሆኑ በድርጅቱ ጠባብ አጀንዳና ዚትግል ስልት እንዲወሰን አስገድዶታል። “ሁለገብ” ዹሆኑ ጋዜጠኞቜን አፍርቷል። ቜግሩ ሁለገቊቹም ልማታዊ ጋዜጠኞቹ ተንደርድሚው ዚወሚደበትን ቁልቁለት ተኚትለው አብሚው መክነፋቾው ላይ ነው። ሕዝብ አማራጭ ስላጣ ዛሬን ሊሰማቾው ይቜላል። አሁን ባሉብት ይዞታ ኹቀጠሉ ግን ኚሕዝብ ጋር መደማመጥ ይቀርና እንደ ወያኔ ሚዲያዎቜ በባዶ ሜዳ ማንቋሹር ብቻ ይሆናል። ልማታዊ በሆኑት ዚወያኔ ጋዜጠኞቜና ሁለገብ በሆኑት ዚግንቊት 7 ጋዜጠኞቜ መካኚል ያለው አንድነትም ሆነ ሁለትነት ግልጜ ነው። ሁለቱም ለተለያዩ ዚፖለቲካ ተቋማት ልሳንነት ማገልገላ቞ው፣ ጠላት ብለው ዚፈሚጁትን አካል ዚሚገልጹበት ያልተገራና ጚዋነት ዹጎደለው ቋንቋ቞ው፣ ወዳጅ ዹሆናቾውን ደግሞ ሜቅብ ሚኚቡበትና ዚሚያሞካሹብት ስልታ቞ው፣ እንዲሁም በብዙ ዚፕሮግራምና ዹዜና አቀራሚብ ስልታ቞ውም ጭምር አንድ አይነት እዚሆኑ መምጣታ቞ው ነው። ሌላው ቢቀር አንዱ “አኬልዳማ” ብሎ ዚድራማ ፊልም ሲሰራ ሌላው “ኊፕሬሜን ሚሊኒዹም” በሚል ኚአዲስ አበባና ኚአስመራ ያሰራጩትነ ዘገባ ልብ ይሉዋል።

ኹላይ ኚተጠቀሱት ዚጋዜጠኝነት መርሆዎቜ አንጻር ሁለቱንም በአንድ ጎራ ተሰልፈው እናያ቞ዋለን። ልማታዊዎቹ ጋዜጠኞቜ ዚወያኔን ባለሥልጣናትና ዚሻቢያን ተቃዋሚዎቜ ቅዱስ አድርገው በሚያቀርቡበትና በሚያሞካሹብት መጠነና ልክ ሁሉ ሁለገቊቹም ግንቊት 7ንና አጋሮቹንፀ እንዲሁም ዚሻቢያ ባለሥልጣናትን በተመሳሳይ ሁኔታ እያቀሚቡ በሕዝብ ጉዳይና በፍትህ እንዲያላግጡና እንዲቧልቱ ሁኔታዎቜን ያመቻቻሉ። ለዚህም በቅርቡ ዚግንቊት 7 ሹማምንትን አጅበው አስምራ ዚኚሚሙትን ዚኢሳት ጋዜጠኞቜ ቆይታ ልብ ይሉዋል። ልማታዊ ጋዜጠኞቹ ዚወያኔን ቱባ ባለሥልጣናት ተኚትለውና ዚህውሃት አርማ ያለበትን መለዮ አጥልቀው ዚድርጅቱን 40ኛ ዓመት ለማክበር መቀሌ እንደ ኚሚሙት ሁሉ ሁለገቊቹ ዚኢሳት ጋዜጠኞቜም ወታደራዊ ትጥቅና አልባሳትን አጥልቀው አስመራ በሚገኝ ሠራዊት መሃል እዚተጎማለሉ ዚተነሱትን ፎቶና ዚቀዱትን ቪድዮ ላስሚጂነት ማቅሚብ ይቻላል።

ሰብአዊነትንም በተመለኹተ በሁለቱም ጎራዎቜ ዚተሰለፉት “ጋዜጠኞቜ” ተመሳሳይ ዹመርህ ግድፈቶቜን ሲፈጜሙ ማዚት ዹተለመደ ነው። ዚዜጎቻ቞ውን መሰሚታዊ መብቶቜና ነጻነቶቜ በመግፈፍ. አለም ያወቃ቞ውን አምባገነኖቜ እያሞካሹ፣ ወንጀላቾውን እዚሞፋፈኑና ዹሌላቾውን ስብዕና እያለባበሱ ማቅሚብ ፍትህን በሚናፍቁት ግፉአን ላይ እንደ ማላገጥ ነው ዚሚቆጠሚው። መለስ ዜናዊንም ሆነ ኢሳያስ አፎርቂን ለሕዝቊቻ቞ው አሳቢና ባለ በጎ ራዕይ ዹአገር መሪዎቜ አድርገው ቢሚያቀርቡ ጋዜጠኞቜ መካኚል ያለው ልዩነት ዚቆሙለት ወገንና ቊታ እንጂ ዹመርህ አይደለም። ለብዙ ንጹሃን ዜጎቜ ህይወት መጥፋት፣ ስቃይና እንግልት ቀጥተኛ ተጠያቂ ዚሆኑትን እነዚህ አንባገነኖቜ እዚካቡ ዚፍትሕና ዚዲሞክራሲ ጠበቃ መሆን አይቻልም። በቅርቡ ዚኢሳት ጋዜጠኞቜ ፕ/ር ኢሳያስን ኚራሳ቞ው ሕዝብ አልፈው ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊያን ዹሚጹነቁ መሪ አድርገው ለማቅሚብ ያደሚጉት ሙኚራ “ዚሁለገብ ታጋይነታ቞ው” ተልዕኮ መገለጫ እንጂ ኚጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባር ዹመነጹ አይሆንም። ባለፉት ሃያ አመታት ወያኔና ሻቢያ በሁለቱ አገራት ሕዝብ ላይ ሲፈጜሙት ዚቆዩትንና ዛሬም እዚፈጞሙት ያለውን አስኚፊ ዹሆነ ዚሰብአዊ መብቶቜ እሚገጣ ዹአለም አቀፍ ዚሰብአዊ መብት ድርጅቶቜ በተደጋጋሚ ያጋለጡባ቞ውን ሪፖርቶቜ እነዚህ “ጋዜጠኞቜ” ዚሚያዩበት መንገድም ሚዛኑን ዚሳተ ነው። ልማታዊዎቹ በወያኔ ዹሚፈጾመውን ጥሰት ዚሚያጋልጡትን ዚሰብአዊ መብት ድርጅቶቜ በሰደቡበት አንደበታ቞ው እነዚህኑ ድርጅቶቜ እያጣቀሱ በኀርትራ ውስጥ ስለሚፈጞመው ዚመብት እሚገጣ ሲተነትኑ በተደጋጋሚ ሰምቻለሁ። ሁለገቊቹ ጋዜጠኞቜም ዚእነዚህን ድርጅቶቜ ሪፖርት እያጣቀሱ ወያኔ ዚሚፈጜመውን ዚመብት እሚገጣ ማጋለጠቾው ይበል ቢያሰኝም ሻቢያ በኀርትራ ሕዝብና ዚሙያ አጋሮቻ቞ው በሆኑ ጋዜጠኞቜ ላይ ጭምር ዚሚፈጜመውን ግፍና በደል እንዳልሰሙ በመምሰልና ቜላ በማለት ፕ/ር ኢሳያስን ለሕዝብ አሳቢና መልካም ስብዕና ያላ቞ው ሰው አድርገው ለማቅሚብ መሞኚራ቞ው ዹሌላኛው ጜንፍ ክሜፈት ነው።

ኹላይ እንደገለጜኩት ክፉና አፋኝ ዹሆነ አንባገነናዊ ሥርዓት በአንድ አገር ውስጥ እሚዘም ላለ ጊዜ ሥልጣን ተቆናጩ በሚቆይበት ወቅት ተመናምነው ዹሚጠፉ በርካታ እሎቶቜ እንዳሉ ሁሉ በምትካ቞ውም መጥፎና መሹን ዹለቀቁ አዳዲስ ልማዶቜ ይፈለፈላሉ። አንዱ ይሄው መደማመጥ ዚሌለበት ዚመጯጯህ ባህል ነው። በ1960ዎቹ ዚተማሪዎቜ እንቅስቃሎ ዹጀመሹን ይህ ፈሊጥ ዛሬም አለቅ ብሎን ጜንፍ በያዙት በነዚህ መድሚኮቜም ዚተለያዩ ሃሳቊቜ አይንሞራሞሩም። በሃሳቊቜ ላይ ያተኮሚ ውይይትና ክርክር ዚሚባል ነገርም ዚለም። ሁሉም ዚራሱን ብጀ ሰብስቊ ሌላኛውን ወገን ሲወቅጥ፣ ሲራገም፣ ሲያነሳና ሲጥል ነው ዚሚታዚው። ተፎካካሪ ሃሳቊቜ በማይፋጩበትና በአንድ ጭብጥ ዙሪያ ዚተለያዚ አመለካኚት ያላ቞ው ሰዎቜ በእውቀት ላይ ዹተመሰሹተ ውይይት በማያደርጉበት መድሚክ ላይ አስር ተናጋራ አቅርቩ ሁሉም ባንድ ሙቀጫ ሌላውን ዚሚወቅጥ ኹሆነ አንዳቜም ጠብ ዹሚል ነገር ዚለውም። ዚአንድ ማኅበሚሰብ ዚፖለቲካ አስተሳሰብ ሊሰፋና ሊያድግ ዚሚቜለው በሃሳቊቜ ዙሪያ በሚደሹጉ ምሁራዊ ክርክሮቜና ውይይቶቜ ነው። ጥላቻና ጜንፍ ዹተሹጋጋና ዹሰለጠነ ዚፖለቲካ ማህበሚሰብ እንዳይፈጠር ትልቅ እንቅፋቶቜ ና቞ው። ሰላማዊ ዹሆነ ዚፖለቲካ ሜግግርም እንዳይፈጠር ያደርጋሉ። ዚፖለቲካ ጜንፍ በያዙ መገናኛ ብዙሃን ዚሚሰራጩት ዚጥላቻና ዚሃሰት ዘገባዎቜ ቀጥተኛ ተጎጂው አገርና ሕዝብ ነው። ዚተጀመሩ ዹሰላማዊ ትግሎቜ ይኮላሻሉ። ንጹሃን ዜጎቜም በሃሰት ፕሮፓጋንዳ ተታለው ለአደጋ ይጋለጣሉ። ደግ ቀን ሲመጣ እናንተም ለትዝብት ትጋለጣላቜሁና ኚወዲሁ አስቡበት።
በቾር እንሰንብት!
ያሬድ ኃይለማርያም

↧

ዚአዲስ አበባ ዚኢህአዎግ ጜ/ቀት ድርጅት ጉዳይ ኃላፊዋ ህወሓትን ኚዳቜ

$
0
0

ኚምርጫ ዘጠና ሰባት በኋላ በኢሕአዎግ አደሚጃጀት ዉስጥ ትልቅ ቊታ ዚነበራት ናት። ኚሎቶቜ አደሚጃጀት ሃልፊ ነበሚቜ። ኚዚያም በአዲስ አበባ ዚኢሕአዎግ ጜ/ቀት ዚድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ሆና እስኚ ቅርብ ጊዜ ድሚስ ትሰራለቜ። በአዲስ አበባ ይለ ዚኢሕአዎግ አባል ዚማያወቃት ዚለም።11052444_614797398655219_5167830822266437067_n

ኚአዲስ አበባ ዚኢሕአዎግ ጜ/ቀት ዚድርጅቱ ጉዳይ ሃላፊነቷ በተጚማሪ በአዲስ አበባ ዚሎቶቜ መዋቅርም ዚአድን ክላስተር ሃላፊም ነበሚቜ። አበባ ገብሚ ሕይወት ትባላለቜ።

አበባ በቅርቡ ለአንድ ስብሰባ ወደ አሜሪካን አገር ባቀናቜበት ወቅት አጋጣሚዉን በመጠቀም፣ ዚፖለቲካ ጥገኝነት ለመጠዹቅ እንደወሰነቜና ወደ አገር ቀት ዚመመለስ ሀሳብ እንደሌላት ለርሷ ቅርበት ያላ቞ው ወገኖቜ ጠቁመዋል፡፡

በተለይም በኢሕአዎግ ዉስጥ ፍጹም ዹሆነ ዚሕወሃት ዚበላይነት ኚመኖሩ ዚተነሳ፣ በሞያ቞ውና በእውቀታ቞ው ዹመወሰንና ዹማገልገል እድል ዚሌላ቞ውና፣ ዚታዘዙትን ብቻ ማድሚግ ዚሚጠበቅባ቞ው ሌሎቜ ዚኢሕአዎግ አባላት ደስተኛ እንዳልሆኑ በስፍት ይነገራል። ብዙዎቜ ባላ቞ው አጋጣሚ ሁሉ ኢሕአዎግን እዚኚዱ እንደሆነ፣ ያሉት ደግሞ ኚዉስጥ መሚጃዎቜ በማቀበል ኹአዝዙ ያላ቞ውን ጥላቻ በማሳዚት ላይ መሆናቾው በግልጜ እዚታዚ ነው።

ኹዚህ በፊትም ሚኒስ቎ር ዎታ ሆነው ሲያገለግሉ ዚነበሩት አቶ ኀርምያ ለገሰን ጚምሮ ብዙዎቜ ኢሕአዎግ እንደኚዱ ይታወቃል።

↧

ትጥቅ ትግል ፣ ሰላማዊ ትግል ፣ ሁለገብ ትግል (ዮናታን ተስፋዬ ሚጋሳ)

$
0
0

(አቶ ዮናታን ተስፋዬ ዚሰማያዊ ፓርቲ ዚሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ና቞ው። ይህ ጜሁፍም ፓርቲን ወክለው ሳይሆን ራሳ቞ውን ወክለው ዚጻፉት ነው)

ወቅታዊ አጀንዳ እና በቁንፅል ዹሚተው ባይሆንኝ ነው – በትግስት አንቡልኝyonatan

ጭቆና ሲበዛ ሰዎቜ ብዙ መንገድን ተጠቅመው መታገል ይሻሉ፡፡ ዹጭቆናውን ቀንበር ለመስበር ጹቋኙን ኹመግደል አንስቶ ራስን እስኚማቃጠል ድሚስ ዚሚደርሱ በርካታ መንገዶቜን ሊጠቀሙ ይቜላሉ፡፡ ኹአገዛዝ ሰንሰለት ራስን ነፃ ለማድሚግ ብዙዎቜ ተጹንቀው ማሰብም አይፈልጉም፡፡ በቃ ገዢውን ወዲያ አሜቀንጥሮ ጥሎ ነፃ መሆን (end of the story end of the oppression)! በተፈጥሮ ነፃ ሆኖ ዹተፈጠሹ ሰው በሂደት እጅግ በተወሳሰበ ዚህይወት መስተጋብር ውስጥ ቢኖርም ዹጭቆናው ለኚት ሲያልፍ ግን ቀስቃሜ ሳያሻው እንደቡድንም ይሁን በግል በነሲብ ወደ ነፃነት ትግል መግባቱ አይቀርም፡፡ ነፃነት ኚብዙ ምክንያታዊነትም በላይ ዚስሜት ሀይሉ ኹፍተኛ ገፊ በመሆኑ ለነፃነት ዹሚደሹገውም እንቅስቃሎ በራሱ ድንገታዊነት ይበዛዋል፡፡ ‘መቌ’ እና ‘እንዎት’ን አያጠይቅምፀ ‘ለምን’ ዹሚለው ብቻ በቂው ነው፡፡
እንግዲህ እዚህ ጋር ነው ዚነፃነት ትግል መሪዎቜ ሚና ወሳኝ ዚሚሆነው፡፡ ጭቆናን ኚምክንያታዊነት በላይ በስሜቱ ተፀይፎ ነፃነቱን ሊቀዳጅ ዚተነሳን ሰው መንገዱን ማመላኚት ዚመሪዎቹ ሚና ነው፡፡ መሪው ዚትግሉን ‘እንዎትነት’ ‘መቌ’ ምን መደሹግ እንዳለበት አፍታቶ ማሳዚት እና እምቅ ዹሆነውን ዚነፃነት ፍላጎት ሀይል በተጠናና በተገቢው ቊታ ጥቅም ላይ እንዲውል ማስቻልፀ በዚህም አኳኋን ታጋዮቜን አስተባብሮ መምራት አለበት፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥም ዚነፃነት ትግል መሪ ኚስሜት በላይ እጅግ ምክንያታዊ እና በአስ቞ጋሪ ሁና቎ዎቜ ውስጥም ለታለመው ግብ ሲባል በርካታ ፈታኝ ውሳኔዎቜንም እንዲያሳልፍ ይጠበቅበታል፡፡
ዚዛሬን መጹቆን ሳይሆን ዹነገን ዹተጹበጠ ውጀት ቀድሞ ማለም ለዛም ዹሚኹፈለውን መስዋእትነት ሁሉ መክፈል ግዎታው ነው፡፡ ኚተራ ውሳኔ አንስቶ በሰዎቜ ህልውና ላይ እስኚመወሰን ዚሚያደርስ ጠንካራ ዚዲሲፕሊን ሰው ዹመሆን ኃላፊነቱ ዚትግሉ መሪ ላይ ይወድቃል፡፡ ኹሁሉም በላይ ግን ሂደቱ ኚዚት ተነስቶ ዚት እንደሚደርስ በጠራ ሁናቮ ዚሚያልምፀ ኚግቡም ለመድሚስ ዚቆሚጠፀ ተግባራዊ እና ለዛም ሁነኛ መላ ቀያሜ ብልሃተኛ መሪ ትግሉን ኚጫፍ ለማድሚስ ይቻለዋል፡፡
ትግል ተፈጥሯዊ ነው – በብልሃት ማስተባበር እና መምራት ደግሞ ትግልን ኚፍሬ ዚሚያደርሱ ነገሮቜ ና቞ው፡፡ ኹዚህ ተነስተን በኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚካሄዱት ዚነፃነት ትግሎቜ እንፈትሜ፡፡ አዋጪነታ቞ውንና ኪሳራ቞ውን እንመዝን፡፡
NOTHING PERSONAL NOR DESTRUCTIVE!
ትጥቅ ትግል በኢትዮጵያ?
———————-
* በ21ኛው ክ/ዘመን ዚትጥቅ ትግል አለማቀፋዊ አንደምታው እጅግ ዚተወሳሰበና ኹፍተኛ ዹሰው እና ዚሉዓላዊነት ዋጋ ዚሚያስኚፍል ነው፡፡ ለነፃነት እሞታለሁ ብሎ ዚወጣን ሰው አስተባብሚህ ኚምታስጣጥቀው መሳሪያ ጀምሮ ዚተለያዩ ሎጀስቲክና ዲፕሎማሲያዊ ድጋፎቜን ማግኘት ግድ ይላል (ኹመጋሹጃ ጀርባ ያለውን ዹዓለም ሎራ ቀመስ ፖለቲካ ትተን)፡፡ እነዚህን ድጋፎቜ ለማግኘት ደግሞ በዓለም ላይ ኹሚገኙ ታላላቅ መንግስታት ጀምሮ ገዢ መሬት ኚሚሰጡህ አካላት ጋር በበርካታ ጉዳዮቜ ላይ ውል መፈፀሙ አይቀርም፡፡
ህወሃት ትጥቅ ትግሉን ድል አድሚጎ ስልጣኑን ለመቆናጠጥ በሀገር እና በህዝብ ላይ እስኚመደራደር ደርሷል፡፡ ለትጥቅ ትግሉ ስኬት ሲባልም ብዙ ታሪካዊ ስህተቶቜም መፈፀማቾው ያልሻሚ ቁስል ነው፡፡
በዚህ ዘመን ደግሞ በትጥቅ ትግል ኢህአዲግን ኚስልጣን ማውሚድ ኹዓለም ነባራዊ ስርዓት አንፃር እጅግ አስ቞ጋሪ እና በአደጋ ዹተሞላ ነው (at this point there is no near-safe deal)፡፡ ስለዚህ ጥያቄው አህአዮግን ለማስወገድ ኚተለያዩ ሀይሎቜ ጋር ዚሚደሚጉት ስምምነቶቜ በእውነት ሚዛን ይደፋሉ ወይ? ዚሚፈፀሙት ስምምነቶቜ ህወሓት (ሊያውም በዘመነ ጊርነት) ካስኚፈለን ዋጋ ምን ያህል ቢሻሉፀ ምን ያህልስ ዚህዝባቜንን እና ዚሀገራቜንን ጥቅም ያስቀደሙ ወይም ኚግምት አስገብተው ዹተፈፀሙ/ሊፈፀሙ ያሉ ናቾው? እነዚህ እና መሰል ጥያቄዎቜ አጥጋቢ መልስ እስካላገኙ ድሚስ በዚህ ዘመን ዹሚደሹገው ዚትጥቅ ትግል ለኢትዮጵያ ዹሚኖሹው ፋይዳ ‘ኚድጡ ወደማጡ’ ኹመሆን ያለፈ አይሆንም!
* ኹዚሁ ጋር በተዛመደ ዚኢትዮጵያ ታጣቂ ሀይሎቜ ዚመሚጡት ገዢ መሬት ዚሙግቱ ዋና ማጠንጠኛ ተደርጎ ሊወሰድ ይቜላል፡፡ ዚሻቢያ ግዛት ኀርትራ፡፡ እዚህ ላይ ስለ ሻቢያ እና ወያኔ ፍቅርና ጠብ – አንድነት እና ልዩነት አሁን ስላላ቞ው ለክፉም ለደጉም ዚእርስ በእርስ መጠባበቅ ማውራቱ ‘አውቆ ዹተኛን . . .’ ካልሆነ በስተቀር ለማንም ምስጢር አይደለም፡፡ ምንአልባትም እነዚህ ሁለት ሀይሎቜ በኢትዮጵያም ይሁን በቀጠናው ጉዳይ ላይ ዚራሳ቞ው ቁማር እዚተጫወቱ ስልጣና቞ውን ለማስቀጠል ምንም ሊያደርጉ እንደሚቜሉም ለሁሉም ሰው ግልፅ ነው፡፡
ይህን ካልን ዘንዳ ኢትዮጵያ ውስጥ በትጥቅ ትግል ለውጥ እናመጣለን ዹሚሉ ሃይሎቜ ኚሻቢያ ጋር በምን መልኩ ሰምምነት አካሂደው ገዢ መሬት አገኙ? በዚህ ትግል ውስጥ ዚሻቢያ ጥቅም ምንድን ነው? በዚትኛው ስሌት ዚኢትዮጵያ ታጣቂ ሀይሎቜ ኚሻቢያ ድጋፍ አግኝተው ዚኢትዮጵያን ጥቅም ያስጠብቃሉ? (በቀደም ለት ዚኀርትራው ፕሬዘዳንት ስለኀርትራ እና ኢትዮጵያ ስላለፈውና መሆን ስላለበት ሲያብራሩ እነዚህ ጥያቄዎቜ ይበልጡኑ አወዛጋቢና በትጥቅ ትግሉ ዚተሰማሩ ሀይሎቜ ግልፅ ሊያደርጓ቞ው እንደሚገቡም ጭምር ተገንዝቀያለሁ!)
ስለሆነም እነዚህ መሰሚታዊ ነጥቊቜ ምላሜ ባላገኙበት ሁናቮ ኢትዮጵያ ልጆቿን ዳግም ወደ እርስ በእርስ ጊርነት ዚምትኚትበት አሳማኝ ምክንያት አይኖርም (ምሬት እና ጭቆና ብቻውን ለውጥ ሊያመጣ እደማይቜል ኹላይ በመግቢያዬ ያሰፈርኩትን ልብ ይሏል) – ዚጊሚኞቹ ዚፖለቲካ ሰዎቜ ይህን መሰሉን ጉዳይ አፍታተው መዳሚሻውን፣ ጥቅምና ጉዳቱን እስካሁን ማሳመንም ሆነ ደፍሹው ለውይይት ሊያቀርቡት አለመቻላ቞ው በራሱ ዚትጥቅ ትግሉ አዋጪ እንዳልሆነ አመላካቜ ነው (there is something fishy behind the silence)፡፡ (እንዲህ አይነቱ ነገር መገለፅ ዚለበትም ዹሚል መኚራኚሪያ እኔ አልቀበልም – ሁላቜንም በሀገራቜን ጉዳይ ያገባናል!)
* እዚህ ጋር አብሮ መነሳት ያለበት ነገር ደግሞ – ይህን ትግል ለመቀላቀል ዹሚፈልጉ ሰዎቜ ዚሚኚፍሉት አላስፈላጊ መስዋእትነት ነው፡፡ ገና ሳይጀመር በባዶ ሜዳፀ በጉዞ ላይ እዚተለቀሙ ዘብጥያ ዚወሚዱትን እግዜር ብቻ ነው ዚሚያውቀው፡፡ ያም ብቻ ሳይሆን ኚምትታገልለት ህዝብ ውጪ ሆነህ ልታገኘው ዚምትቜለው ዚሎጀስቲክና ሌላም መሰሚታዊ ድጋፍ አናሳ ነውፀ ኚናካ቎ውም ላይኖር ይቜላል፡፡ ለምሳሌ ያህል አሁን በኀርትራ ምድር ኹሌላ ሀይል ጋር ውህደት ዹፈፀመው ዚአርበኞቜ ግንባር በተለይ በሰሜኑ ዚኢትዮጵያ ክፍል ኹፍተኛ ድጋፍን ማግኘት ዚቻለና በተወሰነ ደሹጃም ቢሆን ተስፋ ተጥሎበት ነበር፡፡ ምኚንያቱ ደግሞ ይታገል ዹነበሹው በዛው በህዝቡ መሃኹል ሆኖ መሆኑ ነው (ያ አደጋ ዹለውም እያልኩኝ አይደለም ቢያንስ ግን ኚባህሩ ዚወጣ አሳ አለመሆን ያለው ጠቀሜታ ኚጉዳቱ ይበልጣል)፡፡ በዚትኛው መልኩ ጭቆናው በቃኝ ብሎ ለሚያስብ ሰው ‘መንገዱም ጹርቅ’ ለመቀላቀልም ቀና ዹነበሹ ግንባር ነበር፡፡ አሁንስ?
* እርግጥ ዚህዝባቜን ስነ ልቡና ለትጥቅ ትግል ዹቀሹበ መሆኑ አይካድም፡፡ ታሪካቜንም ቢሆን ስልጣን በጊሚኞቜ እንጂ በሰላማዊ መንገድ ተቀይሮ አያውቅም፡፡ ያም ሆኖ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁናቮ ዹዚህን መሰሉን ዚህዝብ ስነ ልቡናዊ ዝግጁነት ጥቅም ላይ ሊያውል ዚሚቜል አስማሚ አጀንዳም ዚለም፡፡ ለዚህ አንዱ ማሳያ ደግሞ ራሱ በትጥቅ ትግል ያሉት ዚተበታተኑ ሀይሎቜ ና቞ው፡፡ ይህ ቜግርም ባልሆነ ነበር ግና ለነፃነት ዋጋ ዹሰጠና ለዛም ለመሞት ዹቆሹጠው ምን ያህል ነው? አምናለሁ ነገርን ዚሚለውጡት ሚሊዮኖቜ ሳይሆኑ ጥቂቶቜ ናቾው – ቢሆንም በኔ እምነት እነሱም ኹላይ በዘሚዘርኳ቞ው ምክንያቶቜ ሌላ አማራጭ እንዲጠቀሙ ይገፏቾዋል (ለዚህ ነው ብዙዎቜ ተስፋ ቢያስቆርጥ እንኳን ለሰላማዊው ትግል ቅድሚያ ዚሚሰጡት)፡፡ ወጣም ወሹደ በዚህ ጉዳይ ላይ ዚማነሳው መሰሚታዊ ጥያቄ ግን በጣም ግልፅ ነው – ይህን ታሪክ እና ባህል ይዘን እንቀጥል ወይስ እንቀይሚው? እውን ትጥቅ ትግል በትጥቅ ትግል ዚሚቀያዚርን ዚስልጣን አዙሪት መስበር ይቜላል? ዹጩሹኛን ህዝብ ስነ ልቡና በጩሹኛ መቀዹር ይቻላልን?
* ሌላው ደግሞ ጊርነት ለሰብዓዊነት ቊታ አለመስጠቱ ነው፡፡ ዹሰው ልጅ አንድ ጊዜ ኹገደለ በኋላ – ደም ካዚ በኋላ ለሌላ ሰብዓዊ መብቶቜ ሊቆሹቆር ዚሚቜልበት ሩህሩህነት አይኖሚውም፡፡ መግደልን ዹተለማመደ አንድ ሰው ጭካኔን እዚተለማመደ መሆኑን ማንም አይክደውም፡፡ በዚህ ሁናቮ ስብእናው ዚሚገነባ ግለሰብም ሆነ ቡድን ደግሞ ለወደፊቱ ህልማቜን አደጋ ነው፡፡ ሰው መጹኹን ዚለበትም እያልኩኝ አይደለም (there may come critical times in life)- ሁሉም ነገር ግን ዚሚቃኝበት መንፈስ እንደ ነገሩ ተጚባጭ ሁናቮ መሆን አለበት፡፡ አሁን ላይ ይህን ያህል ርቀት መሄድ ይቻላል ወይም አለብን? መቀበል ይቾግሹኛል!
ይህን ዹበለጠ ለማብራራት ሩቅ ሳንሄድ ዚሀገራቜንን ዚትናንት ታሪክ እናንሳ፡፡ ዚህወሓት እና ኢህአፓ ታጋዮቜ ብሚቱን እስኪጚብጡት ድሚስ እንደሁላቜን ሰዋዊ ባህሪያ቞ው እንዳልተለያ቞ው ምንም አጠያያቂ አይደለም – አንዮ ሞትን ተኩሰው ኹተፉ በኋላ ግን ዚማያባራ እልቂት ሆነ፡፡ ሰብዓዊነታ቞ው ተሟጩ ግፉ ለኛም ተሹፈ! ትጥቅ ትግል ይህ እንዳይሆን ዹሚሰጠን አንድም ዋስትና ዹለውም! በደም ዚታጠበ እጅ ህሊናው ለመፅዳት ትልቅ ፈተና አለበት፡፡ እሚግጥ ሰብዓዊነት በፖለቲካ አውድ ውስጥ አሻሚ ትንታኔ ቢሰጥበትም በጥቅል ግን ኚትጥቅ ትግል ዚፖለቲካ ትርፍ በላይ በማህበሚስብ ስነ ልቩና ላይ ዹሚኖሹውን ጠባሳ ኹኛ በላይ ህያው ምስክር ያለ አይመስለኝም፡፡ ዹኹፋ ዚሚያደርገው ደግሞ አሁንም ዚአንድ አገር ሰው ወንድም በወንድሙ ላይ እጁን ማንሳቱ ነው፡፡
ሰላማዊ ትግል በኢትዮጵያ?
————————
* ዓለም ዛሬ ዚምትመራበት መርህ እና ሎራው እዚሚቀቀ ቢመጣም አንድ እውነት ግን መቌም ሊሻር አይቜልም! በሰላማዊ ትግል ውስጥ ማናቾውንም ሀይል ኹጎን ለማሰለፍ ትለቁ ነገር አገዛዝን በህግ ዚበላይነት እና ዚሞራል ልዕልና ማጠዹቅ ነው፡፡ መሳሪያ ደግኖ ሲመጣ ደሚትህን ነፍተህ መጋፈጥ ዚመሳሪያውን ብሚት በእቶን እሳት ኚማቅለጥ ያነሰ አይደለም፡፡ ዛሬ አንተን ቢገድል፣ ነገ ጓድህን ቢደግመው – ቀጥሎ ቃታውን ዚመሰብ አቅም አይኖሹውም – ምክያቱም ጓዶቜህ በባዶ እጅ ገጥመው እዚወደቁ ህሊናውን አሞንፈውታል፡፡ ገዳይህ ብቻም ሳይሆን ሌላውም ሀይል ይህን ቆራጥነትህን ኹመቀበል እና ኚመተባበር ውጪ አማራጭ ዚላ቞ውም፡፡
እርግጥ ጚካኞቜ ዹሞቀ ቀታ቞ው ውስጥ ና቞ው፣ ይህን ቆራጥነትህን አያዩትም አይሚዱትም ስሜትም አይሰጣ቞ውም – መጠቀሚያ቞ው ግን ዚሚልኩት ወታደርና ፖሊስ ነው፡፡
በሰላማዊ ትግልም ዚምታሞንፈው ይህንኑ ሀይል እንጂ ጚቋኞቹን አለመሆኑ እሙን ነው፡፡ አፈሙዙን አዙሮ ጚካኞቜን ወደ ዘብጥያ እንዲያወርድ ዚሚገደድበት ዚትግል ስልት ቢኖር ሰላማዊ ትግል ብቻ ነው፡፡ ልትገድለው ሳይሆን ሞትን ደፍሹህ ለነፃነት ኚምታደርገው ትግል በላይ ልቡን አቅልጩ ኹጎንህ ዚሚያሰልፍው ሌላ መንገድም ዚለም፡፡ እንግዲህ ይህ ዚትግል ስልት በርካታ ጚቋኞቜን ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፍ ስርዓቱን ጭምር እዚተፈታተነ ያለ ዚትግል አይነት ነው፡፡
* በሌላ በኩል ይህ ዚትግል ስልት በኢትዮጵያ ያልተሞኚሚ በተግባርም እምብዛም ያልታወቀ ነው፡፡ ዚህዝባቜን ስነ ልቡና በራሱ ለዚህ ዚትግል ስልት ዝግጁ አይደለም፡፡ ለዚህም ነው ኢህአዎግን በሰለማዊ ትግል ኚማስጚነቅ ይልቅ ገና ኚጅምሩ እዚህም እዚያም ትጥቅ ትግል ዚተጀመሚው፡፡ ለዚህም ማሳያው ኹ1998 በኋላ ኹተፈጠሹው ቡድን ውጪ ያሉት ታጣቂዎቜ ኚጅምሩም በሹሃ ወርደው ዚነበሩ መሆናቾው ነው (እርግጥ አንዳንዶቹ ኚህወሓት ጋርም አብሚው ዚገቡ ናቾው)፡፡ ኹ1998 በኋላ ትጥቅ ትግልን ዹመሹጠው ቡድንም ቢሆን ሰላማዊ ትግል ለማካሄድ እምብዛም አልጣሚም፡፡ ኢህአዎግ እንኚን ዚለሜ ምርጫ አደርጋለሁ አለፀ ፓርቲዎቜ ተሰባሰቡፀ እስካሁን ተፅዕኖ መፍጠር ዚቻለ ቅንጅት ፈጠሩፀ እንኚን ዚለሜ ምርጫ ተካሄደ፡፡ ውጀቱ ግን ብዙዎቜን ተስፋ አስቆሚጠ፡፡ ዹዘመነ ዚምርጫ ፖለቲካም አበቃለት! ቀጠለና አንድነት ፓርቲ ሰላማዊ ትግል አካሂዳለሁፀ ህዝብን ዚስልጣን ባለቀት አደርጋለሁ ብሎ ትግል ሲጀምር – ሌሎቜ ደግሞ አይ ህዝቡ ዹሰጠንን ድምፅ በመሳሪያ እናስመልሳለን ብለው ጊርነት አወጁ፡፡ በኔ እምነት ሰላማዊ ትግል በኢትዮጵያ ምድር ላይ አለመጀመሩን ብቻ ሳይሆን ለመጀመርም ያለውን ቜግር ይህ ኩነት ሁነኛ ማሳያ ነው፡፡
ምናልባትም ዹዚህ ዚትግል ስልት ትልቁ ተግዳሮት በህዝቡ ዘንድ አዲስ መሆኑና ለመቀበል እና ለመተግበርም እጅግ ድካምን ዹሚጠይቅ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ነፍጥ አልባ ትግል ለመምራት ዚሚነሱ መሪዎቜም መጥፋት ነው፡፡ አንዱ ወደ እስር ሲጓዝ ሌላው በስሩ ተተክቶ ትግሉን ማስቀጠል ግድ ዹሚል ዚትግል ስልት መሆኑን ብዙዎቜ ይዘነጉታል መሰል አንዱ ሲነካ አስሩ ወይ ቀቱ ይቀመጣል ወይ ይሰደዳል ወይ ጩር ያነሳል፡፡ ይህ ትግል በቅብብሎሜ እንጂ በአንድ ትውልድ ብቻ ዚሚያበቃም ላይሆን ይቜላል፡፡ እስክንድር ሲታሰር ተመስገን ይተካል ተመስገን ሲታሰር ሌላው ይቀጥላል እንጂ አለቀቀ ደቀቀ ሰላማዊ ትግል አይሰራም ሊባል አይቜልም፡፡ አንዷለም ሲታሰር ሃብታሙ ይተካል ሃብታሙ ሲታሰር እኛ እንቀጥላልን እኛ ስንገባ ሌላው ይኚተላል፡፡ አንድነት ፈሹሰ ሰማያዊ ይቀጥላል – ሰማያዊ ሲፈርስ ወይ ሌላ ፓርቲ ወይ በሌላ መልክ ትግሉ ይቀጥላል፡፡ መሪ ብቻ አያሳጣ!
* ነፍጥ አልባ ትግል በመውጣትና በመውሚድ ውስጥፀ በአድካሚና ተስፋ አስቆራቜ ጉዞ ዘላቂነት ያለው ድል ያስገኛል፡፡ በነፍጥ አልባ ትግል ብዙዎቻቜን ሙሮን እንጂ ኢያሱን ልንሆን አንታደልም (ዚህወሓቶቹን ሳይሆን ዚቅዱስ መፅሃፎቹን)፡፡ እንቅፋቶቜም ብዙ ናቾው – በመንገድ ተንጠባጥበው ዚሚቀሩ – በተስፋ መቁሚጥ ውስጥ ዹሚሰናኹሉ በርካቶቜ ለትግሉ በጠላትነት ሊነሱበት ሁሉ ይቜላሉ፡፡ ካዛም አልፎ በሌላው ዓለም እንደታዚው ዘለግ ያለ ጊዜ መውሰዱ አሰልቜነት ቢኖሚውም ውጀቱ ግን በሂደቱ ሁሉ ዹተሹጋገጠ ነውና ተመራጭ ያደርገዋል፡፡ ህዝብን ዚስልጣን ባለቀት እንዲሆን ማስቻል ብቻ ሳይሆን አመለካኚቱንና ሌሎቜ በርካታ ጉዳዮቜንም በሂደቱ እዚታገለና መልክ እያስያዘ ኚግቡ ይደርሳል፡፡
አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ይህን አድካሚ ጉዞ ዚሚያቃልል እና መንገዱንም ዚሚያሳጥር ምቹ ሁኔታ አለ፡፡ ላለፉት 40 እና 50 ዓመታት በደም መፋሰስ ውስጥ ያለፈ ህዝብ በስነ ልቩና ሚገድ ያን ጊዜ ዳግም ለማዚት ፍፁም አይሻም፡፡ ኹዛም ሲያልፍ አዲሱ ትውልድና በእርስ በርስ ጊርነቱ ያልነበሚው ዚህበሚተሰብ ክፍል አሁን ላለው ዓለምአቀፍ ስርዓት ቀሚቀታ ያላ቞ው መሆኑ ለአዲስ ዚትግል ስልት ዝግጁነታ቞ው ኹፍተኛ ዹመሆን እድሉ ቀላል አይደለም (ዚድምፃቜን ይሰማን እንቅስቃሎ ልብ ይሏል)፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ጚቋኞቻቜን ዘመኑን ዚማይመጥኑ በአዲሱም ትውልድ በዓለምም ዘንድ መቀይር እንዳለባ቞ው፣ በእድሜ መግፋትም ቢያንስ ጡሚታ መውጣት እንዳለባ቞ው ዚጋራ ግንዛቀ መኖሩ ዹሰላማዊ ትግሉን ዚሚያፋጥን ነባራዊ እውነታ ነው፡፡
* ሰላማዊ ትግል በምርጫ ፖለቲካ ዚሚገደብ አይደለም፡፡ እርግጥ ምርጫን እንደ ጥሩ አጋጣሚ ሊጠቀም ይቜላል፡፡ ሂደቱ በራሱ ኚአነስተኛ ነገሮቜ በመጀመር እያደገና እዚሚቀቀ ይሄዳል፡፡ በትግሉ ውስጥ በተጠና መልኩ ዚሚንቀሳቀሱ ሰዎቜን ብቻ ሳይሆን በርካታ ዚህብሚተሰብ ክፍሎቜን ዹማቀፍ ባህሪም አለው፡፡ አውቀው ኚሚተገብሩት ባልተናነሰ መልኩ ሳይሰማ቞ውና ሳያውቁት በትግሉ ዚሚሳተፉም እንዲኖሩ እድል ይሰጣል፡፡ በሕቡ እና በግላጭም ሊካሄድ ይቜላል፡፡ ሰላማዊ ሆነው ህግን መጣስ ድሚስም መሄድ ይቻላል – ለምሳሌ ያህልም በሩሲያ Pussy Riot (ዚሎቶቜ መብት ተሟጋ቟ቜ እንቅስቃሎ – በተኹለኹሉ ቊታዎቜ እና ነውር በሆነ ሁናቮ ጭምር ተቃውሞን ማሰማት)፣ በኢትዮጵያ በቅርቡ እዚተደሚገ ያለው በመገልገያ ብር ኖት ላይ ተቃውሞን በማስፈር ማሰራጚት . . . ዚመሳሰሉት . . .
* ሰላማዊ ትግል መነሻው እና መዳሚሻው ዚታወቀ ነው፡፡ ጊዜው ምን ያህል ቢሚዝም እንኳን ውጀቱ ግን ዘላቂነት ያለው ነው፡፡ ስልጣንን ኚጚቋኞቜ ዹማውሹጃ ትግል ብቻ ሳይሆን – ዚጊሚኝነትን ባህልንና ዚህዝብ ስነልቊና መቀዹር ዚሚቜል ትግል ነው፡፡ ያለመሳሪያ ጚቋኞቜን ኚስልጣናቻው ማውሚድ ዚቻለ ህዝብ በራስ ዹመተማመኑ መጠን ኹፍተኛ ይሆናል፡፡ ማንም መጣ ማን ያለምንም ስጋት ዹፈለገውን ዚመሻር ዹፈለገውን ዚመሟም አቅም እንዳለው – እንደሚቜልም ዹሚተማመን ህዝብ ሊኖር ዚሚቜለው በሰላማዊ ትግል በሚመጣ ለውጥ ብቻ ነው፡፡ በተለይ እንደኢትዮጵያ በበርካታ ታሪካዊ ትብታብ እና ግጭቶቜ ውስጥ ላለፉ ሀገራት ሰላማዊ ትግል ዚቱንም ያህል ተስፋ አስቆራጭ እና አድካሚ ቢሆንም አማራጭ ግን ሊቀርብበት ዚሚቜል አይመስለኝም!
* ሰላማዊ ትግል ጭቆናን ኚማስወገድ ባለፈም በአንድ ማህበሚሰብ ውስጥ ዚመተማመን፣ ዚመተሳሰብና ዚመዋደድን ባህል ያሳድጋል፡፡ ሰብዓዊነትን ያጎለብታልፀ ለዓላማ መሞት እንጂ መግደልን ስለማያበሚታታ ሰዋዊ ዹሆኑ እሎቶቻቜንን ጠብቀን ስነምግባር ያለው ህብሚተሰብ እንድንፈጥር ኹፍተኛ ሚና ይኖሚዋል፡፡
ሁለገብ ትግል በኢትዮጵያ?
———————–
* ይህ አይነት ትግል በተለያዩ ሀገራት ተሞክሮ ስኬታማ ሆኗል፡፡ በጥቅል ሲታይም ህዝባዊ እምቢተኝነትን (ዚነፍጥ አልባ ትግል አካል) እና ህዝባዊ አመፅ (ዚትጥቅ ትግል ደጋፊ ‘hot spot for armed struggle’) አቀላቅሎ ዚሚሄድ ዚትግል ስልት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁናቮ ሲቃኝ ኚጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ዹሚበዛ – ዚጚቋኞቜ አፈና እንዲጠናኚር ሰፊ እድል ዚሚሰጥ ነው፡፡
* በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁናቮ ዹዚህ አይነት ትግል ዋነኛ እንቅፋት ደግሞ ዹቆሾሾው ፖለቲካ ባህላቜን ነው፡፡ መተማመን ዚጠፋበት፣ አንዱ አንዱን ማጥፋት ዚሚፈልግበት፣ ሎራ ዚበዛበት እና በተጠና መልኩ መንቀሳቀስ ማናናቅ አዋቂ በሚያሰኝበት ዚፖለቲካ ባህል ውስጥ ውስብስብነት ያለውን ሁለገብ ዚትግል ስልት እንጠቀም ማለት ኢህአዎግ እድሜ ልኩን ሲገዛ ይኑር ኚማለት አይተናነስም፡፡ ይህ ብቻ ቢሆን ደህናፀ ነገር ግን ሁለገብ ትግልን በሀገራቜን ወቅታዊ ሁናቮ ለመተግበር አስ቞ጋሪ ዚሚያደርገው ሌላ መሰሚታዊ ጉዳይ “ዚዚትም ፍጪው ዱቄቱን አምጭው” አይነት ለውጀቱ ብቻ ትኩርት ዚመስጠት ዝንባሌ ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ ግድ ዚለሜ ለሂደቱ ደንታ ዹሌለው አካሄድ በሁለገብ ዚትግል ስልት ኚሚያስገኘው ውጀት በላይ ኪሳራው ዚትዚለሌ ነው፡፡ ስለዚህ በዚሁ ዘግተነው ወደ ማጠቃለያቜን እናሳልጥ!
ማጠቃለያ
———-
በዚህ ሀቲት ውስጥ ለማመላኚት እንደተሞኚሚው ሀገራቜን አሁን ባለቜበት ሁናቮ ኹሁሉም ዚትግል ስልት ይልቅ ሰላማዊ ዚትግል ስልት ውጀታማነቱ ዚሚያሻማ አይደለም፡፡ እርግጥ ማናቾውም መንገድ ዚራሱ ዹሆነ መጥፎና ጥሩ ነገሮቜ ቢኖሩትም ኚሌሎቜ ዚትግል አይነቶቜ በተሻለ ዹተመጠነ ኪሳራ ነገር ግን ዘላቂና ዚሚጚበጥ ውጀት ያለው ዚትግል ስልት መሆኑም አያኚራክርም፡፡ ትልቁ ኃይልም ህዝብ ብቻ መሆኑ ኚተቀሩት በቀጠናው ላይ አይናቾውን ኚጣሉ ዓለምአቀፍ ሀይሎቜ ጋር ሰጥቶ መቀበል ወይም በሌላ ሎራ ዹመጠለፍ አደጋው በእጅጉ ዹቀነሰ ነው፡፡
ነፍጥ አልባ ዚትግል ስልት በሀገራቜን አዲስ ኹመሆኑ አንፃር ገና ዳዎ በማለት ላይ ቢሆንም በጥቂት ጀምሮ እዚሰፋና ኚዳር ዳር እንደሰደድ በመስፋፋት ለሀገራቜን ዘላቂ ለውጥን ለማምጣት ሰፊ እድል ያለው ነው፡፡
ባጠቃላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ (በሀገር ቀትም ሆነ በውጪም) እነዚህን ዚተለያዩ ዚትግል ስልት አይነቶቜ ትርፍና ኪሳራ በመመርመር እና በማገናዘብ ለኢትዮጵያ ዹሚበጀውን መንገድ እንዲመርጥ እና እንዲደግፍ መልእክ቎ ነው፡፡ ኚመነሻዬም እንዳሰፈርኩት ዚትግል ፍላጎት፣ ዚነፃነት ስሜት ገፊ ሀይል እና ጭቆና ብቻውን ለለውጥ አያበቃምና ሀገራቜን በተያያዘቜው ኹአገዛዝ ወደ ነፃነት ዹሚደሹግ ትግልን ዚምትመሩ ቡድኖቜና ግለሰቊቜ ቆም ብላቜሁ መንገዳቜሁን ብትመሚምሩ መልካም ነው፡፡ ኚታናሜ ወንድማቜሁ በሚሆን ምክርም ፅሁፌን ላብቃ – ብቻ ምንም እንወስን ለውሳኔያቜን ቆራጥ፣ ዚተግባር ሰው እና ለሀገራቜን እና ለህዝባቜን ስንል ኚተራ ሎራ፣ በኚንቱ ውዳሎ ኚመኮፈስ ዚፀዳን እንሁን!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

↧
↧

ጃርቷ በበላይነህ አባተ

↧

ዚኀርትራ ነገርፀ ዹኛ ቜግርፀ መርህ አልባ ፍቅር –ተክለሚካኀል አበበ ሳሕለማርያም

$
0
0

1-ዚዛሬ ሁለት አመት አካባቢ አቶ አንዳርጋ቞ው ጜጌ ወደዋሜንግተን ዲሲ መጥቶ ኚኢሳት ጋር ያደሚገውን ቃለምልልስ ተኚትሎፀ በመስኚሚም 2013 በጻፍኩት ጜሁፍ፡ በቃለምልልሱ ላይ አቶ ይሳያስ አፈወርቂን መስቀልና ማጋነን እንዳልነበሚበት ተቜቌ ዹሚኹተለውን ጜፌ ነበር፡፡

በኀርትራና በኢትዮጵያ መካኚል ያንን ደም ያፋሰሰ ታሪክ እንዳልተፈጠሚ አድርገን መናገር አንቜልም። አንክድም። 
 ስለ ሻእቢያና ኀርትራ ክፉ ሳይወጣንፀ ስለኢሳያስ ቅንነትም ብዙ ሳናጋንንፀ ኚኀርትራ ጋር ስለመስራት አስፈላጊነት ልንናነገር እንቜላለን። 
 በዚያ ቃለምልልስ ላይፀ ኚኀርትራ ጋር ዚመስራትን ሀሳብ ለማሳመን ሲል ብቻ አቶ አንዳርጋ቞ው አቶ ኢሳያስን ያልሆኑትን አድርጎ ሳላ቞ው። በዚህ ዚአንዳርጋ቞ው ቅብፀ ራሳ቞ው አቶ ኢሳያስና ኀርትራዊያን ዹሚኹፉ ይመስለኛል። አፍንጫው ድፍጥ ጥዚሆነውን ሰው አፍንጫ ሰልካካፀ አንገቱና ትኚሻው ዚተጣበቀውን ዹኔ ቢጀ ጉጣ መለሎ አስመስለው ቢስሉት እንደስድብ ይቆጠራል።

ለፕሮፓጋንዳውፀ ዚኢቲቪ ግልባጭፀ

2-እነሆ አንዳርጋ቞ውና ግንቊት ሰባት ዚቀዚሱት በደንብ ያልተተነተነ ዚስህተት ፕሮፓጋንዳ ገፍቶፀ ያንን መንገድ ሲጠራጠሩ ዚነበሩት ሁሉ ዚዚያ ወንጌል ሰባኪ ሆነው ኚቜ ብለዋል፡፡ ኚአንድ ጓደኛዬ ጋር ግንቊት ሰባትንና “ይሄንን ኀርትራ ወይም ሞት” ፕሮፓጋንዳ ስናማ እንደተስማማነውፀ ኢሳት ኀርትራ መሄዱ ተገቢ ቢሆንምፀ ኚኀርትራ መልስ ዹሚሰማው ፕሮፓጋንዳ ግንፀ ልክ ኢትዮጵያ ሄደው ዚሚመጡ ሰዎቜ “ፎቅ ታንጟዋልፀ መንገድ ተሰርቷልፀ ግድብ እዚተገደበ ነውፀ ዹኹተማ ባቡር ገብቷልፀ ስለዚህ ዝም በሉ” ብለው እንደሚያወሩት ነው ዚመሰለኝ፡፡ ግንቊት ሰባት ኚኀርትራ ጋር መስራቱ ኚጥንትም ስገፋፋው ዹነበሹና ዚምስማማበት ነገር ነው። ለምሳሌ በነሀሮ 2000 ዓ.ም. ገና ግንቊት ሰባት በይፋ ሳይገባበትፀ ስለፍኖተ-ኀርትራ ይሄንን ዚድጋፍ ጜሁፍ ጜፌ ነበር፡፡

3-ቜግሩፀ ግንቊት ሰባትም ይሁኑ ኢሳትፀ ኀርትራን ዹተመለኹተ በቂ ታሪካዊና ፖለቲካዊ ትንተና ዚሚጎድለው ፕሮፓጋንዳ ውስጥ ገብተዋል። ለምሳሌፀ ይሄ ዚአቶ ኢሳያስ ቆሞ ግድብ ማሰራት ጉዳይ መደበቅ እንጂ መደነቅም መዘገብም ዚሌለበት ነገር ነው፡፡ አሁን ዹምንመለኹተው ኀርትራንና ሻእቢያን ወይንም አቶ ኢሳያስን ቀና ዚኢትዮጵያ አጋር አድርጎ ዚመሳል ፕሮፓጋንዳፀ ዚኢህአዎግ አቶ መለስን ዚኢትዮጵያ ህዳሎ አድርጎ ዚመሳል ፕሮፓጋንዳ ግልባጭ ይመስላል፡፡ ለምሳሌፀ “አቶ መለስ ዜናዊ ዚህዳሎውን ግድብ መሰሚት ጣሉፀ አቶ መለስ 30 ዩኒቚርስቲ አሳነጹፀ ዚህዳሎው ግድብ 33 ኚመቶ መጠናቀቁ ታወቀፀ ዚእድሚገትና ለውጥ እቅዱ ዚአቶ መለስ ጜንስ መሆኑ ተነገሹ” ዹሚለው ዜና ዹሰለቾን ሰዎቜፀ ለምን ዚአቶ ኢሳያስ ቆሞ ግድብ ማሰራት እንዳስደነቀንፀ እንደውም ለዜናነትም እንደበቃም አይገባኝም፡፡ በመሰሚቱ ያንድ አገር ፕሬዚደንትፀ ዚፖለቲካ መሀንዲስ እንጂ ዚግድብ መሀንዲስ አይደለም፡፡ ስለዚህ ቆሞ ግድብ ማሰራቱፀ ወይም ግድብ ግንባታ ላይ በሚያጠፋው ግዜፀ ሌላውን ዹሚመለኹተውን ስራ እንደበደለ ዚሚያሳይ ነው፡፡

4-በዚህ ሰሞን ኀርትራን በተመለኹተ ዚኢሳት ዘገባ ላይፀ ዚኢሳትንና ዚግንቊት ሰባትን ተልእኮ መለዚት ተስኖኛል፡፡ ኢሳት ወደኀርትራ መጓዙና እዚያ አካባቢ ያለውን ነገር መዘገቡ ትክክል ነው፡፡ ዹዘገበውን ነገር መልቀቅ በቂ ሆኖ ሲገኝፀ ያንን ቪዲዮ ይዞ በዚኚተሞቹ ዚመዞሩ ፋይዳ ዚተመለኚቱትን ዚመዘገብ ብቻ ሳይሆንፀ በዚህ መንገድ መጓዝ አለብን በሚለው ሀሳብ ዚማጥመቅ ሙኚራም ይመስላል፡፡ “በኀርትራ ያለው ሁኔታ ተስፋ ስለሚሰጥፀ ዝም ብላቜሁ ያንን መንገድ ተቀበሉ” ዹሚል ይመስላል፡፡ ኢሳት እዚህ ጋር ሚናውን ሚስቷል፡፡ ዚኢሳት ስራ መዘገብና ማቅሚብ እንጂፀ ማሳመንና ማጥመቅ አይደለም፡፡ ኢሳት በቅን ልቡናፀ ትግሉን በቋሚነት በማይጠቅም ፕሮፓጋንዳ ውስጥ ተዘፍቆ ተመልክቌዋለሁ፡፡

5-ዚኢትዮጵያ ህዝብ በኀርትራ በኩል ዹሚደሹገውን ትብብር እንዲቀበል ለማድሚግ መዝፈን ምንም ስህተት ዚለበትም፡፡ ያንን ፕሮፓጋንዳ ግን በተሳሳተ ቅኝት መዝፈን ዚለብንም፡፡ ለምሳሌ ይሄ ፕሮፓጋንዳ ውስጥ ስለኀርትራ ወታደሮቜና ስለአቶ ኢሳያስ ቀናነት ለኢትዮጵ ህዝብ ለማስሚዳት መሞኹር ድፍሚትም ስህተትም ነው፡፡ ዚኢትዮጵያ ህዝብ አቶ ኢሳያስን ዹተመለኹተ በቂ ተሞክሮ አለው፡፡ ይልቅስ ኢሳት ማተኮር ዚነበሚበትፀ በሁለቱ አገሮቜ/ህዝቊቜ መካኚል ስለነበሚው ታሪካዊ ትስስርና ቜግርፀ ኀርትራዊያን ኚኢትዮጵያ እንዲገነጠሉ ስላደሚጋ቞ውና አቶ ኢሳያስ ተዛባ ስለሚሉት ታሪክፀ ስለሁለቱ አገሮቜ ብሄራዊ ጥቅምና ሁለቱ አገሮቜ አንዳ቞ው ያንዳ቞ው ስጋት ሳይሆኑ ስለሚኖሩበት ሁኔታፀ በሁለቱ አገሮቜ መካኚል ለሚኖር ሰላማዊ ግንኙነት እንቅፋት ስለሚሆኑ ነገሮቜፀ ወደፊትም ስለሚጋጥሙ ተግዳሮቶቜ ነው፡፡ ይሄ “እኛ እኮ አንድ ነንፀ መልካቜን አንድ ነውፀ አማርኛ ይናገራሉፀ ዚጥላሁንን ዘፈን ይዘፍናሉ” ዹሚለው ፕሮፓጋንዳፀ በምንም መልኩ በሁለቱ አገሮቜ መካኚል ያለውን ታሪካዊና ፖለቲካዊ ቁርሟ አይፈታውም፡፡ አዳራሜ ውስጥ ዹሚደሹጉ ጭብጚባዎቜና ሜንገላዎቜ ብቻ቞ውንም ዚሚፈይዱት ነገር ዚለም፡፡

አርበኞቜ ግንት ሰባትፀ አንድም ሁለትም ነን

6-ሌላው በዚህ ዚኢሳትና ግንቊት ሰባት ዚኀርትራ ጉዞ በዋንኛነት ዹተዘገበው ነገር ዚግንቊት ሰባትና አርበኞቜ ግንባር ውህድት ነው፡፡ በዚህ ላይ ጥቂት ነገሮቜን እንበል፡፡ አንደኛውፀ ብዙ ግዜ ዚኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎቜ ውህደት/ግንባር ምስሚታ ኚነፍትወቱ በሚመነኩስ መነኩሎ ይመሰላል፡፡ ግንቊት ሰባትና አርበኞቜ ኚተዋሃዱ ስማ቞ውን ወደአንድ ኢትዮጵያ ነክ ስም ዚማይለውጡበት ምክንያት አይታዚኝም፡፡ ሁለቱም ያልሞተ ኢጎ ኹሌላቾው በስተቀር፡፡ ዚኢትዮጵያ ፖለቲካ ድርጅቶቜ ጜኑእ ዚስም ፍቅር አላ቞ው፡፡ ኢህአፓዎቜ ስማ቞ውን ወይ በኩራት ባደባባይ አይጠራቡትፀ ወይ ቀተመዘክር ውስጥ አያስቀምጡትፀ ለምን ስማቜሁን አትለውጡም ሲባሉፀ ሰዎቜ ተሰውተውበታል ይላሉ፡፡ ኢዎአፓና መድህን ሲዋሃዱፀ ኢዎአፓ-መድህን፡፡ አንድነትና መኢአድ ሊዋሃዱ ሲሉ አንዱ ያጚቃጚቃ቞ው ዚስም ጉዳይ ነበር፡፡ ግንቊት ሰባት-አርበኞቜፀ “ድርጅታቜንን አምክነን ተዋህደናልፀ ግን አንድም ሁለትም ነን” እንደማለት ነው፡፡

7-ሁለተኛፀ ይሄ በተልእኮ/በርቀት ዚሚመራ መሪ ነገርም አይገባኝም፡፡ በርግጥ ይሄ ዚድርጅቶቹ ጉዳይ ቢሆንምፀ በዚህ ውህደት ውስጥፀ ዲባቶ ብርሀኑ ነጋን ሊቀመንበር አድርጎ መምሚጥም ስህተት ይመስለኛል፡፡ እስኚምናውቀው ድሚስፀ ብርሀኑ ነጋ ዹሙሉ ግዜ መምህር/ፕሮፌሰር ነው፡፡ በዚያ ላይ ቀተሰብም ግዜ ይፈልጋል፡፡ ዚፖለቲካ ትግሉም ሌላ ዹሙሉ ጊዜ ስራ ነው፡፡ ዹሙሉ ጊዜ ጠላትን በትርፍ ጊዜ ትግል አናሞንፋም፡፡ ጠላቶቻቜን ያሞነፉንም ዚሚመሩንም በሙሉ ጊዜ ትግል ነው፡፡ ስለዚህ እዚህ ሰሜን አሜሪካ ዹሚኖርን ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ ወይም አጠገብ ዚሚታገል ድርጅት መሪ አድርጎ መመሚጥ ብቻውንፀ ዚስልታቜንን ጉድለት ያሳል፡፡ ሊቀመንበሩፀ በዚህ ብዙ በተነገሚለትና ትግሉን ወደሌላ ምእራፍ እንደሚያሻግር በተተነበዚለት ውህደት ላይ ቢገኝ ትልቅ ነገር ነበር፡፡ በድርጅቶቹ ዚአንድ ሳምንት ዚውህደት ስብሰባ ላይ ተገኝቶ ኚአባላቱና ኚአስተናጋጇ ኀርትራ መሪዎቜ ጋር ለመነጋገር ያልቆሚጠ መሪፀ እንዎት ዚድርጅቱ መሪ ሊሆን እንደሚቜልና ወደድል እንደሚወስደን አይገባኝም፡፡ ይሄ በጉዞ ሰነዶቜና አንዳንድ ጉዳዮቜ አለመሟላት መገኘት አልቻሉም ዹሚለው ሰንካላ ምክንያት አያሳምንም፡፡ አንድም ጉዳዩ ትኩሚት አልተሰጠውም፡፡ አለያም ብርሀኑ በዚህ ዚኀርትራን ትግል አላመነበትም፡፡ ስድስት ሰባት አመታት መሪው እግሩን ያልጣለባት አገር ዋና መቀመጫው ዹሆነ ድርጅት መሪፀ ዚድርጅቱ መሪ ባይሆን ይመሚጣል፡፡

ወደኀርትራ ጉዳይ ስንመለስፀ ግንኙነቱ እንዎት ይቃኝ

8-ኹላይ እንዳልኩትፀ ኚኀርትራ ጋር መስራት ምርጫ አይደለም፡፡ ኚኀርትራ ጋር መስራት ዚግድ ነው፡፡ ኚኀርትራ ጋር አብሚን ካልሰራንፀ ጠላት ሆነን እንቀጥላለን፡፡ አንዳቜን አናት ሌላኛቜን ሾሆና ስንቀጠቅጥ እንኖራለን፡፡ ቜግሩፀ ኚኀርትራ ጋር በተያያዘፀ አሁን ያለው ዚግንቊት ሰባትም ይሁን በኀርትራ በኩል ዚሚሰሩ ሌሎቜ ዚብሄርም ሕብሚ-ብሄርም ድርጅቶቜፀ ተስፋ ዚሚጣልበት አመራር ማሳዚት አልቻሉም፡፡ ኹዚህ ጋር በተያያዘ በሰኔ 2004/2012 ኚኀርትራ ጋር ስለመስራት አንድ ጜሁፍ ጜፌፀ በዚያ ጜሁፍ ላይ ዹሚኹተለውን ብዬ ነበር፡፡

ኚኀርትራ ጋር ዚኀርትራን ሉአላዊነት ያወቀና ዚኀርትራንም ዚኢትዮጵያንም ብሄራዊ ጥቅም ያስቀመጠ ውል መግባት አንዱ ዚትግል አማራጫቜን ነው። በኀርትራ በኩል ያለው ትግል (ወደፊት) ያልገፋው ኚኀርትራ ጋር በግልጻና በይፋ ዹሚዋዋል ጠንካራና ደፋር ሀገር ወዳድ ድርጅት ስላልተገኝ ነው። ያንን ክፍፈት ሊሞላ ዚሚቜል ደግሞ ኚግንቊት ሰባት ዚተሻለ ዚለም። ግንቊት ሰባት ግን እስካሁን ድሚስ በዚህ ጉዳይ ላይ ተሻሞ እንጂ አልቆሚጠም።

9-ግንቊት ሰባት ኀርትራ ኚገባ ጥቂት አመታት ቢያልፈውምፀ እስካሁንም ድሚስ ኚኀርትራ ጋር ዚተድበሰበሰ እንጂፀ በግልጜ ሰነድና ውል ላይ ዹተመሰሹተ ግንኙነት አልፈጠሚም፡፡ ኚኀርትራ ጋር ለመስራት ግልጜ ዹሆነና ዚሁለቱን አገሮቜ ብሄራዊ ጥቅም ኚግምት ያስገባ ስምምነት ያስፈልጋል፡፡ ይሄ ዚኀርትራን ጉዳይ መወሰን ወይንም “ኚኀርትራ ጋር ዹሚኖሹንን ዹውጭ ግንኙነት ዹመወሰን ስልጣን ዚኢትዮጵያ ህዝብፀ ወይም ሕዝቡ ዹሚመርጠው ዎሞክራሲያዊ መንግስት ጉዳይ ነውፀ እኛ አሁን አንወስንም” ዹሚለው ዚግንቊት ሰባት አባባልፀ አንድም ሀላፊነትን ሜሜት ነውፀ ሌላም በሻእቢያ ዘንድ አመኔታን ዚሚያሳጣ ነው፡፡ አንደኛፀ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ነጻ አውጣኝ ብሎ ዹላኹው ድርጅት ዚለም፡፡ ስለዚህ ዚህዝብ ውክልና ዚምንጠብቅ ኚሆነፀ ኀርትራ በመግባት ጉዳይ ላይ ራሱም ህዝብ ድምጜ አልሰጠበትምና ስህተት ነው፡፡ ሁለተኛፀ ሻእቢያ ኚጥንትም ዚአንድነቱን ሀይል ይጠራጠራል፡፡ ሻእቢያዎቜ በፖለቲካውና ትግሉ ውስጥ ብዙ ቆይተዋል፡፡ ለጊዜው ያለምንም ስምምነት እርዳታ቞ውን እንቀበልና ኚድል በኋላ እንፈነግላ቞ዋለን ብለን ዚምንሞውዳ቞ው ሀይሎቜ አይደሉም፡፡ ዚኀርትራን ሉአላዊነት በግልጜ ሳንቀበልፀ ዚባህርበርን ጉዳይ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ወደፊት ይወስናል እያልን ዹምንቀርበው ዚኀርትራ መንግስትፀ እንዎት አድርጎ በሙሉ ልብ ተማምኖብን እንደሚሚዳን አይታዚኝም፡፡

ዚኀርትራና ዚኢትዮጵያ ተቃዋሚዎቜ መርህ-አልባ ግንኙነት

10-አሁንም ቢሆንፀ ኚኀርትራ ጋር ለመስራት ዚሚያስፈልገንፀ ሻእቢያን/ኢሳይያስን ቅዱስ አድርጎ ዚመሳል አካሄድ ሳይሆንፀ ዚሁለቱን ሀገሮቜ መሰሚታዊና ብሄራዊ ጥቅም ኚግምት ያስገባ ፕሪንሲፕልድ ዹሆነ አካሄድ ነው፡፡ ኀርትራ አገር ነቜ፡፡ ቢቆጭምፀ ያጣና቞ው ሀሰብና ቀይባህርም ዚኀርትራ ና቞ው፡፡ ይሄንን በደንብ በይፋ ማመንና መቀበል ያስፈልጋል፡፡ ዚኢትዮጵያ ሉአላዊነት ሁልግዜም ቢሆን ፈተና ላይ ዚሚወድቀው በኀርትራ በኩል መሆኑንና ሁለቱ አገሮቜ በምስራቅ አፍሪካውና በቀይ ባህር በኩል ደህንነታ቞ው ተጠብቆ እንዲኖሩ መተባበራ቞ውና አብሚው መስራታ቞ው ዚግድ እንደሆነ ኚግምት ያስገባፀ ኢትዮጵያ ደህንነቷፀ ኀርትራም ህልውናዋ ተጠብቀው ሊኖሩ ዚሚቜሉት አንዳ቞ው ካንዳ቞ው ጋር መስራት ኚቻሉ ብቻ እንደሆነ ባሰመሚ ስምምነት ላይ ዹተመሰሹተ ግንኙነት ነው፡፡ ኢትዮጵያ ጠንካራ አገር ሆና እንድትቀጥል በኀርትራ በኩል ያለው ደህንነቷ አስተማማኝ መሆን አለበት፡፡ ኀርትራም ያለስጋትና ሰቀቀን እንድትኖር ዚኢትዮጵያ ቡራኬ ያስፈልጋታል፡፡ ግንቊት ሰባትፀ ይሄንን ዚሁለቱን አገሮቜ ብሄራዊ ጥቅም በግልጜ ያስቀመጠ ስምምነት ላይ ማተኮር ተስኖትፀ ደሹጃወን ባልጠበቀና ውሀ በማይደፋ ፕሮፓጋንዳ ውስጥ ሲዳክርፀ ኢሳትም ዹዚህ ዚግንቊት ሰባት ፕሮፓጋንዳ ሰለባ ዹሆነ መስላል፡፡

11-በኀርትራና በኢትዮጵያ በነበሹው ዚታሪክ ኡደትፀ በመቶ ሺሆቜ ዚሚቆጠሩ ወታደሮቜና ሲቪሎቜ ሞተዋል፡፡ አያሌ ሺኆቜ አካለጉዳተኞቜ ሆነዋል፡፡ ብዙዎቜ ተዋርደውና እርቃና቞ውን ተፈናቅለዋል፡፡ ዚአገሮቹ አንጡራ ሀብትም በጊርነት ባክኖ ሕዝቊቹን ለድህነትና ለሰቆቃ ኚዳሚጉት ነገሮቜ ዋንኛው ይሄ በሁለቱ ህዝቊቜ መካኚል ዹነበሹው ሹጅም ጊርነት ነው፡፡ በዚህ ጊርነት አያሌ ሺሆቜም ያለወላጅ ቀርተዋል፡፡ ኢሳትም ይሁን ሌሎቜ ተቃዋሚ ሀይሎቜ ኚኀርትራ ጋር መስራት ካለባ቞ው ይሄንን ያለፈ ቁርሟ እያነሳን ባናለቅስበትምፀ ምንም እንዳልተፈጠሚና አንድ እንደሆንን አድርገንም ወሬ ማብዛት ዚለብንም፡፡ ይልቅስ ፕሮፓጋንዳው ማተኮር ያለበትፀ ዚሁለቱን አገሮቜ ብሄራዊ ጥቅሞቜ መሰሚት ያደሚጉ ውይይቶቜና ጥናቶቜ ላይ ነው፡፡ እንደውም በኢትዮጵያና አካባቢው ታሪክ ውስጥ እንደኀርትራ ጉዳይ ለሰፊ ውይይትና ትንታኔዎቜ ዚሚመቜ ጉዳይ ዚለም፡፡ ዚኀርትራ አካባቢ ኚአጌ ዮሀንስ እስኚ አጌምኒሊክፀ ኚጣሊን ወሚራ እስኚ ኀርትራ ቅኝ-ግዛትፀ ኀርትራውን ኚኢትዮጵያዊን ጋር ወይም ዚኢትዮጵያ አካል ሆነው ካደሚጉት ተጋድሎ እስኚ መጀመሪያው ድምጞውሳኔፀ ዚሻእቢያ ዚሰላሳ አመት ዚነጻነት ትግልፀ ሁለተኛው ዚኀርትራውያን ውሳኔድምጜፀ ዚኢህአዎግና ዚሻእቢያ ግንኙነቶቜፀ ዚቅርብ ግዜው ዚሁለቱ አገሮቜ ጊርነትፀ ሰፊ ውይይት ሊደሚግባ቞ው ዚሚገቡና አሁንም ድሚስ ዚአካባቢቜንን ፖለቲካ ዚሚዘውሩ ጉዳዮቜ ና቞ው፡፡ እነዚህን ጉዳዮቜ ሳናነሳ ዹምናደርገው ዚኀርትራ ጉዞ ለድልም ለገድልም አያበቃንም፡፡ እንጂ አሁን እንዳደሚግነውፀ ዚፕሮፓጋንዳውን ቅኝት ዚአቶ ኢሳያስ ደግነት ላይ መትኚል ዚዋህነት ነው፡፡

12-ግንቊት ሰባትና ኀርትራም አብሚው መስራት ካለባ቞ው በሁለቱ አገሮቜ መካኚል ዚተካሄደውን ዚሰላሳ አመት ጊርነት እንዳልነበር ሚስቶፀ ወይንም ዚሁለቱ አገሮቜ ቜግር ኢህአዎግ/ሕወሀት ዹፈጠሹው አይነት አስመስሎ በመናገር መሆን ዚለበትም፡፡ በዚህ መርህ አልባ በሆነ አካሄድ ተሂዶ ኢህአዎግ ኚስልጣን ቢወገድም እንኳንፀ በሁለቱ አገሮቜ መካኚልፀ ሻእቢያና ሕወሀት ደርግን ኚጣሉ በኋላ እንደተፈጠሚው አይነት ዚተዛባ ግንኙነት መፈጠሩናፀ በዚያም ወደሌላ ጊርነት እንደማንገባ ዋስትና ዚለም፡፡ ግንቊት ሰባት ይሄንን ጉዳይ ፊትለፊት መግጠም ፈርቶ በይደር ትቶታል፡፡ ኢሳትም በቋሚ ጥቅሞቻቜን ላይ ዚተሰመሚት ጥልቅ ታሪካዊፀ ማህበራዊፀ ፖለቲካዊፀ ስትራ቎ጂካዊ ውይይት ማድሚግና ማመቻ቞ት ሲገባውፀ በመርህ-አልባ ፍቅር ያበደፀ ግለሰቊቜን መሰሚት ያደሚገናፀ ዚተመሚጡ ቃለምልልሶቜ ላይ ያተኮሚ ዚብሜሜቅ ዝግጅት ላይ አተኩሯል፡፡ ለብሜሜቅ ለብሜሜቅ እኔ ኚሶፊያ ጋር ያደሚኩት ቃለምልልስ በቂ ነበር፡፡ ብሜሜቅ ሲያልፍ ግንፀ እውነተኛ ፖለቲካ እያደር ፈጩ ይጋፈጠናል፡፡ ስለዚህ ግንቊት ሰባትም ኢሳትም መርህን መሰሚት ወዳደሚግ ዚሁለቱ አገሮቜ ግንኙነትና ጉዳይ ያተኩሩ፡፡

እንደማስታወሻፀ ይሄንን ዚምጜፈው ለምንድነው? አንድም ስለሚያገባኝ ነው፡፡ ሌላም በንጜጜርፀ ኢትዮጵያን ሊያድን ዚሚቜልፀ ነገር ግን ካቅሙ በታቜ እዚሰራ ያለ ድርጅት ግንቊት ሰባት ነው ብዬ ስለማምንናፀ ግንቊት ሰባት ምናልባት አስተያዚ቎ን ኚተቀበለውፀ ቅኝቱን እንዲያስተካኚል እድል ለመስጠትፀ እንዲሁም ትቜ቎ ሀሜት ሆኖ እንዳይቀር ለማድሚግ ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎቜፀ ታዲያ ለምን በግል አትነግራ቞ውምፀ ብለው ይጠይቃሉ፡፡ ለዚህ ብዙ መልስ አለኝ፡፡ ዋንኛው ግንፀ በግል ሲነገሩ ትኩሚት ዚማንሰጥባ቞ው ነገሮቜፀ ባደባባይ ሲነገሩ ዹበለጠ ትኩሚት ያገኛሉፀ ዹሚለው ነው፡፡ በተጚማሪምፀ ይሄንን ዚምጜፈውፀ አለሁፀ ለማለትም ነው፡፡ ኚጠፋሁምፀ በዚህ ተጠምጄ ነው፡፡ ማስታወቂያ ነገር መሆኑ ነው፡፡

ተክለሚካኀል አበበ ሳሕለማርያም፡፡ ቶሮንቶፀ መጋቢት ፳፻፯፡፡ ለጀናማ አስተያዚትፀ tekle@tekle.net

↧

ዚባህርዳር ኹተማ አስተዳደር ዚትብብሩን ሰልፍ እውቅና ነፈገ –ነገሹ ኢትዮጵያ

$
0
0

‹‹ህገ መንግስታዊ መብታቜን ኹቩሊ ቩል ስፖርት በታቜ ሆኗል››

አቶ አዲሱ ጌታነህ
ዚባህርዳር ኹተማ አስተዳደር እሁድ መጋቢት 20/2007 ዓ.ም ዹ9ኙን ፓርቲዎቜ ትብብር በባህርዳር ኹተማ ሊያደርገው ዹነበሹውን ሰላማዊ ሰልፍ እውቅና እንዳልሰጠውና ሰልፉን ማድሚግ እንደማይቻል ዚትብብሩ አባልና ዚባህርዳር ሰልፍን አስተባባሪ ለሆነው ሰማያዊ ፓርቲ በላኹው ደብዳቀ አስታውቋል፡፡

አስተዳደሩ ለሰልፉ እውቅና እንዳልሰጠ ዹገለፀው ‹‹ሁለተኛውን አገር አቀፍ ዚትምህርት ቀቶቜ ስፖርት ውድድር እያስተናገድን በመሆኑ›› እና ‹‹ዚህዳሎውን ግድብ ዚቊንድ ሳምንት በኚተማቜን በዹማዕኹሉ እዚሰራን በመሆኑ›› ሰልፉን ለመጠበቅ ዚሚያስቜል ዚፀጥታ ኃይል ዹለም በሚል ነው፡፡

ዹሰልፉ አስተባባሪዎቜ ወደ ኹተማው ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በተደጋጋሚ ባቀኑበት ወቅት አመራሮቹ ሲጠፉ እንደቆዩ ዹገለፀው ዹሰልፉ አስተባባሪ አቶ አዲሱ ጌታነህ በመጚሚሻ ሁለቱን ጥቃቅንና ዚፀጥታ ኃይል ለመላክ ዚማያግዱ ጉዳዮቜን ጠቅሰው ሰልፉ እንዳይደሚግ ወስነዋል ብሏል፡፡
ዚምርጫ ወቅት እንደመሆኑ ለሰላማዊ ሰልፉ ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባ ነበር ያለው አቶ አዲሱ ‹‹በሁለተኛ ደሹጃ ተማሪዎቜ መካኚል በሚካሄድ ስፖርት ይህ ነው ዚሚባል ዚፀጥታ ኃይል አያስፈልግም፡፡ ቊንድም ቢሆን በባንኮቜ በኩል ነው ዚሚሞጠው፡፡ ያም ሆኖ ባህርዳር ዹክልሉ ዋና ኹተማ እንደመሆኗ ኹፍተኛ ቁጥር ያለው ፖሊስና መኚላኚያ አለ፡፡ በመሆኑም ምንም አይነት ዚፀጥታ ኃይል እጥሚት ዚለም፡፡›› ሲል ውሳኔው ትክክል አለመሆኑን ለነገሹ ኢትዮጵያ ገልጟአል፡፡
አቶ አዲሱ አክሎም ‹‹በእነዚህ ጥቃቅን ምክንያቶቜ ሰልፉን ሆን ብለው ማገድ ፈልገዋል፡፡ ዹሁለተኛ ደሹጃ ተማሪዎቜ ስፖርት ውድድር ተጠቅሶ ሰልፍ እንዳይደሚግ መወሰኑ ህገ መንግስታዊ መብታቜንን ኹቩሊ ቩል ስፖርት በታቜ እንዳደሚጉት ትልቅ ማሳያ ነው፡፡›› ብሎአል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ትብብሩ መጋቢት 20/2007 ዓ.ም በተመሳሳይ ጊዜ ሰልፍ ለማድሚግ ባቀደባ቞ው 14 ኚተሞቜ ዹሚደሹገው ሰልፍ እንደተጠበቀ ሲሆን ዚአዲስ አበባው ካሳንቺስ ኹሚገኘው ዚሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ተነስቶ በአራት ኪሎ፣ አምስት ኪሎ፣ ሾዋ ዳቊና ግንፍሌ አድርጎ ወደ ቀልዚር ሜዳ እንደሚያቀና ታውቋል፡፡10428113_685829248209403_4052969711816874267_n

↧

ዹዓሊ ቢራ ዚጥበብ ሥራዎቜ ዚኊሮሞ ሕዝብ ብቻ ሀብት ናቾው እንዎ?!፡- ቋንቋዎቻቜን ዚልዩነት፣ ዚጥላቻና ዚዘሚኝነት ጜኑ ግምብ ሲሆኑብን! በኒቆዲሞስ

$
0
0

ዚሃይማኖት ሊቃውንት በጥንት ዘመን ፍጥሚት ሁሉ በአንድ ቋንቋ ይነጋገር እንደነበርና ቆይቶ ግን ይህ በአንድ ቋንቋ ዚመግባባት ጉዳይ ብዙም ሳይዘልቅ እንደ ተቋሹጠ ያትታሉ፡፡ ምክንያቱን ሲያብራሩም ጥንታውያኑ ባቢሎናውያን ገናና ሥልጣኔያ቞ው ጫፍ በነካ ማግሥት ሰማይን ዚሚታኚክና ዚፈጣሪን መኖሪያ፣ ክብሩንና ልዕልናውን ዚሚዳፈር ሹጅምና ግዙፍ ዹሆነ ታላቅ ግምብ ለመገንባት ተነሡ፡፡

ይህን ጊዜ ታዲያ ዚልባ቞ውን ትቢዕት፣ ክፋትና ዓመፃ አስቀድሞ ያዚው ፈጣሪም እርስ በርሳ቞ው እንዳይግባቡ ቋንቋቾውን ደበላለቀው ይሉናል እነኚሁ ዚመጜሐፍ ቅዱስ ምሁራን፡፡ እናም ዹዚህ ሁሉ ቋንቋ መፈጠር መንሥኀው ዹሰው ልጅ ዓመፃ ውጀት ነው ሲሉ ያስሚዳሉ፡፡ ሳይንስ ደግሞ በበኩሉ ቋንቋ ዹሰው ልጆቜ ዚሥራና ዚማኅበራዊ ኑሮ መስተጋብራ቞ው ድምር ውጀት ነው ሲል ይደመድማል፡፡
በዓለም ያሉት ቋንቋዎቜ ዚሃይማኖት ሊቃውንት እንደሚሉት ዹሰው ልጆቜ ዚኃጢአት/ዚክፋት ውጀትም ይሁኑ አሊያም ደግሞ ዚሳይንስ ጠበብቶቜ እንደሚሉት ዹሰው ልጆቜ ዚሥራና ማኅበራዊ መስተጋብር ውጀት፣ ኚፍጥሚት ሁሉ ዹላቀው ዹሰው ልጅ በዚህም ቢሆን በዚያ መንገድ ይባል አሳቡንና ስሜቱን ዚሚገልጜበት ዚበርካታ ቋንቋዎቜ ባለቀት ለመሆን ቜሏል ወይም በቅቷል፡፡

ዚጜሑፌ ዐቢይ መልእክት ስለ ቋንቋ ጅማሬ ሃይማኖትና ሳይንስ ዚሚያነሷ቞ውን ዚመኚራኚሪያ እሳቀዎቜ እያነሡ ለመተንተን አይደለም፡፡ ግና በአገራቜን በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ቋንቋዎቻቜን ‹‹እነርሱና እኛ›› በሚል ዚጥላቻንና ዚዘሚኝነትን ግምብ ዚገነባንባ቞ው፣ ዚእርስ በርስ ልዩነቶቻቜን እያሰፉ ያሉ ዚልዩነትና ዚጥላቻ መስመር ያሰመርንባ቞ው፣ ጜኑ ዹሆኑ ዚመለያያ ግምብን ዚገነባንባ቞ው፣ ዚዘሚኝነትና ዚጥላቻን ቜካል ዚ቞ኚልንባ቞ው መሚገምቶቻቜን እዚሆኑ እንደመጡ እያስተዋልን ነው፡፡

ለዛሬው ጜሑፌ መነሻ ዹሆነኝ ባለፈው ሳምንት ዚተዋዳጁ ዹሙዚቃ ባለሙያ ዚአርቲስት ዓሊ ቢራ ዚኀምሳ/፶ኛ ዓመት ዚጥበብ ጉዞው በዓል በተኚበሚበት ወቅት ዹሆነ ክስተት ነው፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው ዹዓሊ ቢራን ዚ፶ኛ ዓመት ዹሙዚቃ ዚስኬት ጉዞ ለማክበር ኚተዘጋጁት ዝግጅቶቜ አንደኛው በአዳማ ኹተማ በሙዚቃ ሥራዎቹ ላይ በተለያዩ ምሁራን ጥናታዊ ጜሑፎቜ ዚሚቀርብበት ዝግጅት ነበር፡፡ ታዲያ ዚማታ ማታ ዚዝግጅቱ አስተባባሪዎቜ ኹአፋን ኊሮሞ ቋንቋ ውጭ በሌላ ቋንቋ ዚቀሚቡ ጥናታዊ ጜሑፎቜ በምንም መልኩ እንደማያስተናግዱና ተቀባይነት እንደሌላ቞ው አስታወቁ፡፡

እንግዲህ ልብ በሉ ይህ ይህ ውሳኔ ደግሞ አስቀድሞ ዹተነገሹ አይደለም፡፡ እንደ ውኃ ደራሜ ድንገት ዹሆነ ውሳኔ ነው፡፡ መቌም ዓሊ ቢራ ይህን ውሳኔ ይቀበለዋል፣ ይደግፈዋል ብዬ ለማመንና ለመቀበል እ቞ገራለኹ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ዓሊ ቢራ ዹሙዚቃ ሥራዎቹ በኊሮምኛ ቋንቋ ብቻ ዚተሰሩ አይደሉምና፡፡ ባለኝ መሹጃ ዓሊ ቢራ በአማርኛ፣ በአደሪኛ፣ በዐሚቢኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎቜ ዘፍኗል፡፡ እነዛ ዘመናትን ዚተሻገሩ ዹዚህ ድንቅ ዚጥበብ ሰው ሥራዎቹ ብዙዎቻቜን ልብ ውስጥ ዛሬም ድሚስ ትልቅ ክብርና ሥፍራ አላ቞ው፡፡ ዓሊ ቢራ ስለ ነጻነት፣ ስለ ፍቅር፣ ስለ ጥበብ፣ ስለ አገሩ ውበትና ተፈጥሮ ያዜማ቞ው ዜማዎቹ እኮ ዘርና ቋንቋ ሳይለዩ ዹሰው ልጆቜን ሁሉ ማዕኹል ያደሚጉ እንደሆኑ ነው ዚሚገባኝ፡፡

ዹዚህ ዝግጅት አስተባባሪዎቜ ዹዚህን አንጋፋና ታላቅ ዚጥበብ ሰው ሰው ሥራዎቜ በምን አመክንዮ ኹአፋን ኊሮሞ ውጭ ሊዳሰሱ፣ ሊተነተኑ እንደማይቜሉ ዚደሚሱበትን ውሳኔያ቞ውን በግልጜ ቢነግሩን መልካም ነው፡፡ እንደሚገባኝ ይህ ውሳኔያ቞ው ፈጜሞ ለጥበብና ለጥበብ ሰዎቜ ዚሚሆን፣ ዚሚስማማ አካሄድ አይደለም፡፡ ደግሞስ ዚጥበብ ሥራ ዚቋንቋ፣ ዹዘር ድንበር አለው እንዎ?! ይህ ውሳኔ ዹወሰኑ ሰዎቜ በፍቅርና በአክብሮት ዚምንግራ቞ው ነገር ቢኖር ይህን በማድሚጋ቞ው ዹዛን ታላቅ ዚጥበብ ሰው፣ ዹዓሊ ቢራን ድንቅ ዚጥበብ ሥራ ያሳነሱና ያኮሰሱ መሆናቾው ሊገባ቞ው ይገባል፡፡

ቢሆንልን ሁሉም በዹቋንቋው ዹዚህ ዚጥበብ ሰው ሥራዎቜ ያላ቞ውን ፍቅርና አድናቆት፣ እንዲሁም ትቜትና አስተያዚት እንዲገልጹ ዕድል መስጠት ሲኖርብን እንዲህ ጠቩና አንሶ ኹአፋን ኊሮሞ ውጭ እንዎት ተደርጎ ዹዓሊ ቢራ ዹሙዚቃ ሥራዎቜ ይተነተናሉ፣ ይጠናሉ፣ ይተቻሉ፣ ይሔዚሳሉ ብሎ ማለት ጀነኛ አካሄድ አይደለም፡፡ እነዚህ ሰዎቜ አሳባ቞ውና ዓላማቾው ዚኊሮሞ ሕዝብን ቋንቋና ባህል ለማሳደግ ኹሆነ ዚመሚጡት ይህ መንገድ ትክክለኛ አይመስለኝም፡፡ ጥብብም ሆነ ዚጥበብ ሰው ዹቋንቋ ድንበር ዹለውምና!!
ኹዛም አልፎ ይህ እነዚህ ሰዎቜ ዚወሰዱት ውሳኔ ቋንቋና ዘር ሳይለይ ተዋድኖ ተጋብቶ በኖሹው ዚኢትዮጵያ ሕዝብ መካኚል ሌላ ዚጥላቻና ዚመለያዚት ግምብ መገንባት፣ ዚጥላቻ ክፉ ዘርን መዝራት ነው ዚሚሆነው፡፡ እስኚማውቀው ድሚስ ዓሊ ቢራ በኊሮሞነቱ፣ በቋንቋው፣ በባህሉ ዚሚኮራውን ያህል ኢትዮጵያዊነቱ በደሙ ያለ፣ ማንም ሊነጥቀው ዚማይቜለው በልቡ ውስጥ በደማቅ ዚታተመ ክብሩና መኩሪያው እንደሆነ ነው ደግሞ ደጋግሞ ሲገልጜ ዚሰማነው፡፡

በዓሊ ቢራ ዚጥበብ ሥራ ውስጥ ተደጋግሞ ዚተዘፈነለት ዚኊሮሚያ ምድርና ዚታላቁ ዚኊሮሞ ሕዝብ ዹሹጅም ዘመናት ታሪክና ሥልጣኔ፣ ቋንቋ፣ ባህል፣ አኩሪ ዚነጻነት ተጋድሎው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን በትልቁ ያደመቀና ያስዋበ ዚጥበብ ሾማ ነው፡፡ ‹‹በትናንትናዋም ሆነ በዛሬዋ ኢትዮጵያ ታሪክ መልክና ገጜታ ውስጥ ኊሮሞ ግንድ ነው፡፡›› እንዲሉ ዚፖለቲካ ምሁሩ ፕ/ር መሚራ ጉዲና፡፡ ይህ ታላቅ ሕዝብ ኚአማራው፣ ኚትግሬው፣ ኚአፋሩ፣ ኚሱማሌው፣ ኚሐሚሪው፣ ኚጉራጌው፣ ኚደቡብ ሕዝብ ጋር በጜኑ ዹፍቅርና አንድነት፣ ዚአብሮነት መሠሚት ላይ ዚተሳሳሚ፣ ዹተዋሐደ ታላቅ ሕዝብ ነው፡፡

ይህ በምሥራቅ አፍሪካ ኹሚገኙ ነገዶቜ መካኚል በሕዝብ ብዛቱ ተወዳዳሪ ዹሌለው ዚኊሮሞ ሕዝብ ታሪኩ፣ ቋንቋው፣ ባህሉ፣ ሙዚቃው
 ወዘተ እንዲስፋፋ፣ በአፍሪካና በመላው ዓለም ተሰሚነት እንዲኖሚው ለማድሚግ መጣር ሲገባ በአጉል ጥላቻና ጠባብነት ተይዞ ጥበብንና ዚጥበብ ሰዎቜን በአንድ ቋንቋ ብቻ መወሰን፣ መገደብ ትልቅ ስህተት ነው፡፡ ይህን ውሳኔ ያደሚጉ ሰዎቜም ዞር ብለው ውሳኔያ቞ውን እንዲያጀኑ፣ በዚህ ውሳኔ ውስጥም ዹዓሊ ቢራ እጅ ካለበት ይህ ለጥብብና ለጥበብ ሰው ዹማይበጅ አካሄድ፣ ጥላቻንና መለያዚትን ዚሚያነግሥ እንደሆነ በአክብሮት ለመግለጜ እወዳለሁ፡፡

ዚፍቅር፣ ዚተፈጥሮ፣ ዚውበት፣ ዚነጻነት፣ ውብና መገለጫ፣ ዹሰው ልጆቜ ሁሉ ዚመግባቢያ ሹቂቅ ቋንቋ ዚሆነቜ ሙዚቃን በዚህ ደሹጃ አውርዶና አዋርዶ፣ ኹዘመን ፖለቲካ ጋር አጋብቶና አዋሕዶ እንዲህ አመንዝራ እንድትሆን ማድሚግ ዚሚገባ አካሄድ ነውን?! ይህ ያደሚጉ ሰዎቜ ምክንያታ቞ውን በግልጜ አብራርተው ሊነግሩን ይገባል ባይ ነኝ፡፡ ኹዚህ ጋር አያይዀም ዹሁሉም ሕዝቊቜ ሀብት በሆነው ዹዓሊ ቢራ ዚጥበብ ሥራዎቜ ውስጥ ኊሮሞነትን ኚኢትዮጵያዊነት ለይተውና ነጥለው፣ በአንድ ቋንቋ ብቻ ገድበው ለማዚት፣ ለመተንተን ለሚፈልጉ ሰዎቜም አንድ ገጠመኜን በማንሳት ጥቂት ነገሮቜን ለማለት እወዳለሁ፡፡

በ1990ዎቹ መጚሚሻ አካባቢ በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ያሉ ዚኊሮሞ ብሔር ተወላጅ ተማሪዎቜ፣ ዚኊሮሚያ ዋና ኹተማ ፊንፊኔ መሆን አለባት በሚል ለዓመታት ዹቆዹውን ሙግት እንደገና ነፍስ እንዲዘራ በማድሚግ እንደ አዲስ ለጥያቄ አቅርበውት ነበር፡፡ በወቅቱ ደግሞ ዚፌዎራሉ መንግሥት ዚኊሮሚያ ዋና ኹተማ አዳማ እንጂ ፊንፊኔ አይደለቜም ባይ ነበር፡፡ እናም ይህን አጀንዳ ማለትም ዚኊሮሚያ ዋና ኹተማ ፊንፊኔ እንጂ አዳማ አይደለም ዹሚለውን አቀታታ቞ውን ለመንግሥት ለማሰማት ዚኊሮሚያ ብሔር ተወላጅ ተማሪዎቜ በአንድነት ተሰባስበው በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ፕሬዝዳንት ቢሮ ፊት ለፊት ኹሚገኘው አስፋልት ላይ ዹተቃውሞ ሰልፍ አድርገው ነበር፡፡

በዚህ ለግማሜ ቀን በዘለቀው ዚተማሪዎቹ ተቃውሞ ኚቢዝነስና ኢኮኖሚክስ፣ ኹቮክኖሎጂ ፋኩልቲ፣ ኚፋርማሲ ት/ቀትና ኚአራት ኪሎ ዩኒቚርሲቲ ዚመጡ ዚኊሮሞ ክልል ተወላጆቜም ሰልፉን ተቀላቅለውት ነበር፡፡ ሰላማዊ ዹሆነ ተቃውሞአቾውን በተለያዩ መፈክሮቜና መዝሙሮቜ ያሰሙት ተማሪዎቹ በኋላ ላይ ዚዩኒቚርሲቲው ፕሬዝዳንት ቢሮ ኚሚገኝበት ፊት ለፊት ካለው አስፋልት ላይ በፀጥታ ተቀምጠው ዚዩኒቚርሲቲው ኹፍተኛ ኃላፊዎቜ ምላሜ ይሰጧቾው ዘንድ መጠባበቅ ያዙ፡፡

ዘግይቶም ቢሆን በወቅቱ ዚአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ አካዳሚክ ቫይስ ፕሬዝዳንት ዚሆኑት ዶክተር ዚተማሪዎቹን አሳብና አቀቱታ ለመቀበል በርጋታ እዚተራመዱ ወደእነርሱ መጥተው ተቀላቀሏ቞ው፡፡ ተማሪዎቹም ዚዩኒቚርሲቲውን ባለ ሥልጣን በአክብሮት ኹተቀበሏቾው በኋላ በቢሮአ቞ው ፊት ለፊት ለግማሜ ቀን ያህል ለተቃውሞ እንዲሰበሰቡ ወዳደሚጋ቞ው ወደ ዋና ጉዳያ቞ው በቀጥታ አመሩ፡፡
ሰልፈኞቹ ተማሪዎቜም ኚመካኚላ቞ው ዹሚወክላቾውን ተማሪ መርጠው ጥያቄያ቞ውን ለሚመለኹተው ዚመንግሥት አካል፣ ለጠ/ሚሩ ጜ/ቀት እንዲያቀርቡላ቞ው ለእኚህ ሰው በቃል አቀሚቡ፡፡ በዚህ ሒደት ነበር በግሌ ያስገሚመኝን አንድ ነገር ዚታዘብኩት፡፡ ዚኊሮምኛ ተናጋሪ ዹሆነው ዚተማሪዎቹ ተወካይ አማርኛ ለመናገር ባለመፈለጉ ብቻ ሳይሆን አማርኛ ዚነፍጠኞቹ፣ ዹቅኝ ገዢዎቹ ዚአቢሲኒያውያን ቋንቋ ነው በሚል ድምዳሜ ዚተነሣ እርሱ በኊሮምኛ ቋንቋ ዚሚያቀርበውን አቀቱታ ሌላኛው ጓደኛው በእንግሊዝኛ ለዩኒቚርሲቲው አካዳክሚክ ቫይስ ፕሬዝዳንት እያስተሚጎመ መናገር ጀመሚ፡፡

ይህ ዚኊሮሞ ብሔር ተወላጅ ዹሆኑ ተማሪዎቜ ዙሪያ ጥምጥም አካኌድ ስለአማርኛ ቋንቋ ያላ቞ውን ዚተሳሳተ ግምትና ጥላቻ በግልጜ ያሳዩበት እጅጉን ዚተገሚምኩበት አጋጣሚ ነበር፡፡ ዹአማርኛ ቋንቋ ዚአገሪቱ ወይም ዚፌዎራሉ መንግሥት ዚሥራ ቋንቋ ነው ተብሎ በሕገ መንግሥቱ በግልጜ በተቀመጠበት ዚኊሮሞ ብሔር ተወላጅ ዚኟኑት ተማሪዎቜ አማርኛ ቋንቋን ሜሜታ቞ው ለጊዜውም ቢሆን ግራ አጋባኝ፡፡ ዹሆኖ ሆኖ ግን ተማሪዎቹ በወደዱት መንገድ አቀቱታ቞ውን ካቀሚቡ በኋላ ሰልፉ በሰላማዊ መንገድ ተጠናቆ ተበተነ፡፡

ይህ በወቅቱ ዚታዘብኩት ነገር ዛሬ ደግሞ ዹዓሊ ቢራን ዚጥበብ ሥራዎቹን ኹአፋን ኊሮሞ ውጭ እንዎት ሲባል ጥናት ይደሚግበታል ዹሚሉ ሰዎቜን አካሄድ ጋር ተዳምሮ እጅጉን ግራ አጋባኝ፡፡ ለመሆኑ አማርኛ ዚአገሪቱ ወይም ፌዎራል መንግሥቱ ዚሥራ ቋንቋ አይደለም እንዎ ስል ለመጠዹቅ ተገደድኩ፡፡ ዚኊሮሚያ ተወላጅ ዚሆኑት ተማሪዎቜ ነገሹ ሥራ቞ው በወሬ እሰማው ዚነበርኩትን ‹‹ዚአማርኛ ቋንቋ ዚአቢሲኒውያን ዹቅኝ ገዢዎቜ ቋንቋ ነው፡፡›› በሚል ዚፈሚጁበት ዚተሳሳተ ታሪካዊ ድምዳሜና ትርክት እውነታውን በተግባር በአደባባይ አይቌና ሰምቌ በማሚጋገጀ መገሹምና ግራ መጋባትን ሞላኝ፡፡ ቆዚት ብዬ ደግሞ ድንጋጀና አንዳንቜ ዚፍርሃት መንፈስ ውስጀን ሲያርደው ተሰማኝና ሜምቅቅ አልኩኝ፡፡

እናም በወቅቱ ለመሆኑ ወዎዚት እዚሔድን ነው፣ በዚህ ዚተሳሳተ ዚታሪክ ትንታኔና ሚዛናዊ ያልሆነ ትርክት ድምዳሜ ዕጣ ፈንታቜን ምን ይሆን፣ ይህ ዚእርስ በርስ ጥላቻና ንቅት ወዎዚትኛው ጎዳና ያደርሰን ይሆን በሚል ጥያቄ ውስጀ ተወጥሮ ነበር፡፡ እንደው ዚሆነስ ሆነና ዚኊሮሞ ብሔር ተወላጅ ዹሆኑ አንዳንድ ምሁራንና ዚኊሮሞ ሕዝብ ነጻ አውጪ ታጋዮቜ ነን ባዮቜና ኊሮሚያ በአቢሲኒያ በቅኝ ግዛት ሥር ዹኖሹ ነው ዹሚለውን አሳብ አቀንቃኞቜ እንደሚሉት፣ አቢሲኒያ በቅኝ ገዝታ቞ው ቢሆንስ ኚእንግሊዝኛ ቋንቋ ይልቅ ዚትኛው ቋንቋ ነው ዚሚቀርባ቞ው፣ ዚሚቀላ቞ውስ አልኩኝ ለራሎ፡፡
እነዚህ ዚኊሮሚያ ተወላጅ ተማሪዎቜ አማርኛን ቋንቋን ላለመናገር ዚሔዱበት ዚዙሪያ ጥምጥም መንገድ ፍርሃትን አጫሚብኝ፡፡ አቢሲኒያ በቅኝ ገዝታናለቜ በሚል ሰበብም ዹቅኝ ገዢዎቻቜን ወይም ዚነፍጠኞቜ/ዚአማሮቜ ቋንቋ ኚልባቜንም ኚአንደበታቜንም ፈጜሞ ይራቅ፣ ውጉዝ ይሁን ያሉበት ጥላቻ ዹወለደው አካኌዳ቞ው በውስጀ ሌላ ልጋፈጠው ዚሚገባ ዚታሪክ ጥያቄንና ሙግትን ፈጠሚብኝ፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ቆይታቜን ዚአፍሪካን ኮሎኒያልና ዚነጻነት ትግል ታሪክ ያስተማሩን እጅጉን ዚምናኚብራ቞ውና ዚምንወዳ቞ው፣ ምስጉንና ምሁራዊ ጚዋነትን በእጅጉ ዚተላበሱ ዚኊሮሞ ብሔር ተወላጅ ዚኟኑ ዚታሪክ ፕሮፌሰር ና቞ው፡፡ ዚአፍሪካ ዹቅኝ ግዛት ታሪክ ጥናታቜን አውሮፓውያን አፍሪካውያን ሕዝቊቜ ኚታሪካ቞ው ተነቅለው፣ ቋንቋቾው ተሚግጊ፣ ቅርሳ቞ውና ማንነታ቞ው ተዋርዶ፣ ዚእንሰሳ ያህል እንኳን ክብር ተነፍጓ቞ው፣ ወደ አውሮፓ ተጓጉዘው በዛ በሚገኙ ታላላቅ ቀተ መዘክሮቜ/ሙዚዹም ውስጥ ፍጹም ኢሰብአዊ በሆነ መልኩ እንደ ዱር አራዊት በብሚት አጥር ተኹልለው ለትዕይንት እንዲቀርቡ ዚተደሚጉበትን አስኚፊ፣ አሳፋሪ ዚባርነትና ዹቅኝ ግዛት ዘመናትን እንዳሳለፉ ነበር ዚተማርነው፡፡

በአገራቜንም በኢትዮጵያ ለአምስት ዓመታት ዚቆዩት ኢጣሊያውያኑ ቅኝ ገዢዎቜ ተመሳሳይ በሆነ መንገድ ነጭና ጥቁር በሚል ዚዘሚኝነት መርዝ ስብኚታ቞ውና ዹነጭ ዚበላይነት ባሰፈነው በኹፋፍለህ ግዛው ስልታ቞ው ለጥቂት ዓመታትም ቢሆን ሕዝባቜንን ለመኚራ እንደዳሚጉት ነው ታሪክ ዚሚነግሚን፡፡ ኢትዮጵያውያን ኚዐራተኛ ክፍል በላይ እንዳይማሩ፣ ኢጣሊያውያኑ በሚዝናኑበት፣ በሚኖሩበትና በሚንቀሳቀሱበት በማንኛውም ቊታ ለጉልበት ሥራ ብቻ ካልሆነ በቀር ሐበሻ ዝር እንዳይል በሚደነግገው ሕጋቾው ሕዝባቜን ዹቅኝ አገዛዝን አስኚፊ ገጜታውን በመጠኑም ቢሆን ለመሚዳት ቜሎ ነበር፡፡
እንግዲህ በአጭሩም ቢሆን ዹቅኝ አገዛዝ ገጜታውና መልኩ ይህ ነበር፡፡ ይህን ዚታሪክ እውነታ ይዘን ዚኊሮሞ ተወላጅ ወንድሞቻቜንን አቢሲኒያ በቅኝ፣ በኃይልና በነፍጥ ገዝታናለቜ ትርክትን ወይም ታሪካዊ ሙግትን ስንገመግም አንዳንድ ዚተሳሰቱ ነገሮቜ እንዳሉ ይታዩናል፡፡ ለመሆኑ ቅኝ መገዛት ማለት ምን ማለት ነው? በእርግጥስ በአገራቜን ታሪክ ነገሥታቱና ገዢዎቜ በገብር አልገብርም፣ ዚግዛት ማስፋፋትና ዚኢኮኖሚ ዚበላይነትን ለማስጠበቅ ዹተደሹጉ ዘመቻዎቜና ወሚራዎቜ ዹቅኝ አገዛዝ ባሕርያትና ገጜታዎቜ ነበሩት ወይ ብለን በእርጋታ መጠዹቅ ያለብንም ይመስለኛል፡፡

መቌም በአቢሲኒያ/በኢትዮጵያ ታሪክ ኊሮሞ በመሆኑ በሌሎቜ አፍሪካውያን ወንድሞቻቜን እንደሆነው አስኚፊ ዹሆነ ዹዘር መድሎ ዚደሚሰበት፣ እስኚ ዐራተኛ ክፍል ብቻ እንዲማር ዚተገደደ፣ አቢሲኒያውያን በሚሔዱበት ጋሪ፣ አውቶቡስ አሊያም ባቡር እንዳይሔድ ዚተኚለኚለ፣ አቢሲኒያውያን በሚገቡበት ሆቮል እንዳይገባ፣ በሚማሩበት ትምህርት ቀት እንዳይማር፣ በሚዝናኑበት መዝናኛ ቊታዎቜ ፈጜሞ እንዳይገኝ ዹተደሹገ ዚኊሮሞ ተወላጅ እንዳለ አንድም ዚታሪክ ሐቅ ማቅሚብ እንደማይቜሉ ራሳ቞ው አቢሲኒያ ቅኝ ገዝታናለቜ አቀንቃኝ ዹሆኑ ዚኊሮሞ ምሁራን ሳይቀሩ ልባ቞ው በሚገባ ያውቀዋል፡፡
ይህን ስል ግን በተለያዩ ዘመናት በኊሮሞም ይሁን በሌሎቜ በአገራቜን በሚገኙ ብሔር ብሔሚሰቊቜና ሕዝቊቜ ላይ ጭቆና፣ ዚመብት ሚገጣ አልደሚሰም፣ በቋንቋቾው እንዲያፍሩ፣ ታሪካ቞ው እንዲደበዝዝ፣ ባህላ቞ውና ቅርሳ቞ው እንዲናቅ፣ ኚማንነታ቞ው እንዲነቀሉ ወይም እንዲሰደዱ አልተደሹገም ማለት ግን አይደለም፡፡ ይህ ግን ዛሬ አንዳንዶቜ እንደሚሉት ዓይነት አንድ ሕዝብ ዹሌላውን ሕዝብ ታሪክ፣ ቋንቋ፣ ቅርስንና ባህልን ሆን ብሎ ለመጥፋት ዹተደሹገና አንዳንዶቜን ደፍሹው እንደሚሉት ዹዘር ማጥፋት ዘመቻ ዓይነት መልክ አልነበሚውም፡፡ አሊያም ደግሞ ዛሬ ዛሬ በድፍሚት እንደሚባለውም ዹቅኝ ግዛትና ዚአፓርታይድ ዓይነት መልክ ወይም ገጜታ በጭራሜ አልነበሚውም፡፡

እንዲህ ዓይነቶቹ እውነተኛ መሠሚት ዹሌላቾው ዚታሪክ ትንታኔዎቜና አተያዚቶቜ በኢትዮጵያ ሕዝቊቜ መኚካል ልዩነትንና ጥላቻን በማራገብ፣ ተዋዶና ተፈቅሮ ዹኖሹውን ሕዝብ በጥርጣሬና በጥላቻ ዓይን እንዲተያይ እያደሚጉ ያሉ አጋጣሚዎቜን በተለያዩ ጊዜያት እያዚን ነው፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት በአዳማ ኹተማ በዓሊ ቢራ ዹሙዚቃ ሥራዎቜ ላይ ጥናታዊ ጜሑፋ቞ውን ለማቅሚብ በተገኙ ምሁራን ላይ ኚኊሮምኛ ቋንቋ ውጭ ያሉ ጥናታዊ ጜሑፎቜን ዹአንቀበልም ውሳኔም ኹላይ ካነሳሁት ዚአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ገጠመኜና ኹዚሁ ኚአዳማው ክስተት ጋር ተያይዞ አንድ ዹሚነግሹን ሐቅ አለ፡፡
ይኾውም በአገራቜን በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ቋንቋዎቻቜን ‹‹እነርሱና እኛ›› በሚል ዚጥላቻንና ዚዘሚኝነትን ግምብ ዚገነባንባ቞ው፣ ዚእርስ በርስ ልዩነቶቻቜን እያሰፉ ያሉ ዚልዩነትና ዚጥላቻ መስመር ያሰመርንባ቞ው፣ ጜኑ ዹሆኑ ዚልዩነትን ግምብ ዚገነባንባ቞ው፣ ዚዘሚኝነትና ዚጥላቻን ቜካል ዚ቞ኚልንባ቞ው መሚገምቶቻቜን እዚሆኑ እንደመጡ እንዳለን በተግባር ያሚጋገጠልን ያለ እውነታ ነው፡፡

ለመሆኑ ዓሊ ቢራ ኚኊሮምኛ ውጭ በአማርኛ፣ በአደሪኛ፣ በእንግሊዝኛ፣ በዐሚቢኛ ቋንቋዎቜ አልዘፈነም እንዎ?! ዹዓሊ ቢራ ዚጥበብ ሥራዎቜ ዚኊሮሞ ሕዝብ ብቻ ሀብት ብቻ ናቾው ያለውስ ማን ነው?! ሙዚቃ ዹቋንቋና ዹዘር ድንበር ዚሌላት ሰው ልጆቜ ሁሉ ሀብትና መግባቢያ ሹቂቅ ቋንቋ እንደሆነቜ አይደለም እንዎ ዓለም ሁሉ በአንድ ድምፅ ዚተስማማው?! እናስ ዹዚህን ታላቅ ዚጥበብ ሰው ሥራዎቜ ኚኊሮምኛ ቋንቋ ውጭ ሊታዩ፣ ሊጠኑ፣ ሊገመገሙ አይገባም ማለትን ምን አመጣው?!

በመጚሚሻም ተዋዳጁን አርቲስት ዓሊን ቢራን ዘመን ለማይሜራ቞ው ድንቅ ለሆኑ ዚጥበብ ሥራዎቜህ ፶ኛ ዓመት እንኳን በሰላምና በጀና አደሹሰህ በማለት ልሰናበት፡፡
ሰላም!

nikodimoswise.7@gmail.com

↧
↧

ወይ ቀን ድኩማኑፊአምላክ ፍርፋሪ ለቃሚ ኹመሆን ያውጣን!

↧

ውዳሎ ዘኢሳያስ (ፕሚዘዳንት) በዳዊት ምትኩ

↧

ኢትዮጵያና ዐባይ –ግብፅና እስልምና!! አንተነህ ሜፈራው (ኢ/ር

↧
Viewing all 1809 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>