Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all 1809 articles
Browse latest View live
↧

ወጣቱ እና የነጻነት ትግል መስዕዋትነት (ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ)

$
0
0

የአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ህልውና የሚወሰነው ወጣቶች ባላቸው ሚና ላይ ሲሆን በብዙ ሀገራት እንዳየነው እና እንደተመለከትነው ወጣቶች ስለ ነፃነታቸው ፊት ለፊት መንግስታትን በመጋፈጥ ለመብታቸው ታግለዋል መስዋህትነትም በመክፈል የፈለጉትን አለማና ግብ አሳክተዋል::ለዚህም የሰሜን አፍሪካ አገሮችንና የመካከለኛው ምሥራቅን የለውጥ አብዮት ያቀጣጠሉትን ወጣቶች ዞር ብሎ መመልከት ያሻል:: የአንባ ገነኖች የስልጣን አገዛዝ አልዋጥላቸው ያላቸው እነዚህ የሰሜን አፍሪካ አገሮች እንደነ ግብጽ ፣ ቱኒዚያ እና ሊቢያ ያሉ ሀገሮች የሚኖሩ ወጣቶች በጊዜው ለናፈቁት እና ለተመኙለት ነጻነት ብዙ መስዋትነትን በመክፈል ዓላማቸውን አሳክተዋል:: በወቅቱ የነበረው የዓረብ የፖለቲካ ትኩሳት መነቃቃት ለብዙ ሀገራት ወጣቶች ትምህርት ሰጥቶ ያለፈ ታሪክ ነው::

ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ ስንመለስ የኢትዮጵያን የፖለቲካ አካሄድ ወደ ኋላ ዞር ብለን በምናይበት ጊዜ በኢትዮጵያ ሲደረግ በነበረው የፓለቲካ እንቅስቃሴ ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ትልቁን ሚና ይጫወት እንደነበር ከታሪክ መረዳት እንችላለን::እነሆ በኢትዮጵያ ረዥም ታሪክ ውስጥ እያንዳንዱ ትውልድ በተለያየ ጊዚና ወቅት የራሱን አሻራ ጥሎ አልፏል፡፡ በተለይ በንጉሡ ጊዜ የመሬት ላራሹንና ሌሎችንም የፖለቲካዊ ጥያቄዎች አንግቦ ሲንቀሳቀስ የነበረው የተማሪ ንቅናቄ ዛሬ ላይ በኢትዮጵያ የፖለቲካ የታሪክ ጉዞ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ሲሆን በዚያን ጊዜው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የነበሩትና ግንባር ቀደሞቹ ዋለልኝ መኮንንና ጥላሁን ግዛው በድንገት በወታደራዊው ኃይል ቁጥጥር ሥር ለወደቀው የተማሪው አብዮት ተጠቃሾች ሲሆኑ፣ በዘመኑ ለነበረው ሃይለኛ እና ወኔን የታጠቀ ትውልድም መታወቂያ ሆነው ማለፋቸውን የታሪክና የፖለቲካ ተንታኞች ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ የሚያወሱት የታሪክ ትውስታ ነው፡፡

ከቅርብ አመታት በፊትም ማለትም በ97 ምርጫ ሁሉም ሰው እንደሚያስታውሰው ይህ ወቅት ኢህአዴግ ወጣቶችን ሙሉ በሙሉ የገፋበት ወቅት ጊዜ እንደነበር እና መንግስት ስራ አጥተው የሚንከራተቱ ወጣቶችን “አደገኛ ቦዘኔ” የሚል ታፔላ በመስጠት የተለያዩ እስሮችና የማንገላታት እርምጃዎችን የወሰደበት እና የፈፀመበት ወቅት እንደነበር በብዙዎች ዘንድ ይታመናል፡፡ ይህ አይነቱ የመንግስት ግብታዊ እርምጃ ወጣቱን ወደ ተቃውሞ ጐራ እንዲያዘነብል አድርጐታል፡፡ ለዚህም ይመስላል በወቅቱ በምርጫ 97 ዋዜማ ኢህአዴግ ያቀረባቸውን የተለያዩ ማባበያዎች “አደገኛ ቦዘኔ ራሱ ወያኔ” የሚል ዜማ በማቀንቀን ለተቃዋሚዎች ድጋፍ የሰጠው፡፡ ኢህአዴግ በምርጫ 97 የደረሰበትን አስደንጋጭ ሽንፈት ተከትሎ በተፈጠረው ውዝግብ ቀዳሚ ተጠቂ የሆነውም ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል እንደነበር እናስታውሳለን፡:ለዚህም ነው ምርጫ 97 ተከትሎ በጊዜው በአቶ መለስ መንግስት ከሃያ ሺ በላይ ወጣቶች በእስር ቤቶችና በወታደራዊ ካምፖች ታሰረው የተሰቃዩት እና ከ200 በላይ የሆኑ ባብዛኛው ወጣት የሆኑ ንፁሀን ዜጐች በግፍ በአደባባይ የተገደሉት::ይህንን ለነጻነት ትግል የተደረገን የወጣቶች የህይወት መስዋትነት ሁል ጊዜ ስናስታውሰው የምንኖረው ነው::

እንደሚታወቀው በአሁን ወቅት በሀገራችን ኢትዮጵያ ከሚኖረው ህዝብ ከፍተኛውን ቁጥር ይዞ የሚገኘው ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል መሆኑ ይታወቃል:: ይህንንም ተከትሎ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከወጣቶች ብዙ የምትጠብቀው ነገር መኖሩ የማያጠያይቅ እውነታ ነው;; ምክንያቱም የኢትዮጵያ ሀገራችን የወደፊት ሁለንተናዊ ህልውናዋ ያለው እና የሚወሰነውም በእነዚሁ በዛሬዎቹ የኢትዮጵያ ወጣቶች ስለሆነ :: ከላይ እንደገለጽኩት በሀገራችን ኢትዮጵያ ከሚኖረው ሕዝብ አብዛኛውን ቁጥር የያዘው ወጣቱ እንደመሆኑ ይሄ ወጣት የህብረተሰብ ክፍል በስልጣን ላይ ባለው ስርዓት ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ፍላጐቱ ሊሞላለት አልቻለም:: ከዚያም ባለፈ ወጣቶች የነጻነትም ሆነ የመብት ጥያቄያቸውን ወይም ፍላጐታቸውን መግለጥ እና መናገር የሚችሉበት አግባብ የተዳፈነ በመሆኑ፣ በአለም ላይ ኢትዮጵያን የተገፉ ወጣቶች የበረከቱባት ሀገር እና ሀገራቸውን እየጣሉ ከሚሰደዱ ወጣቶች መካከል ቅድሚያውን እንድትይዝ አድርጓታል፡፡

የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት በስልጣን በቆየባቸው ባለፉት አመታቶች እየበደለ እና እያሰቃየ ያለው በመላ ሀገሪቱ ላይ የሚኖረውን ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ቢሆንም ይበልጥኑ በወያኔ ራዳር ውስጥ በመግባት በአገዛዙ ጭቆናና ግፍ እየደረሰበት ያለው በሀገራችን የሚኖረው ወጣቱ ዜጋ መሆኑ የታወቀ ነው:: ዛሬ የአማራው፣ የትግራዩ፣ የጋምቤላው፣ የኦሮሞው ፣የደቡቡ፣ የአፋሩ መላው የኢትዮጵያ ወጣት ዜጋ ለነጻነቱ በሚያደርገው ትግል በወያኔ ጨካኝ መንግስት እያተደበደበ፣ እየታሰረና እየተገደለ ለነጻነቱ መስዕዋትነትን በመክፈል ላይ ይገኛል :: ለዚህ ማሳያ የሚሆነን በሀገራቸው ፖለቲካ በመሳተፍ የተቃዋሚዎችን ጐራ የተቀላቀሉ እንደነ አንዱ አለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንን እና ኦልባና ሌሊሳ የመሳሰሉ ወጣት ፖለቲከኞች እንዲሁም እንደነ እስክንድር ነጋ፣ ውብሸት ታዬ እና ርዮት አለሙን የመሳሰሉ የወደፊቶ ኢትዮጵያ ተስፈኞች ብዙ የምትጠብቅባቸው ወጣት ጋዜጠኞች የወያኔ መንግስት እያራመደ ካለው የዘረኝነት ፖለቲካ የተለየ አቋም በመያዛቸው እና በተለያዩ ጋዜጦች ላይ ሀሳባቸውን በመግለፃቸው ብቻ በአሸባሪነት ተከሰው ወደ እስር ቤት በግፍ መወርወራቸው የኢትዮጵያ ወጣቶች በገዥው ስርዓት ምን ያህል መብታቸው እየተረገጠ እና ነጻነታቸው እየታፈነ በወያኔ የግፍ አለንጋ እየተገረፉ እንደሚኖሩ አመላካች ነው፡፡

የወያኔ መንግስት በወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል እየወሰዳቸው ያለው እነዚህ በግፍ የተሞሉ እርምጃዎች ወጣቶች እጃቸውን አጣጥፈው እንዲቀመጡ አላደረገም፡፡ ይባሱኑ ወጣቱ ሀይሉን እያጠናከረ እና ወደ ተቃዋሚ ጎራ በመግባት ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ለወያኔ ኢህአዲግ መንግስት የእግር እሳት እየሆነበት ይገኛል.: በዚህ አጋጣሚ ዛሬ በአዲስ አበበ በተካሄደው የሴቶች 5ሺ ሜትር ሩጫ ላይ ተሳታፊ የነበሩትን እና የተለያዩ ፖለቲካዊ ጥያቄዎችን በማንሳት ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍትህ፣ ዴሞክራሲ እንዲሁም ርዕዮትና ሌሎች የህሌና እስረኞች ይፈቱ እያሉ ሲጮኹና ድምጻቸውን ሲያሰሙ የዋሉትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ወጣት ሴቶች እህቶቻችንን ሳላደንቅ አላልፍም :: በጣም የሚያኮራ ተግባር በመፈጸም ምንም ነገር ሳይፈሩ ለወያኔ መንግስት የፍም እሳት በመሆን የተነሱለትን አላማ ‹‹ለነጻነት እንሩጥ›› የሚለውን መሪ ቃል በማሳካተቸው ጀግኖች ብያቸዋለው:: በነገራችን ላይ እነዚህ ወጣት ሴት እህቶቻችን ሮጫቸውን ጨርሰው ሲገቡ ለታገሉለት ነጻነት መስዋዕትነትን ከፍለዋል:: ሲከታተሏቸው በነበሩት የወያኔ ተላላኪዎቸ በሆኑት የፖሊስና የደህንነት ኃይሎች መያዛቸውና መታሰራቸው ተገልጾል::

የነጻነት፣ የእኩልነት፣ የፍትህ፣ እና የዴሞክራሲውን ጥያቄ የሰማያዊ ፓርቲ ፣ የአንድነት ፓርቲ ወይም የሌሎቹ የፖለቲካ ድርጅቶች ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ በተለይም የኢትዮጵያውያን ወጣቶች ጥያቄ መሆን ይገባዋል:: ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወጣት የኢትዮጵያን ህልውና ለማስጠበቅ በተለያየ የትግል መስክ በመሰማራት ኢትዮጵያችንን ከወያኔ ፋሽስታዊ ስርዓት ለመታደግ፣ የሀገራችንን ሕልውናና ክብር ለመመለስ በወያኔ መንግስት ላይ የፍም እሳት በመሆን መነሳት በእንቢ አልገዛም ባይነት መንፈስ በጽናት በመታገል ከወያኔ የዘረኝነት አገዛዝ ኢትዮጵያንና እራሱን ነጻ በማውጣት ለታሪክ የራሱን አሻራ ጥሎ ማለፍ ይጠበቅበታል::

የድል ቀን እንዲፋጠን ሁላችንም ወጣቶች እጅ ለእጅ ተያይዘን እንነሳ !

gezapower@gmail.com

↧

“የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት ዘመቻ” ግርማ ሞገስ

↧
↧

የጎሣ ፖለቲካ፣ የጎሣ ግጭቶች እና መዘዛቸው በኢትዮጵያ (በዘመነ ወያኔ) ከያሬድ ኃይለማርያም

$
0
0

መግቢያ

ይህ ጽሑፍ በኢትዮጵያ ላለፉት አስርት አመታት ጎሣና ኃይማኖትን መሰረት አድርገው በተደጋጋሚ ጊዜያት በተከሰቱት ግጭቶች ዙሪያ እና ግጭቶቹ ባስከተሉት ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት ላይ የሚያተኩር ነው። በተለይም ከ1983 ዓ.ም. ወዲህ ጎሣን መሰረት ያደረገውን የኢሕአዴግ ፌዴራላዊ የመንግስት አወቃቀር ተከትሎ በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች ውስጥ የተከሰቱ ዋና ዋና ግጭቶችን ይዳስሣል። ለግጭቶቹ መንስዔ ተደርገው የሚጠቀሱትን ጉዳዮች፣ በግጭቶቹ ሳቢያ በሰው ሕይወትና በሕዝብ ንብረት ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን፣ ግጭቶቹ እንዳይከሰቱ ለመከላከልም ሆነ ከተከሰቱ በኋላም ለማብረድ እና ዘላቂ በሆነ መልኩ ለመፍታት በመንግስት የተወሰዱ እርምጃዎች፣ የመንግስት የግጭቶች አፈታት ስልት፣ እና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮችን ይህ ጽሑፍ በመጠኑ ይዳስሳል።

የጽሑፉም ዋነኛ ዓላማ ጎሣን እና ኃይማኖትን መሠረት አድርገው የሚቀሰቀሱ ግጭቶች፤ ሰብአዊ መብቶች በገፍ በሚጣሱበት፣ ዴሞክራሲያዊ መብቶችና ነፃነቶች በማይከበሩበት እና የሕግ ልዕልና ባልተረጋገጠበት፤ እንዲሁም ነፃና ገለልተኛ የፍትሕ ተቋማት በሌሉበት እንደ ኢትዮጵያ ባለ አገር ውስጥ የሚኖራቸውን መጥፎ ገጽታ ማሳየት ነው። በተለይም የኢሕአዴግን የጎሣ ፖለቲካ አወቃቀር ተከትሎ በአገራችን ተደጋግመው በመከሰት ላይ ያሉት የጎሣ ግጭቶች በአገሪቱ የልማት እንቅስቃሴዎችና በሕዝቡ ሰላምና ደኅንነት ላይ የሚያስከትሉትን ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ቀውሶች ማመላከት ነው።

ወደዚህ ጽሑፍ ዋና ክፍል ከመግባቴ በፊት ለአንባቢዎቼ ከላይ ከገለጽኳቸው የጽሑፉ አላማዎች በተጭማሪ የተወሰኑ ነገሮችን ከግምት ውስጥ እንድታስገቡልኝ ለማሳሰብ እወዳለሁ። በመጀመሪያ ይህን ጽሑፍ ለማዘጋጀት ምክንትያት የሆነኝን ነገር ልግለጽ። ለስምንት አመታት በሰብአዊ መብት ጥሰቶች አጣሪነት በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) ውስጥ ተቀጥሬ ባገለገልኩበት ዘመን ድርጅቱ ተከታትሎና አጣርቶ መግለጫ ባወጣባቸው በርካታ የጎሣና የኃይማኖት ግጭቶች ውስጥ በምርመራ ሥራ ተሳትፌአለሁ:: የተወሰኑትን ግጭቶች ከሌሎች የሥራ ባልደረቦቼ ጋር በመሆን ሥፍራዎቹ ድረስ በመገኘት፤ የተቀሩትን ደግሞ ሌሎቹ የድርጅቱ የምርመራ ሠራተኞች፤ በአካል ተገኝተው ካሰባሰቡዋቸው መረጃዎች በመነሳት ያካፈሉኝን እውቀትና መረጃ በመንተራስ ነው። ለዚህም ጽሑፍ በዋነኛነት ኢሰመጉ በግጭቶቹ ዙሪያ የወጣቸውን መግለጫዎች በማጣቀሻነት እጠቀማለሁ። እንዲሁም ሌሎች አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ያወጡዋቸውን መግለጫዎችና ሰነዶች በአባሪነት እጠቅሳለሁ።

ይህ ጽሑፍ ሦስት ክፍሎች ሲኖሩት፤ በመጀመሪያው ክፍል በጎሰኝነት ስሜት ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ አደረጃጀት እና አስተሳሰብ፣ የጎሣ ግጭቶች እና ከሰብአዊ መብቶች አጠባበቅ ጋር ያላቸውን ግኝኙነት በተመለከተ አለም አቀፍ ድንጋጌዎችን እና ሌሎች ሰነደችን በማጣቀስ የሚዳሰስበት ክፍል ነው። የዚህ ክፍል አላማም በኢትዮጵያ ውስጥ እየታየ ያለውን የጎሠኝነት ስሜትና እያስከተለ ያለውን ግጭት ባህሪይ እና አካሄድ በቅጡ ለመረዳት ይረዳ ዘንድ መሰረታዊ በሆኑ ጠቅላላ አስተሳሰቦችና በሌላው የአለም ክፍልም ይህ አይነቱ ችግር ያለውን ገጽታ በመጠኑ የሚዳስስ ነው። ሁለተኛው ክፍል በኢትዮጵያ ውስጥ በተደጋጋሚ ስለተከሰቱትና እየተከሰቱ ባሉት ግጭቶች ላይ የሚያተኩር ነው። በዚህ ክፍልም ውስጥ ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰቱትን ግጭቶች ባህሪ፣ መንሰዔያቸውን፣ የደረሱትን ጉዳቶች፣ የመንግስትን ሚና እና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ያነጣጠረ ነው። የመጨረሻውና ሦስተኛው ክፍል የኢሕአዴግ መንግስት የሚከተለው ፖሊሲ፣ ያወጣቸው ሕጎች፣ ግጭቶችን ቀድሞ እንዳይከሰቱ የመከላከልና ሲከሰቱም በቀላሉ ተቆጠጥሮ ዘለቄታዊ መፍትሔ የመስጠቱ ሂደት ምን እንደሚመስል በመጠኑ የሚፈትሽ ነው።

I.ጎሠኝነት፣ የጎሣ ግጭቶች እና ሰብአዊ መብቶች

1.1. ጎሠኝነት

የሰው ልጆች ሁሉ በሰብአዊ ፍጡርነታቸው ክቡር መሆናቸውን፤ እንዲሁም እኩልና ሊነጣጠሉ የማይችሉ መብቶች እና ነፃነቶች ያሏቸው መሆኑን በአለም አቀፍ ድንጋጌዎች ላይ ሰፍሯል። የእነኚህ መብቶች እና ነፃነቶች በአግባቡ መረጋገጥና መከበር ለአለም ሰላም እና ለሕዝቦች ደኅንነት ዋነኛ ምሰሶም እንደሆነ ተገልጿል። የሰው ልጆች በሰብአዊ ፍጡርነታቸው ተገቢውን ክብር በማያገኙበት፣ ሰው በመሆናቸው ብቻ የተጎናጸፉዋቸው መብቶች እና ነፃነቶቻቸው ባልተረጋገጠበት እና በገፍ በሚጣሱበት ሥፍራዎች ሁሉ አይነታቸውና ደረጃቸው ይለያይ እንጂ ግጭቶች፤ ከፍ ሲልም ጦርነቶች ይከሰታሉ። በመላው አለም መብቶቻቸው የተረገጡባቸውና ሰብአዊ ክብርን የተነፈጉ ሰዎች ለነፃነቶቻቸው መረጋገጥ እና ከጨቋኞቻቸው ነፃ ለመውጣት የሚያደርጉትን ትግል ተከትሎ በርካታ ጦርነቶች እና ግጭቶች በአለም ተከስተዋል፤ አሁንም በተለያዩ ሥፍራዎች ይታያሉ። አለማችን እጅግ ዘግናኝ የሆኑ እና በሚሊዮኞች ለሚቆጠሩ የሰው ልጆች መጥፋት ምክንያት የሆኑ በዘር ጥላቻና በጎሠኝነት ስሜት የተቀጣጠሉ በርካታ ግጭቶችን እና ጦርነቶችን አስተናግዳለች።

የተባበሩት መንግስታት ባወጣቸው የተለያዩ ሰነዶች ላይ እንደተጠቆመው ድርጅቱ ከተቋቋመበት፣ እ.ኤ.አ. ከ1945 ወዲህ እንኳን ከተከሰቱት በርካታ ጦርነቶች ውስጥ ዐብይ በሚባሉት ከመቶ በላይ በሆኑ ትላልቅ ጦርነቶች ብቻ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሞተዋል። በአሥር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ደግሞ በጦርነቶቹ ሳቢያ ለስደት፣ ለርሃብ፣ ለድህነት እና ለበሽታ ተዳርገዋል። አብዛኛዎቹ ግጭቶች የዘር ልዩነትን መነሻ ባደረጉ ውጥረቶች፣ ያመረረ እና ጽንፍ የያዘ ብሔራዊ ስሜትና አክራሪ ጎሠኝነትን ተከትለው የተቀሰቀሱ ናቸው። አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት ከሆነ ከሁለተኛው የአለም ጦርነት ወዲህ በመላው አለም በፖለቲካ ብጥብጥ ሳቢያ ከሚሞቱ ሰዎች መካከል 80 በመቶ የሚጠጉት በጎሣ ግጭቶች ምክንያት ነው። በአለም ታሪክ ውስጥ ጎላ ብለው ከሚጠቀሱት ግጭቶች መካከል በአይሁዳዊያን ላይ የደረሰው ስቃይና የጅምላ ጭፍጨፋ፣ በጂፕሲዎችና በሶዶማዊያን ላይ የተካሄደው እልቂት፣ በሩሲያ እስታሊን በሰው ዘር ላይ የፈጸመው አሰቃቂ ወንጀል፣ በደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ ሥርዓት፤ እንዲሁም በዚምባብዌና በናሚቢያ ንኡሳን ነጮች (አውሮፓዊያን) የፈጸሙዋቸው እልቂት፣ በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በሱዳን፣ በሱማሌ እና በሌሎች የአፍሪካ አገሮች በተከሰቱ የእርስ በርስ ግጭቶች ሳቢያ ሚሊዮኖች ያለቁባቸውን ሁኔታዎች መዳሰስ እንችላለን።

በመጀመሪያ ደረጃ በጎሣ (ethnicity) እና በዘር (racial) ማንነት መካከል ያለውን ልዩነትና ዝምድና በመጠኑ ለመዳሰስ እወዳለሁ። የጎሠኝነት ስሜትና ማንነት የሚመነጨውና የሚጎለብተው እያንዳንዱ ሰው እራሱን ከአንድ በቋንቋ፣ በባሕል፣ በአካባቢያዊ ሁኔታ፣ ልማዶች እና ሌሎች ማኅበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከተሳሰረ የዘር ግንድ ጋር መነሻ በማድረግ የተደራጀ ወይም የተሰባሰበ የኅብረተሰብ ክፍል አባል አድርጎ ሲቆጥር እና በእነዚሁም መስፈርቶች እራሱን ከሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች የተለየሁ ነኝ ብሎ ማሰብ ሲጀምር ነው።[1] በዘር ላይ የተመሰረተው ማነነት በርካታ ጎሣዎችን በውስጡ ያቀፈ ሲሆን ተመሳሳይ የሆነ ተፈጥሮአዊ የሆነ አካላዊ መገለጫዎችን መሰረት በማድረግ የቡድንኑ አባላት እራሳቸውን ከሌሎች ለይተው የሚገልጹበት ወይም በሌሎች ዘንድ የተለዩ የተርገው የሚገለጹበት ሁኔታ ነው፡፡ ይህ አይነቱ የቡድን ዘር መገለጫ በሥነ-ተፈጥሮ ሳይንስ የተደገፈ ሳይሆን ለቡድኑ መገለጫ በሚሰጠው ሰው አስተሳሰብና ምርጫ ላይ የተመሰረተ ነው።[2] በሁለቱ መካከል ያለው ትልቁ ልዩነት የጎሣ ማንነት በእያንዳንዱ የጎሣው አባል መርጫና ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ነው። አንድ ሰው የአንድን ጎሣ ባህል፣ ቋንቋ፣ ልማዶች እና ሌሎች መገለጫዎችን ወዶና ፈቅዶ ሲያደርጋቸውና እራሱ የዛ ጎሣ አባል አድርጎ ሲቆጥር ነው የማንነቱ መገለጫ የሚሆነው። የዘር ማንነት መገለጫ ግን በእያንዳንዱ ሰው ፍላጎትና ምርጫ ሳይሆን በሌሎች አካላት ውሳኔ የሚጫን ነው። ለጥቁሮች መገለጫ የተደረገውን negro የሚለውን አገላለጽ የወሰንድ እንደሆነ በነጭ አክራሪዎች በመላው አለም ጥቁር የቆዳ ቀለም ላላቸው የሰው ልጆች ሁሉ የሰጡት መጠሪያ ነው።

የጎሣ ማንነት ቋንቋን፣ ባህልን፣ ኃይማኖታዊ ሥርዓቶችን ለማስተዋወቅ፣ ለማበልጸግ እና ይዞ በማቆየትም ከትውልድ ትውልድ እንዲተላለፉ ለማድረግ በመነጨ ፍላጎት ላይ ብቻ ሲወሰን እና ከዚህ አልፎ ለፖለቲካ ፍጆታ ሲውል የሚኖረው ውጤት እና ገጽታ ፍጹም የተለያየ ነው። በመጀመሪያው የአስተሳሰብ መስመር ላይ የተመሰረተው የጎሣ ማንነት ልዩነቶችን አጉልቶ በማውጣት ለመናቆሪያ ሳይሆን እንደ ጥለት ክር የተጠላለፉት የእያንዳንዱ የኅብረተሰብ ክፍል ባህሎች፣ ቋንቋዎች፣ ኃይማኖታዊ እና ታሪካዊ ትውፊቶች ለጠቅላላው ማኅበረሰብ የጥንካሬ እና ኅብረ ውበት ምንጮች ተደርገው ነው የሚቆጠሩት። በዚህ አይነቱ ማኅበረሰብ ውስጥ የአንዱ ክፍል ቋንቋ፣ ባህልና ሌሎች ማኅብራዊ እሴቶች ሁሉ የሌሎቹ የኅብረተሰብ ክፍሎች ሃብትና ጌጦች ናቸው። አንዱ ያለሌሎቹ፤ ሌሎቹም ያለአንዱ ውበትና ጥንካሬ የላቸውም። ይህ አይነቱ ማኅበረሰብ በውስጡ ግጭቶችና ቅራኔዎች ባያጡትም አንዱ የሌላውን ዘር ከምድረ ገጽ ለማጥፋት በመነሳት ወደሚፈጸሙ ዘግናኝ እልቂቶች አያመሩም። ልክ በአንድ ቤተሰብ አባላት መካከል ግጭቶች ተነስተው በእርቅ እንደሚፈቱት ሁሉ በዚህ አይነቱ ማኅበረሰብ ውስጥም የሚነሱ ቅራኔዎችና አለመግባባቶች በየአገሩ ወግና ባህል ወይም በሕግ አግባብ አፋጣኝ መፍትሄ ሲለሚያገኙ ወደ እልቂት አያመሩም።

ሁለተኛውና ለፖለቲካ ግብ ማሳለጫ መንገድ ተደርጎ የሚወሰደው ጎሣን መሰረት ያደረገው የማንነት መገለጫ እና የኅብረተሰብ ክፍሎች መቧደን ከላይ ከተጠቀሰው የጎሣ ምልከታ ጋር ከሚጋራው አንድ ነገር ውጪ እጅግ የተለየ መልክ እና ይዘት ያለው ነው። ሁለቱም የጎሣ ምልከታዎች መነሻቸው አንድ ነው። ይህውም በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ በቋንቋ ወይም በባህል ወይም በኃይማኖት ወይም በሌሎች የማንነት መገለጫ ተደረገው በልማድ በሚወሰዱ ልዩነቶች ዙሪያ የተሰባሰቡ የኅበረተሰብ ክፍሎች መኖራቸው ነው። አንድ ወጥ የሆነ ቋንቋ፣ ባህል፣ ኃይማኖትና ታሪክ ባለው ማኀበረሰብ መካከል የተለያየ የኅብረተሰብ ደረጃዎችና ክፍሎች ቢኖሩም የጎሣና የጎሠኝነት ጎዳዮች ጭርሱኑ የሚታሰብ ነገሮች አይደሉም። የጎሣ ልዩነቶች ከኅብር ውበት መገለጫነትና ባህልን፣ ቋንቋን፣ ታሪክን እና ኃይማኖታዊ እሴቶችን ለማስተዋወቅና ለማዳበር ከሚኖረው ፋይዳ ባለፈ የፖለቲካ አስተሳሰቦች ማቀንቀኛ እና የፖለቲከኞች የመታገያ መሳሪያ መሆን ሲጀምር ውበቱ ይደበዝዛል ወይም ጭርሱኑ ይጠፋል። ጎሠኝነት ፖለቲካዊ ገጽታው እጅግ ተጋኖና ጎሎቶ በወጣ ቁጥር ያንን ማኅብረተሰብ አቆራኝተው እና አፋቅረው ያቆዩትን ሠንሰለቶች የመበጣጠስ ኃይል አለው። በጎሣ በተሰበጣጠረው የኅብረተሰብ ክፍል ውስጥ የሚኖረው አወንታዊ ሚና ይቀርና የልዩነት ግንብ ይሆናል። የእያንዳንዱ ጎሣ ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክና ኃይማኖታዊ እሴቶች የራሱ ብቻ ይሆናሉ። አንዱ የሌላው ውበትና የጥንካሬ ምንጭ መሆኑ ይቀርና በፉክክርና በመበላለጥ ስሜት ላይ የተመሰረተ ልዩነት ይፈጥራል። ከዚያም አልፎ በጠላትነት የመተያየት ስሜት ይመነጫል። እያንዳንዱ ጎሣም በልዩነት ግንብ ውስጥ የራሱን ደሴት ይመሰርታል። በእንዲህ አይነቱ ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረው ጎሣን መሰረት ያደረገ ቅራኔ ሁለት መልክ ይይዛል።

የመጀመሪያው በእያንዳንዱ የጎሣ ክፍል ውስጥ ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ፉክክርና ግብግብ ጥላቻን ይወልድና ወደ አካላዊ ግጭትም ያመራል። ጎሠኝነት ከዘረኝነት ጋር የተዛመደ እንደመሆኑም የጎሠኝነት ስሜት የሚመነጨውና የሚጎለብተው እያንዳንዱ ሰው የኔ የሚለው የዘር ሀረግ ወይም ጎሣው ከሌሎች ሰዎች ዘር ወይም ጎሣ የተሻለ ወይም የበለጠ ነው ብሎ ማሰብ ሲጀምር ነው። ይህ አይነቱ አስተሳሰብም ሰዎች ሁሉ በፈጣሪያቸው ፊት እኩል እንደሆኑ የሚገልጸውን ኃይማኖታዊ አስተሳሰብ የሚቃረንና ይህንኑ መሰረት በማድረግም “ሰዎች ሁሉ እኩል ክብርና መብቶች ይዘው ነፃ ሆነው ተፈጥረዋል። የማሰብና የማመዛዘን ችሎታ በተፈጥሮ ስለታደሉ እርስ በርሳቸው በወንድማማችነት መንፈስ ሊተያዩ ይገባል።” በማለት የሚደነግገውን የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳን አንቀጽ 1 የሚጥስ ነው።

ሁለተኛው ግጭት ደግሞ በእያንዳንዱ የጎሣ ቡድን ወስጥ የሚፈጠረው የግለኝነትና ጤናማ ያልሆነ የመበላለጥ ስሜት ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች አንድ አድርገው ይዘው ያቆዩትን ታሪካዊ እና ሌሎች አገራዊ መገለጫዎች ይንዳል፤ እንዲሁም የጋራ ጥቅምን ማስከበሪያ የሆነውን ሕገ-መንግስታዊ ሥርዓትን ያናጋል። አልፎ ተርፎም አገርን እስከማፍረስ የሚዘልቅ ችግርን ያስከትላል። በዚህ አይነቱ ችግር ምክንያት በርካታ ትላልቅ አገሮችች ፈርሰው በጎሠኞች ደሴቶች ተቀይረዋል። የጎሠኝነት ስሜት በጠነከረና አብጦ በወጣ ቁጥር አገራዊ ስሜት ይከስማል፣ የአብሮነት ታሪክ ይዘነጋል፣ ጠባብነትና ጎጠኝነት ይነግሳሉ። እዚህ ደረጃ ላይ የደረሰ ማኅበረሰብ በበቀልና በጥላቻ ስሜት ተወጥሮ ስለሚቆይ የእልቂት አፋፍ ላይ ነው የሚቆየው። ተያይዞ ለመጥፋትና ቁልቁል መቀመቅ ለመውረድ ትንሽ ነገር ይበቃዋል። በሩዋንዳና በሌሎች የአለማችን ክፍሎች አስከፊ በሆነ መልኩ የተፈጸሙት የዘር ማጥፋት ወንጀሎች ምንጫቸው ይሄው ነው።

በአለም አቀፍ ደረጃ የተደረጉ አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ጎሠኝነትን ወይም የጎሣ-ብሔረተኝነትን መነሻ ያደረጉ ግጭቶች ባህሪያቸው እና መገለጫቸው የተለያየ ነው። ጥቂቶቹን ለመዳሰስ ያህል፤ የፖለቲካ ሥልጣንን በማዕከላዊነት በያዘ የኅብረተሰብ ክፍል እና ከፖለቲካ ምህዳሩ ተገልሎ የዳር ተመልካች እንዲሆን በተደረገ የኅብረተሰብ ክፍል ማካከል ያለውን ቅራኔ መሰረት ያደረገው የጎሣ ግጭት አንዱና በዋነኝነት የሚጠቀሰው ነው። ሁለተኛው ደግሞ በብሄር ምንጫቸው ምክንያት ወይም በቆዳ ቀለማቸው ወይም በሚከተሉት እምነት ወይም በኃይማኖታቸው ወይም በሌሎች ምክንያቶች የተነሳ በእኩልነት የመኖር መብታቸውን እና መሰረታው መብቶቻቸውን በተነፈጉ እና ጥላቻን መሰረት ላደረገ መድልዎ እና ጥቃት የተጋለጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚያነሱትን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ የእኩልነት ጥያቄዎችን ተከትሎ የሚቀሰቀሰው የጎሣ ግጭት ነው። ሦስተኛው ደግሞ፤ በሚኖሩበት ማኅበረሰብ ውስጥ ተገቢውን የፖለቲካ እና ኢኮኖሚያዊ ድርሻ ተነፍገናል ወይም የሚገባንንን ያህል አላገኘንም የሚል ጥያቄን መነሻ በማድረግ ከሌላው ማኅበረሰብ ተገንጥዮ የራሴን አገር እና ግዛት እመሰርታለው የሚሉ ኃይሎች የሚያነሱትን ጥያቄ መነሻ አድርጎ ከሌላው የኅብረተሰብ ክፍል ጋር የሚደረገ ግጭት ነው። አራተኛው የጎሣ ግጭት ደግሞ በአንድ ግዛት ውስጥ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ የጎሣ ቡድኖች መካከል የኢኮኖሚና የፖለቲካውን የበላይነት ለመቆናጣጠርና የማዕከላዊውን መንግሥት ሥልጣን በበላይነት ለመቆጣጠር የሚደረጉ ፉክክሮችን ተከትሎ በሚፈጠር አለመግባባት የሚቀሰቀስ ግጭት ነው።

ከላይ የተጠቀሱት የጎሣ ግጭቶችና መንሰዔዎቻቸው በግልጽ እንዲሚያሳዩት ጎሠኝነትን መሠረት ያደረጉ የማንነት መገለጫዎች የፖለቲካ ግብ ማሳኪያ ሲሆኑ መድረሻቸው ጥላቻና ሌሎችን ‘የእኛ ጎሣ አካል አይደሉም’ የሚሉዋቸውን የኅብረተሰብ ክፍሎች ማግለልና ሲከፋም ዘራቸውን ከምድረ-ገጽ ለማጥፋት እስከ መሞከር ይዘልቃል። ይህ ችግር የተከሰተው እንደ ኢትዮጵያ ባለ እጅግ በተሰበጣጠረ ማኅበረሰብ ውስጥ ሲሆን የዘረኝነት መርዙ በብዙ መንገዶች ሊንጸባረቃ ይችላል። በልማት እንቅሳቅሴ፣ በትምህርት ዘርፍ፣ በኢኮኖሚና የንግድ ዘርፍ፣ በመሬት አጠቃቀም ፖሊሲ፣ በግብር አከፋፈል ሥርዓት፤ እንዲሁም በተለያዩ አስተዳደራዊ ዘርፎች ሁሉ የጎሠኝነቱ ስሜትና ውጤቱ በግልጽ ይስተዋላል። ለምሳሌ በፊሊጲንስ ቅጥ አጥቶ የነበረው ጎሠኝነት በአገሪቱ የኃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል አጠቃቀም ላይ ጭምር በግልጽ ይስተዋል ነበር። በማሌዢያ እና በታንዛኒያ ደግሞ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት አቅርቦት ላይ የጎሣ መድልዎ አፍጥጦ ይታይ ነበር። በሌሎች አገሮችም የተለያዩ መገለጫዎች ያላቸው ጎሠኝነትን መሰረት ያደረጉ ክፍፍሎችና መድልዎች ተስተውለዋል፤ አስከፊ ግጭቶችንም አስከትለዋል።

በጎሣ የሚደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች መነሻቸው ከሁለት ክስተቶች የሚመነጭ ነው። የመጀመሪያው ውስጣዊ ምክንያት ነው። ይኽውም በእያንዳንዱ የጎሣ ክፍል ውስጥ ካለው ማኅበረሰብ ከራሱ የሚመነጭ ነው። የአንድ ጎሣ አባላት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፓለቲካዊ ጥቅማቸውን በተሻለ ሁኔታ ለማስጠበቅ ሲሉ በፖለቲካ የሚደራጁበት ሁኔታ ነው። ሁለተኛው ደግሞ ውጫዊ ምክንያት ነው። ይኽውም የአንድ ጎሣ አባላት በተደጋጋሚ ከአንድ ወይም ከሌሎች ጎሣዎች ጥቃት ሲደርስባቸው፣ ከሌሎች ጎሣዎች በተለየ መልኩ መድሎና መገለል ሲደርስባቸው፣ ከኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅሞችና ተሳትፎዎች እንዲገለሉ ሲደረግ እና በሌሎች ተመሳሳይ ምክንያቶች አደጋ ሲጋረጥባቸው ይህን መሰሉን ጥቃት ለመከላከል በሚል አካባቢው በፈጠረባቸው አስገዳጅ ሁኔታ በመነሳት የጎሣቸውን አባላት ጥቅም እና ደኅንነት ለማስጠበቅ በማሰብ በፖለቲካ የሚደራጁበት ሁኔታ ነው። በመሆኑም ጎሣን መሰረት አድርገው የሚመሰረቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ የሚያገኙት እንወክለዋልን ከሚሉት የኅብረተሰብ ክፍል ብቻ ስለሆነ የሚታገሉትም ሆነ ሥልጣን ሲቆናጠጡ ቅድሚያ ተጠቃሚ የሚያደርጉት የደገፋቸውን እና የሚወክሉትን የጎሣ ክፍል ብቻ ነው። ጎሣን መሰረት ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከጠቅላላው ማኅበረሰብ ጥቅም አንፃር እጅግ ጠባብ የሆነ የቡድን ፍላጎትና አጀንዳን ነው የፖለቲካ ግብ አድርገው የሚነሱት። እነዚህ ኃይሎች የፖለቲካውን ሥልጣን በተቆናጠጡበት ሥፍራ ሁሉ ታዲያ የእኛ ከሚሉት ጎሣ ክፍል በተነጻጻሪ ባለው ቀሪው የኅብረተሰብ ክፍል መካከል ግልጽ የሆነ የጥቅምና የመብት መበላለጥን ይፈጥራሉ። ይህ ሁኔታም እያደር ቅራኔንና ጥላቻን ያራባል።

የጎሠኝነት ስሜት አብጦ በወጣበትና ድርጅታዊ ቅርጽ ይዞ በጎለበተበት አገር ሁሉ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችና አስተሳሰቦች የሚመዘኑትና የሚመነዘሩት በእያንዳንዱ ጎሣ መስፈርት ነው። የፖለቲካ ፓርቲዎችም የሚደራጁትና የሚታገሉት ጎሣዎችን መሰረት በማድረግ ነው። የጎሠኝነት ስሜት ገኖ በሚታይበት ሥፍራ ሁሉ ሰብአዊ መብቶችን ችላ ማለት፣ አሰቃቂ የሆኑ የመብት ጥሰቶችን በሌሎች ላይ መፈጸምና ሰዎችን በፍርሃትና በከፋ ችግር ውስጥ መጣል የተለመዱ ተግባራት ናቸው። ይህ አይነቱ ሁኔታ እጅግ በተከፋፈለ ማኅበረሰብ ውስጥ ሲከሰትና ፓርቲዎችም የጎሣን መስመር ተከትለው መደራጀት ሲጀምሩ ጠንካራ የፖለቲካ ተፎካካሪ ኃይሎች መሆናቸው ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል። ምክንያቱም ድጋፍ የሚያገኙት ከሚወክሉት ጎሣ አባላት ብቻ ስለሆነ። ከዚህም ባሻገር ለጠቅላላው ሕዝብ ጥቅም የሚቆሙ ብሔራዊ የፖለቲካ ኃይሎች እንዲዳከከሙ እና እንዲጠፉም ምክንያት ይሆናል። ለዚህም ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ፣ ኢስያ እና ካረቢያን አገራት ዛሬ የሚገኙበትን ሁኔታ ማጤን በቂ ነው። በዚህ መጠነኛ የዳሰሳ ጽሁፍ ውስጥ የጎሠኝነተን አስተሳሰብ፣ መሰረታዊ እና ታሪካው ምንጭ እንዲሁም በጎሣ ግጭቶች ዙሪያ የሚነሱ የተለያዩ ሃሳቦችን ሁሉ ለማካተትም ሆነ በመጠኑም እንኳን ለመቃኘት አይቻልም። እራሱን የቻለ ሰፊ ጥናትና ምርምር የሚጠይቅ ስለሆነ ይህ ዳሰሳ ለዚህ ጽሁፍ ቀጣይ ክፍሎች እንደ መንደርደሪያ ተደርጎ እንዲወሰድ ለማሳሰብ እወዳለሁ።

በቀጣዩ ክፍል እስከምንገናኝ በቸር እንሰንብት።

ያሬድ ኃይለማርያም

↧

የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ –የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄን በተመለከተ የአዉሮፓ ሕብረት አንድነትን አነጋገረ

$
0
0

በኢትዮጵያ የአዉሮፓ ሕብረት ልኡካን ቡድን መሪ አምባሳደር ቻንታል ሔበሬሽ፣ በአዉሮፓ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ እና የሕንድ ዉቂያኖስ አካባቢ ዴስክ ኦፌሴር ቪክቶሪያ ጋርሲያ ጉሌን እንዲሁም ቶማስ ሁይገባርቴስ የተሰኙ ፣ የአዉሮፓ ሕብረት ሃላፊ ፣ በነርሱ አነሳሽነት፣ ከአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ጋር ሰፊ ዉይይት አደረጉ።

ከአንድ ሳምንት በፊት በኢትዮጵያ ስላለው የዲሞክራሲ ግንባታ ዙሪያ ከጠ/ሚኒስተር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር እንደተነጋገሩ የገለጹት የአዉሮፓ ሕብረት ባለስልጣናት፣ የአንድነት ፓርቲ በጠራዉ የሚሊዮኖች ድምጽ ሁለተኛ ዙር ንቅናቄ እንዳሳሰባቸው በመገለጽ፣ አንድነት በሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ዙሪያ፣ ፓርቲው ፍቃደኛ ከሆነ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው፣ ጠይቀዋል።

የአንድነት ፓርቲ ወክለው ከአዉሮፓ ሕብረት ጋር የተነጋገሩት ሊቀመንበሩ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራዉና የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊው አቶ ሃብታሙ አያሌው በበኩላቸው ያሉትን ሁኔታዎች ለማስረዳት ሞክረዋል።

አንድነት አሁን የሚያደርገው የሚሊዮነሞች ንቅናቄ ከዚህ በፊት ከተደረገው የቀጠለ እንደሆነ ያስረዱት የአንድነት አመራር ፣ ፓርቲዉ አዲስ አበባ ጨምሮ በ17 ከተሞች ፣ በፍትህ እና በላንድ ሪፎርም ዙሪያ ፣ ከሕዝብ ጋር ዉይይቶችን እንዲሁም ሰላማዊ ስለፎች እንደሚያደርግ ገልጸዋል። አንድነት ከዚህ በፊት ባደረጋቸዉ በርካታ ሰልፎች አንዳች አይነት በሰውም ሆነ በንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ የገለጹት የአንድነት አመራር አባላት ፣ ወደፊት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች፣ ሰላማዊና ሕዝባዊ እንደሚሆኑ በማስረዳት ፣ አንድነት አገር አቀፍ መዋቅሩን እያሰፋ እንደሆነም ለማሳየት ሞክረዋል።

የአዉሮፓ ሕብረት ተወካዮች፣ አንድነት ይዞት የተነሳዉ የመሬት ጥያቄ ተገቢና ወቃታዊ፣ ለኢትዮጵያ ጥቅም የሚያመጣ እንደሆነ የገለጹ ሲሆን፣ በመጪው የ2010 ምርጫ ዙሪያ አንድነት ያለውን አቋም እንዲያስረዳቸው ጠይቀዋል። «ለምርጫ አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረገን ነው። በሁሉም ክልሎች ለፌዴራልም ሆነ ለክልል ተወዳዳሪዎች ከወዲሁ እያዘጋጀን ነው» ሲሉ የመለሱት የአንድነት አመራሮች ፣ በምርጫ መሳተፉና አለመሳተፉ ግን ወደፊት የሚወሰን እንደሆነ ገልጸዋል። «ኢሕአዴግ ሁሉንም ነገር ከዘጋዉና የፖለቲካ ምህዳሩን ካጠበበው. የምርጫ ቦርድ የመሳሰሉ ተቋማት ገለልተኝነት ከሌላቸው፣ ምርጫ መሳተፉ ዋጋ እንደማይኖረዉ የገለጹት የአንድነት አመራራ፣ በምርጫዉ ጉዳይ፣ ኳሷ ኢሕአዴግ ሜዳ ላይ እንዳለች አስረድተዋል።

የፖለቲካ እስረኞችን ሁኔታ የጠየቁት የአዉሮፓ ሕብረት ተወካዮች «እስረኞችን ለመጠየቅ ይፈቅድላቹሃል ወይ ? » ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄ፣ አንዱዋለም አራጌን አንድ ጊዜ ለመጠየቅ እንደቻሉ ነገር ግን ርዮት አለሙን፣ እስክንደር ነጋ እና ናትናኤል ሞኮንን እንዳይጠይቁ መከልከላቸውን የአንድነት አመራሮች አስረድተዋል።

በፊታችን ኤፕሪል በብራሰልስ፣ በአዉሮፓ ሕብረት እና በአፍሪካ ሕብረት መካከል ስብስባ እንደሚደረግ የገለጹት የአዉሮፓ ሕብረት ተወካዮች፣ የአንድነት ፓርቲ በስብሰባው እንዲገኝ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ በገዠዉ ፓርቲ ዘንድ የፊታችን ምርጫ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ እንደሚሆን ቃል እንደተገባላቸው ተናግረዋል።

የአንድነት አመራሮች ግን ገዢዉ ፓርቲ የሚናገራቸውና ተግባራቶቹ አንድ እንዳልሆኑ፣ ይሄ ነው የሚባል፣ የዲሞክራሲ ግንባታዉን የሚያግዝ የተጨበጠ እርማጃ እንዳልወሰደ መረጃ ላይ በመደገፍ ገለጻ አድርገዉላቸዋል። «ጋዜጦቻችንን ማተም አልቻልም። ደጋፊዎቻችን ይታሰራሉ። ከሥራ ይባረራሉ። ሰልፍና ስብሰባዎች ስንጠራ ብዙ ጊዜ እንግልት ይደርስብናል» ሲሉም በአገዛዙ እየተፈጸሙ ያሉ ከፍተኛ የሰባአዊ መብት ጥሰቶችን ዘርዝረዋል።

በዉጭ አገር ስላሉ ኢትዮጵያዉያንም የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል። «በዉጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ወደ 2 ሚሊዮን ይጠጋል። በርካታ ደጋፊዎች አሉን። በተለያዩ ቦታዎች በተለይም በአሜሪካ የድጋፍ ድርጅቶች አሉን» ያሉት የአመራሩ አባላቱ፣ የድጋፍ ድርጅት ዉስጥ የሌሉ፡ ነገር ግን የምናደርጋቸውን ከፓርቲ በላይ የሆነውን የሚሊየኖች ንቅናቄን የሚደገፉ በርካታ ኢትዮጵያዊ የሲቪክ እና የፖለቲካ ድርጅቶች እንዳሉም አስረድተዋል። የትግሉ አካል ከሆኑና በዉጭ ካሉ ኢትዮጵያዉያን ጋር ለመነጋገር፣ አንድነት የልኩካን ቡድኖች በቅርቡ ወደ ዉጭ እንደሚያስማራም ለአዉሮፓ ሕብረት ተወካዮች ገልጸዋል።

በአገሪቷ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት እንዲቻል የተሻለዉና የሰለጠነው አማራጭ፣ መነጋገር እንደሆነ ያስረዱት የአንድነት አመራር አባላት፣ አንድነት ከኢሕአዴግ ጋር ሆነ ሽብርተኞች ተብለው ካልተሰየሙ ደርጅቶች ጋር ሁሉ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለመነጋገር ፍቃደኛ እንደሆነ፣ ለዚያም ጥሪ እንዳቀረቡ ገልጸው፣ አገዛዙ ግን ቅድመ ሁኔታዎች እያስቀጠ በተደጋጋሚ ለመነጋገር ፍቃድኛ እንዳለሆነ ተናግረዋል።

↧

አንድነት ፓርቲ 2ኛውን ዙር የሚሊዮኖችን እንቅስቃሴ በተለያዩ ከተሞች ሊጀምር ነው

$
0
0

ማጋቢት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ለሦስት ወራት በሚካሄደው ክፍል ሁለት “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ሪፎርም” በሚለው ዘመቻ፣ በዋነኛነት በተመረጡ 14 ከተሞች እና በሦስት ተጓዳኝ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍና ህዝባዊ ስብሰባ ይካሄዳል።

የመሬትን አጀንዳ የሁለተኛው ዙር የመታገያ አጀንዳ ለምን እንዳደረገ ፓርቲው ሲያብራራ፣ “በባለሃብት ስም ገበሬው ከይዞታው መፈናቀሉ፤ በከተሞች በልማት ስም ዜጎች እየተፈናቀሉ ለጎዳና ላይ ኑሮ መዳረጋቸው፤ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መበቶቻቸው እየተጣሱ ለማህበራዊ ቀውስ መዳረጋቸውው ዛሬም ተጠናክሮ መቀጠሉንና በተበጣጠሰ ትንንሽ የመሬት ይዞታ ላይ በኃይል የመፈናቀል ተራቸው እስከሚደርስ እየተጠባበቁ ያሉትም ቢሆኑ ዛሬም በዶማ እና በበሬ አፈር እየገፉ ከአቅማቸው በላይ በሆነ የማዳበሪያ እዳ ተቀፍድደው አንገታቸውን ደፍተው በሰቀቀን ለመኖር ተገድደዋል” ብሎአል።

“መሬትን ዋነኛ የሙስና ማዕከል ያደረገውን ሥርዓት በመቃወም የህዝብ የለውጥ ፍላጎት እንዲከበር አደባባዮች በለውጥ ፈላጊ ሰላማዊ ታጋይ ህዝብ እንዲሞሉ እንዲሞሉ ለማድረግ እንደሚንቀሳቀስ የሚገልጸው አንድነት፡ አምባገነናዊ ሥርዓቱ በሰላማዊ ትግል ተሸንፎ ዜጎች የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት እንዲሆኑ፤ ሃብት የማፍራት፤ የመያዝ እና የማስተላለፍ መብታቸው እንዲጠበቅ፤ በኮሚኒቲ /በማህበረሰብ/ በጋራ ከተያዘ፤ በመንግስት ይዞታነት ከተከለለ እና በተቋማት ይዞታነት ከታወቀ መሬት በቀር በዜጎች የተያዘ መሬት የግል ይዞታ ሆኖ እንዲከበር ለማድረግ እንደሚታገል አስታውቋል።

በህዝባዊ ንቅናቄው የአደበባይ ህዝባዊ ስብሰባ እና ሰላማዊ ሰልፍ የሚደረግባቸው ቦታዎች አዲስ አበባ፣ ደሴ፣ ሐዋሳ፣ አዳማ/ናዝሬት/፣ መቀሌ፣ ደብረታቦር፣ ደብረማርቆስ፣ ድሬዳዋ፣ ጂንካ፣ ቁጫ፣አሶሳ፣ ነቀምት፣ ለገጣፎ፣ ወልዲያ፣ ጋምቤላ፣ ምዕራብ አርማጭሆ/ አብርሃ ጅራ/፣ይሆናሉ ብሎአል።

አንድነትና መኢአድ ፓርቲዎች በቅርቡ በባህርዳር በብዙ ሺዎች የሚቀጠር ህዝብ ለተቃውሞ እንዲወጣ አድርገዋል። ፓርቲው በመጀመሪያ ዙር የሚሊዮኖች ድምጽ በተለያዩ ከተሞች የተሳካ የተቃውሞ ሰልፎችን ማድረጉ ይታወቃል።993754_546619252089680_666940779_n

↧
↧

የብርሃኑ ዳምጤ (አባመላ) ቅልቅል ክንፉ አሰፋ

$
0
0

ብርሃኑ ዳምጤ እንደገና ሲገለበጥ የአስር አመት ልጅ ሳለሁ ያጋጠመኝን አንድ ክስተት አስታወሰኝ። በሰፈራችን ውስጥ ልጆችን ሁሉ የሚጠሉ አንድ ሰውየ ነበሩ። አንድ ቀን በድንገት ተነሱና የሰፈሩን ሰው ሁሉ መሰናበት ጀመሩ። በእጃቸው 3 ሜትር የሚያህል ርዝመት ያለው ገመድ ይዘዋል። “የሰፈሩ ልጆች ስላስቸገሩኝ ራሴን ልስቅል ነው። ደህና ሁኑ…” እያሉ ሁሉንም ተሰናብተው ሲያበቁ ለመሰቀል መንገዳቸውን ጀመሩ። የእኝህ ሰው ውሳኔ ለመንደሩ ሰው ሁሉ ደንታ አልሰጠውም።

የሰፈር ልጆች ግን ተከተልናቸው። ብዙ ነበርን። ሰውየው ተራራ ሲወጡ አብረን ወጣን። ቁልቁል ሲወርዱም አብረን ወረድን። ጉዞው አሰልቺ ነበር። ግን ተስፋ ሳንቆርጥ ጉዱን ለማየት ስንል ተከተልናቸው። በመጨረሻ አንድ ዛፍ አገኙና የሚሰቀሉበትን ገመድ እዛፉ ላይ ማሰር ጀመሩ።

ሰው ሲሞት አይተን ስለማናውቅ ሁኔታውን እንደ ልብ አንጠልጣይ ፊልም ነበር በጉጉት የምንከታተለው። ሰውዬው በዚህ ሁኔታ ለመሞት መወሰናቸው ብዙም አላስደነገጠንም። ይልቁንም ከኛ እየቀሙ በግቢያቸው ያጠራቅሙዋቸው ኳሶቻችን ነጻ ሊወጡልን ነው ብለን ተደስተናል።

ገመዱን አስረው ራሳቸውን ለመሰቀል ካመቻቹ በኋላ ዘውር ብለው እኛን ተመለከቱን። «እባኮን ይተው!» የሚላቸው አንድ እንኳን ሰው አልነበረም። ለደቂቃዎች በአትኩሮት ከተመለከቱን በኋላ እንዲህ አሉ። «እንዲያውም ደስ አይበላችሁ። ሃሳቤን ቀይሬአለሁ። አልሰቀልም!»

ዛፉ ላይ ያሰሩትን ገመድ ፈቱትና ወደ ሰፈር አቀኑ። ካልተሳከው የጎልጎታ መሰውያ ሲመለሱ እመንገድ ላይ ያገኛቸው አንድ ሰው ሲመክራቸው ሰማን። «ሌላ ግዜ መሰቀል ከፈለጉ ለሰው አይናገሩ። ድምጽ አጥፍተው ለብቻዎ ያርጉት። የዚህ ሰፈር ልጆች አብዝተውታል። ሰው በሰላም እንኳን እንዳይሞት እያደረጉ ነው።»

ሰውየው ለመካሪያቸው ምንም ምልስ አልሰጡም- ግን ወደኛ እየተገላመጡ «እርሱት። አታገኙዋትም!» የማለት አይነት በአይናቸው እየዛቱብን እቤታቸው ገቡ።

ከልጅ ጋር የሚጫወቱት እንቁልልጬ መሆኑ ነው። ለዚያማ ማን አክሎን። የባሰ እልህ ውስጥ አስገቡን። … በመጨረሻ ብቻቸውን መንገድ ላይ እያወሩ መሄድ ሲጀምሩ ተውናቸው። …

የሳይበሩ አንበሳ የመታጠፉ ፍጥነት ሳይገርመን የድጋሚ ቅልቅሉን በከአዲስ ዜማ አከለበት። “እንደውም ደስ አይበላችሁ። ወያኔን ተቀላቅያለሁ!” የሚል ዜማ። የልጅነት እንቁልልጬ ጨዋታ ይመስላል። ለመዞርማ ምድርም ብርሃንና ጨለማን ለማፈራረቅ በራስዋ ዛቢያ ላይ ትዞራለች። የኋላውን ለማየት ሲል አንገትም ይዞራል። ብረትም ይዞራል – በእሳት ሲፈተን። … ቆርቆሮ ግን እንዲሁ ይጠመዘዛል።

«..እኔ እንኳን ትንሽ መቆየት ፈልጌ ነበር።» አለ ኦቦ ዳምጤ፤ ለሁለተኛው ዙር ከወያኔ ጋር ያደረገውን ቅልቅል ሲያበስር። ይህችን አነጋገር የተጠቀመባት ያለ ምክንያት አልነበረም። ወደዚህኛው ጎራ የገባው የጥምር ሰላይ (double agent) ስራ ለመስራት እንደሆነ ለማስመሰል መሞከሩ ነበር። ፈረንጆቹ (match fixing) ማች ፊክሲንግ የሚሉት በእግር ኳስ አለም ውስጥ ለተቃራኒው ተገዝቶ የመስራት ውስልትና አይነት መሆኑ ነው። እንዲህ የተራቀቀ ቢሆንማ ኖሮ እናደንቀው ነበር። ግና በዚያው ቃለ-ምልልስ ላጠፋው ጥፋት ይቅርታ ጠይቆ ጨዋታውን አበላሸው። ድንጋይ በትከሻው ባይሸከምም ህሊናውን ዝቅ አድርጎ ከአክራሪ ዲያስፖራ ጋር በመዋሉ በጣም ተሰምቶታት። ወያኔዎች ይቅርታ የሚላቸውን ለምን እንደሚወዱ አይገባኝም። ይቅርታ የሚጠይቋቸውን ሰዎች በጣም ሲወድዱ እንጂ ምህረት ሲያደርጉላቸው ግን አይተን አናውቅም። ታምራት ላይኔን በፓርላማ ካዋረዱት በኋላ ቀፈደዱት። ሰለሞን ተካልኝም ከይቅርታ አልፎ ከዲያስፖራው ርኩስነት ለመጽዳት ሲል አባን ጸበል እርጩኝ ብሎ ነበር – በዘፈን። መቀሌ ድረስ ሄዶ በኢህአዴግ ጸበል ቢጠመቅም፣ እነሱ ግን ቂማቸውን አልረሱም። ሁሉንም ማኖ እያስነኩ በአየር ላይ ያንሳፍፏቸዋል።

አባመላ ከነሱ ጋር ተጣልቶ ወደ ተቃውሞ ጎራ በሄደ ጊዜ ወያኔዎች አንድም ነገር አልተነፈሱም ነበር። ምክንያቱም ጸቡ የመርህ እንዳልነበር ያውቁታል። ጉዳዩ የግል ጥቅም ነው። መፍትሄውም ቀላል። በፈለጉት ግዜ እንደ ቆላ በሬ አሞሌ ጨው አልሰው እንደሚመልሱት አስቀድመው ያውቁታል።

በቃለ-ምልልሱ አባ መላ በካፒቴን ሀይለመድህን አበራ ዙርያ የተነሳውን ክርክር ሊቋቋመው እንዳልቻለ አልካደም። በክርክር ሲሸነፍ እንደመፍትሄ የወሰደው የወያኔን ጎራ መቀላቀል መሆኑም አዲስ ነገር አይደለም። ያኛው ጎራ በሃሳብ የተሸነፉ መሃይማን መሰብሰብያ ጎራ ከሆነ ሰንበትበት ብሏል።

ንግግር መቻል አንድ ነገር ነው። እየቀለዱ ሰውን ማሳቅም ቀላል ሊሆን ይችላል። በመናገር ሰዎችን ማሳመን መቻል ግን ሌላ ጉዳይ ነው። ይህ ጥበብን፣ ብስለትን እና አስተዋይነትን ይጠይቃል። በንግግር ሰዎችን ማሳመን መቻል ደግሞ ሮኬት ሳይንስ መሆንን አይጠይቅም። አንዳንዶች በትምህርት ያገኙታል። ሌሎች በማንበብ ይለወጣሉ። የህይወት ተመክሮም በራሱ ብዙ ነገር ያስተምራል። ከስህተታቸው እየተማሩ የሚበስሉ ሰዎችም ብልሆች ናቸው።

«አቶ መለስ ዜናዊ እድሜ ልካቸውን የአማራን ህዝብ ሲሳደቡ ሰንብተው፤ አንድ አማራ ሲሰድባቸው ግን ደግም ላይመለሱ አሸለቡ።» የሚል ቀልድ ሰምቼ በጣም ነበር የሳቅኩት። ነገሩ ልክ ነው። በሌላው ላይ የሚቀልዱ ሰዎች በራሳቸው ላይ ሲደርስ በቶሎ ይሰበራሉ ይባላል።

እናም በሃይለመድህን ጉዳይ «ከጽንፈኞች» ሳይስማማ በመቅረቱ የጠፋው በግ ወደ ቤቴ ተመለስኩ ነው እያለን ያለው። ይህ ሰው ግን ስንት ጊዜ ነው ከቤቱ የሚጠፋው?

ደግሞ ፍጥነቱ። የብርሃን ጉዞም እንደብርሃኑ ዳምጤ አይፈጥነም። ወደዚያኛው ጎራ ሲቀየስ የለበሰውን የዲያስፖራ ማልያ እንኳ ለመለወጥ ግዜ አልወሰደም። የቡናን ማልያ ለብሶ ለደደቢት የሚጫወት አይነት ሰው ነው የሆነው።

እንደዚህ አይነት ሰዎች ስብእናቸውን የሚሸከም አንገት ስለሌላቸው ወደግራም ሆነ ወደቀኝ፣ ወደፊትም ሆነ ወደኋላ ለመተጣጠፍ ችግር የለባቸውም። ይህ ሰው ወደ ቀኝ ታጥፎ በነበረበት ግዜ ከአንዴም ሶስቴ ደውሎ በስልክ አናግሮኝ ነበር። አቀራረቡ፣ አነጋገሩና ጨዋታው ያራዳ ልጅ ይመስላል። ተግባሩ ግን የአራዳ ልጅ አይደለም። ያራዳ ልጅ ባልንጀራውን ይረዳዋል እንጂ በቁሙ ሊያርደው አይዳዳም።

ወያኔ የመሆን መብቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህንን ለመሆን የሄደበት መንገድ ግን በጣም ይደብራል። ድርጊቱ ሰሞኑን በፈረንሳይ ሃገር ከተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ ጋር ተመሳሳይ ነው የሆነብኝ። የክህደት ትንሽ የለውም። ልዩነቱ አባ መላ ያስጠጉትን ወገኖች በቁም አለመግደሉ ብቻ ነው።

አንዲት የዋህ ወይዘሮ፤ በፓሪስ ከተማ እመንገድ ላይ ወድቆ የሚለምን ኢትዮጵያዊ ወገን አግኝተው እጅግ አዘኑለት። እቤታቸውም ወስደው ማረፍያ ሰጡት። መሰረታዊ የሆነውን ነገር ሁሉ አሟሉለት። አምነው ያሳደሩት ይህ ሰው ግን ውለታቸውን በአሰቃቂ ሁኔታ መለሰላቸው። አራት ወር እንደቆየ ይህንን የሶስት ልጆች እናት ከትንሽ ልጃቸው ጋር በሴንጢ አርዶ ተሰወረ። አባመላ አብረውት ሲሰሩ የነበሩትን በቢላ ባያርዳቸውም በአነጋገሩ ስጋቸውን እንደበላው ነው የሚቆጠረው። አምነው አስተጉት ይህ ሰው እንደጴጥሮስ ጎህ ሳይቀድ ካዳቸው። የክህደት ቁልቁለት ይሏል እንዲህ ነው። «የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ!» ይላሉ አበው። ቃልን ማጉደል ምን ያህል ከባድ ነው!

ታማኝ በየነ እና አበበ ገላው ከብርሃኑ ዳምጤ ጋር በሳውዲው ቀውስ አብረው መስራት ሲጀምሩ በፍጹም ቅንነት እና በየዋህነት ነበር። ይህንን በማድረጋቸውም በርካታ ትችት ቀርቦባቸዋል። እነሆ አባ መላ ዛሬ ለቅልቅሉ እጅ መንሻ እነሱን በመሳደብ እንደመስዋዕት አቀረባቸው።

የብርሃኑ ዳምጤ አካሄድ ያሳሰባቸው ሁለት ወዳጆቼ በዚያን ሰሞን በዚሁ ጉዳይ ላይ በሰል ያለ አስተያየት ጽፈው ነበር። በልጅግ ዓሊ (ከፍራንክፈርት) እና እንግዳሸት ታደሰ (ከኦስሎ)። እነዚህን ጽሁፎች እንደገና እንድታነቧቸው እመክራለሁ። በልጅግ ዓሊ «ዘመንን ለማሰር» በሚለው ጽሁፉ ይህ ሰው እንደ ጴትሮስ ይክደናል ነበር ያለው።
…ለአንዲት የሰሙኑ የፖለቲካ ጥቅም ሲባል ብርሃኑ ደቡርን እላይ የሰቀላችሁት በኋላ እንደለመደው ሲክዳችሁ ስትንጫጩ መስማታችን አይቀርም። ትንቢት እንዳይመስላችሁ ደቡርን በደንብ አድርገን እናቀውቀዋለን። ቆዳችሁን ገፎ ይሸጠዋል፣ ደቡር ሃገሩን አይደለም እናቱንም ቢሆን ይደልላል። አታውቁት እንደሆን መርካቶ ላይ ሄዳችሁ የተሰራውን ግፍ ጠይቁ። እንኳን የቀይ ሽብሩን ፣ እነ ሽብሬን ረስተን የለም እንዴ !!  ምን ይደንቃል።
ብሎ ነበር። እንግዳሸት ታደሰ ከኖርዌይ የጻፈውም ተመሳሳይ ነገር ነበር። «አባ መላ ልብ ሲበላ! » በሚለው መጣጥፉ «የዲያስፖራ ኃይል በአራዳ ስልትና በወያኔ ቆረጣ ለመሰንጠቅ ፣ የሚደረግም ጨዋታ ሊሆን ይችላል ብሎ መገመትም የዋህነት አይመስለኝም።» ነበር ያለው። እነዚህን መጣጥፎች ደግሜ ሳነባቸው ትንቢት ነው የመሰሉኝ። በወቅቱ ግን እነዚህን ጽሁፎች በድረገጽ በማውጣቴ የስድብ ናዳ ወርዶብኝ ነበር። አንዱ የፓልቶክ ታዳሚ እንዲህ ብሎ ነበር የጻፈልኝ። «የማናውቅህ እንዳይመስልህ! አንተ የዳዊት ከበደ ወንድም!»
የትኛው ዳዊት እንደሆነ ግን ግልጽ አላደረገልኝም። የአትላንታው ወይንስ የአውራምባው?

እርግጥ ነው። በፖለቲካ ቋሚ ወዳጅ ወይንም ቋሚ ጠላት የለም – ጥቅም እንጂ። በመርህ ላይ ሳይሆን ይልቁንም ለግል ጥቅም ሲሉ የሚዋዥቁ ሰዎች ናቸው ሀገርን የሚያጠፉት። በተለምዶ መሃል ሰፋሪዎች ይባላሉ። እንደዚህ አይነቶቹ ሰዎች በተቃዋሚውም ጎራ ነፍ ናቸው። ደጋፊ ሳይሆን ተደጋፊ ሆነው ለመኖር ሲሉ ብዙ ጥፋት ይሰራሉ። የሃይል ሚዛኑ እስካዘነበለ ድረስ ለአለቆቻቸው እጅግ ታማኝ ይሆናሉ። የሃይል ሚዛኑ ሲዛባ ደግሞ ለመካድ የመጀመርያዎቹ ናቸው።

ይህ የመርካቶ ቁጭበሉ ሼም አያውቅም። ትንሽ ብትጠብቁት እንደገና ይመለሳል። በዚህ አይነት ሰው ላይ እምነት መጣል እና መስጋት ከየዋህነት ያለፈ ነው። አንድ ጅል ትምህርት ቤት ሲሄድ የሙዝ ልጣጭ አዳልጦት ወደቀ። ከትምህርት ቤት ሲመለስ ያችኑ የሙዝ ልጣጭ አይቶ ቆመ። ከዚያም ማልቀስ ጀመረ። ለምን እንደሚያለቅስ ሲጠየቅ ወደ ልጣጩ እያመለከተ እንዲህ አለ። «እንደገና ልወድቅ ነው።»

↧

ኢ.ኤም.ኤፍ –ሃረር እየታመሰች ነው !

↧

አንድነት- አንድነት ፓርቲ ክስ የመሰረተባቸው የመንግስት ተቋማት መቃወሚያቸውን አሰሙ –በአሸናፊ ደምሴ

$
0
0

በዴሞክራሲያዊ መንገድ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ህገመንግስታዊ መብቴን ጥሰውብኛል ሲል አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ክስ የመሰረተባቸው ሶስት የመንግስት ተቋማት በትናንትናው ዕለት በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ፍትሃብሔር ችሎት ቀርበው መቃወሚያቸውን አሰሙ። ፓርቲው ክስ የመሰረተባቸው የአዲስ አበባ ከንቲማ ጽህፈት ቤት ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የአዲስ አበባ ፖለስ ኮሚሽን ሲሆኑ በጠበቆቻቸው በኩል የክስ መቃወሚያቸውን በፍ/ቤቱ አቅርበዋል።

የአንድነት ፓርቲ በጠበቃው በኩል የመሰረታቸው ክሶች የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ተሻሽሎ በተሰጠው ቻርተርና የፖሊስን የእለት ተእለት ስራ በአግባቡ አልተከታተለም። ሁለተኛ ፖሊስ ፓርቲው በህግ የተፈቀደለትን ቅስቀሳ በሚያደርግበት ወቅት እገታ ተፈፅሞበታል፤ በራሪ ወረቀቶችን ተቀምቶ ቅስቀሳውን አስተጓጉለዋል የሚል ሲሆን ማዘጋጃ ቤቱን በተመለከተ በህግ መፈቀድ ያለበትን ቦታ ትቶ በጦር ካምፕ አካባቢ 50 ሜትር እርቀት ውስጥ ሰላማዊ ሰልፉ ማድረግ ክልክል መሆኑን እያወቀ ከህግ የተጣረሰ ፍቃድ ሰጥቷል የሚል ቅሬታ ማቅረባቸውን በክስ ዝርዝራቸው አስረድተዋል።

ፓርቲው ክስ ከመሰረተባቸው የመንግስት ተቋማት ጠበቆች በኩል ክሱን ለመቃወም የቀረበው ሀሳብ ፍርድ ቤቱ ይህን ጉዳይ የመመልከት ስልጣን የለውም የሚል ሲሆን፤ ጉዳዩ መታየት ያለበት በማዘጋጃ ፍርድ ቤት በኩል ነው የሚል ሀሳብ ቢቀርብም ፓርቲው በበኩሉ ያቀረብኩት ጉዳይ ህገመንግስታዊ እንጂ የከተማና የቦታ ጉዳይ አይደለም ሲል የክስ መቃወሚያው ውድቅ እንዲደረግለት ጠይቋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ በበኩሉ የፌዴራል ፖሊስን በተመለከተም መግባት አለበት ይህን ጉዳይ የሚከታተለው ተቋም እርሱ ነው የሚል የክስ መቃወሚያ ለችሎቱ አቅርቧል። ከዚህም ሌላ የቀረበው መቃወሚያ ፓርቲው ከ500ሺህ በላይ ህዝብ ይመጣል በማለቱ የጃን ሜዳ እንደፈቀዱለት አስረድተዋል።

አንድነት በአባላቶቼ ላይ የደረሰው ጉዳት በማስረጃ የተደገፈ ነው ያለ ሲሆን ከ100 በላይ የሰው ምስክሮችን ማቅረብ እንደሚችልም አስቆጥሯል። ከዚህ በተጨማሪ በጋዜጣ የወጣው ዘገባ እና የፓርቲው አመራሮች እስከበላይ ባለስልጣናት ድረስ የተፃፃፏቸውን ደብዳቤዎች በሰነድ ማስረጃነት ለፍርድ ቤት አቅርቧል።

የግራቀኙን የክርክር ሂደት የተከታተለው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ፍትሐብሔር ችሎትም በጉዳዩ ላይ ብይን ለመስጠት ለሚያዚያ 7 ቀን 2006 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

↧

የሚሊየኖች ድምጽ –የሚሊየኖች ድምጽ እንቅስቃሴ ለመደገፍ በዉጭ ግብረ ኃይል ተቋቋመ !

$
0
0

አገራችን ኢትዮጵያ ያለችበትን አሳዛኝ ሁኔታ ከማንም የበለጠ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ይረዳዋል ብለን እናምናለን። የኢሕአዴግ መንግስት፣ ላያ ላዩን «በዴሞክራሲ አምናለሁ» ቢልም፣ ፍጹም አምባገነን በሆነ መልኩ ፣ ሕዝቡን አፍኖ፣ እያሰራ፣ እየገደለ፣ ዜጎችን እያፈናቀለ፣ ከሃያ አመታት በላይ ቆይቷል። በአብዛኛዉ ሕዝብ ዘንድ እየተጠላ፣ ይሄን ያህል አመት በስልጣን መቆየት የቻለው፣ አገዛዙ በዋናነት ኢትዮጵያዊያን መከፋፈል በመቻሉና ዜጎች ደፍረው ለመብታቸው እንዳይቆሙ በፍርሃት እንዲተበተቡ በማድረጉ ነው። ይሄንን ለማስቆም ሕዝቡን ማስተባበርና ማደራጀት ቀዳሚና ብቸኛ አማራጭ ነው።

አገር ቤት በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ በርካታ የፖለቲካ ድርጅቶ አሉ። ከነዚህ ድርጅቶች መካከል አንዱ የአንድነት ፓርቲ ነው። የአንድነት ፓርቲ «የሚሊዮኖች ድምጽ ለፍትህ» እና «የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት» በሚል ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን ለማድረግ ተዘጋጅቷል። ይህ እንቅስቃሴ የአንድ ፓርቲ እንቅሳቅሴ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንቅስቃሴ እንደመሆኑ፣ በአገራችን ዴሞክራሲና የስርዓት ለዉጥ እንዲመጣ የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ ሊቀላቀሉት፣ ሊደግፉት፣ የራሳቸው ሊያደርጉት የሚገባ እንቅስቃሴ ነዉ። ይህ እንቅስቃሴ የሚሊዮኖች እንቅስቃሴ ነው። የእያንዳንዳችን እንቅስቃሴ ነው።

በቅርቡ በባህር ዳር አስደናቂ ሰልፍ መደረጉ ይታወሳል። በቦታዉ የተገኙ ወገኖች ድምጻቸውን ያሰሙት አንድን ፓርቲ ብለው አልነበረም። ኢትዮጵያን ብለው ነዉ እንጂ። የባህር ዳሩ ሰልፉ ያማከለው በአንድ ድርጅት ዙሪያ አልነበረም። ነገር ግን በኢትዮጵያ ዙሪያ እንጂ። ይህ በባህር ዳር የተደረገውን አይነት የነጻነት እንቅስቃሴ በተጧጧፈ መልኩ በመላው አገሪቷ ማድረጉ አስፈላጊ ነው።

በአገሪቷ ሕገ መንግስት አንቀጽ 30 መሰረት፣ የዜጎች የመሰባሰብ ፣ በሰላም ትእይንተ ሕዝብ የማድረግ ሙሉ መብት የተረጋገጠ ነው። በመሆኑም ይህ የሚሊዮኖች ለነጻነት ንቅናቄ ሰላማዊና የአገሪቷ ሕግ በሚፈቅደው መሰረት የሚደረግ በማንም ዜጋ ወይንም ቡድን ላይ ያላነጣጠረ፣ የተወሰኑትን ጠቅሞ ሌላዉን የሚጎዳ ያልሆነ፣ በዘር፣ በሃይማኖት፣ በመደብ፣ በጾታ ልዩነት ሳያደርግ፣ ኢትዮጵያዉያንን በሙሉ ለፍትህና ለነጻነት ለማሰባሰብና ለማንቀሳቀስ ታሰቦ የታቀደ እንቅስቃሴ ነው።

በዳያስፖራ ያለው ማህበረሰብም የኢትዮጵያ ሕዝብ አካል እንደመሆኑ፣ የድርሻዉን መወጣት ይጠበቅበታል። በመሆኑም ይሄን የሚሊዮኖች ድምጽ ወይንም በባህር ዳር የተደረገዉን አይነት እንቅስቃሴ በሌሎች ከተሞች እንዲደረግ ለመርዳትና ለማጠናከር፣ የዳያስፖራ የሚሊዮኖች ድምጽ ግብረ ኃይል ተቋቁሟል። ይህ ግብረ ኃይል በዳያስፖራ ባሉ የአንድነት ፓርቲ ድጋፍ ማህበራት አነሳሽነትና በዉጭ ካሉ የአንድነት ፓርቲ ድጋፍ ማህበራት በተጨማሪ፣ ከተለያዩ የሲቪክ ማህበራት፣ አገር ቤት የሚደረገዉን ሰላማዊ ትግልን በሚደገፉ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ሲቪክ ማህበራት ፣ ፓልቶክ ክፍሎችና ግለሰቦች ተባባሪነት፣ «እኛም የሚሊዮኖች አንዱ አካል ነን» እያሉ ቀናና የሚያኮራ ኢትዮጵያዊ ምላሽ እየሰጡ ያሉና ለመስጠትም የተዘጋጁ፣ በአለም ዙሪያ ሁሉ ያሉ ኢትዮጵያዉያንን ለነጻነትና ለፍትህ ለማሰባሰብ የተዋቀረ ነው።

የሚሊየነሞች ንቅናቄ አዲስ አበባ እና ድረደዋ አስተዳደሮችን ጨምሮ፣ በኦሮሚያ የአዳማ፣ የላፍቶና የነቀምቴ ከተሞችን፣ በደቡብ ክልል፣ የአዋሳ፣ የጂንካና የቁጫ ወረዳዎችን፣ በትግራይ ክልል የመቀሌ ከተማን፣ በአማራዉ ክልል ደሴ፣ የወልዲያ፣ ደብረ ታቦር ፣ ደብረ ማርቆስ እና በምእራብ አርማጭሆ የአብርሃ ጅራ ከተማን ፣ በቤኔሻንጉል ጉሙዝ የአሶሳን ከተማ፣ በጋምቤላ ክልል የ ጋምቤላ ከተማ የሚያዳርስ ይሆናል።

የሚሊየምን እንቅስቃሴን በተመለከተ በየጊዜዉ ወቅታዊ መግለጫ የምንሰጥ መሆናችንን እየገለጽን። በዉጭ የሚገኘው ኢትዮጵያዊ እንደከዚህ በፊቱም ታላቅ ድጋፉን እንዲያበረክት በአክብሮት እንጠይቃለን። አገራችን ኢትዮጵያ የሁላችንም የጋራ አገር ናት። ለአገራችን መነሳታችን ሊያስከፋ የሚችለው፣ ወይንም ዝምታን ተስፋ ቆርጠን መቀመጣችን ሊያስደስት የሚችለው አምባገነኖችን ብቻ ነው። በሕዝባችን ላይ ግፍ የሚፈጽሙ አይደሰቱ። እንነሳ። የድርሻችንን እንወጣ። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን !

በምትኖሩበት ከተማ ተደራጅታችሁ፣ ከዚህ ግብረ ኃይላ ጋር በመስራት በአገር ቤት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ስፖንሰር ማድረግ የምትፈልጉ በሚከተሉት አድራሹ ሊያገኙን ይችላሉ

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !

millionsforethiopia@gmail.com
404- 518-7858

↧
↧

ትዝብት –ደርሶ መልስ ዲያስፖራ (አንደኛ) አትክልት አሰፋ (ቫንኩቨር)

$
0
0

ነገሩ የሆነው አዋሳ ዩኒቨርሲቲ ነው። ቆነጃጅት ወጣት ሴት ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውጭ ባሉ የከተማው ደለላዎች ጋር በመተባበር እጅግ ዘግናኝ ስራ ይሰራሉ። ደላሎቹ የቆነጃጅቶቹን ተማሪዎች ፎቶ የያዘ ትልቅ ካታሎግ ይዘው ከአዲስ አበባም ሆነ ከአቅራቢያው ከተሞች አለዚያም ከዚያው ከአዋሳ ከተማ ብቅ የሚሉ ሃብታም ደንበኞቻቸውን የተማሪ ኮረዶችን ፎቶ በመስጠት ያስመርጣሉ።

ሰውየው ውብ ወጣት ተማሪ ኮረዳ እንደሚፈልግ በሰው በሰው የተገናኘውን ደላላ ይጠይቃል። እናም ከተሰጠው የፎቶ ድርድር ላይ ማመን ያቃተውን የአንዷን ውብ ፎቶ እያሳየ ‘ይህችን ታውቃታለህ?’ ሲል ይጠይቃል። የደላላ መልስ አንድ ነው… ሁሉንም ስለሚያውቃቸው አልተቸገረም ‘አዎ እሷን ይፈልጋሉ?’ ሲል ይጠይቃል። ሰውየውም ‘እባክህ’ ሲል በመማጸን ፈቃደኝነቱን ይገልጻል። ከፊቱ የመጣለትን ገቢ ተደራድሮ ልጅትን ለመጥራት ይሮጣል። ደላላው።

እናም ቆንጅት ተበጃጅታ፣ አምራና ደምቃ ትመጣለች። በቀጥታ ወደ ሰውየው መኪና ስትደርስ ሰውነቷ ይርዳል። በቁጣ አይኑ የተንቀለቀለው ሰውየም ወደ ልጅቷ ያፈጣል… በቀጥታ ተንደርድሮ የልጅቷን ክርን ይይዛል… ደላላው እየሆነ ያለውን ሊረዳ አልቻለም… የልጅቷን እጅ የያዘው ሰው (ደንበኛ) የልጅቷ ወላጅ አባት ኖሯል።

ኢትዮጵያ ደርሶ የሚመጣ የውጭ ሀገር ነዋሪ (ደርሶ መልስ ዲያስፖራ) በተለያየ አይነት እይታ የተለያዩ እውነታዎችን ይዞላችሁ ይመጣል።

አንዳንዱ የህንጻውን ግንባታ አዳንቆ ሲያወራ፤ ሌላው ስለጭፈራ ቤቶች ይዘክራል። ጓደኞቹን በስራ ብዛት ሊያገኝ እንዳልቻለ የሚያወራላችሁ እንደመኖሩ ሁሉ በስራ አጥነት ችግር የተነሳ ዱርየ መበራከቱን የሚተርክላችሁ አታጡም። የቆነጃጅቶችን ውበትና የዳንኪራ ቤቶችን ሁናቴ የሚነግራችሁ፤ በየቡና ቤቱ ብሎም በየትምህርት ቤቱ ያሉ ወጣቶችን ችግር ያስረዳችኋል። የሀገሪቱን እድገት በኮንስትራክሽን መጥለቅለቅ የሚያጫውታችሁ፤ በመንገዱን መቆፋፈር ሰው ስለመማረሩ በማንሳት ያትትላችኋል። አዲስ አበባን በመመስረት ላይ እንዳለች ታላቅ ከተማ አድርጎ የሚተርክም አታጡም።

ይሄ ሁሉ እንደ እድገት በአንዲት መንግስት የሚባል አካል አላት በተባለች ሀገር መታየቱ ምኑ ይገርማል?። አንዳንዴ ሀገሩን አይቶ ዘመድ ወዳጅ ጠይቆ መምጣትም ሆነ ሰው ሀገሩ ደርሶ መመለሱ እጅግ መልካም ነገር ነው። ያየውን ግልብ ነገር ከራሱ አይን ጥግ ስር አንጻር ብቻ ተመልክቶ በሰዎች ላይ የሚደርስን ስቆቃ ሸፋፍኖ ያለጥናት የተሰሩ መንገዶችንና ህንጻዎችን እንደትልቅ ለውጥ ማውራት ግን የሞራል ጥያቄን ያመጣል።

በእርግጥ የውብ ሀገር ነችና ውቦች ሊኖሩ ይችላሉ። መሸታ ቤቶቹም ደማምቀው ሊሆን ይችላል። ህንጻ ግምባታውም ቢጧጧፍ አያስነውርም። መንገዶች ተንጣለው ቢታዮም ጸጸት የሚገባው የለም። ነገር ግን ሰው በቀላሉ ቆሎ ሽጦ ይኖርበት ከነበረ መንደር ተባሮ መግቢያ ያጣበት ሀገር፤ ውሃ ልማት የቆፈረውንና ውሃ ቧንቧ ቀብሮ ያበጀውን መንገድ ነገ ቴሌ የሚያፈርሰው ከሆነ… ከዚያም ማዘጋጃ ቦይ ተደፈነ ብሎ ከተረተረው… ወጣት እንስት ህጻን ታናሽ እህቷንና ወንድሟን ትምህርት ቤት ለመስደድ መንገድ ከወጣች፤ ጥቂት የባለጊዜ ልጆች የሚሰሩት አጥተው በተንፈላሰሱባት ሀገር መለመንን ተጠይፈው ዱሮ የነበራቸውን ጽዱ ልብስ ለብሰው ፊታቸውን የከለሉ ሰዎች በየጥጋጥጉ የሚለምኑባት ሀገር ከሆነች… አባት ትምህርት ቤት ብሎ የላካት ወጣት በኮሌጅ ያለውን ፍላጎቷን ለማሳካት ገበያ መውጣት… ዘግናኝ ነው…

የሚሰራው መንገድ ተሸርሽሮ ከአመት በላይ አገልግሎቱ አልቆለት ተቦርቡሮና ውሃ ቋጥሮ የሚታይበት ሀገር እየገነቡ መሰረት መጣል አይቻልም ነው ጥያቄው። ደረጃቸውን ባልጠበቁና በይድረስ ይድረስ የተሰሩ ህንጻዎች ጋጋታ የከተማንም የሀገርንም እድገት ሊያሳዩ አይችሉም ነው እየተጮኸበት ያለው ነገር። ፍትህ ራሷን ችላ የምትራመድበትን ሀገር የሚመራ መንግስት ይኑር ነው ልፈፋው። የህወሃት ሰዎችና ጥቂት አሸርጋጆች የሚያደርጉት አገራዊ ጥፋት ይቁም። ልጆቻችን እርስበርስ የዚህና የዚያ ብሄር ወይንም ከወዲያ አለዚያም ከወዲህ መንደር የመጡ እየተባባሉ በጥርጣሬ እየተያዩ የሚኖሩበትንና የሚያድጉበትን ሀገር እናፈራርስ ነው እሪታው። የህወሀት አለያም ጥቂት ሽርጉደኞች በገፍ የሚገነቧቸው ህንጻዎች ከሙስና ባሻገር ሆኖ ራሳቸው ኢንጂኒዬርና አርክቴክት ሆነው የሚገነቡት ሀገር ሀገር አይሆንም ነው ጉዳዩ።

22 አካባቢ የተሰራው ጎላጎል ህንጻ ባለጊዜው ባለቤት ህንጻውን ሲያስገነባ ዋናው መንገድ ውስጥ መግባቱን ያየ መሀንዲስ ወይንም ኢንጂኒዬር ‘አግባብ አይደለም፤ ወደፊት መንገድ ይዘጋል’ ብሎ ምክር ቢሰጠው ‘እኔ ያልኩህን አድርግ’ ብሎ ጀርባውን የተማመነው ባለቤት ሲያዘውና ያ ባለሙያ የታዘዘውን በማድረጉ ግንባታው ከተጠናቀቀ በኋለ አሁን መንገዱን የዘጋውን ህንጻ የሚደፍረው ጠፍቶ፤ መረማመጃው ዘግቶ መታየቱ የሚወራው ዝም ብሎ ከመሬት ተነስቶ አይደለም።

አሁንማ የህወሃት ሰዎች እጅግ ከመድፈራቸው የተነሳ አዲስ አበባ ውስጥ በስማቸው ሆኗል ፎቅ የሚያስገነቡት ተክላይ ህንጻ፣ ገብረጻዲቅ ህንጻ… ብሎ ያጫወተኝ ወዳጄ ታዲያ ምን ችግር አለው? ስለው ‘ምንም ችግር የለውም በህዝቡ ውስጥ ግን የማህበራዊ ህይወት መራራቅንና ሃሜትል ያስከትላል ብሎም ህዝቡን እነሱ እና እኛ የሚያስብል የሳይኮሎጅ ጣጣ ውስጥ ከቶታል።” አለኝ
ሀገሪቱን የህወሃት ጄኔራሎችና መኮንኖች ብቻ በሀብት የወረሯት ሀገር ተሸክሞ የት እንደሚደረስ ማሰብ ሰው መሆን ነው። ይህ ወዳጄ ታዲያ በአንጻሩ የሽንኩርትን ገበያ ለማየት ጉሊት ወርዶ ያየውን ጉድ በልኩ አስተውሎ መጥቷል። አንድና ሁለት ራስ ትንንሽ ሽንኩርት አልያም ቲማቲም ለሳምንት ለማብቃቃት የሚሰቃይ ህዝብን ይዞ ጉዞው የት ነው የሚያደርሰን።

የአገሪቱን የዘር ችግር ጥግ ላይ መድረስ ባለፈው 767 አውሮፕላንን ይዞ ጄኔቫ የገባው ወጣት ረዳት አብራሪን በሚመለከት መግለጫ የሰጡት ሬድዋን ሁሴን “ጠላፊው ከየት ነው?’ ተብለው ሲጠየቁ ‘ኢትዮጵያዊ ነው’ ብለው ሲመልሱ አረ ከየትኛው ክልል ተብለው መጠየቃቸው ጉድጓድ ውስጥ የሚከት ቅሌት ነው። መልሳቸውም እረሪሪሪሪሪ የሚያስብል ነበር። ‘ከየትኛው ብሔር እንደሆነ አልታወቀም።’

መጠጥና ዳንኪራ ቤቶች

ከ5 ሚሊየን ህዝብ በላይ (እስከ 8 ሚሊዮን ይገመታል) የሚኖርባት አዲስ አበባ የጭፈራ ቤቶችን ብዛትና የጨፋሪውን አይነት የነገረኝ ወዳጄን ቀኑን ሙሉ ሲተራመስ የሚውለው አዲሳቤ በጊዜ በ12 ሰዓት ከቶ በየፊናው ሲገባ ከተማው ምን ያህል ጭር እንደሚል አላስተዋለም። 100 የማይበልጡ ምሽት ቤቶች (አጋንኘው ነው) 100 ሰው እያንዳንዳቸው ቢያገኙና ቢያስጨፍሩ 10ሺህ ሰው… እንጨምረው እና 50ሺህ ሰው በምሽት ስለጨፈረና ስለደነከረ ሀገር በጥጋብ እንደዘለለ ማውራት ነውር ነው ነው ጨዋታው። ይሄንኑ ግምት እናስላው ከተባለ የገዥው ህወሃት/ኢህአዴግ ባለስልጣናትና ጥቅም ተሻራኪዎች 70 በመቶውን ቢያነሱ 15 በመቶ በዲያስፖራና ዘመዶች እንዲሁም የተቀረው ለፍቶ አዳሪ አለያም ከቤተሰቡ የሚቃርም ሊሆን ይችላል።
ለነገሩማ የዘመነኞቹ ሰዎች ልጆች የሚገቡበት ቡና ቤት ውስጥ ቀድሞ የገባ ሌላ ደንበኛ ሾልኮ እንዲወጣ የሚደረግባት ምድር። በድርድር የታሰረ ብር ለአስተናጋጅ ተሰጥቶ ቆጥረሽ ውሰጅ የሚል ረብጣው ያጨናነቀው የዘመኑን ሰው ማየት የተለመደ መሆኑንም እየሰማን ነው።

ምን እዚህ እኛ በብርድ እየወጣን ሰላማዊ ሰልፍ እያልን እንጮሃለን እነሱ ሚሊየነሮች ሆነዋል ያለኝና ሀገር ቤት ሄዶ በጓደኛው የቀና ሰው ያጫወተኝም አለ። ያ ጓደኛው ከዘመንኛ ሰዎች ጋር ገጥሞ ህዝብ እየቦጠቦጠ መሆኑን የነገረኝ ደርሶ መልስ ዲያስፖራ… አሁንም እዚህ ኖርዝ አሜሪካ ከተመለሰ በኋላ እዚያው አገር ቤት ቢሆን እንደጓደኛው ሚሊየነር ይሆን እንደነበር ሲያወጋኝ በመቆጨት ነበር። ዘመንኞቹና ጓደኛው የሚቦጠቡጠው ህዝብ ስቃይ በሚሊየን ብር ተጋርዶበት። አረ እየተስተዋለ! እዚያኮ ሀገር እየተቆራረሰ ነው! አረ ስለአምላክ! ሀገሪቱም በመንደር እየተተበተበችኮ ነው! ስለእመብርሃን! ምድራችን ፍትህ የጠፋባት ሆናለችኮ! በሽብርተኛ ስም ስንቱ ታጎረ… አረ ስለአላህ! ሰው ኑሮ መረረኝ እያለ ነው እኮ! እንኳን ከአሜሪካ ከመንግስተ ሰማያትም አመጣኻለሁ የሚል ለስራው ብቁ ያልሆነ ሰው የሚሾምበት ሀገር ውስጥ የሚኖር ህዝብ እኮ ነው የያዝነው። ጭራሽ የሶማሌ ክልል ባለስልጣን ይባስ ብሎ ምኒባስ ታክሲ በከተማ እንዳይገባ ብሎ በራሱ ስልጣን አግዶ እገዳውን የጃፓን መንግስት ቢመጣም እንኳን አልቀበልም እያለ እኮ ነው ጎበዝ… ሰሚ የለም እንዴ በግዜር!?

ለዛሬ ላብቃ!
ቸር ለእናንተ!!!

↧

ሰንደቅ –የአውሮፓ ኅብረት መንግስትና ተቃዋሚዎችን እያነጋገረ ነው (በዘሪሁን ሙሉጌታ)

$
0
0

የፖለቲካ ምህዳር መስፋት፣
የ2007 ምርጫ፣ የታሳሪዎች ጉዳይ በአጀንዳነት ተነስቷል

በአውሮፓ ኅብረት የአፍሪካና የኢትዮጵያ ቋሚ አምባሳደር የኢትዮጵያ መንግስትንና የተቃዋሚ ፓርቲዎችን እያነጋገረ ነው። የኅብረቱ ቋሚ አምባሳደር አማካኝነት መካሄድ የጀመረው ውይይት በሀገሪቱ የፖለቲካ መህዳር መስፋት፣ በ2007ቱ ምርጫ፣ ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ የታሰሩ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች እንዲሁም በሀገሪቱ ስላለው የሰብአዊና የዴሞክራሲ መብቶች ዙርያ መሆኑ ታውቋል።

ባለፈው ዓመት የኅብረቱ ቋሚ አምባሳደር በመሆን የተሾሙት አምባሳደር ቻንታል ሔብሪች ኅብረቱን በመወከል በኢትዮጵያ ውስጥ የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች የበለጠ የሚከበሩበትን ገንቢ አማራጭ እያፈላለጉ ነው። በዚህም የአምባሳደሯ እንቅስቃሴ መሠረት የካቲት 26 ቀን 2006 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በመገኘት ከሌሎች የአውሮፓ ሀገራት አምባሳደሮች ጋር በመሆን በሀገሪቱ አጠቃላይ የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ዙሪያ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ውይይት አካሂደዋል። አምባሳደሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ውይይት ካካሄዱ ከአምስት ቀናት በኋላ በሀገሪቱ ካሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አንዱ ከሆነው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አመራር አባላት ጋር በጽ/ቤታቸው ውይይት አካሂደዋል።

በአውሮፓ ኅብረት የአፍሪካና የኢትዮጵያ አምባሳደር ቻንታል ሔብሪች ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ጋር በተወያዩበት ወቅት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩ ዴሞክራሲያዊ ሕጋዊ መሠረት የተከተለ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ላይ ቢሆንም፤ የበለጠ መሻሻል በሚገባቸው ቀሪ ስራዎች መወያየታቸው መዘገቡ ይታወሳል። በተጨማሪም በመጪው ዓመት የሚካሄደው ብሔራዊ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ በሚሆንበት ጉዳይ ላይ መወያየታቸው አይዘነጋም።

በተመሳሳይ ባለፈው ሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2006 ዓ.ም በአውሮፓ ኅብረት ጽ/ቤት የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራውና የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ከኅብረቱ አምባሳደር ቻንታል ሔብሪች እንዲሁም በአውሮፓ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድና የህንድ ውቅያኖስ ክፍል ኃላፊ ጋር ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱም በአጠቃላይ ፓርቲው እያደረገ ስላለው እንቅስቃሴና “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚለው የፓርቲው ክፍል ሁለት ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ላይ ማብራሪያ መጠየቃቸውን፣ የገዢው ፓርቲ የመሬት ፖሊሲ በሀገሪቱ መሬት የጥያቄ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ጥያቄ በመሆኑ በጥቅሉ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ጤናማ እንዳይሆንና መንግስታዊ የሙስና ሥርዓት እንዲጎለብት መደረጉን አርሦ አደሩም ከድህነት እንዳይወጣ በማድረግ ዋነኛ የዴሞክራሲ ማፈኛ መሆኑን ማስረዳታቸውን በውይይቱ የተሳተፉት አቶ ሀብታሙ አያሌው ለሰንደቅ ጋዜጣ ገልፀዋል።

ከዚህ ጎን ለጎን በእስር ስለሚገኙ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች የፓርቲው አመራሮችን በተመለከተ ማብራሪያ መስጠታቸውን፣ አቶ አስራት ጣሴ ስለታሰሩበት ምክንያት፣ ምርጫ 2007 ላይ ፓርቲው ስላለው አቋም፣ በኢትዮጵያ የመብት ጥሰቱ በምን ደረጃ ላይ እንዳለና በስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርት፣ የሚዲያ ሞኖፖሊና የግል ፕሬሱ ወዳከም ጋር የተያያዙ ችግሮች ዙሪያ ውይይት ማካሄዱን ከአቶ ሀብታሙ ገለፃ መረዳት ተችሏል።

በመጪው ሚያዚያ ወር ብራስልስ ላይ የአውሮፓ ኅብረትና የአፍሪካ ኅብረት በሚያካሂዱት የግራ ስብሰባ ላይ የአንድነት ፓርቲ ተወካይ ተገኝቶ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ ላይ ንግግር እንዲያደርግ ጥያቄ መቅረቡንም አቶ ሀብታሙ አያይዘው ገልፀዋል።

የአውሮፓ ኅብረት በገዢው ፓርቲ እና በተቃዋሚዎች መካከል ገንቢ ውይይት ተደርጎ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱ ከፍ ማድረግ አለበት ያሉት አቶ ሀብታሙ፣ ይህ ካልሆነ ግን በምስራቅ አፍሪካ አደገኛ ወደሆነ የፖለቲካ አለመረጋጋት ሊፈጠር እንደሚችል ገልፀዋል።

የአውሮፓ ኅብረት ከተለያዩ ሀገራት ጋር ሰፊ የልማት፣ የቴክኒክ ድጋፎች እንደሚያደርግ ይታወቃል። በምትኩ ሀገራቱ የዜጎቻቸውን ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲያከብሩ ከፍተኛ ግፊት ያደርጋል። ኢትዮጵያም የሎሜ ኮንቬንሽንን እ.ኤ.አ በ1975 ዓ.ም ከፈረመች ጊዜ አንስቶ ከኅብረቱ ጋር የልማት ትብብር መስርታለች፤ ኅብረቱም በአውሮፓ የልማት ፈንድ (European Development Fund) (EDF) እገዛ ያደርጋል። በተለይ በትራንስፖርት፣ በገጠር ልማት፣ ባልተማከለ የማኅበራዊ አገልግሎት ድጋፍ፣ በንግድ፣ በጾታ በሰብአዊ እርዳታ ድጋፍ እና በአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ላይ ሀገሪቱን ይደግፋል። የድጋፍ መጠኑም በቅርቡም ወደ 600 ሚሊዬን ፓውንድ ይደርሳል።

አዲሲቷ የኅብረቱ ቋሚ አምባሳደር በመንግስትና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል የተካረረውን ግንኙነት በማለዘብና ወደ ገንቢ ውይይት እንዲመጡ ማበረታታታቸው በበጎ ዓይን እየታየላቸው ነው። አምባሳደር ቻንታል ባለፈው ዓመት የሹመት ደብዳቤአቸውን ከማስገባታቸው በፊት በአውሮፓዊቷ ኪርጊስታን ሀገር የኅብረቱ ቋሚ አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል። የቤልጂየም ተወላጅ የሆኑት አምባሳደር ቻንታል በኢትዮጵያ የኅብረቱ ቋሚ አምባሳደር የነበሩትና ባለፈው ግንቦት ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን የሀገራቸውን ልጅ አምባሳደር ቫቪየር ማርሻልን ተክተው ወደ ኢትዮጰያ መምጣታቸው ይታወሳል።

↧

የተቃዋሚ ፓርቲዎች ለምርጫ 2007 ያላቸው ብቃትና ዝግጅትን በተመለከተ ከሰንደቅ የተወሰደ

$
0
0

አንድነት ን በተመለከተ
=============

አንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ወይም አንድነትን በተመለከተ የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነቱ ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው በበኩላቸው ተጠይቀው በቅድሚያ ፓርቲያቸው በምርጫ የሚያምን ፓርቲ እንደመሆኑ ሕዝቡ ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ ተጠቃሚ መሆን አለበት ብሎ እንደሚያምን ገልፀዋል። ለ2007ቱም ምርጫ ፓርቲያቸው የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶች እያደረገ መሆኑን፣ የመጀመሪያው ፓርቲው የቆመለትን ፖሊሲ ለሕዝብ ለማቅረብ በሚመች መልኩ የአማራጭ ፖሊሲ ትንተና እየተሰራ መሆኑን፣ የፓርቲው የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ ክለሳም ከምርጫው እና ወቅቱ ከሚጠይቀው ነባራዊ የፖለቲካ ሁኔታ ጋር ተብራርቶ ተዘጋጅቶ በቅርቡም ለሕዝቡ ለውይይት እንደሚቀርብና ጎን ለጎንም ማኒፌስቶ የሚያዘጋጅ ኮሚቴ ተዋቅሮ ዝግጅቱ እየተጠናቀቀ ነው ብለዋል።

የፓርቲውን ድርጅታዊ አቅም በማጎልበት በኩል አዲሱ የፓርቲው አመራር ከተመረጠ በኋላ በቀጣይ ሦስት ወራት ውስጥ በመላ ሀገሪቱ 34 ጽ/ቤቶች ይከፍታል ያሉት አቶ ሀብታሙ በቅርቡም በአዳማ፣ በሻሸመኔ፣ በሐዋሳ፣ በአዴት እና በደብረ ማርቆስ ከተሞች ላይ አዳዲስ ጽ/ቤት ተከፍተዋል ብለዋል። በአዲስ አበባም የፓርቲው የአዲስ አበባ ም/ቤት መቋቋሙን የጠቀሱት ሕዝብ ግንኙነቱ የአዲስ አበባው ም/ቤት 138 መቀመጫ እንዲኖረው በማድረግ ለአዲስ አበባ አስተደደር አቻ ቁጥር ም/ቤት መቋቋሙን ገልፀዋል። ከ23 ወረዳዎች ስድስት አባላት ተወክለው ም/ቤቱ መሰየሙን አስረድተዋል። በተመሳሳይ 24 ወረዳዎች ተመሳሳይ ም/ቤቶች ተመስርተው ወደ ቀበሌ ደረጃ እየወረድን ነው ብለዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የዳያስፖራው ተሳትፎ አግባብ ባለው ሁኔታ እንዲመራና ተጠያቂነት ያለው አሰራር እንዲሰፍን አዳዲስ የድጋፍ ቻፕተሮችን ይከፍታል ብለዋል። በቅርቡም የፓርቲው ልዑክ ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜን አሜሪካ እንደሚያቀና ገልፀዋል።

ጎን ለጎን ከዲፕሎማሲው ማኅበረሰብ ጋር ጠንካራ ግንኙነት ለመፍጠር ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ልዩ የመረጃ ምንጭ ሆኖ የሚያገለግል ድረገፅ መዘጋጀቱንም ጠቅሰዋል። በተያያዘም የምርጫ ሂደቱ አካል ነው ያሉት ፓርቲዎችን ወደ ውህደትና ትብብር የማምጣት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። የፓርቲውንም ልሳን ወደ ሕትመት ለመመለስ የማተሚያ ማሽን ተገዝቶ ከጥቂት ቀናት በኋላ ወደ ሕትመት ይገባልም ብለዋል።
አንድነት ፓርቲ የቤት ስራውን ሳይሰራ በገዢው ፓርቲ ተፅዕኖ ላይ ስንፍናውን አያላክክም የሚሉት አቶ ሀብታሙ ፓርቲያቸው ከወዲሁ የዕጩ ምልመላና ታዛቢዎችን ማደራጀት መጀመሩን ጠቅሰው ነገር ግን ገዥው ፓርቲ የፖለቲካ ምህዳሩን ማጨለሙን መቀጠሉ ግን ያሳስበናል ብለዋል። ገዢው ፓርቲ የአውራ ፓርቲ ሚናነቱን በመተው ወደ መድበለ ፓርቲ ስርዓት እንዲመጣ አሳስበዋል።

በቅርቡም የተጀመረው “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” የሚለውን ሕዝባዊ ንቅናቄ ለማካሄድ በ14 ዋና ዋና ከተሞች እንዲሁም በሦስት ተጓዳኝ አነስተኛ ከተሞች የምናደርገው እንቅስቃሴ ከወዲሁ ለመግታት እንቅፋቶች እየተፈጠሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዚሁ ሕዝባዊ ንቅናቄ ላይ በአዲስ አበባ ሕዝባዊ ውይይት ለማድረግ በኢትዮጵያ ስብሰባ ማዕከልና በመብራት ኃይል አዳራሽ ሕዝባዊ ውይይት ለማድረግ ከፍተኛ ችግር ማጋጠሙን ጠቅሰዋል። ይህም የፖለቲካ ምህዳሩ መጥበብና የጉልበት ፖለቲካ መቀጠሉን ማሳያ ነው ብለዋል።

የሀገሪቱ ስርዓት በምርጫ መለወጥ አለበት የሚለውን ሕገ-መንግስታዊ ድንጋጌ አክብረው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሀብታሙ፤ ፓርቲያቸው ለምርጫው በሙሉ አቅሙ ተዘጋጅቶ ሲያበቃ ገዢው ፖርቲ አፈናውን ከቀጠለ በዓለም ላይ ያሉትን ከ150 በላይ የሰላማዊ ትግል ስልቶች አሙዋጦ እንደሚጠቀሙ ገልፀዋል። ገዢው ፓርቲ የአፈና ስርዓቱን ከቀጠለ በሰላማዊ ሕዝባዊ እምቢተኝነት እናስገድዳለን ብለዋል። ይህንንም ከምርጫው ዝግጅት ጎን ለጎን ገዢው-ፓርቲ በሕገ-መንግስቱ በተቀመጠው መልኩ ስልጣን በምርጫ መያዝ ያለበት የሚለውን ድንጋጌ እየሻረ የአፈና ስልት የሚጠቀም ከሆነ ሕዝቡ እምቢ እንዲል በማድረግ የኢትዮጵያ አደባባዮች በሰላማዊ ታጋዮች እንዲሞሉ እናደርጋለን። ከዚህ ሁሉ በፊት ግን እኛ የውስጥ የቤት ስራችንን በመስራት ላይ ነን ብለዋል፡፡ በቀጣይ ሳምንት የኢህአዴግን ጨምሮ የሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የቅድመ-ምርጫ ዝግጅት ለመቃኘት እንሞክራለን።

መኢአድን በተመለከተ
=============

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅትም (መኢአድ) በአሁኑ ወቅት በክልል፣ በዞንና በወረዳ ያሉ መዋቅሮቹን መልሶ የማጠናከር (revisit) ከማድረግ ባለፈ ለ2007ቱ ጠቅላላ ምርጫ የተለየ የምርጫ ሰትራቴጂ አለማዘጋጀቱን የገለፁት ደግሞ የፓርቲው ፕሬዚደንት አቶ አበባው መሐሪ ናቸው። አቶ አበባው እንደ ሌሎቹ የፓርቲ አመራሮች የቀጣዩ ዓመት ምርጫ ዴሞክራሲያዊነት ሊለካ የሚችለው ገዢው ፓርቲ በሚከፍተውና በሚያጠበው የፖለቲካ ምህዳር ብቻ የተወሰነ መሆኑን ገልፀዋል።

እንደ አቶ አበባው ገለፃ፤ ፓርቲያቸው ሙሉ በሙሉ ወደ ምርጫ ሲገባ አባላቱ ከስራ እንዲፈናቀሉ፣ ገበሬዎችም መሬታቸውን የሚነጠቁበት ሁኔታ በመሆኑና በምርጫው ውስጥ ከሚደረገው የተሳትፎ ጥረት ጎን ለጎን አባላቱ ላይ የሚደርሰውን ማዋከብ ዋነኛውን የምርጫ ጊዜአቸውን እንደሚሻማ ነው ያስረዱት።

በአቶ አበባው እምነት፤ በምርጫው ጠንካራ ዝግጅት ለማድረግ በቅድሚያ የፖለቲካ ምህዳሩ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለማካሄድ ዋስትና የሚሰጥ መሆኑን የሚጠቅሱት አቶ አበባው፣ የፖለቲካ መድረክ ነፃ እስኪሆን ድረስ ሕዝቡን ለማንቀሳቀስ እንኳ አስቸጋሪ እንደሆነ ነው ያስረዱት።

በአሁኑ ወቅት ተዋህዶ በጋራ የመስራት እና በክልል ያሉ መወቅሮችን የማጠናከር ስራ ጎን ለጎን እየተካሄደ እንደሆነ አቶ አበባው የጠቀሱ ሲሆን፤ የፓርቲው የምርጫ ማኒፌስቶ ወቅታዊ ከማድረግ ባለፈ በመሰረታዊነት የሚለወጥ አለመሆኑን ነው የገለፁት። ዋናው ችግር ምርጫው መምጣቱን ተከትሎ አባሎቻችን ላይ የሚደርሰው ማዋከብ ነው ብለዋል።

የ2007ቱ ጠቅላላ ምርጫ ሥርዓት የመለወጥ አቅም ይኖረዋል የሚል ግምት ለመያዝ ከወዲሁ አስቸጋሪ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አበባው፤ የፖለቲካ ለውጥ ተለዋዋጭ በመሆኑ ጊዜውን መጠበቅ ነው ብለዋል። ለአሁኑ ግን ፓርቲያቸው ለምርጫው ሲል የተለየ ዝግጅች እያደረገ አለመሆኑን ጠቅሰው፤ ይልቁኑ ኢህአዴግ ለመድብለ ፓርቲ ሥርዓት መጠናከር ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት መክረዋል።

በአሁኑ ወቅት እየተባባሰ የመጣው የኑሮ ውድነት፣ የዋጋ ግሽበት ችግር፣ ሥራ አጥነትና ውስብስብ የሆነው የማኅበራዊ አገልግሎት ችግሮች ስር እየሰደዱ በመምጣታቸው የራሱ የኢህአዴግ ካድሬዎች በማጉረምረም ላይ መሆናቸውን አቶ አበባው አስረድተዋል። አሁን ካለው የተባባሰ ችግር አንፃር በ2007ቱ ምርጫ ኢህአዴግ በስልጣን ላይ ሊቀጥል የሚችለው ምርጫውን በዱላ ወይም በኃይል ከተጠቀመ ብቻ በመሆኑ ሁሉም ነገር በገዢው ፓርቲ እጅ ነው ብለዋል።

ኢዴፓን በተመለከተ
===========

የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲ ፓርቲ (አዴፓ) መድረክና ሌሎች ፓርቲዎች የሚያነሱዎቸውን አቤቱታዎች ያነሳል። አቤቱታዎቹን የሚያነሳባቸው የአገላለፅ መጠን (tone) እንደሌሎቹ ፓርቲዎች አይደለም። ይሄ ፓርቲ ከ1997ቱ ምርጫ በኋላ ከሌሎች ተቃዋሚዎች ዘንድ የተአማኒነት ጥያቄ ስለሚነሳበት የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ከሰጠው ሕጋዊ እውቅና በተጨማሪ ከሌሎች ፓርቲዎች ዘንድ የፖለቲካ እውቅና ይፈልጋል።
የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ወጣት ኤርምያስ ባልከው የሚያረጋግጡትም ይሄንኑ ነው። ፓርቲያቸው በቅርቡ ጉባኤ አድርጎ አዲስ አመራር በመረጠበት ወቅት ጉባኤው ካሳለፋቸው ውሳኔዎች መካከል በ1997ቱ ምርጫ የተፈጠሩ ስህተቶችን በማረምና ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለአዴፓ የፖለቲካ እውቅና የሚሰጡ ከሆነ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር አብሮ ለመስራት ዝግጁነት መኖሩን አስታውቀዋል።

አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ፓርቲው ቀደም ሲል በየክልሉ የነበሩ መዋቅሮቹን ለማጠናከር በሰሜን፣ በምስራቅና በደቡብ የሀገሪቱ አንዳንድ ክፍሎች መጠነኛ እንቅስቃሴ ከማድረጉ ባለፈ፤ አንድ ዓመት ለቀረው የ2007 ምርጫ አመርቂ እንቅስቃሴ እያደረገ አለመሆኑን ከፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ገለፃ መረዳት ይቻላል። በቀጣይ ጊዜአት የ2007 ምርጫ ማኒፌስቶ ዝግጅትና የዕጩ ምልመላ ስራዎች ለማካሄድ ገና በዝግጅት ላይ መሆናቸውን አቶ ኤርሚያስ ሳይገልፁ አላለፉም።

የ2007ቱ ጠቅላላ ምርጫ ስርዓትን የመለወጥ አቅም ይኖረዋል ብሎ ለመገመት አስቸጋሪ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ኤርሚያስ ፓርቲያቸውን ግን ኅብረተሰቡ ውስጥ ካሉ ስር የሰደዱ ችግሮች አንፃር ሕዝቡ በገዢው ፓርቲ ላይ ካለው ቅሬታ አንፃር ጠንካራ ተፎካካሪ የመሆን እድል እንዳለው ገልፀዋል። ፓርቲው የመራጬን ልብ ለመግዛት የሚያዘጋጀው ማኒፌስቶ እንዳለውም አቶ ኤርሚያስ የጠቀሱ ሲሆን፤ በተለይ ፓርቲያቸው ኢህአዴግን ጨምሮ አዴፓ በሚሳተፍበት የጋራ መድረክን ደንብ በማሻሻል ጭምር በ2007 ምርጫ የነቃ ተሳትፎ እንደሚያደርግ ጠቅሰዋል።

ለምርጫው አጀንዳ የሚሆኑ በርካታ የኅብረተሰቡ ችግሮች መኖራቸውን ያወሱት አቶ ኤርሚያስ የአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ አፈፃፀም፣ የኑሮ ውድነቱ፣ የኢኮኖሚ ጥያቄዎችና የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች አለመከበር ጨምሮ በርካታ አጀንዳዎች ተዘርዝረው የሚቀርቡበት መሆኑንም ጠቁመዋል።

መድረክን በተመለከተ
============

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) የ2007ቱን ምርጫ በተመለከተም አመርቂ ዝግጅት እያካሄደ አይመስልም። የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ አባልና የሕዝብ ግንኙነት አባል አቶ ጥላሁን እንዳሻው ግን መድረክ “የዝግጅት ችግር የለበትም” ይላሉ። የመድረክ መሰረታዊ ችግር የፖለቲካ ምህዳሩ መጥበብና ዜጎችን አንድ ለአምስት የሚጠረንፈው የገዢው ፓርቲ “የምርጫ ሠራዊት” የምርጫ ስትራቴጂ ነው ብለዋል።

መድረክ እንደ መድረክ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ገዢው ፓርቲ ውጤታማ ሆኜበታለሁ የሚለውን “የምርጫ ሠራዊት” ስትራቴጂ ሊያስለውጥ ወይም ሊፈትን የሚችል አዲስ ስትራቴጂ ይዞ መቅረብ አልቻለም። ፓርቲው ምርጫው ሊካሄድ የአንድ ዓመት ጊዜ ያህል ቢቀረውም በፓርቲ ደረጃ የምርጫ ስትራቴጂና እቅድ አላዘጋጀም። ከዚህ ይልቅ አቶ ጥላሁን ቀደም ሲል ይነሱ የነበሩ አቤቱታዎችን አሁንም የማስተጋባትን ስልት ቅድሚያ የሰጡት ይመስላል። በአቶ ጥላሁን ገለፃ ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና የተወዳዳሪነት መንፈስ እንዲኖረው ገዢው ፓርቲ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል። የአቶ ጥላሁን አቤቱታ (Old Complain new election) እንደሚባለው የ2007ቱ ምርጫ በሀገሪቱ የምርጫ ታሪክ ለአምስተኛ ጊዜ ቢካሄድም ምርጫውን በተመለከተ መድረክ አዲስ ነገር መፍጠር እንዳልቻለ አመላካች ሆኗል። በመድረክ በኩል የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት ረገድ እንደ ፓርቲ የቀየሰው ስልት እንደሌለም ከአቶ ጥላሁን ገለፃ መረዳት ይቻላል። በእሳቸው አገላለፅ ኢህአዴግ የዘጋውን የፖለቲካ ምህዳር ለማስከፈት ከፓርቲው ይልቅ በአግባቡ ያልተደራጀው ሕዝቡ እንዲወጣው የሚፈልጉ ይመስላል።

ከዚህ በተጨማሪ “የሕዝብ ድጋፍ ችግር የለብንም” የሚሉት አቶ ጥላሁን ሕዝብ መድረክን በደፈናው ይደግፋል ከማለታቸው ባለፈ የሚደግፋቸውን ሕዝብ በአግባቡ ስለማደራጀታቸው የሰጡት ማረጋገጫ የለም። መድረክ እንደ መድረክ ሕዝብን ከማደራጀት ይልቅ የብሶት ጋጋታ በገዢው ፓርቲ ላይ ከማጧጧፍ ባለፈ ጠንካራ ሕዝባዊ መደላደል የፈጠረ አይመስልም። የሕዝባዊነት መደላድል ለመፍጠር የሄደበት እርቀት ገዢውን ፓርቲ ለመውቀስ ከሄደበት እርቀት አንፃር ሊመጣጠን የቻለ አይመስልም። ገዢው ፓርቲ በስልጣኑ ለመቀጠል ሲል ይፈጥራቸዋል የሚባሉትን የአስተዳደር፣ የፖለቲካ የሕግና አልፎ አልፎ ሕገወጥ የኃይል እርምጃዎችን በማጋለጥ ብቻ የፖለቲካ ትግል ማድረጉ ውጤታማ እንደማያደርግ በቂ ግንዛቤ የተያዘ አይመስልም።

በ2007ቱ ምርጫ የአባይ ግድብ ለምርጫ ፍጆታ መዋል የለበትም ሲሉ አጠንክረው የተከራከሩት የመድረክ ተወካይ አቶ ጥላሁን ፣ ግድቡ የኢህአዴግ ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያውያን የባንዲራ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። መድረክ በ2001 ባዘጋጀው ማኒፌስቶ ውስጥ አባይን እና ሌሎች ድንበር ተሻጋሪ ተፋሰሾችን ለመገደብ አቅዶ እንደነበርም ጠቅሰዋል።

መድረክ ከኢህአዴግ የሚለይባቸው ሌሎች የፖሊሲ ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ዋነኛ አጀንዳው የአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መክሸፉን፣ በኑሮ ውድነቱ ሳቢያ በኅብረተሰቡ ላይ እያደረሰ ያለው ጫና እንዲሁም ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር የተያያዙ ማኅበራዊ ችግሮች እንዲሁም በየደረጃው ያሉ አስከፊ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አጉልቶ እንደሚያወጣ ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት እየተገነቡ ያሉትም የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ከኅብረተሰቡ የዕለት ተዕለት ገቢና ጥቅም ጋር እየተገለፁ አለመምጣታቸው፤ በዚያው መጠን ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እያስከተሉ መሆኑን ሕዝቡ እየተገነዘበ የመጣበት በመሆኑ የመድረክ ትኩረት በሕዝቡ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካና ማኅበራዊ ችግሮች ላይ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልፀዋል። ለሁሉም የምርጫ ሂደቱ ስኬታማና ውጤታማ ሊሆን የሚችለው ግን ኢህአዴግ የዘጋውን የፖለቲካ በር ሲከፍት እና ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ታማኝ ሆኖ ሲገኝ ብቻ ነው ብለዋል። “ተዘግቷል” ያሉትን የፖለቲካ በር ለማስከፈት ግን ፓርቲያቸው የነደፈው ስልት እንደሌለ በደፈናው “ሕዝቡን ይዘን” ከማለት ባለፈ ምንም አይነት ዝግጅት እንደሌለ ከአጠቃላይ ገለፃቸው መገንዘብ ይቻላል።

በሙሉ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ !

↧

በሐረር ክልል ሕዝብ ላይ የደረሰውን ከፍተኛ ጉዳት አንድነት በቸልታ አይመለከተውም!! –ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

$
0
0

የካቲት 30 ቀን 20006 ዓ.ም በታሪካዊቷ የሐረር ከተማ በጀጎል ሸዋበር በደረሰው ቃጠሎ እና ከዚያም በኋላ የክልሉ ፖሊስ በወሰደው እርምጃ በዜጎች ላይ ጉዳት መድረሱ የፓርቲያችንን አመራሮች፣ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጪ ያሉ አባላትና ደጋፊዎችን በእጅጉ አሳዝኗል፡፡

ምንም እንኳን የቃጠሎው መንስኤ ተጣርቶ ይፋ ያልተደረገ ቢሆንም በጀጎል ሸዋ በር እየደረሰ ያለው ተደጋጋሚ ቃጠሎ ድንገቴ ነው ለማለት የሚያስደፍር አይደለም፡፡ በተለይም በየካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም የተነሳውን ቃጠሎ በተገቢ ፍጥነት ለመቆጣጠር የክልሉ መንግስት ፍላጎት ያልታየበት መሆኑ፤ ይልቁንም ግሬደር መኪና አስጠግቶ ቦታውን ለማፅዳት መሞከሩ አጠያያቂ ነው፡፡ የክልሉ መንግስት ቃጠሎውን ለመቆጣጠር ተገቢውን ሁሉ ባለማድረጉ የጉዳቱ ሰለባ የሆነው ህዝብ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖበት ክፉኛ እንደ ተማረረ በዚሁ ምክንያትም ቁጣ ተቀስቅሶ ፖሊስ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ጉዳት ማድረሱንም በክልሉ የሚገኙ የፓርቲያችን አመራሮች መረጃውን አድርሰውናል፡፡

በመሆኑም ፓርቲያችን የክልሉ መንግስት ትክክለኛው የቃጠሎ መንስኤ በአስቸኳይ ተጣርቶ ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግ፤ በማንኛውም ምክንያት ኃላፊነታቸውን በብቃት ያልተወጡ የመንግስት ኃላፊዎች በግልፅ ለተጠያቂነት እንዲቀርቡ፤ የክልሉ ፖሊስ በህዝቡ ላይ የወሰደው የኃይል እርምጃ በገለልተኛ አካል ተጣርቶ ይፋ እንዲደረግ፤ የክልሉ ፖሊስ በወሰደው የኃይል እርምጃ ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች ብዛትና የጉዳቱ መጠን በአስቸኳይ ለህዝብ ይፋ እንዲደረግ ተገቢ ህክምና እና ካሳ እንዲከፈላቸው፤ ይህንን የፈጸሙ አካላትም ለፍርድ እንዲቀርቡ በአጽንኦት እንጠይቃለን፡፡

በአንድነት ፓርቲ በኩል ይህንኑ በህዝብ ላይ የደረሰ ጉዳት ለማጣራትና ለመከታተል በስራ አስፈጻሚው አስቸኳይ ግብረ ኃይል ተቋቁሟል፡፡ ግብረ ኃይሉ ወደ ቦታው በማቅናት ጉዳዩን ካጣራ በኋላ የደረሰበትን መረጃ እና በፓርቲያችን የሚወስደውን ተጨማሪ አቋም በተመለከተ በቅርቡ ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር
መጋቢት 4 ቀን 2006 ዓ.ም

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)UDJ-SEAL

↧
↧

2006 ዓ/ም የኢትዮጵያውያን የሰማእታት ዓለም አቀፍ አከባበር

$
0
0

የ2006 ዓ/ም የኢትዮጵያ ሰማእታት ቀን በየካቲት ወር 12 ሐገሮች በሚገኙ በ27 ከተሞች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተከናውኗል። የአከባበሩም ስነሥርአት በሰላማዊ ሰልፍ፤ በሕዝባዊ ጉባኤ፤ ወይም በጸሎት ነበር። አዲስ አበባ የተከናወነው የካቲት 12 አደባባይ ሲሆን የአበባ ጉንጉን ኃውልቱ ሥር በማስቀመጥና ንግግር በማሰማት ነበር።

እንደሚታወቀው፤ የሰማእታት ቀን በየዓመቱ የሚከበረው፤ በየካቲት 19-21፣ 1929 ዓ/ም ፋሺሽቶች አዲስ አበባ በሶስት ቀኖች ውስጥ 30፣000 ሰው ጨፍጭፈው ስለ ነበር ነው። በተጨማሪም፤ በኢጣልያ አሰቃቂ የወረራ ዘመን አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ተሰውተዋል፤ 2000 ቤተ ክርስቲያኖችና 525000 ቤቶች ወድመዋል። ብዙ የኢትዮጵያ ንብረት ተዘርፎ አሁንም በቫቲካንና በኢጣልያን መንግሥቶች እጅ ይገኛል። እጅግ የሚያሳዝነው ጉዳይ፤ ለዚህ ሁሉ ግፍ ኢትዮጵያ ተገቢውን ፍትሕ አለማግኘቷ ነው።

ክብረ በዓሉን በማዘጋጀት እንዲሁም በስነሥርዓቱ በመሳተፍ ለተባበሩት ሁሉ ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ – የኢትዮጵያ ጉዳይ ምሥጋናውንና አክብሮቱን በትሕትና ይገልጻል።
ክብረ በዓሉ የተከናወነባቸው ሐገሮችና ከተሞች፤ (1) በኢትዮጵያ (አዲስ አበባ)፤ (2) በአሜሪካ (ዋሺንግተን ዲ.ሲ፤ ኒው ዮርክ፤ ዳላስ፤ ሒዩስተን፤ አትላንታ፤ ሲያትል፤ ሎዛንጀለስ፤ ቦስተን፤ ታምፓ፤ ማያሚ፤ አውሮራና፤ ላስቬጋስ)፤ (3) ኢጣልያ (ሮም)፤ (4) ጀርመን (ኮሎኝ)፤ (5) ስዊድን (ስቶክሆልም)፤ (6) እሥራኤል (ኢየሩሳሌም፤ ቴል አቪቭ)፤ (7) አውስትራሊያ (አደሌይድ፤ ሲድኒ)፤ (8) ካናዳ (ቶሮንቶ፤ ቫንኩቨር)፤ (9) ታላቋ ብሪታኒያ (ለንደን)፤ (10) ደቡብ አፍሪካ (ጆሐንስበርግ፤ ፕሪቶሪያ)፤ (11) ስዊትዘርላንድ (ጅኒቫ)ና (12) ጃሜይካ (ኪንግስተን)።

የአንዳንድ ከተሞች የክብረ በዓሉ ተሳታፊዎች፤ በዓለም አቀፍ ሕብረት አማካኝነት የተዘጋጀውን አቤቱታ ለኢጣልያንና ለቫቲካን ኤምባሲዎች አቅርበዋል።
ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ – የኢትዮጵያ ጉዳይ የሚታገልባቸው መሠረታዊ ዓላማዎች፤ (ሀ) ቫቲካን የፋሺሽቶች ተባባሪ ስለ ነበረች የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ፤ (ለ) ኢጣልያ ለፈጸመችው ግፍ ተገቢውን ካሣ እንድትከፍል፤ (ሐ) በይዞታቸው የሚገኘውን የተዘረፈ የኢትዮጵያ ንብረት ኢጣልያና ቫቲካን እንዲመልሱ፤ (መ) የተባበሩ መንግሥታት ድርጅት በኢትዮጵያ ላይ የተፈጸመውን የፋሺሽት ግፍ በይፋ እውቅና እንዲሰጥና (ሠ) በቅርቡ የተመረቀው የግራዚያኒ ኃውልት እንዲወገድ ናቸው።

ኢትዮጵያ የሚገባትን ፍትሕ እንድታገኝ የሁላችንም ሕብረት አስፈላጊ ነው። ቫቲካን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ ዓለም አቀፍ አቤቱታውን ለመፈረም www.globalallianceforethiopia.org መመልከት ይቻላል።

“ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሀ ሐበ እግዚአብሔር”

↧

አሜሪካ የበለጠ ትናገር! ከጸጋዬ ገ.መ. አርአያ

$
0
0

“ ነፃነቴን ካልሰጣችሁኝ ሞትን እመርጣለሁ”
ፓትሪክ ሔንሪ Give me Liberty or Give me Death

ፍሬደሪክ ዳግላስ (1818- 1895) ከባርያ እናትና ከነጭ አባት የተወለደና ራሱም ቢሆን በቦልቲሞር (ሜሪላንድ) የቤት አሽከር ሆኖ የቆየ ሰው ነበር። አንድ ማለዳ ጁላይ 4 ቀን 1852 ን ተንተርሶ (አንተርሶ) በሮቼስተር ከተማ (ኒውዮርክ) ንግግር እንዲያደርግ ጥሪ ይደርሰዋል። ደብዳቤው ሲደርሰው እንደ እብድ ከራሱ ጋር መነጋገር ያዘ። መቸም አንዳንድ ጊዜ እንዲህ ያለ ለማመን የሚከብድ አጋጣሚ ሲመጣብህ ናላህ ይበጠበጣል። ፍሬደሪክ ዳግላስም “በእርግጥ ይህ ደብዳቤ ለእኔ የተጻፈ ነው? የተቀባይ ስምና አድራሻ ስሕተት ተፈጽሞ ይሆን?” ሳይል አልቀረም። ዳግላስ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ጭንቅላቱን ሲበጠብጥ ቆይቶ ትንሽ አረፍ አለ። ሲነቃ ይኸ ዕድል እንዳያመልጠው ፈለገ። ይልቁንም የሚናገርበት ርዕስ መጣለት። “ በመሰረቱ እኔን ባርያውን በዚህ በዓል ላይ እንድገኝ- ለዚያውም ተናጋሪ መሆኔን ሳስበው ይህ ሁሉ ግብዝ- የግብዝም ግብዝ ነው አለ። ይበልጥ ደግሞ ለተሰብሳቢው ስለጁላይ 4 (ነፃነት በዓል) እንድናገር እኔን ባርያውን መጋበዛቸው ሌላው ግብዝና ነው ” አለ። ለማንኛውም ንግግሩን አዘጋጀ። በዚያ ወቅት በሮቼስተር ከተማ ያደረገው ንግግር እስከ ዛሬ ድረስ ከዓለም ታላላቅ ዲስኩሮች አንዱ ለመሆን በቅቶአል። “ጁላይ 4 ቀን ለመሆኑ ለባርያው ምኑነው? What to the Slave is the Fourth of July?

ዛሬ ከብረት በከበደ ክንድ ኢትዮጵያን እየገዙአት የሚገኙት ጌቶች- አዳዲስ መሳፍንት- አዳዲስ መኳንንት፣ አዳዲስ ዲታዎች…የንግስ በዓል ከሳምንታት በኋላ ይከበራል። (በዩጐዝላቩ ጂላስ The New Class, ወይም ከሮማውያን ዘመን አንስቶ Nouveau Riche ቀላል ድግስ አያውቁም። ስለዚህ ጉንበት 20 ቀን በታላቅና ታይቶ በማያውቅ ድምቀት ይከበር ዘንድ ዝግጅቱ እየተሟሟቀ ነው። አገር ያፈራው ትልልቁ የሐረር ሰንጋ፣ ወደል ወደል የሚያክለው የወለጋ ላታም በግ ወዘተ ተመርጦ ተመርጦ ይቀርባል። ሻምፓኙ፣ ውድ ውዱ አይሪሽ መጠጥ- ዊስኪ፣ ድራንቡዬ፣…የፈረንሳይ ኮኛኮች፣ ምርጥ ወይን ጠጆች..ያልፍላቸዋል። ምንም ማጋነን የለበትም። ጫካ ውስጥ በነበሩበት ጊዜ እንኳ ለድግስ ስንትናስንት ሚሊዮን ብር ሲያወጡ እንደነበረ ከጉያቸው የወጣው ጠንካራ ኢትዮጵያዊ…ገብረ መድኅን አርአያ ገልጦታል።

“ኑና ጉንበት 20ን አብረን እናክብር” ተብለው የተጠሩ ወይም እንጠራለን ብለው ቀኑን እንደወላድ እየቆጠሩ- የራቀባቸው ሰዎች የሉም አትሉም። እናንተም እንደኔ። ከውጭ የሚጋበዙ በርካታ ሰዎች ይኖራሉ። አዳራሾች-ሆቴሎች- በየደረጃው… ላይበቁ ነው። እሸሸ ገዳሜው፣ አስረሽ ምቺው ደግሞ የሚጠበቅ ነው። ስለገዢዎቻችን ሀብትና ንብረት ያልተባለ ነገር የለም። ይኸ ደግሞ የሞራሉን ቁልቁለት ምንኛ እንደ ተያያዙት ስም እየጠቀሰ መረጃ የሚሰጠንን ውስጥ አወቅ ኢየሩሳሌም አርአያን ማድነቅ እወድዳለሁ። በሽምግልናና ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ በሚገባቸው ዕድሜ የእኝኝ ብላ ባዝራዎች፣ አንድና ሁለት (በቀን) የማይበቃቸው የወንድ መለኮኖች አሉባቸው። ከዚህ ተራ ውስጥ ሁለት ሰዎችን ብቻ (በረከተ-መርገም ስምዖንና ስዬ አብርሃ) ነፃ ያወጣቸው ደግሞ ተስፋዬ ገብረ-አብ ነው። ስለሆነም ዳንኪራውና ስድ የሆነው በዓል የሚጠበቅ ነው። እኛም የኢትዮጵያ ጉስቁሎች የሌላ ሕዝብ በዓል በሥነ ሥርዓት መጠበቅ አለብን። የበዓሉን መንፈስ ማደፍረስ፣ ማደናቀፍና ማቃወስ በአሸባሪነትና በመሳሰለው አንቀጽ ያስቀጣል። አዎን ጉንበት 20 ቀን የድግሦች ድግሥ፣ አውራ በዓልና የድግሦችና የበዓሎች ሁሉ እናት ናት። ማን ያውቃል? ድሮ ጃንሆይ አጤ ኀይለ ሥላሴ ሐምሌ 16ን “የትዮጵያ የልደት ቀን” እንዳሉአት እነዚህ አዳዳሶቹ መሳፍንትም ጉንበት 20ን “እውነተኛው የኢትዮጵያ ናጽናት ቀን” ቢሉት አይደንቀኝም። ( ብቻ ማን ነበር- የአንዱ ሕይወት የሌላው መርዞ ነው- ያለው?)

በአገራችን የድግስ ነገር ሲነሳ ትንሽ የማስታውሳቸው ነገሮች አሉ። በአጤው ጊዜ ጃንሆይ የተወለዱበት (ሐምሌ16) እንዲሁም የነገሱበት (ጥቅምት 23) ይከበሩ ነበር። ለኢትዮጵያ ባሕልና ፖለቲካ እንግዶች የሆናችሁ ወጣቶች ምናልባት አታውቁት ይሆናል እንጂ በክብርም ቢሆን ቤተ መንግስት ስትጠሩ ግርግሩ ብዙ ስለሆነ ትንሽ ጨፈቃ ትቀምሳላችሁ። እንጀራው በእግር የተቦካ ነው ይባላል። ለማንኛውም “የንጉስ በረከት” አይናቅም ትባላላችሁ። (ይህንን የበለጠ ለማወቅ ፍቅር እስከ መቃብርን ያነብቡአል) ወደኋላ ጊዜ የሐምሌ 16 በዓል አከባበር ለአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ተሰጥቶ ነበር።

የድግስ ነገር- በመንግስት ሰፈር- ብዙ ምልኪ አለበት። ስለ ጃንሆይ መንግስት አወዳደቅ ብዙ ቢባልም ለጊዜው አንዱን አነሳለሁ። አንዳንድ ሚኒስትሮች እጅግ ከቅብጠትም ባሻገር ስለሄዱ ክራር ይዘው ወደ መሸታ ቤት መሄድ አብዝተው ነበር። የዛሬዎቹ ከእነዚያ ጋር ባይወዳደሩም ትንሽ ትንሽ ሕዝብንና አኗኗሩን ወደ መርሳቱ ደርሰው ነበርና ሌላው ቀርቶ ከመሳፍንቱ አንዱ የነበሩት ጄኔራል ዐቢይ- “አውቀን እንታረም” የሚል መጽሐፍ ደርሰው ነበር። ጠንቃቃው ጄኔራል “አውቀን ካልታረምን ሌላው ቀርቶ ሬሳችን እንኳ የወደቀበት አይታወቅም” ብለው ነበር። አዎን አርማጌዶን በዓለም ፍጻሜ ላይ የሚከሰት ሳይሆን ያልታሰበ የእልቂት መውረድም አርማጌዶን ሊባል ይችላል። ያ ወቅት የሞራል ድቀት ሥጋና ደም ገዝቶ የሚታይበት፣ ሕዝብ ሲያልቅ አንዳንድ ሹማምንት መንደላቀቅ ያበዙበት ነበር። ደርግ ጃንሆይን ከሥልጣን ሲያወርድ “ሕዝብ በሺህ ቤት ሲረግፍ እነሱ በእሸሸ ገዳሜ ተጠምደው…” እያለና የቀለጠ ድግስ በቴሌቪዥን እያቀረበ ነበር። ድግስ….

ደርግ ራስዋ በራስዋ ያመጣችው ጣጣም አለ። ወደ ሥልጣን የመጣበትን ቀን ለማክበር ብልጭልጩንም ማናምኑንም ሰልፉንም…ሲያበዛ የእንግሊዝ ጋዜጠኞች በሁለት መቶ ሺህ ዶላር ውስኪ ሸጥን አሉና…የደርግ መሰላል ወደታች ብቻ የሚያወርድ ሆነ። ድግስ እየተኮነነ መጣ። ድግስ እየተጠቀሰበት ወረደ። ሁለት መቶ ሺህ ሕዝብ በረሃብ አለቀ ብሎ ተሳለቀ ተባለ። በራሱ ጊዜ ዘጠኝ ሚሊዮን ሕዝብ ተርቦ ውስኪ ተራጩ ተብሎ ለወያኔ ፕሮፖጋንዳ ተመቸ። እዚህ ላይ ያነሳሁት የጉንበት 20 አከባበር ያንኑ እድል ይከተል ይሆናል- ይከተላልም- ቁልቁለቱን ጀምሮአል በሚል ነው። ድግሶች በሦስቱ መንግስታት- የሥልጣን መልቀቂያ ጊዜ ምልክቶች- ብልሽትሽቱ የወጣ መንግስት ማክተሚያ ወቅቶች ሆነው አይተናቸዋል። ( ሁሉም የእጁን ያገኛል- ብድሩን ወይም ብድራቱን ተከፈለ- በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀርም የሚባል አነጋገር ያለ ይመስለኛል። የእንግሊዝኛው ፈሊጥ ግን Poetic Justice ይለዋል) “ያርግላቸው!” አሜን ያድርግላቸው!!

ደርግ የተወነጀለበት 200ሺህ ዶላር ዛሬ አንድ ባለ ጊዜ ወያኔ ለልጁ ልደት ከሚደግሰው በታች ነው። በ1997ዓ.ም አባዱላ ገመዳ ለልጃቸው ዘኪያስ አባዱላ 24ኛ ልደት በዓል የ100ሺህ ዶላር ኮብራ ዘመናዊ መኪና በስጦታ መልክ አበርክተዋል። በ1994ዓ.ም በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ 14ሚሊዮን ሕዝብ ለረሃብ ተጋልጦ ነበር። መለስ ዜናዊ ከ10 ዓመት በኋላ “በቀን ሶስት ጊዜ ትበላላችሁ” ባሉበት ዓመት መሆኑ ነው። የመለስ ዜናዊ መንግሥት ለተራቡት ወገኖች ደንታ አልነበራቸውም። በድርጅታቸው የተፈጠረው ቀውስ ላይ በማተኮርና ለእርሳቸው የሥልጣን ዕድሜ ማራዘሚያ ሲሉ “ተሃድሶ” ብለው ለሰየሙት ቱማታ 280ሚሊዮን ብር ባጀት መድበው ካድሬዎቻቸውንና ተከታዮቻቸውን በድግስና በውስኪ ያምነሸንሹ ነበር። በዛው ዓመት ልጃቸው ሠማሃል መለስ የልደት በዓልዋን በግዮን ሆቴል ዳስ ተጥሎ አክብራለች። ለኬክ ብቻ ግማሽ ሚሊዮን ብር ነበር ወጪ የተደረገው። የመለስ ልጅ ልደትዋን በምታከብር እለት በግዮን ሆቴል ደጃፍ በርካታ በረሃብ የገረጡ ወገኖች የሚላስ የሚቀመስ አጥተው ወድቀው ነበር።

ስለ ድግስ ዝርዝር ለመጻፍ ፍላጐቱ የለኝም። ደግሼም አላውቅም። መንግስት ሲቀናጣ፣ እሸሸ ገዳሜው ልክ ሲያጣ፣ የሞራል ድጡ መጠነ ቢስ ሲሆን፣ ሰብአትካትን- ሰዶምና ገሞራን ወይም የጥፋት ውሃን ዘመን ሊያመለክተን ይችላል። ራስ ተፈሪዎች “ባቢሎን” ይሉታል። እንዲያውም በቀድሞው መንግስት በጠቅላይ ሚኒስቴር ሚኒስትር የነበሩት ዶክተር ሥዩም ሐረጐት The Bureaucratic Empire, Serving Emperor Haile Selassie በሚለው መጽሐፋቸው ያነሱት አንድ ነጥብ ስለድግስና ስለመሳሰሉት ጉዳዮች ነበር። ኮረኮረኝ። ሥዩም ሐረጐት እንደጻፉት የቀ.ኀ.ሥላሴ ባለስልጣኖች የታሰሩት ጠጅ ለመጣል ምቹ ቅዝቃዜ በነበረው ሥፍራ ነበር። ከላይ የደርግ አባላት ስብሰባ ሲካሄድ፤ ሑካታ ሲፈጠር፣ ጭብጨባ ሲበዛ ወዘተ በእሥረኞቹ ላይ ይፈጠር የነበረውን የመንፈስ ጭንቀት ይነግሩናል። አሳሪዎች የእሥረኞች ሥቃይ ሊታያቸው ከቻለ በእርግጥ “ሰው” የመባል ሙሉ ባሕርይ አላቸው ለማለት ይቻላል። (የደርጉን ዘመን ግፍ ለማውራት የምደፍርበት ወኔ የለኝም። ራሳቸውን እየቀደሱ በሌሎች ግለሰቦች ላይ ከሚደነፋፉም ጋር ጠበል የምጠጣ አይደለሁም። አንድ ነገር ላይ ከተስማማችሁልኝ ደርግ በውሃ አጥምቆ ቢሆን ወያኔ ይኸውና በእሳት እያጠመቀ ይገኛል። የጥምቀቱ ተቀባይ ደግሞ መላው ወገኔ ነው።)

የአሜሪካ መንግሥት ባለፉት ቀናት የኢትዮጵያን ድንኳን ገለጥለጥ አድርጐ የአገሪቱን የሰብአዊ መብት አጠባበቅ፣ የፖለቲካ እሥረኞች አያያዝ፣ በገጠር ያለውን ብሔረሰቦችን የመከፋፈል መንግስታዊ ጫናና ወንጀል አሳውቆናል። አሳውቆልናልም። በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ሰማንያ ሺህ የፖለቲካ እሥረኞች አሉ። ከእነዚህም መካከል ስድሳ ከመቶው አእምሮ እስከ መሳት መድረሳቸውን በምስክርነት አቅርቦልናል። ዝርዝሩ ብዙ ነው። ታላቅ ወንድም (የተጠጋኸው ትልቅ መንግሥት በፖለቲካው ቋንቋ ቢግ ብራዘር ይባላልና) ምናልባትም የእሥረኛውን ቁጥር ቀንሶት ይሆናል እንጂ በኢትዮጵያ እየኖረ ወያኔንና ትውልደ ወያኔ ያልሆነ ለመሆኑ ያልታሰረ – አለዚያም እሥራት የማያስጨንቀው ማነው? ብለው የሚጠይቁ የትየለሌ ናቸው። ያልታሰሩ የሚመስላቸው ሰዎች ደግሞ የጥርስ ችግር እያለው ሕመም ሳይሰማው በመጨረሻ ላይ አምስትና ስድስት ጥርሶቹ ሲረግፉለት ለቃቅሞ ወደ ሐኪም ቤት እንደሚሮጥ ሰው ናቸው።

እንደሁም ልጆቻቸው ወይም የአገር ወጣቶች በነቂስ እየታረዱ ኅዘኑ ከቤታቸው የማይገባ፣ የቤተሰብ አውራ በባለቤቱ ፊት ታስሮ ሚስት ስትነወር፣ ንብረቱ ሲድፋፋ፣ ጐታው ሲደፋ ልቅሶውና ዋይታው ከጆሮአቸው የማይደርስ ጐረቤት ወገናችን አለ። የድንጋይ ልብ የገባለት። አንዳንድ የማውቃቸው ሰዎች – ጐይትኦም ብቻ ሳይሆን- ደባልቄና አምበርብርም ጭምር – ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ ሄደው ሲመለሱ ተመሣሣይ ትዝታ ይዘው ይመጡላቸዋል። አዲስ አበባ ውስጥ የሚሠራው የእድገት ምልክት የሚገለጥ አይደለም። የአለቃ ደስታና የተሰማ ግጽው መዝገበ ቃላት በቂ ቃላት የላቸውም። “እንዲያውም በእንግሊዙ ንገረኝ” ትለዋለህ። አንተም አሿፊ እሱም አሹዋፊ ትባላላችሁ። ጓድ መንግሥቱ ኅይለማርያምን ብጠቅስ እንደማትቀየሙኝ ተስፋ አደርጋለሁ። በኢትዮጵያ ራዲዮ በሠራሁባቸው ዓመታት አንድ ቀን ስለ ራዲዮ አሠራር ስንገልጽላቸው ምርር ትክን ብለው “ ዘፈኑና ጭፈራው አልበዛም ወይ? ለመሆኑ ወገኖቻችን በጠላቶቻችን ሰይፍ እየተመቱ፣ አብዮታዊ ሠራዊታችን በግራም በቀኝም – በሰሜንም በምሥራቅም፣ በመሐል አገር ደግሞ በአምስተኛ ረድፈኞች ጓዶቻችን ሁሉ እተየረሸኑ..እያለቅን አይደለም ወይ? ኢትዮጵያ ራስዋ እንደ አንድ ልቅሶ ቤት መታየት የለባትም ወይ? እንዴት ነው በዚህ ሁሉ ልቅሶኛ ላይ እሸሸ ገዳሜ ዘፈን ለማሰማት ፈቃድ የምትፈልጉት? ፈቃድ የሚጠየቅበት አይደለም። እንደየስሜታችሁ ነው። ደስ ካላችሁ ዝፈኑ። አስዘፍኑ። አለዚያም ዳኝነቱ የእናንተ ነው” ብለው ነበር። አንዱ ሲደሰት ሌላው ያዝናል። ዓለም ጉራማይሌ!

ሕይወት ከዚህ መሠረታዊ አመለካከት ይጀምራል። ግን ከአለቃችን ንግግር ውስጥ ማንንም ሊነካ የሚገባው ለአገራቸው ባበረከቱት ቅንና ሕጋዊ አገልግሎት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥረው ወደ ወህኒ ዓለም የተወረወሩትን ሰማንያ ሺህ ኢትዮጵያውያን በዓይነ ሕሊናችሁ ጐብኙልን። አሜሪካ የምትነግረን- የማናውቅወን አይመስለኝም። ራስዋን በምስክርነት አቅርባለች። ከተጠቀምንበት። ወይም ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ አንድ ሰሞን ይሉ እንደነበረው “በደርግ ጊዜ አሜሪካ በክምር ሳር ውስጥ የወደቀች መርፌ ይታያት ነበር። አሁን ግን በእልፍኝ ውስጥ የቆመው ዝሆን እንዳይታያቸው አንድ ዓይነት ግርዶሽ (ማዮፕያ) ተፈጥሮባቸዋል” አይደለም? ጉዳዩ የኢትዮጵያውን ጉዳይ ነው ተባብለናል። የኢትዮጵያን ዋና ዋና ትግሎች (ጦርነቶች) በቅጥረኛና ካልሆነም በአሜሪካ አማካይነት የምንዋጋቸው አይደሉም። ይልቁንም ዛሬ አሜሪካ የነገረችን ሁላችንም እሥረኝነት እንዲሰማን ይመስላል። ጐበዞቻችን በወህኒ እየማቀቁ ነው።

ስለ እስክንድር፣ ስለ በቀለ፣ ስለ አንዱዓለም፣ ስለ ርእዮት….ሰምተን ነበር? ከእነሱ ሌላ ሰማንያ ሺህ ማን ያውቃል 180ሺህ ሰዎች በወህኒ ዓለም ይማቅቃሉ። ሌሎች ያልታሰሩ ግን “በመተካካት መልክ” ሊገቡ ወረፋ እየጠበቁ ናቸው። አፍጥጦ የመጣብን- እስካሁንም ያልተመለሰው ከባድ ጥያቄ- ለመሆኑ እኛስ አልሞትንም ወይ? መቸም ወደፊት እንደምንተሳሰበው ከሞቱት አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ አምሳ ሺህ ውስጥ አይደለንም ወይ? የመኖር ያለመኖር ማረጋገጫ (ምናልባት ሰርተፊኬት ወይም ሊቸንሳ) አግኝተናልን? ራስ ቢተወደድ መኮንን እንዳልካቸው “አልሞትሁም ብዬ አልዋሽም” ነበር ያሉት? ሙኩሼዬ ጸጋዬ ገብረ መድኅን ቀዌሳ ደግሞ ልዑል ሐምሌት የሚያንበለብለውን ዘላለማዊ ስንኝ እንዲህ ብሎ በከፊል ወደ አማርኛ መልሶታል።

መኖር አለመኖር እዚህ ላይ ነው ምሥጢሩ
የዕድል ፈተና አለንጋ ሲወናጨፍ ወስፈንጥሩ

ይህ ዕድል ያልደረሰውና የፈተናውም አለንጋ ያልገረፈው አለ ወይ? ይለናል። ኦስካር ዋይልድ ይመስለኛል በሶሻሊዝም ሥር የሰው ነፍስ (The Soul of Man under Socialism) ድርሰቱ “መኖር እጅግ ብርቅ ከሆኑ ባሕርያት ዋነኛው ነው። ብዙ ሰዎች እንዲሁ አሉ። ግን አይኖሩም ” ያለው (To live is the rarest thing in the World. Most people exit, that is all ) ይለናል በአንክሮ። የእኔው የትግል አድባር (አያውቀኝም) ፕሮፌሰር ሐጐስ ገብረ ኢየሱስ እናቱን ለመጠየቅ ጓድ መንግሥቱ ሔሊኮፕተር አዘዙለትና ወደ አድዋ ሔዶ ነበር። ሲመለስ A Requiem of History በሚል ያቀረበውን መጣጥፍ አልረሳውም። በዚያው ሰፊ ጽሑፉ ውስጥ እንደ ፈርጥ ያየሁለት “እናቴ በእርግጥ በሕይወት አለች። እየኖረች ግን አይደለም። She was alive, but Not living.” ይላል።
በ1980ዎቹ ካነበብኋቸው መጻሕፍት መካከል በሔንሪ ኪየምባና በዴቪድ ማርቲን የተገለጡ አስደንጋጭ አጋጣሚዎች በአእምሮዬ ውስጥ የተከሉት ክፉ ትዝታ አለ። በኢዲአሚን ኡጋንዳ ጊዜ የተፈጸመ ነው። እንዲያውም የ“State of Blood” የሚለው ጸሐፊ የኡጋንዳ የጤና ጥበቃ ሚኒስተር የነበረው ሔንሪ ኪየምባ ነው። ወደ ወጉ እንመለስና ኢዲአሚን በየቀኑ ሥፍር ቁጥር የሌለው ኡጋንዳዊ የሚገድልበትና የጭፍጨፋው ወፍጮ እንበለ እረፍት የሚሠራበት ሥፍራ ነበር። በዚህ “ሥራ” ላይ የተሰማሩት ባለሙያ ነፍሰ- ገዳዮች ትንሽ ፋታ ካገኙ ወደ ሰፈር መሸታ ቤት ይሄዱና ካቲካላና ቡቅር ከሚመስለው “ነፍስን ጭምር” ከሚያስረሳው መጠጥ ይጨልጣሉ። ግድያው እንደ ጫት ሐራራ ስለሆነባቸው በማይገድሉበት ሰዓት ሁሉ ሲያፋሽጉ ይውላሉ።

አንድ ቀን ያለወትሮው ግድያው በምሽት ሰዓት ሊጠናቀቅ ስላልቻለ ዋናው ገዳይ እስረኞቹን ይሰበስብና “ዛሬ ስለመሸ ሄዳችሁ ከቤተሰቦቻችሁ ጋር እደሩና ነገ በጠዋት መጥታችሁ መቃብራችሁን ቆፍራችሁ ትገደላላችሁ። አሁን ሂዱ። መልካም ዕድል” ይላቸዋል። በማግስቱ እስረኞቹ ተሽቀዳድመው በመሰለፍ መቃብራቸውን ቆፍረው በተሰጣቸው ትልልቅ መዶሻ አንዱ ሌላውን ገደለ ይባላል። ተረት ወይም የፈጠራ ድርሳን አይደለም። ዴቪድ ማርቲን በኦብዘርቨር ጋዜጣ ላይ በተከታታይ ያቀርብ የነበረውን ሐተታና ከላይ በርእሱ ያመለከትሁትን የሔንሪ ኪየምባ መጽሐፍ ያነብቡአል።

ገዥዎቻች፣ አንዱን ጠባብ፣ ሌላውን ነፍጠኛ በማለት የሰየፉት ወገን ቁጥር ይታወቃል? ከምዕራብ ወደ ደቡብ፣ ከደቡብ ወደ ምዕራብ እያንከራተቱ በየኪሎ ሜትሩ የረገፈው ወገናችን ቁጥር ይታወቃል? በአኅዝ የማይገለጠው መከራውና ሰቆቃው በምን ይተመን? እዚህስ ደረጃ አልደረስንም የሚያሰኝ ምን ምልክት አለ? አሁንም ለእርድ የተዘጋጀን ነን- ሁላችንም ባንሆን አብዛኞቻችን። ንጹሐን ዜጐችን ግደሉ ብንባል ዓይናችንን የማንጨፍን አለን። አሁንም ቢሆን እኛን በእኛ እየጨረሱንም እያጫረሱንም ነው። አይደለምን? የኢዲአሚኑ ሪፖርት ይዘገንናልን?

ያንን የምታውቁትን ለፍቶ ያስተማረኝ የኢትዮጵያ ገበሬ ሲባልለት የቆየውን “ናስቲለው”…አልፎ አልፎ ታስታውሱታላችሁ? ትዝ ሲላችሁ ዓይናችሁ እንባ ይቋጥር ይሆን? (ናስቲለው በሰሜን ኢትዮጵያ ገበሬ ማለት ነው።) አሜሪካ ስለ ኢትዮጵያ ገበሬ በመንግስት መሰቃየት ያርዳን? አቦ! አቦ! እንደ ብዕርና ወረቀት ያስጠላኝ ነገር የለም። ካሣ ተሰማ ትዝ አለኝ። ድንቀኛው ጸሐፊ ጓደኛዬ ብርሃኑ ዘሪሁን ካሣ ተሰማን አንድ ቀን አነጋግሮት ነበር። ለመነን መጽሔት ነበር። ብርሃኑ ወርቅ የሆነውን የካሣን ፕሮፋይል ሲያቀርበው “ቧንቧ ሠራተኛው ካሣ” በማለት ነበር። ካሣ ክራር መደርደር የለመደው በስሜት ነው። ከተቃጠለ አንጀቱ የሚያወጣውን ትንፋሽ በዘፈን ለማብረድ ነው። ካሣ ይዘፍናል። ስሜቱ ወደ ጽርሐ-አርያል ይከንፋል። እሱም ራሱ እንደ ማኰብኰብ ሲለው ክራሩን ሰባብሮ ሲጃራ መግዣ ፍለጋ ይሄዳል።

ይኸ ሁኔታ ዛሬ ይገባኝ ጀምሮአል። ከክራሩ ባሻገር የሚሰማው ድምፅ ያለ ይመስለኛል። ከመላእክት ጋር ሲነጋገር ቆይቶስ ቢሆን? ከአድማስ ባሻገር ከታላላቆቹ ተራሮች ላይ ሆኖ ስለዚች አገር ዕድል- ስለሚደርስባት አደጋ፣ ስለ ትንንሽ ልጆችዋ መቀጨት፣ እንደ ዛሬ ስላለው የመከራ ሌሊት ያጫወቱት እንደሆነ ማን ያውቃል? እንዲያ ሆኖ ሆኖ ካሣ ወደ ቧንቧ ሥራው ይመለሳል። እሱም ዘመንን ቆጥሮ ወደ መሬቲቱ ተመለሰ። ወደ ማኅፀናዋ።
እኛንም ደካሞች ልጆችዋንም እነሱንም ባሊጊዜና ቅምጥል አዳዲስ መኳንንትና መሳፍንት የኢትዮጵያ መሬት እኩል ትበላናለች ወይ? ስለ ጄኔራል ደጐል ያነበብሁት አንድ ታሪክ አለ። ጄኔራል ደጐል ሽባ ሆና የተወለደች ልጅ ነበረቻቸው። ወላጆች እጅግ እያዘኑ ልጅቱ በመንፈስ እንድትጠነክር የማያደርጉት አልነበረም። የሚችሉትን ጥረት ሁሉ ካሙዋጠጡ በኋላ ልጅቱ ትሞታለች። እናት መሆን አይቀርምና ማዳም ደጐል ምርር ብለው ያለቅሳሉ። ያዝናሉ። እሳቸውን ማጽናናትም ከባድ ሆነ። በዚህ ጊዜ ጄኔራል ደጐል ባለቤታቸውን “እስካሁን ድረስ ምኞታችንና ጸሎታችን ሁሉ እግዚአብሔር ከሰው እኩል እንዲያደርጋት ነበር። ይኸውና በሕይወት ባይሆን በሞት ከሁሉ ጋር እኩል ሆናለችና ልቅሶሽን ተይ…” በማለት ባለቤታቸውን አጽናኑአቸው።

ኢትዮጵያውያን ሽባ ሆነን አልተፈጠርንም። ወይም አዳዲሶቹ ዲታዎች (ኖቮሪሽ) በአፋቸው ላይ የወርቅ ፍልቃቂ እየነከሱ ከማኅፀን አልወጡም። ሕዝብ የሚገዛው እንዲህ ነው ተብለው ጊንጥ የሚመስል አለንጋ የሰጣቸው አንዳች ኅይል የለም። ለምን ገዥና ተገዥ፣ ገራፊና ተገራፊ ሆነን ቀረን? አንመራመር። አስፈላጊ ወዳልሆነ እሽኰለሌም አንግባ። ይልቁን ከሞት በፊት ስላለው እኩልነት እናንሳ። በሞት ሕይወትን ስለማምጣት፣ በደምና በአጥንት ነፃነትንና እኩልነትን ስለመቀዳጀት።- ውይይይይ ለአፍ አይገድም። ትግሉን፣ መስዋዕትነቱን በወረቀት ላይ ጨረስነው አይደል? በሃያኛው ክፍለ ዘመን መነሻ የተጫነው የእኩልነት ትግል እነ W.E.B Du Bois የጀመሩት የጥቁር አሜሪካውያን ተጋድሎ ስትራተጂ የሚነደፍበትና ፕሮግራሙ በሥራ ላይ የሚውልበት ስልት የሚወጣበት ነበር። ታላቁ ዱብዋ ተፈጥሮ ለሰው ልጆች እኩል የሰጠችውን መብት ከሰው ልጆች መለመንን የመሰለ ውርደት እንደሌለ ይገልጣል። የመብትና የነፃነት ልመናን የመሰለ ወራዳ አቋም የለም። W.E.B Du Bois The Souls of Black Folk በሚል ድሮ ባሳተመው መጽሐፍ “ተነሥ! የምታጣው ሰንሰለትህን ነው” ወደሚለው የተራማጆች ፍልስፍና ያመራል። እንዲያውም ሎወልን በመጥቀስ-

“Twixt old systems and the word
Truth forever on the scaffold
Wrong forever on the throne
yet that scaffold sways the future
And behind the dim Unknown
Standeth God within the shadow Keeping watch above His own”

ይላል። እውነት ዘወትር በመሰቀያው ሥፍራ፣ ውሸትና የማይገባው ሁሉ ዘወትር በዙፋኑ (በአልጋው) ላይ የመገኘቱ ነገር- ያ የመሰቀያው ጣውላ የወደፊቱን ሁሉ እየነቀነቀ መገኘቱ፣ እነሆ በጭላንጭሉ መሐል ደግሞ እግዚአብሔር ከፍ ብሎ ቆሞ የራሱን ወገኖች የማበረታታቱ ጉዳይ ዘላለማዊ ነው።

ልመለስ ወደ አሜሪካ ዓመታዊ የሰብአዊ መብት መግለጫ። ከላይ ያነሳሁአቸው የዱብዋ (አሜሪካኖች ዱባይስ ይላሉ ፈረንሳዮችን ለማብሸቅ) ወይም የፍሬደሪክ ዳግላስ ታሪኮች ለእነሱ ብዙ ይጥማቸው እንደሆነ አላውቅም። በተለይ ለሪፐብሊካኖቹ። እንደዚያም ሆኖ ይህ በእነሱ ድጋፍና ርዳታ ሞልቃቃ ሆኖ የተወለደውና የሚጨፍርብን ሥርዓት (መንግሥት) ፀረ ሕዝብ፤ ፀረ አገር፣ ፀረ እንጨት፣ ፀረ ሳር፣ ፀረ ሕዝብ፣ ለመሆኑ- እደግመዋለሁ- የእነሱ እማኝነት አለን። ጊዜው- የመለያያው- ደረሰና ነው ምሥጢሩን ሁሉ ያፈነዱት? ሊሆንም ላይሆንም ይችላል። እዚያ ላይ ያለውን ነጥብ የምንመለስበት ይመስለኛል። ለአሁኑ ግን አሜሪካ በአንድ በኩል ልትረዳን የምትችላቸውን ጉዳዮች ባነሳ- ከአንባብያን ድጋፍ ካገኘሁ።

አንደኛ- እስካሁን ድረስ አሜሪካ እንዲህ ያለ በሰብአዊ መብት አከባበር ረገድ የተበላሸ አቋም፣ በፖለቲካና በአገር አንድነት ጥበቃው ረገድ አሳፋሪ ሪኮርድ፣ በሕዝብ ሰላም ጥበቃና የፍትሕ መስተንግዶ መላሸቅ ረገድ ያልሆነላቸውን መንግሥታት ወይ Evil ኤምፓየር- ወይ Rogue State አለዚያም አሸባሪ (Terrorist) ሲሉ ባጅተዋል። ወያኔ ምንድነው? በእኛ ምደባ Terrorist Regime ሊባል ይገባዋልና ስያሜው በዚሁ እንዲሆን እንጠይቃለን።

ሁለተኛ፥ ይኸ ሁሉ ከተወሳና የወያኔዎች መንግሥትም ከሕዝብ የብድርና የርጥባን ገንዘብ 20 ቢሊዮን ዶላርስ ጠልፎ ወደግል ሂሳብ ያዋለ እንደመሆኑ- የዋና ዋና ሌቦችን የስም ዝርዝር እናቅርብና ወደየምዕራቡ መዲና ሲገቡ እንዲያዙና እንድንፋረዳቸው።- ገንዘባቸው እንዳይንቀሳቀስ እንዲደረግ- ከምዕራባውያን የሚሰጣቸው ማናቸውም ርዳታ ያለ ቅድመ ሁኔታ እንዲቋረጥ- ኢኮኖሚው ራሱ የተጠለፈና ወደ ግል ኩባንያነት የተዛወረ ስለሆነ የትኛውም አገር ከወያኔዎች ጋር የንግድ ልውውጥ እንዳያደርግ ዘመቻችንን እንዲቀበለን ትብብር እንጠይቃለን።- ከናይን ኢለቨን ጋር በተያያዘ አሜሪካ እንዳይደርሱ እግድ የነበረባቸው አንዳንድ ዘራፊና አቀባባይ ሌቦች እንደገና ወደ አሜሪካ ብቅ እያሉ የለመዱትን የሞራል ድቀት ትርኢታቸውን እያሳዩ ናቸው። ከእነዚህ መካከል አንዱን አረብ ግለሰብ የኢትዮጵያ ትውልድ ሁሉ የሚፋረደው ስለሆነ ተይዞ እንዲመረመር እንጠይቃለን። ወርቃችን፣ ሌሎች የማዕድን ሀብቶቻችን ወዘተ በዚሁ ሰው እንደ ትንሽ ዕቃ በየቀኑ እየተጫነ እንደሚወሰድ እናውቃለን። እናስረዳለንም። …………

በ1980ዎቹ Republic of Fear በሚል ርእስ ስለ ሳዳም ሑሴን ጨለማ አገዛዝ የሚያወሳው መጽሐፍ በእጅጉ ያሸማቅቃል። ጸሐፊው ኬናን ሜኪያ ይባላል። የኢትዮጵያ የዛሬ ሁኔታ ደግሞ ሌላ ባሕርይ ያለበት ይመስለኛል። ስለ ዋናዎቹ አምባገነኖች ሲነሣ አብዛኛዎቹ ነጠላ ናቸው። በቺሊ ፒኖቼ- በሩማንያ ቻይቼስኮ፣ በኢራቅ ሳዳም ሑሴን፣ በሊቢያ ጋዳፊ…ናቸው። ለወርቅ ጥጃቸው የማይንበረከክ፣ ለምስላቸው የማይሰግድ ከሁለት ስፍራ ይከፈላል። ያማቸው፣ ስማቸውን ያጐደፈ…የሚሰቃይበት አዳዲስ መሣሪያ አስፈልፍለዋል። ዝርዝር የማሰቃያውን ስልትና ድርጅት ከማእከላዊ ምርመራ ሠራተኛነት አምልጠው የወጡ ሰዎችን ማነጋገር ይቻላል። ባይሆን አንድ ጥያቄ በአእምሮአችሁ የሚመላለስ ወገኖቼ አትታጡም። መለስ ከሞተ በኋላም ይኸ አገር በአምባገነን የሚመራ ነው ለማለት ይቻላል ወይ? በእኔ በኩል ከሰዎች ጋር ስወያይ “አምባገነኑ የማይታወቅ አምባገነን መንግሥት” A Dictatorship without a Dictator ግን አገዛዙ መንጋ ጨካኖች፣ ነፍሰ- ገዳዮችና በዝባዦች ቢኖሩትስ? የፈረንሳዩ ታላቅ ምሁር ዣን ፍራንስዋ ሬቨል Without Marx or Jesus በሚለው መጽሐፉ እንዲህ ያሉትን አምባገነኖች ባሕርይ Collective Mediocrity and Collective bestiality ይለዋል። ነገሩ እንዲህ ነው። መለስ ሲሞት የእሱ እጓለማውታ (Orphans) መፈላለግ ያዙ። ሰብሳቢ አጣን ብለው ወደ ትካዜው ዓለም ተሰደዱና መጠራራቱን አንድ መፍትሔ አደረጉት። ምንጣፉን ቶሎ ብለው የረገጡት እነ እንቶኔ ደግሞ አራት ኪሎን የተጫጫነውና አሁንም የሚገዛውን መንፈስ በፍጥነት በማናቸውም አስማት ለማስወጣት አልቻሉም። ትንሽ ፋታ ሳያስፈልጋቸው አልቀረም። ጥቂት ጊዜ ከገዙ በኋላ የፕሮፓጋንዳውም መሣሪያ ትንሽ ትንሽ ይደፍረዋል። “መለስኮ ሰው ነው” ማለት ይጀምራል። ሰው መሆኑን ዛሬ ነው ያወቁት አትበሉአቸው። እኛ መለስን ከመቃብር አውጥተን አንፋረደውም። እነሱ ራሳቸው ከሳሽም ፈራጅም ይሆናሉ። ጠብቁ ብቻ።

በደርግ ጊዜ ስለአባካኝነትና አሻጥር ትልቅ ጉባኤ ተዘርግቶ ነበር። በንቁዝ (ኮራፕት) ባለሥልጣኖችና በመሳሰሉት ላይ ጥብቅና ወሳኝ የሆነ ርምጃ ስለሚወሰድበት ሁኔታ ውይይት ሲካሄድ በየቦታው ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙ አሳብ ይቀርባል። በዚያ መድረክ ላይ የአገር አስተዳደር ሚኒስትር የነበሩት ጄኔራል ታዬ ጥላሁን የተናገሩት ትዝ ይለኛል። በአጤ ምኒልክ ዘመን እቴጌ ጣይቱ “ለአገሬ ለየጁ ያለው አንድ አፈንጉሥ ብቻ ስለሆነ ሌላ እንዲጨመርለት እጠይቃለሁ” ሲሉ እቴጌይቱን በአደባባይ ተቃውመው የማያውቁት ንጉሠ ነገሥት “እንኳን ሌላ ተጨምሮበት አንዱም ቢሆን አልተቻለም” አሉ ይባላል።

በዛሬዪቱ ኢትዮጵያ ከመለስ ሞት በኋላ አንድ ታዋቂና በአደባባይ ስሙና ሹመቱ የተገለጠ አምባገነን ባይኖርም ሟቹ በመጠኑ ራቅ ያደረጋቸው ሰዎች አልጋው ላይ የተረባረቡ ይመስለኛል። አቦይ ስብሐት፣ ጌታቸው አሰፋ፣ ዐባይ ወልዱ፣ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ወዘተ ወዘተ…በአንድ አገር የስለላው መረብ እንዳለ ወደ ፍጹማዊ ኅይል ሲለወጥ ደግሞ የዜጐች ሁሉ (መካከለኛ ደረጃ ያሉት ወያኔዎች ሳይቀሩ) መብት ወደ ኢምንትነት ይለወጣል። የሥነ መንግሥት ምሁራን በመንግሥት ውስጥ መንግሥት (ኤስቴት ዊዝን ኤ ስቴት) የሆነውን እንዲህ ያለውን ሥርዓት “መሪ” የሚባለውን ግለሰብ ጭምር ሽባ አድርጐ የሚቀፈድደው ያደርጉታል። በአሁኑ ሁኔታ ቀስ በቀስ የመለስ የቅርብ ሕዝብ አጫራሾች ዕጓለማውታ (ኦርፋንስ) ቢመስሉም ሌሎች በርካታ አምባገነኖች ጡንቻቸውን እያፈረጠሙ ናቸው። ወትሮ አንድ አምባገነን ያልቻለው የኢትዮጵያ ሕዝብ የብዙ አምባገነኖች ተሸካሚ ሆኖዋል። ሁሉም ነፍሰ ገዳዮች! ነፍሰ ገዳይ የማይፈራስ ማነው?
ለጊዜው በመንጋ ተንኮለኞች- ነፍሰ ገዳዮችና የዝርፊያ ሠራዊት እየተገዛን እንገኛለን። ስለእነሱ ድግስ፣ ስለ እነሱ ጥቅም፣ እነሱ የትኛዋን ጋለሞታ እንደሚጐበኙ፣ የትኛዋን መለኮን ዛሬ እንደወሰዱ እንወያያለን። በጥቃቅን ጉዳዮች አእምሮአችንን አስጨንቀናል። ወጣጥረነዋል። ይልቁን በሌላው ዓለም እየተቀጠቀጠ ማረፊያ ያጣው መንግሥታዊ አሸባሪነት የሙጥኝ ብሎ የሚገኘው በኢትዮጵያ መሆኑን እንተባበር። ይህን የሽብር መንግሥት ሌላው ቀርቶ በብረት መሞከርን ካህናቱና መነኮሳቱም መደገፍ አለባቸው። ከቶውንም ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በፋሺስቶች ጥይት ሊደበደቡ ጥቂት ሰከንዶች ሲቀራቸው “ልጆቼ ኢትዮጵያውያን ለፋሺስቶች እንዳትገዙ አውግዤአለሁ” ማለታቸው ይጠቀሳል። አዳዲስ ካሕናትና የዚህ ትውልድ ቀሳውስት ነገሩን ቸል እንኳ ቢሉ የአቡነ ጴጥሮስ ግዝትና ውግዘት አለብን። ቋሚ ነው- እስከማዕዜኑ።

ትግልና ታጋይ የሚጠይቁት አንድ ነገር ብቻ ነው። በደረትህ ውስጥ ጤነኛ ልብ፣ በጭንቅላትህ ውስጥ ጤናማ አእምሮ ካለህ ማናቸውም ችግር አይፈታህም። ጥይት አይመታህም። ድንፋታ ትርጉም አይሰጥህም። ቅጥፈትና ማስፈራራት ትጥቅህን አያስፈታህም። ልጆቼ ልላቸው የምችለው እነ እስክንድር፣ በቀለ፣ አንዱአለምና ርእዮት ይህን ወኔ በሰፊው የተቀዳጁ ናቸውና እንኮራባቸዋለን። እነሱ ወኅኒ ዓለም ሲገቡ የከዳናቸውና የቆሙለትን ዓላማ ጭምር የረሳንባቸው ከመሰላቸው ደግሞ አደራ በላነት ሊሰማን ይገባል።

ይህን ጽሑፍ የጀመርሁት በወያኔ የልደት በዓል ምክንያት ትንሽ የምለውን ለማቃመስ ነበር። ምናልባትም እንደ ፍሬደሪክ ዳግላስ ለእነዚህ ሰዎች “ጉንበት 20- ጉንበት ሃያ ትሉናላችሁ ጉንበት ሃያ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሥቃይ ሁሉ እናት የሆነችው ስቃይ የመጣችበት ቀን። ጉንበት 20 የባርነትና ወደር የሌለው ውርደት መታሰቢያ ቀናችን ናት። ጉንበት 20 ለእሥራታችን መታሰቢያችን ናት።” ልንላቸው እንችላለን። ይኸ የደፋሮቹ ጋዜጠኞች – የጀግኖቹ የፖለቲካ መሪዎችና ገበሬዎች የተባበረ ድምጽ ነው። በሬሳችን ላይ የሚጨፍሩበት፣ በመቃብራችን ላይ የሚያሽካኩበት፣ ቤትና ንብረት አሳጥተው ለስደት ያበቁንና በዚህ ደስታ የሚሰክሩበት በዓላቸው- የእኛ የልቅሶ ዕለት፣ የእኛ የመከራ ቀን መታሰቢያ ነው።

በመጨረሻም እንደገና ለአሜሪካ በማቀርበው ጥያቄ ላይ ይህችን ነጥብ እደግማለሁ። ይህ መንግስት ኢቭል የምትሉት አይነት ነው? ወይስ አሸባሪ? የወያኔ ኦሮሞዎች በኢትዮጵያውያን ኦሮሞዎች ላይ የሚፈጽሙትን እልቂት፣ የወያኔ አማራዎች (እነበረከት አምሮች ከተባሉ) በኢትዮጵያውያን አማሮች ላይ የሚያካሄዱትን መጠነ ሰፊ ድምሰሳ፣ የወያኔ ሙስሊሞች በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ እያደረሱ የሚገኙትን ወከባና ወደር የሌለው ጥቃት፣ ሟቹ የመለስ የሃይማኖት የይስሙላ ፓትርያርክና እንደ ሩሲያዊው ራስፑቲን የሚቆጠረው አባ ጳውሎስ በኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ያካሄደውን ሥቃይ አሜሪካ ከእኛ በላይ እንደማያውቀው ለዴሞክራሲ፣ ለሰብአዊ መብትና ነፃነት ስትል ርምጃ ለመውሰድ አቅዳለች? አጤ ኅይለሥላሴ በቀድሞው የመንግሥታት ማኅበር ጉባኤ ላይ ያደረጉትን ንግግር ለመጥቀስ እገደዳለሁ – “ታሪክና ትውልድ ፍርዳችሁን ይጠባበቃሉ!”

እነሆ ዛሬ በኢትዮጵያ የሰው ዘር ጠላት የሆነ ሥርዓት አለ። የሒትለርን ፀረ ሕዝብነት ለመረዳት የፖላንድ መወረር፣ የሃምሳ ሚሊዮን ሕዝብ ማለቅ፣ የስድስት ሚሊዮን አይሁድ መጨፍጨፍ መጠበቅ ይገባል? ታሪክ አላስተማራችሁምን? በአሜሪካ ላይ ስንት ክህደትና ቸልታ እንቁጠር? በፋሺስት ወረራ ዘመን ሩዝቬልትና ሴክሬተሪ ሐል ያሳዩን ክሕደትና ቸልታ አይረሳንም። አሜሪካ የበለጠ ትናገር! እግዚአብሔር ሁላችሁንም ይጠብቃችሁ!!

↧

በአሜሪካ የሚኖረው የሕወሐት ወንጀለኛ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

$
0
0

የሕወሐት አባል የሆነውና በአሜሪካ የሚኖረው ብስራት አማረ በርካታ ወንጀሎችን እንደፈፀመ የቅርብ ምንጮች አጋለጡ። ሕወሐት በረሃ እያለ የባዶ 6 እስር ቤት ዋና ሃላፊ የነበረው ብስራት አማረ የኢ.ህ.አ.ፓ አባላት የነበሩት እነ ፀጋዬ ገ/መድህን (ደብተራው) ጨምሮ በሕወሐት የተያዙትን በሙሉ ወረኢ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ በነበረ እስር ቤት በጅምላ አሰቃይቶ እንደገደላቸው ምንጮቹ አረጋግጠዋል። በሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ ሰዎች « ኢዲዩና ፊውዳል..» በሚል ባዶ 6 ተብሎ ይጠራ በነበረው እስር ቤት ተሰቃይተው እንዲገደሉ የተደረጉት በብስራት አማረ መሆኑን የጠቆሙት ምንጮቹ ከዚህ በተጨማሪ የድርጅቱን በርካታ አባላት እንዳስገደለ አያይዘው ገልፀዋል።

እነተክሉ ሃዋዝ በዚህ ወንጀለኛ ከተገደሉት ይጠቀሳሉ ሲሉ ያክላሉ። በ1983ዓ.ም ሕወሐት/ኢህአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ የሟቹ የደህንነት ሹም ክንፈ ገ/መድህን ምክትል የነበረው ብስራት አማረ ከቤተ መንግስት የጃንሆይ የነበረ ከፍተኛ ወርቅ በመዝረፍ መውሰዱን ያጋለጡት ምንጮቹ በዚህ የዘረፋ ወንጀል ሆለታ እስር ቤት እንዲገባ መደረጉን ያመለክታሉ። በነስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ትእዛዝ እንዲፈታ ተደርጐ ወደ አሜሪካ የተሸኘው ብስራት አሜሪካ ሲጓዝ የዘረፈውን ወርቅ ይዞ እንደነበረ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ምንጮች በግርምት ይገልፃሉ። ብስራት አማረ አሜሪካ ከመጣ በኋላ ቅርስ የሆኑትንና የዘረፋቸውን ወርቆች መሸጡንና አንዲት ሴት ለማሻሻጥ የተቀበለችውን 1ኪሎ ወርቅ ከወሰደች በኋላ እንደካደችው ማወቅ ተችሎዋል። ብስራት አማረ ስለዚሁ ጉዳይ ተበሳጭቶ የነገራቸው ምንጮች ማረጋገጫ ይሰጣሉ። የብስራት ታናሽ ወንድም የሆነውና በደህንነት ቢሮ ይሰራ የነበረው ታጋይ ጠስሚ ( ጠስሚ -ትርጉሙ ቅቤ ማለት ነው) ከስራው በመልቀቅ የአስመጪና ላኪነት ትልቅ ቢዝነስ መክፈቱን የጠቆሙት ምንጮቹ አክለውም፥ ድርጅቱ የተከፈተው ብስራት አሜሪካ ከገባ በኋላ በላከለት ገንዘብ መሆኑን አስታውቀዋል።

(ስለዚሁ ጉዳይ በ1995 ዓ.ም በኢትኦጵ ጋዜጣ መረጃው ይፋ መደረጉና የብስራት ወንድም ቅቤ ኢትኦጵ ቢሮ ድረስ በመምጣት የጋዜጣውን አዘጋጅ በድንጋጤ ተውጦ “ የራሴን ቢዝነስ ተቋም ነው፤ እነማን መረጃ እንደሚሰጧችሁ አውቃለሁ። እባካችሁ የእኔንም፣ የወንድሜንም ስም አታንሱ? ” በማለት ተማጽኖ አቅርቦ ነበር።) ብስራት አማረ ከሽማግሌው ስብሃት ነጋ ጋር ባለው የጠበቀ ግንኙነት ወደ ኢትዮጵያ ሲመላለስ መቆየቱን ያወሱት ምንጮቹ፣ ወንጀለኛውና ዘራፊው መቀሌ ሄዶ አስገደ ገ/ስላሴን እንደከሰሰ አስታውቀዋል። የደርግ ወንጀለኞች ከአሜሪካ በገዢው ፓርቲ እየተወሰዱ ነገር ግን የኢ.ህ.አ.ፓ አባላትንና ሌሎች ንጹሃን ዜጎችን በጅምላ የፈጀና የአገር ቅርስ የዘረፈ ወንጀለኛ ጠያቂ ማጣቱ አስገራሚ ነው ብለዋል ምንጮቹ። ጠያቂ አካል ካለ- በወንጀለኛው ብስራት አማረ ላይ ለመመስከር ፈቃደኛ መሆናቸውን አክለዋል። ይህን ምስክርነትና ማረጋገጫ ሊሰጡ የሚችሉና በአሜሪካ የሚኖሩ ሶስት የቀድሞ የሕወሐት ሹሞች እንዳሉና የብስራትን ወንጀል ጠንቅቀው የሚያውቁ መኖራቸውን አያይዘው ጠቁመዋል።

↧

አሉባልታና ጫጫታ እናስወግድ በበላይነህ አባተ

↧
↧

ሚሊየነች ድምጽ –ሸንጎና የኢትዮጵያ የሽግግር ምክር ቤት ለሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ አጋርነታቸውን ገለጹ !

$
0
0

ወደ ስድስት የሚጠጉ የፖለቲካና የየሲቪክ ማህበራት ስብስበ የሆነው የኢትዮጶያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት፣ በዚህ ሳምንት በዳያስፖራ ለተቋቋመው የሚሊዮኖች ድምጽ ግብረ ኃይል በጻፉት ደብዳቤ ፣ ድርጅታቸው፣ በአገር ቤት ከፍተኛ መስዋእትነት እየከፈሉ ላሉ ታጋዮች ያላቸዉን አድናቆትና አክብሮት በመገጽል፣ አገር ቤት እየተደረገ ያለዉን የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ ጎን እንደሚቆሙ አረጋገጡ።

ድርጅቶቹ በደብዳቤ ድጋፋቸውን ከመግለጽ ባሻገር ፣ በግብረ ኃይሉ የሚሳተፉ ተወካዮችን የላኩ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ መሰረታዊ ለዉጥ እንዲመጣ ከተፈለገ የኢትዮጵያዉያን መሰባሰብ አስፈላጊ እንደሆነም አስምረዉበታል።

ሸንጎም ሆነ የሽግግር ምክር ቤቱ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ አጀንዳዎችን በመያዝ ሕዝቡን ለትግል ለማነሳሳት ከፍተኛ
ጥረት ሲያደርጉ የቆዩ፣ በተለያዩ ጊዜያትም አገር ቤት የሚደረገዉን ትግል ሲደግፉ የነበሩ ድርጅቶች እንደሆኑ ይታወቃል።

በዳያስፖራ የተቋቋመው የዳያስፖራ ድምጽ ንቅናቄ ከሸንጎ እና የሽግግር ምክር ቤቱ በተጨማሪ በርካታ ድርጅቶችን በማሰባሰብ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ የሚሊዮኖችን ድምጽ በመደገፍ አንጻር ከፍተኛ መነሳሳት እየታየ ነው። ግብረ ኃይሉ ከአዲሲቷ ኢትዮጵያ ሶሊዳሪቲ ንቅናቄ፣ ከማርች ፎር ፍሪደም ሲቪክ ማህበር፣ ከኢትዮጵያዊነት ሲቪክ ማህበር፣ ሎስ አንጀለስ ከሚገኝ የኢትዮጵያ የዲሞክራሲኦና ሰብአዊ መብት ሲቪክ ማህበር ፣ ከቃሌ፣ ከደብተራዉ እና ከረንት አፌር ፓልቶክ ክፍልም አዎንታዊ ምላሽ እያገኘ ነው።

↧

ሚሊየነች ድምጽ – ላስ ቬጋስ የአዲስ አበባዉን የመጀመሪያ ስብሰባ ስፖንሰር አደረገች!

$
0
0

ሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በአገሪቷ ዉስጥ ባሉ አሥራ ሰባት ከተሞች፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንደሚያደርግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ሕዝባዊ ስብሰባ በማድረግ የሚጀመር ሲሆን፣ በሌሎች ከተሞች ከአንድነት ጽ/ቤቶች ወደ አደባባይ በሚሄድ ትይንተ ሕዝቦች ይደረጋሉ።

addis_lasvegas-1

ላስ ቬጋስ፣ ኔቫዳ፣ ከአዲስ አበባ ጋራ ሶሊዳሪቲ በመመሰረት ፣ በዚያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን፣ በአዲስ አበባ ለሚደረገዉ ሕዝባዊ ስብስበ የሚያስፈልገውን ወጭ ሙሉ ለሙሉ ለመሸፈን የተዘጋጁ ሲሆን፣ «ከሚሊዮኖች አንዱ ነን» እያሉም ነው።

ይህ የሚሊየነሞች እንቅስቃሴ የአንድ ፓርቲ እንቅሳቅሴ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንቅስቃሴ እንደመሆኑ፣ በአገራችን ዴሞክራሲና የስርዓት ለዉጥ እንዲመጣ የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ ሊቀላቀሉት፣ ሊደግፉት፣ የራሳቸው ሊያደርጉት የሚገባ እንቅስቃሴ ነዉ። ይህ እንቅስቃሴ የሚሊዮኖች እንቅስቃሴ ነው። የእያንዳንዳችን እንቅስቃሴ ነው።

በዳያስፖራ የሚሊየነሞች ግብረ ኃይል፣ በላስ ቬጋስ ያሉ ኢትዮጵያዉን ላሳዩት አኩሪና ኢትዮጵያዊ እንቅስቃሴ ያለዉን አድናቆት እየገለጸ፣ በሌሎች ከተሞችም የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እራሳቸውን እያደራጁ ፣ አገር ቤት ከፍተኛ መስዋእትነት እየከፈለ ካለው ሕዝብ ጎን እንዲቆሙ፣ ትግሉን እንዲቀላቀሉና ከሚሊዮኖች አንዱ እንዲሆኑ ጥሪ ያቀርባል።

በምትኖሩበት ከተማ ተደራጅታችሁ፣ ከዚህ ግብረ ኃይል ጋር በመስራት በአገር ቤት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ስፖንሰር ማድረግ የምትፈልጉ፣ በሚከተሉት አድራሻ ሊያገኙን ይችላሉ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !

millionsforethiopia@gmail.com
404- 518-7858

↧

የታደስ ውግዘት ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

↧
Viewing all 1809 articles
Browse latest View live