Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all 1809 articles
Browse latest View live

አቡጊዳ –«አሁን ባለንበት ሁኔታ ውህደት የሚባል ነገር ቦታ የለውም» የሰማያዊ አመራር አባል

$
0
0

የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራርና የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊዉ ወጣት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ድርጅታቸው «ውህደት ፈጽሞ አያስፈልግም ብሎ የማያምን እንደሆነ የገለሱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን ዉህደት እንደማይታሰብ አሳወቁ። ፓርቲዉ ከሌሎች ድርጅቶ ጋር አብሮ ለመስራት እና ለመዋሃድ ፈጽሞ የተዘጋ በር እንደሌለው የገለጹት አቶ ብርሃኑ ከዉህደት በፊት ግን መቅደም ያላባቸው ጉዳዮች (የቤት ስራዎች) እንዳሉ ይናገራሉ።

መሰራት ያላባቸውን የቤት ሥራዎች ምን እንደሆነ አቶ ብርሃኑ በጽሁፋቸ ያልገለጹ ሲሆን፣ «አሁን ባለንበት ሁኔታ ውህደት የሚባል ነገር ቦታ የለውም» ሲሉ የቤት ሥራቸዉን የሰሩ ደርጅቶች እንደሌሉ በማመላከት የሚነሱ የዉህደት ጥያቄዎችን ዉድ አደርገዉታል።

በኦፌስል ከሰማያዊ ፓርት ጋር ለመዋሃድ፣ ከአንድነት ፓርቲ በስተቀር ጥያቄ ያቀረበ ድርጅት ስለመኖሩ፣ ብዙ የሚታወቅ ነገር የለም። አቶ ብርሃኑ ተከላ ያሬድ በአሁኑ ወቅት የዉህደት ጥያቄ አቀረቡ የሚሏቸውን ድርጅቶች በተመለከተ «እንደ ፓርቲ መቀጠል ስላልቻሉ ብቻ ድክመታቸውን ወደ ሌላው በማጋባት ህልውናቸውን ለማስቀጠል የሚደረግ ሙከራ የመጠፋፋት ድርጊት እንጂ ውህደት አይደለም» ሲሉም የዉህደት ጥያቄ ያነሱትን ድርጅቶች የዉህደት ጥያቄ ጥሪ አጣጥለዉታል።

በዚህ በዉህደት ዙሪያ የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባላት አመለካከት አንድ እንዳልሆነ የገለጹት አቶ ብርሃኑ፣ «በውህደት ላይ የፓርቲው አመራር አካላት የያዙት አቋም የሁሉም አቋም ላይሆን ቢችልም ሰማያዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እንደመሆኑ መጠን የአብዛኛውን አቋም የማራመድ ግዴታ እንዳለባቸው እንዲሁም ይህንንም ግዴታቸውን በአግባቡ እየተወጡ መሆናቸውን ፓርቲው ያምናል» ሲሉም የሚወሰኑ ዉሳኔዎች ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መሆኑንም ለማስረዳት ሞክረዋል።

አቶ ብርሃኑ ተከላያሬድ ያቀረቡትን ጽሁፍ እንደሚከተለው አቅርበናል፡

============================================================
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተለያዩ ፓርቲዎች፣ ሚዲያዎች እና ግለሰቦች የሰማያዊ ፓርቲን በውህደት ላይ ያለውን አቋም ሲኮንኑት ይስተዋላል፡፡ ኩነናው ፓርቲው በውህደት ላይ ያለውን አቋም የግለሰብ አቋም ነው እስከ ማለት ይደርሳል፡፡ ስለዚህም የዚህ ጽሑፍ አላማ የፓርቲውን በውህደት ላይ ያለውን አቋም እንዲሁም እውን ፓርቲው በግለሰብ ፖለቲካዊ አቋም የሚመራነውን? የሚለውን ለአንባብያን ለማብራራት እና ለመመለስ ያሰበ ነው፡፡

እኔ እስከማውቀው ፓርቲው በውህደት ላይ ፈጽሞ የተዘጋ አቋም የለውም፡፡ ለዚህም ነው በተለያዩ ጊዜያት ፓርቲው በሚሰጠው መግለጫ ላይ አሁን ባለንበት ሁኔታ ውህደት የሚባል ነገር ቦታ የለውም የሚለው፡፡ ፓርቲ እንደ ፓርቲ የተለያዩ የቤት ስራዎች እንዳሉበት ስለሚያምን እነዚህንም የቤት ስራዎቹን በአግባቡ እና በጥራት ለመስራት ስለሚያስፈልግ ከዚህም ባሻገር ሌሎችም ፓርቲዎችም ከውህደት በፊት በአግባቡ የቤት ስራቸውን መስራት እንደሚኖርባቸውም ከማመን የተነሳ የተያዘ ጊዜያዊ እና ወቅታዊ አቋም መሆኑን ለአንባቢ ማስገንዘብ እፈልጋለሁ፡፡

በሃገራችን የፓርቲ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ የፓርቲዎች የመዋሃድ እና እርስ በእርስ የመበላላት ታሪክ ቢኖርም ዋናው መነሳት ያለበት ነገር ግን ከእነዚህ ታሪኮች ምን ተምረናል የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ ታሪክ አሁንም የሚነግረን ከታሪክ የማንማር የታሪክ ቱባ መሆናችንን ነው፡፡ የቅርብ ጊዜ ታሪካችን የሆነው እና የኢትዮጵያን ፖለቲካ ወደ ኋላ የመለሰውን የ1997 ዓ.ም ምርጫ እንደ ማሳያ ሊቀርብ ይችላል፡፡ቅንጅት እንዴት ተቋቋመ? ማን ምን አተረፈ? ማንስ ምን ተጎዳ? ስንት ፓርቲዎች ህይወታቸውን ወይም ህልውናቸውን አጡ? የሚሉት እና የመሳሰሉት ጥያቄዎች በአግባቡ መልስ ማግኘት ይኖርባቸዋል፡ እነዚህ የትናንት ታሪኮቻችን ፍንትው አድርገው የሚያሳዩን ከፓርቲዎች ውህደት በፊት ምን መሰራት እንዳለበት ነው፡፡

‹‹ወንዙን ስንደርስ እንሻገረዋለን!›› በሚል አስተሳሰብ የሚደረግ ውህደት ወንዙንም ተሻጋሪውንም የሚጎዳ ስለሆነ ፈጽሞ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ቅንጅት በወቅቱ ባደረገው የወረቀት ውህደት ወንዙ ጋር ሳይደርሱ ተራራው ላይ ሲፈረካከሱ ለማየትተችሏል፡፡ ይህም ሆድን በጎመን ቢደልሉት ልበት በዳገት ይለግማል የሚለውን የሃገራችን ብሂል እንድናስታውስ ያደርጋል፡፡ ከውህደት በፊት ቅድሚያ አንድ በሚያደርጉን ጉዳዮች ላይ አብረን ለመስራት ያለን ተነሳሽነት ምን ያህል እንደሆነ ማስተዋል ይኖርብናል፡፡

እነዚህ ውህደትን የሚያቀነቅኑ ፓርቲዎች ሰማያዊ ፓርቲ እንደ ፓርቲ ባደረጋቸው የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እና ዝግጅቶች ላይ ድጋፍ ለማድረግም ሆነ ለመሳተፍ እንዲሁም አብሮ ለመስራት ካደረጉት ጥረት ይልቅ ባይሳካላቸውም እንቅስቃሴዎቹን ለማሳነስ እና ለማጥላላት የተደረጉ ሙከራዎች ይብሱ ነበር፡፡ ከዚህ በፊት ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25/2005 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ባካሄደ ጊዜ ሰልፉን በጋራ ከማሳካትና ከመሳተፍ ይልቅ ከአንዳንድ የፓርቲ አመራሮች ሳይቀር እንዴት ተፈቀደላቸው ብለው ገዢውን ፓርቲ ለመውቀስ የዳዳቸውም ነበሩ፡፡

ታዲያ የራሳቸውን የቤት ስራ እንኳን በአግባቡ መስራት የተሳናቸው ፓርቲዎች እንዴት ጣታቸውን ወደ ሰማያዊ ለመቀሰር እንደሚችሉ ፈጽሞ ሊገባኝ የሚችል ጉዳይ አይደለም፡፡ ፖለቲካን ማኪያቶ መጠጫ ያደረጉ ፓርቲዎችም እንኳን ሳይቀሩ ፓርቲው በውህደት ላይ ያለውን ጊዜያዊ አቋም ለመኮነን ሲሞክሩ ማየት አስቂኝም አሳዛኝም ጉዳይ ነው፡፡ የዚህ ጽሑፍ ባለቤት እንደ ግለሰብ ከውህደት በፊት አንድ በሚያደርጉን ነገሮች ላይ ተቀራርበን ለመስራት ፈቃደኛ መሆን ይኖርብናል ብሎ ያምናል፡፡ አንዳንዶች በውስጣቸው ካለው “የብሔር ተዋጽኦ አናሳነት” አንጻር ውህደትን ሲያራግቡ መመልከት የተለመደ ነው፡፡

ሲጀምር አሁንም እንደ አምባገነኑ ኢህአዴግ ከፋፋይ የጎሳ ፖለቲካን ለማስቀጠል ከሚደረግ ሙከራ ተለይቶ አይታይም፡፡ ይህም ደግሞ መጽሐፉ ኢትዮጵያዊ ቀለሙን እንዲሁም ነብር ዥንጉርጉርነቱን ሊቀይር አይቻለውም እንደሚለው ትውልደ ኢህአዴጋውያን በፓርቲዎች ውስጥ አላግባብ ባገኙት ዜግነት የሚያራምዱት እና የሚያቀነቅኑት አስተሳሰብ መሆኑ የሚካድ አይደለም፡፡ ክፍተቶቻችንን በጊዜያዊነት ለመደፋፈን ሲባል የሚደረግ የጥድፊያ ውህደት መጨረሻው አሁን ካለንበት የፖለቲካ አዘቅት ለመውጣት የሚደረግ ትግልን እንዲሁም የህዝብን አመኔታ ለማግኘት የሚደረገውን ጥረት ወደኋላ ሊመልሰው ይችላል ብዬ አምናለሁ፡፡

መቼም እባብ ያየ በልጥ ይበረያል እንደሚባለው ሊሆን ቢችልም እንኳን እንደ ፓርቲ መጠንቀቁ አይከፋም፡፡ በአግባቡ የቤት ስራችንን ሳንሰራ በፍጹም የቤት ስራቸውን በአግባቡ ካልሰሩ ፓርቲዎች ጋር ውህደት መፈፀምም ተገቢ ነው ብዬ አላምንም፡፡ ቅድሚያ ሁላችንም ያለንበትን በእሾክ የተሞላውን የዴሞክራሲያዊ ፖለቲካ ምህዳር በመጥረጉ አንድ ላይ መስራት ይኖርብናል፡፡ ወንዙን በመሻገር አግዘኝና ይህንን እሰጥሃለው የሚባል ትብብርም ለህወሓት እና ሻዕቢያም እንዲሁም ለህወሓት እና ኦነግም አልበጀም፡፡ ትርፉ በደም እና በስጋ የተሳሰሩ ህዝቦችን በጠላትነት ከማፈራረጅ እና በደም ከማቃባት የዘለለ አልሆነም፡፡

ስለዚህም ትብብራችንም ሆነ ውህደታችን ከጥቅም ተኮርነት እና ጊዜያዊ ሆሆይታ ባሻገር የህዝብን የወደፊት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ዛሬ ዳቦ ያቋረሰ እና ፈንዲሻ ያስበተነ ውህደት ወይም ትብብር ነገ ሃገር ሊያቋርስ እና ህዝብን ሊበትን ይችላልና ጥንቃቄ ሊወሰድ ይገባል፡፡ ውህደት ማለት የልብ እንጂ የወረቀት መሆን የለበትም፡፡ ሁሉም የቤት ስራውን ሰርቶ ሲጨርስ መሰረታዊ ልዩነቶቹ ላይ በጠረጴዛ ዙሪያ ድርድር በማድረግ ውህደት ለመፈጸም በሩን ከፍቶ የሌሎችን መምጣት ሚጠባበቅ ብቻ ሳይሆን የሌሎችንም የተዘጋ በር በተደጋጋሚ የሚያንኳኳ መሆኑ ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በውህደት ላይ ያለውን አቋም የአንድ ግለሰብ አቋም አድርገው በማቅረብ የፓርቲውን እና የአባላቱን ስም ለማጉደፍ የሚደረግ ሙከራ እውነትነት የሌለው ፍሬ አልባ ነገር መሆኑን ለማስረዳት ሰማያዊ ፓርቲ እንዴት እና ለምን ተፈጠረ የሚለውን ብቻ ማየት በቂ ይመስለኛል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ የተቋቋመው ግለሰቦች ከህግ በላይ ሆነው መተዳደሪያ ደንብ እና መርህ እየተጣሰ መቀጠል የለብንም በሚል አቋም ከፓርቲ ጥለው በወጡ ግለሰቦች መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ ታዲያ እነዚህ ህግ እንጂ ግለሰብ አይመራንም ያሉ አባላት እንዴት ዛሬ ለግለሰብ አስተሳሰብ ተገዢ ሊሆኑ ይችላሉ ተብሎ ይታሰባል? እዚህ ጋር መዘንጋት የሌለበት ሁሉም የፓርቲ አባላት እንደ ፋብሪካ ውጤት ተመሳሳይ የሆነ አቋም አላቸው ተብሎ ሊወሰድ አይገባም፡፡ከአባላት ውስጥ ውህደትን የሚደግፉ ሊኖሩ ቢችሉም የእነዚህን አባላት አመለካከት ፓርቲው ለፓርቲው ጥቅም ከማሰብ መሆኑን ቢገነዘብም አብዛኛው የፓርቲው አባላት ለውህደት ጊዜው አሁን አይደለም ብለው የሚያምኑ በመሆናቸው የተያዘ አቋም እንጂ የአንድ ግለሰብ አቋም አይደለም፡፡

የፓርቲው ሊቀ-መንበርም ሆኑ የተቀሩት አመራር አካላት አብዛኛው የፓርቲው አባላት የሚያራምዱትን አቋም የራሳቸው ሆነም አልሆነም የማራመድ ግዴታ ያለባቸው መሆኑን የሚያውቁ እንጂ የራሳቸውን ሃሳብ በሌሎች ላይ ለመጫን የሚደረግ ምንም አይነት ሙከራ የለም ብሎ ደፍሮ መናገር ይቻላል፡፡ በውህደት ላይ የፓርቲው አመራር አካላት የያዙት አቋም የሁሉም አቋም ላይሆን ቢችልም ሰማያዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እንደመሆኑ መጠን የአብዛኛውን አቋም የማራመድ ግዴታ እንዳለባቸው እንዲሁም ይህንንም ግዴታቸውን በአግባቡ እየተወጡ መሆናቸውን ፓርቲው ያምናል፡፡

በመጨረሻም ፓርቲዬ ሰማያዊ ውህደት ፈጽሞ አያስፈልግም ብሎ የማያምን እና ከፓርቲዎች ውህደት በፊት ብዙ ስራዎች ሊሰሩ እንደሚገቡ የሚያምን መሆኑ እንዲሁም ሌሎች እንደ ፓርቲ መቀጠል ስላልቻሉ ብቻ ድክመታቸውን ወደ ሌላው በማጋባት ህልውናቸውን ለማስቀጠል የሚደረግ ሙከራ የመጠፋፋት ድርጊት እንጂ ውህደት አይደለም ብሎም ያምናል፡፡በመሆኑም በአሁኑ ሰዓት ከየትኛውም ፓርቲ ጋር አንድ በሚያደርጉን ሃገራዊ ጉዳዮች ላይ ልዩነቶቻችንን ተቻችለን እና ተከባብረን ለመስራት የምንፈልግ እና እየሰራንም የምንገኝ መሆኑን ሊታወቅ ይገባል፡፡ የሆሆይታ ውህደት ከታሰበው ጥንካሬ ይልቅ ድክመትን ሊያመጣ ይችላልና በሰከነ አዕምሮ ቢታይ ይሻላል፡፡ ካልሆነ ግን ከላይ እንዳልኩት ‹‹ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት በዳገት ይለግማል፡፡»


መልክዓ-ሌንጮ (ከጉራማይሌ ፖለቲካ ክፍል 2 ) –ተመስገን ደሳለኝ

$
0
0

ሌላኛው ሰሞነኛ ጉራማይሌ የፖለቲካችን ገፅ አንጋፋውን የኦሮሞ ልሂቅ ሌንጮ ለታን የተመለከተው ርዕሰ-ጉዳይ ነው፡፡ ኦነግን በመመስረትም ሆነ ፖለቲካዊ ቁመና ይዞ ህልው እንዲሆን ከዮሀንስ ለታ በላይ ማንም የለፋ እንደሌለ ይነገራል፤ ዮሀንስ ከጓዶቹ ጋር ተባብሮ ድርጅቱን ሲመሰርት ካነገበው አጀንዳ አኳያ ያለውን ተዛምዶ ገልፆ ባይነግረንም፣ ከልጅነት እስከ ጎልማሳነት ይታወቅበት የነበረውን መጠሪያ ስሙን ‹ሌንጮ› በሚል ቀይሮታል፡፡

ኦነግ እስከ 1983 ዓ.ም ድረስ የሻዕቢያ እና የህወሓትን ያህል ባይሆንም ያለፈውን ስርዓት ለመቀየር የጠመንጃ ትግል አድርጓል፡፡ ከዚህም አኳያ ይመስለኛል የመንግስቱ ኃይለማርያም አስተዳደር ግብዓተ-መሬት መፈፀሙ የቀናት ጉዳይ ብቻ እንደሆነ በታመነበት ወቅት በሀገረ እንግሊዝ፣ ሰሞኑን ‹ባድመን ለኤርትራ ስጡ› እያለ በሚወተውተን ኸርማን ኮህን አርቃቂነት በተዘጋጀው የለንደኑ ኮንፍረንስ ከሁለቱ ድርጅቶች ጋር የተቃውሞውን ፖለቲካ ወክሎ እንዲገኝ የተደረገው፡፡ ኋላም የታመነው ደርሶ አገዛዙ ሲወድቅ ኦነግም የሽግግር መንግስቱ መስራች አባል ሆኖ የመተዳደሪያ ቻርተሩን ዋነኛ አዕምዶች (የመሬት የመንግስት ባለቤትነት፣ የመገንጠል መብት እና ቋንቋ ተኮሩን ፌደራሊዝም) ከማርቀቅ ባለፈ እስከ 1984 ዓ.ም የመጨረሻ ወራት ድረስ የሥልጣን ተቋዳሽ ቢሆንም፣ ኢህአዴግ ባደረሰበት ጫናና ግፊት ሥልጣኑን ለቆ ተመልሶ ወደ በረሃ መግባቱ አይዘነጋም፡፡

ግና! ይህችን ለብዙ አስርታት በታጋዮቹ ስትማተር የነበረችውን የኦነግ የመኸር አንዲት ዓመትን ተከትሎ፣ በኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ላይ መውረድ የጀመረው የመከራና የዕልቂት መዓት ዛሬም ድረስ አላባራም፡፡ እስከዚህች ቀንም እልፍ አእላፍ ንፁሃኖች በኦሮሞነታቸው ብቻ አስከፊውን የቃሊቲ ማጎሪያ ጨምሮ በተለያዩ ገሀነም-መሰል እስር ቤቶች የምድር ፍዳቸውን እየተቀበሉ ነው፡፡ በደርግ ዘመን የኤርትራ ነዋሪዎችን ‹‹ሻዕቢያ››! በማለት በአደባባይ ገድሎ መሄዱ ቀላል የነበረውን ያህል፣ ኢህአዴግም ሃያ ሁለቱን ዓመታት ሙሉ በኦሮምኛ ተናጋሪዎች ላይ ተመሳሳዩን ታሪክ ደግሞታል፡፡ የነገይቱን ኢትዮጵያ ህልውና በሚያጠይቅ ሁኔታም በግዙፉ ቃሊቲ ‹የእስር ቤቱ ቋንቋ ኦሮምኛ ነው› እስኪባል ድረስ ያለ አሳማኝ ክስ እያነቀ ግቢውን እንዲያጥለቀልቁት አድርጓል፡፡ የዚህ ሁሉ መነሻ ሰበብ የእነሌንጮ ለታ ድርጅት መሆኑ አይካድም፡፡

ኦነግ ከ1980ዎቹ መጨረሻ ወዲህ ለስርዓቱ አስጊ እንዳልነበር እና ይዞታውን ከባሌ ወደ አስመራ እና ሚኒሶታ ማዘዋወሩን፣ በስሙ ለተፈፀመው ዕልቂት ቀማሪና አዛዡ ህወሓትም ሆነ አስፈፃሚው ኦህዴድ ጠንቅቀው የሚያውቁት ቢሆንም፤ ‹‹በስመ-ኦነግ›› ከሚፈነዱና ከሚከሽፉ ፈንጂዎች ጋር እያያዙ የክልሉን ተወላጆች የጥቃት ኢላማ ማድረጉ መደበኛ መንግስታዊ ስራ ከሆነ ሁለት አስርታት ተቆጥረዋል፡፡ የዚህ መነሾም የህወሓት ኦሮምኛ ተናጋሪ ክንፍ ከሆነው ኦህዴድ ይልቅ፣ በኃይል የተገፋው ኦነግ በብዙሀኑ ልብ ማደሩ ያነበረው ፍርሃት አንዱ ሲሆን፤ ሌላው ደግሞ ኦህኮ እና ኦፌዴን (ባለፈው ዓመት ‹‹ኦፌኮ›› በሚል ስያሜ መዋህዳቸው ይታወሳል) ያላቸውን ቅቡልነት መጨፍለቅን ያሰላ ይመስለኛል፡፡
በዚህ የተቀነባበረ ጥቃትም ብዙዎች ለህልፈት፣ እልፍ አእላፍቶች ለእስርና ለስደት ተዳርገዋል፤ ቤተሰብ ተበትኗል፤ ህፃናት ያለ አሳዳጊ፣ አረጋውያን ያለ ጧሪ ቀርተዋል፡፡ እርግጥ ይሄ ጉራማይሌ አይደለም፤ አያሌ ማስረጃ ሊቀርብበት የሚችል ተጨባጭ እውነታ እንጂ፡፡ በአናቱም ይብዛም ይነስ የቀድሞ የኦነግ መስራችና የአመራር አባሉ ሌንጮ ለታ፣ ለዚህ ሁሉ ስቃይና መከራ የድርሻውን ያህል የታሪክ ተወቃሽ (ተጠያቂ) መሆኑ አከራካሪ አይደለም፡፡

የሆነው ሆኖ በሌንጮ ኦነግ ስም ለተገደሉት ገዳዮቻቸው ለፍረድ ሳይቀርቡ፣ የታሰሩት ሳይፈቱ፣ የተሰደዱት ሳይመለሱ፣ የፈረሱ ጎጆዎች ሳይቀለሱ፣ ሌላው ቀርቶ ከኢትዮጵያም አልፎ ከኬኒያ ‹ኦነግ› እያሉ አፍነው በመውሰድ ለእስር መዳረጉ (በቅርቡ በወህኒ ቤት ሕይወቱ ያለፈውን ኢንጂነር ተስፋዬ ጨመዳን እናስታውሳለን) ዛሬም ቀጥሎ እያለ ኦቦ ሌንጮ ለታ ‹‹የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር›› የተሰኘ አዲስ የፖለቲካ ድርጅት መስርቶ፣ ለሚቀጥለው ምርጫ እያሟሟቀ ከመሆኑም በላይ በቅርቡ ወደ ሀገር ቤት ገብቶ ታሪክ እንደሚሰራ የተናገረውን ማድመጣችንን ነው ለጉራማይሌ ፖለቲካ ማሳያ ያደረኩት (ሌንጮ ኦዴግን ከመሰረተ ጀምሮ ላለፉት በርካታ ወራት ‹‹ገብተን እንታገላለን›› ማለቱን ስንሰማ ከርመናል) በተያያዘም ሰውየው የኖርዌይ መንግስት የአፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ መሆኑን ስንጨምር፣ በአንድ ወቅት ራሱም ‹‹እዚህ ኖርዌይ ቁጭ ብዬ ምን እሰራለሁ?›› እንዳለው የአማካሪነቱን ከፍተኛ ደሞዝ ጭምር ትቶ ለመምጣት መወሰኑ፣ ቀጣይ ሚናው ላይ ያለውን የመተማመን ልክ ማየት እንችላለን፡፡ ርግጥ ሌንጮ ከ40 ዓመታት በፊትም የቅርብ ዘመዱ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ለታሪክ ትምህርት ወደ ጀርመን ለመሄድ አዲስ አበባ ላይ በተገናኙበት ጊዜ ‹አንተ ታሪክ ተማር፤ እኛ ደግሞ ታሪክ ሰርተን እንጠብቅሀለን› ማለቱ አይዘነጋም፡፡ ዛሬም ከአንደበቱ የሚወጡ ቃላቶች ስለታሪክ መጨነቁን ያመላክታሉ፡፡ ይሁንና ሌንጮ ‹ታሪክ መስራት› የሚለው የእነአባዱላ ገመዳን አይነት ወዶ-ገብት ከሆነ ሀፍረቱ ለሁላችንም መሆኑ አይቀሬ ነው፡፡

በነገራችን ላይ ኦሮሚያን ለመደለል ሌንጮን በዝውውር የማምጣቱ ሥራ የተጀመረው በአቶ መለስ ዜናዊ ዘመን ነው፤ የዊክሊክስ ዘገባም እንደጠቆመው፣ መለስ ዜናው ‹‹ሌንጮ ማድረግ ያለበት እኔን ለማግኘት መሞከር ብቻ ነው፤ ይህን ደግሞ እንዴት ማድረግ እንዳለበት ያውቃል›› ማለቱን አስነብቦናል፡፡ እንዲሁም እ.ኤ.አ በ2007 ዓ.ም ኢንተር አፍሪካ ግሩፕ ባዘጋጀው፣ በአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ሕገ-መንግስታዊነት ጉዳይ ላይ በተካሄደ ኮንፈረንስ፣ የቀረበውን የሌንጮ ለታን ጥናታዊ ፁሁፍ መከራከሪያዎችን በማብራራት ተጠምዶ የነበረው የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ፕ/ር እንድሪያስ እሸቴ እንደነበረ ስናስታውስ፣ በሌንጮ የመምጣት ድርድር ውሳኔ ውስጥ የፕ/ሩን (የመንግስትን) የሰነበተ ሚና እንድንገምት እንገደዳለን፡፡ እርሱም ቢሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ፊንፊኔ ላይ የታየው በ2004 ዓ.ም እንደሆነ ይነገራል፡፡ ከዚህ ሁሉ ጀርባ ደግሞ የአሜሪካ፣ ብሪታኒያ እና ኖርዌይ እጅ እንዳለበት ተሰምቷል፡፡ ባለፈው ዓመት ህዳር ወር መጀመሪያ ሳምንት ሌንጮና አባዱላ ገመዳ አሜሪካን ሀገር በሚገኝ አንድ ሆቴል ውስጥ አርፈው የነበረ መሆኑም የአጋጣሚ ጉዳይ አይመስለኝም፡፡
ኢህአዴግ ስጋት ላይ ከጣሉት የፖለቲካ ድርጅቶች ውስጥ ግለስብን ገንጥሎ ማማለልን ተክኖበታል፤ ከሶስት ዓመት በፊት መለክት ተንፍቶለት ወዶ የገባው አባቢያ አባጆቢር (ከኦነግ መስራቾቹ አንዱ የነበረ ሲሆን፣ ለእንግሊዘኛው ‹‹ዘ-ሪፖርተር›› ጋዜጣ በሰጠው ቃለ-መጠይቅ፣ የድርጅቱ የመጀመሪያ ፕሮግራም ላይ ስለመገንጠል የሚያወራውን አንቀፅ በወቅቱ ተቃውሜ ነበር ማለቱ ይታወሳል) ዛሬ ድምፁ አይሰማም፡፡ ከኦብነግ ጋርም ተደረሰ በተባለ ስምምነት የመጡትን ግለሰቦች፣ ድርጅታቸው አሁንም አፈመዝ ካለመድፋቱ አኳያ ስናየው ጨዋታው ዕቃቃ እንደነበር ይገባናል፡፡ በዚህ ሰሞን ደግሞ ዶ/ር መራራ ጉዲና ከፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ጋር ሊወያይ ወደ ጀርመን አምርቷል፤ ሌንጮ ለታም አዳዲስ አባላትን ሊመለምል እዛው ጀርመን ይገኛል (ሁለቱ ጉምቱ የኦሮሞ ልሂቃኖች ተገናኝተው ይሆን?) በርግጥ ሌንጮ የጀርመን ቆይታውን ሲጨርስ፣ በሆላንድ ያቀደውን ተመሳሳይ መረሃ ግብር አከናውኖ በይፋ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለስ ለጉዳዩ ከሚቀርቡ የመረጃ ምንጮቼ ሰምቻለሁ፡፡

ይሁንና እዚህ ጋ የሚነሳው ጥያቄ ሌንጮ ወደ ሀገሩ ለምን መጣ? የሚል አይደለም፤ እነበቀለ ገርባን የመሳሰሉ ፍፁም ሰላማዊ እና እጃቸው በንፁሀን ደም ያልጨቀየ ፖለቲከኞችን መታገስ ያልቻለ ስርዓት፣ ለሌንጮ የሚሆን ይቅር ባይነትን ከወዴት አገኘ? የሚል ነው፤ ሁለት አርፍተ ነገር የተናገረ ሁሉ ተለቃቅሞ እየታሰረ ሌንጮ ምን ተማምኖ መጣ? በኦሮሚያ ላይ የነገሡት እነአፄ አባዱላና ኩማ ደመቅሳስ ቢሆኑ ከሌንጮ አዲሱ ድርጅት ተነፃፅሮ የሚነሳባቸውን የቅቡልነት መገዳደር ለመጋፈጥ እንዴት ፍቃደኛ ሆኑ? ምናልባት መተካካት የሚባለው ይህ ይሆን እንዴ? ወይስ መረራ ጉዲና ‹‹የኦሮሞ ሕዝብ በቁመቱ ልክ ሥልጣን ይገባዋል!›› እንዲል፣ ሌንጮ ለታም በራሱ ቁመት የተቀነበበ ሥልጣን ቃል ተገብቶለት ይሆን? …የእነዚህና መሰል ጥያቄዎች ምላሽ ዛሬም በሙት መንፈስና በታመመ ሰው እንድትመራ በተፈረደባት ኦሮሚያ ላይ በቀጣይ ከሚኖረው ፖለቲካዊ አሰላለፍ ጋር መጋመዱ አይቀሬ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡

ከዚህ ባለፈ ‹‹ጀግናው›› ኢህአዴግ የሌንጮ ድርጅትን ኦፌኮን ወይም አንድነትን እንደመሳሰሉ ፓርቲዎች ነፃ ተቃዋሚ ሆኖ እንዲንቀሳቀስ ይፈቅድለታል ብሎ ማሰቡ እጅግ በጣም የዋህነት ይመስለኛል፡፡ በርግጥ ኦቦ ሌንጮ ከሳምንታት በፊት ለጀርመን ድምፅ ራዲዮ በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ፣ በቀጣዩ ምርጫ ለመሳተፍ ስለመወሰኑ ሲጠየቅ ‹‹ፖለቲካ በምርጫ በመሳተፍ ብቻ አይወሰንም፤ ሕዝቡን ማስተማርና ማንቃቱም አንዱ መንገድ ነው›› የሚል መንፈስ የያዘ መልስ ሰጥቷል፡፡ የሆነው ሆኖ ሌንጮ ለምርጫ ቅስቀሳ አሊያም ለንቃተ ህሊና ስብከት ፊቱን ወደ ኦሮሚያ ከማዞሩ አስቀድሞ የሚከተለው ጥያቄ ተጋፋጭ ተግዳሮት እንደሚሆንበት ይታሰባል፡- በሽግግር መንግስቱ ወቅት ሥልጣን ላይ የነበርክበትን ጊዜ ተከትሎ አንተን እና ኦነግን አምነው ከቤታቸው የወጡ ልጆቻችንን፣ ወንድሞቻችንን፣ አባቶቻችንን የት ጥለሀቸው መጣህ? ሰማዕታቶቻችንንስ በማን ስም እንዘክራቸው? … Akka dhufaa jirtu barree carraa garii (sihaaqunamu)

አዲስ አድማስ –የአዲስ አበባ ከንቲባና ፖሊስ ኮሚሽነር በ“አንድነት” ተከሰሱ

$
0
0

«ከንቲባ ድሪባ ኩማና ኮሚሽነሩ መከራከሪያቸውን ለፍ/ቤት ያቀርባሉ »

«አንድነት፣ የመንግስት አካላትን በተከታታይ እከሳለሁ ብሏል»

አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት)፣ የአዲስ አበባ ከንቲባና የፖሊስ ኮሚሽነራቸው ላይ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 8ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የመሰረተ ሲሆን ተከሳሾች መልሳቸውን ይዘው እንዲቀርቡ ለየካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጠ፡፡

አንድነት ፓርቲ፤ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” የተሰኘ አገር አቀፍ የ3 ወር ንቅናቄ ማጠቃለያን በአዲስ አበባ ባካሄደበት ወቅት በከተማ አስተዳደሩና በፖሊስ ኮሚሽን እስርና ወከባ እንደተፈፀመበት ገልፆ፤ በደላቸውን በማስረጃ በመዘርዘር ክስ መመስረቱን አስታውቋል፡፡
በፖሊስ ተፈፀመ በተባለ በደል ከንቲባውን በቀጥታ ለምን እንደከሰሰ ፓርቲው ሲያስረዳ፣ የአዲስ አበባ መተዳደሪያ ቻርተር ከንቲባው የከተማዋን ፖሊስ የእለት ተእለት እንቅስቃሴ የመቆጣጠር ኃላፊነት እንዳለበት ስለሚደነግግ ከንቲባውን በቀጥታ ተጠያቂ ያደርጋቸዋል ብሏል፡፡

ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የፓርቲው አመራሮችና አባላት በጅምላ በፖሊስ ታስረው መዋላቸውን ፓርቲው ጠቅሶ፣ የቅስቀሳ ቁሳቁስ ተነጥቀናል፤ ፖስተሮችን እንዳንለጥፍ ተከልክለናል ብለዋል። የፖሊስን የእለት ተእለት እንቅስቃሴ የመከታተል ሃላፊነት የተጣለባቸው ከንቲባውና ኮሚሽነሩ፣ የፖሊስን ህገወጥ ተግባር በቸልታ አልፈውታል ብሏል – አንድነት ፓርቲ፡፡
“በቂ ማስረጃ ከተደራጀ በኋላ ነው ወደ ክስ የሄድነው” ያሉት የፓርቲው አመራሮች፤ ክሱን የመሰረቱት ጠበቃ ተማም አባቡልጉ እና ረዳታቸው መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ከንቲባውና ኮሚሽነሩ የካቲት 24 ቀን መልሳቸውን ካቀረቡ በኋላ መጋቢት 2 ቀን ክርክር ይካሄዳል ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ ፍ/ቤት የለም ብለው እንደሚያምኑ የተናገሩት የፓርቲው መሪዎች፤ የመንግሥት አካላት የሚፈፅሙትን አፈና በይፋ ወደ ፍ/ቤት በመውሰድ የፍትህ ስርአቱን መፈተንና ለህዝብ ማጋለጥ አንዱ የትግል አላማችን ነው ብለዋል፡፡
ከሰኔ እስከ ነሐሴ 2005 ለ3 ወራት፣ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል በመላ አገሪቱ የተደረጉት ሰላማዊ ሰልፎችና ህዝባዊ ስብሰባዎች ህዝብን በማነቃቃት ስኬታማ ውጤት አግኝተንባቸዋል ሲሉ የፓርቲው መሪዎች ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል፤ በፀጥታው ኃይል እና በገዢው ፓርቲ ካድሬ መካከል ልዩነት አለመኖሩን አይተናል፤ በአገሪቱ በተዘረጋ የአፈና መዋቅር ከፍተኛ የህግ ጥሰት እንደሚፈፀም አረጋግጠናል ያሉት የፓርቲው መሪዎች፤ የመንግስት ጫና ሳያሸብረው ፓርቲው ተመሳሳይ ንቅናቄዎችን በተከታታይ ያዘጋጃል ብለዋል፡፡

“የፀረ-ሽብር አዋጁን ለማሰረዝ የሰበሰባችሁትን ድምፅ የት አደረሳችሁት” የሚል ጥያቄ ከአዲስ አድማስ የቀረበላቸው አመራሮቹ፤ “የተሰበሰበውን የህዝብ ድምፅ ወደ ፍ/ቤት ለመውሰድ የህግ ባለሙያዎች እየመከሩበት ነው፣ በሁለተኛ ዙር የክስ ሂደት ውስጥ የሚካተት ይሆናል ብለዋል፡፡ በተካሄደው የ3 ወር የህዝብ ንቅናቄም መንግሥት ለጉዳዩ ይበልጥ ትኩረት እንዲሰጥ ፓርቲው ጫና ማሳረፉን የሚያመለክቱ ውጤቶች መታየት መጀመራቸውን የጠቀሱት የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሃብታሙ አያሌው፤ የፀረ-ሽብር አዋጁ ከመፅደቁ በፊት ለህዝብ ውይይት መቅረብ ሲገባው አዋጁ ወጥቶ ብዙዎችን ሰለባ ካደረገ በኋላ መንግስት ራሱን ለመከላከል የፕሮፖጋንዳና የስልጠና ዘመቻ ጀምሯል ብለዋል፡፡ ይህም ፓርቲያቸው ይዞት የተነሳው ጥያቄ ጫና ማሳረፉንና ትክክለኛ እንደነበር የሚያረጋግጥ መሆኑን አቶ ሃብታሙ ገልፀዋል፡፡

“ማንም ሰው ወይም አካል ከህግ በላይ ሊሆን አይችልም” ያለው ፓርቲው፤ ህግ በሚጥሱ የመንግስት አካላት ላይ በተከታታይ ክስ እመሰርታለሁ፤ በቅርቡም በመንግሥት ከፍተኛ አመራሮችና በገዢው ፓርቲ ላይ ተጨማሪ ክስ ለመመስረት እየተዘጋጀሁ ነው ብሏል፡፡

አቡጊዳ –ደራሲና የአንድነት አመራር አባል፣ አቶ አንዳርጌ መስፍን ፖሊስ ፊት እንዲቀርቡ ታዘዙ

$
0
0

ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ አቶ ዳንኤል ተፈራ ፖሊስ ጣቢያ እንዲቀርብ መጠየቁ በስፋት መዘገቡ ይታወቃል። አቶ ዳንኤል መጀመሪያ ላይ እንዲቀርብ የተጠየቀዉ በስልክ፣ ሲሆን፣ ሕጋዊ መጥሪያ ወረቀት ካልመጣለት በቀር ለመቅረብ ፈቅደኛ ሳይሆን እንዳልቀረ ለማወቅ ተችሏል።

ከአቶ ዳንኤል ተፈራ በተጨማሪ፣ የአንድነት ብሄራዊ ምክር አባል የሆኑትና በርካታ መጽሃፍት በመጻፍ የሚታወቁት አዛዉንቱ አቶ አንዳርጌ መስፍንን፣ ፖሊስ ለመከሰስ እንደተዘጋጀ፣ እንዲቀርቡም እንዳዘዘ ለማረጋገጥ ችለናል።

አቶ አንዳርጌ መስፍን ከጻፏቸው በርካታ መጽሃፍት መካከል «ጥቁር ደም» የሚለው ታዋቂ መጽሃፍ ይገኝበታል። ከአቶ መለስ ዜናዊ ሕልፈት በኋላም፣ «የመለስን ራእይ እናስቀጥላለን» የሚል አቶ መለስን እንደ አምላክ የማቅረብ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ከልክ ባለፈበት ወቅት «በሞት መንፈስ አገር ሲታመስ» የሚል መጽሃፍን የጻፉ ደራሲ ናቸው።

አቶ አንዳርጌ መስፍን፣ በአንድነት ፓርቲ ዉስጥ በአዲሱና ከዚያም በፊት በነበረው የብሄራዊ ምክር ቤት አባል አመራር አባል ሆነው እያገለገሉ ሲሆን፣ የፍኖት ጋዜጣ ኤዲቶሪያል ቦርድ ዉስጥ ሰርተዋል።

ኢሕአዴግ በአቶ ዳንኤል ተፈራና አንዱ አንዳርጌ መስፍን ላይ ምን አይነት ክስ እንደሚያቀርብ ገና የታወቀ ነገር ባይኖርም፣ የአንድነት አመራር አባላትን እና ደጋፊዎች ለማስፈራራት፣ ለፍርድ ቤት መመሪያ በመስጠት፣ እስከ ስድስት ወራት የእስራት ቅጣት ሊበየንባቸዉ እንደሚችል የአንድነት አመራር አባላት ይናገራሉ።

በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየት የሰጡን የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ አቶ ሃብታሙ አያሌዉ ፣ አቶ ዳንኤልም ሆነ አቶ አንዳርጌ መስፍን ፍጹም ሰላማዊ፣ ሰው አክባሪና አገር ወዳድ እንደሆኑ በመግለጽ፣ በነርሱ ላይም ሆነ በሌሎች የአመራር አባላት ላይ እየተደረገ ያለው ጥቃት፣ በሕዝብ ዘንድ የበለጠ ተቀባይነትን ድጋፍ እያገኘ የመጣዉን የአንድነት ፓርቲ ሆን ብሎ ለማዳከም ሲባል በፖለቲካዊ ዉሳኔ የሚደረግ እንደሆነ አስረድተዋል።

«ወያኔ የሚል ቃል ተጠቅመሃል» በሚል ክስ እርሳቸዉም ቀርቦባቸዉ ከአሥራ አንድ ጊዜ በላይ፣ ፍርድ ቤት እየተመላሱ እንደሆነ የገለጹት አቶ ሃብታሙ «ያለ ምንም ጥርጥር ወደፊት እንሄዳለን። መታሰሩ በጣም ቀላል ነገር ነዉ። የሰላማዊ ትግሉ ይቀጥላል» ሲሉም የርሳቸውም ሆነ የሌሎች የአመራር አባላት መታሰር አንድነትን እንደ ፓርቲ፣ ትግሉን እንደ ትግሉ የሚያጠናክር እንጂ የሚጎዳ እንዳለሆነ አሳስበዋል።

“ጥቁሩ ሰው” –የጥቁር ሕዝብ አባት (ከስንሻው ተገኝ)

$
0
0

አንድ ዘመን ሥርዓተ መንግስቱ በመቆየትም ሆነ አባላቱ የአሥራ ሰባተኛው ክፍለ ዘመን የተረት ዓለም ሰዎች ስለ መሰሉን- ሁሉም ነገር ስለገለማን አዲስ ሥርዓት፣ አዲስ መሪ፣ አዲስ ዘመን መናፈቅ ይዘን ነበር። ሰዓሊ ሁሉ፣ ደራሲ ሁሉ፣ ጸሐፌ -ተውኔት ሁሉ እጁን የሚያሟሸው በቴዎድሮስ ሥዕል፣ ተውኔትና ታሪክ ሆነ። ብርሃኑ ዘሪሁን- የቴዎድሮስ እንባ -(መጽሐፍ) ከዚያ በፊት ደጃዝማች ግርማቸው ተክለሐዋርያት- ቴዎድሮስ (ተውኔት) አቤ ጉበኛ – አንድ ለእናቱ (ታሪካዊ ልቦለድ) ጸጋዬ ገብረ መድኅን – ቴዎድሮስ (ተውኔት)…ሥዩም ወልዴ -ሥዕል..ታደሰ ወ.አ….ቅርጻቅርጽ እና የሥነ ጥበባት ትምህርት ቤት ሥስት አራተኛ ተማሪዎች..የቴዎድሮስ ሥዕል ግጥም -ቅኔ- ሥዕል አለፈላት።

ከአሮጌና ከገለማ ሥርዓት ነፃ የሚያወጣ አመጸኛና አመጻ የሚመራ ጀግና ስንፈልግ ባጀንና ቴዎድሮስን አገኘን። ከመቶ አመት በኋላ ነው ቴዎድሮስ የተፈለገው። በአጤው ሥርዓት በአንዳንድ ደራስያንና የዘመን ታሪክን በውዳሴና በነቀፋ በሚያቀርቡ ግለሰቦች ዘንድ እንደጭራቅ ይቆጠር የነበረው መይሳው ካሣ በለውጥ መሪነት የተፈለገበት መሪ ነበር። አብዮታዊው መሪ ጓድ መንግሥቱ እንኳ፥ “ቴዎድሮስ” (ምናልባትም ዳግማዊ ቴዎድሮስ) እኔ ነኝ። የዚህን ሕዝብ አብዮት እንድመራም ከሙታን የተጠራሁ ነኝ” እስከ ማለት ደርሰው ነበር። በቴዎድሮስ መንገድ አልተጓዘም እንጂ። በተረተኞች፣ በተረበኞችና በዋልጌዎች፣ በጐታቾችና በክፍፍል በኖሩ ዘንድ ተወዳጅ ያልሆነው ሕልመኛው ቴዎድሮስ በእርግጥ ከዘመኑ አርቆና አልቆ የሚያይ ስለሆነ ከወቅቱ ደባትርና ከመሳሰሉት ጋር ስምምነት አልነበረውም።

የአገር አመራር በተበላሸና ሕዝቡ የሚያምነው መንግስት ባጣበት፣ ብሔራዊ አንድነቱና ዳርድንበር አስከባሪ በሚሻበት ሰዓት ከመሐሉ የወጣ የጐበዝ አለቃ ሲያደንቅ ይገኛል። እንዲያ ካልሆነ ደግሞ ከአባት መሪዎቹ መካከል ያደነቀውን፣ የሚያደንቀውናና የሚያከብረውን መናፈቅ ይጀምራል። ባያውቀውም። ዛሬን ያስቡአል። አገር እንደ አቃቂ በሰቃ (ኮሎናልቤ) ከስኩት ፍርክስክሱ በወጣበት፣ ሕዝብ እንዲከፋፈልና እንዲጨራረስ ማናቸውም ዓይነት ሴራ በሚጐነጐንበትና መቀበሪያ ሳይቀር “እናገኝ ይሆን” የሚል ስጋት በተጫጫነን ሰዓት “የአንድነትን ጌታ” የአገሪቱን እውነተኛ አባት መናፈቅ ያለ ነው። እነዚህማ ሸጡን። እነዚህማ ለወጡን። መሬቱን ጋጡት። ከትውልዱ አባልነት መብታችን አንዲቱንም አላከበሩልንም። የአንድነትን አባት፣ የዘላለም ኩራታችን ምንጭ፣ ሁሉንም አበሻ በእኩልነት የመራውን ጀግና እንድንናፍቅ ጊዜው አስገድዶአል። ምኒልክን! ይኸ ደግሞ ከመካከላችን እንደ ምኒልክ ያሉ የአንድነት እምነት አራማጆች እስኪንቀሳቀሱ ድረስ ነው።

ነፃነት አንድን ሕዝብ ወደፊትና ወደላይ የሚያንደረድር (የሚወስድ) ኅይል ይሻል። ስለዚህ እውነተኛና ከዚህ በኋላ የሚመሩን (ከዘመኑ ቀድሞ እንደ ተወለደው ምኒልክ) ሰዎችም ወደፊት ብቻ ሳይሆን ወደ “ላይም” ሊመሩን የተዘጋጁ ናቸው። እነዚህ ቆነጃጅት አልተወለዱም አይባልም። እንዲያውም አይተናቸዋል። ዳስሰናቸዋል። ዓለምም አውቆአቸዋል። እኛ ግን ከጥቃት፣ ከእሥራት፣ ከእንግልት…ከመከራ አላዳናቸውም፥ እስክንድርን፣ አንዱዓለምን፣ በቀለን…ካድናቸው። ለወያኔ ወረወርናቸው ለአውሬ። አገርን የሚያድን መሪ ብቻ አይደለም። ዋናው ሕዝቡ ነው። በአድዋ ወሳኙን የመሪነት ሚና የያዘው ምኒልክ ነበር። የተዋጋው ሕዝቡ ነበር። ሕዝባችን ቅንና ጀግና መሪ፣ መሪውም ታማኝና ቆራጥ ሕዝብ ያገኘበት አንድ ወቅት ይኸ ነው።

በአንጻሩ በአመራር የጊዜ ማኅፀን ውስጥ ያሉት ወይም ቢወለዱም በአመራር ጉልምስና ዘመን ላይ የሚገኙት “መልካካም የኢትዮጵያ ልጆች” ወደ አገር አዳኝነቱ መንበር ሲመጡ የሚገጥማቸው ፈተና የትየለሌ ነው። ሁላችሁም አስቡት። የተሸጠ አገርና መሬት የማስመለስ ግዴታ ሊሸከሙ ነው። የተከፋፈለ የሕዝብ ይዞታ ሊያስተካክሉ ነው። የኢኮኖሚውን ሥርዓት መስመር ሊያስይዙት ነው። “ወደ ላይ መምራት” ባልሁት የአመራር ፈርጅ ደግሞ የሚጠብቃቸው ከዚህ ሁሉ በላይ ነው። በታላላቅ ዲታዎችና መንግሥታት ትእዛዝና መሪነት ሥር የወደቀችውን አገር ዜጐችዋ ባለሥልጣናት ይሆኑ ዘንድ መንገዱን መጥረግ አለ። የሕዝብን ነፃነት፣ መብትና ሕዝቡ በአገሪቱ ላይ ያለውን ሉዓላዊነት ማወቅና ማክበር አንዱ ነው። የሕብረተሰቡን መንፈሳዊና ባሕላዊ መብቶች ማረጋገጥና የመንግስትን ጣልቃ ገብነት ማስወገድ፣ የጽሑፍና አሳብን በነፃ የመግለጥ ተፈጥሮአዊ መብቶቹን መንከባከብ፣ ፍትሕና ርትእ በራሳቸው ጐዳና ከመጓዝ እንዳይታወኩ ማድረግ ማለት ነው። ዝርዝሩ በዚህ ይቀጥላል። በመሰረቱ ደግሞ ታሪክ ስትቆፍሩ ብትውሉ አገር የሸጠ፥ የአገር መሬት የቸበቸበ መሪ ታይቶ ተሰምቶ አይታወቅም። በውጭ ምስጢር ባንክ የተቀመጠውን ገንዘብ ቁልፍ መለስ ለሚስቱ ካልሰጣት እሱም በሞቱ ከስሮአል። እኛም ያንን ለማስተካከል ብዙ ጥረት ማድረግ ይጠበቅብናል። የእሱን ወንጀል።

ጆርጅ ኦርዌል በ1984 መጽሐፉ በአምባገነኖች አገዛዝና ዘመን “እውነት ውሸት፣ ማይምነት እውቀት፣ ጥላቻ ፍቅር..ይሆናል” ይላል። ስለዚህ የወያኔን ባሕርያት የምንረዳው ዛሬ አይደለም። አብረን ኖረን የመንግስት ጠባያት ያልሆኑ- መሆንም የማይገባቸውን ስርቆትን፣ ተራ ውንብድናን፣ ቅጥፈትን፣ የጅምላ ግድያን፣ ፀረ ሃይማኖት አቋምን፣ የመብት ረገጣን…በየዓይነቱ እንደ ቡልኮ ተከናንቦ አይተነዋል። አንዳንድ ፀረ ሕዝብ ተግባራት ከየት መጡ ሳይባል እንኳ “የእሱ ሥራዎች ናቸው” ማለት ቀላል ሆኖአል። ትግርኛ ተናጋሪ ወገኖቼ ፀላዔ ሰናይ ይሉአቸዋል። አንዳችም በጐነት ያልተፈጠረባቸው ለማለት ነው። የሰሞኑን ደንባራ ፖለቲካ ለአብነት ማውሳት ለተነሳንበት ጉዳይ ብርሃን ይፈነጥቃል ባይ ነኝ።
በቅጥፈት የተካነው ሰውየ ከተለያቸው ወዲህ ወያኔዎች ያንኑ የተለመደ ውሸት ከመደጋገም በቀር ሌላ መፍጠር፣ በሌላ ስልት ማወናበድ አልሆንላቸው ብሎአል። ውሸት እንደ ቅርስ በነገሠበት አምባቸው ደግሞ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ ያላትና ያፈራችው መንፈሳዊና ስጋዊ ቅርስ ሁሉ አንደኛ መጥፋት አለበት፣ ዳግመኛም- አገሪቱ ካልጠፋች..ታሪክዋ ከዛሬ ተጀመረ መባል አለበት። ታሪክ ከእነሱ አልነሳ ሲላቸው አሁንም ያለፈውን በጐ ታሪክ፣ አኩሪ ባሕልና ጀግንነት፣ የአንድነት ጥበቃ መንፈስ…እንደ ቀላል ነገር ለመግደል ወጥተዋል።

ውሸታቸው ባያልቅም እውነት መናገር እንጀምር

ለዚህ ሥርዓት ማንኛውም ያለፈ ታሪክ፣ ታላላቅ ጀግኖች፣ ዳር ድንበር…የረከሰና የተናቀ፣ መለወጥና መደምሰስም አለበት። ሁላችሁም ለወያኔ ዓላማና ዛቻ፣ ቅጥፈትና ፀረ አንድነት እንግዳ አንዳለመሆናችሁ የሟቹንም ዛቻና አቋም ታስታውሳላችሁ። ስለ ሰንደቅ ዓላማ ምን አለ? ስለ አገሪቱ አንድነት ምን አለ? ምንስ ፈጸመ? ተከታዮቹስ ምን እያሉና ምን እያደረጉ ናቸው? በአጭሩ የሚነገረው ውሸት፣ የፈጠራ ታሪክና ከፋፋይ ፕሮፖጋንዳ አልቆ እናርፈዋለን ብለን ስናስብ ከቶውንም ወፍጮው ይበልጥ እየፈጨ ስለሆነ በውሸቱ መካከል ስለእነሱም እውነቱን መናገር መጀመር ያለብን ይመስለኛል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትሩማን “ሪፐብሊካኖች ስለእኛ ውሸት መናገርን ካላቆሙ ስለእነሱ ያለንን እውነት መናገር መጀመር ያለብን ይመስለኛል” ብለው ነበር።

ስለ ዳግማዊ ምኒልክ ጥቂት ከመናገሬ በፊት ስለ መለስ ጥቂት-እጅግ ጥቂት ለማለት እወድዳለሁ። የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ሲዘልፍ..ዋና ዓላማው የኢዮጵያን ስም መለወጥ ነበር። ስለዚህ ለብዙ ዓመታት ኢትዮጵያን በስም ከመጥራት ይልቅ “አገሪቱ” ነበር የሚለው። ሥልጣን ሲጥመውና አገሪቱም የማትፈርስ (በቀላሉ) ስትመስለው “ኢትዮጵያ” ማለት ይዞ ነበር።

ቀደም ሲል ጆርጅ ኦርዌልን ያነሣሁበት ምክንያት “ውሸት እውነት” የሚሆንበትን ትክክለኛ አጋጣሚ መከሰት በሚመለተው ነው። እንደሚባለው በአምባገነን መንግሥት ሥር የመጀመርያው ጥቃት የሚደርሰው “በእውነት” ላይ ነው። በሕዝባዊ እውነት ላይ! በታሪኩ ላይ ነው። በጀግኖቹ ላይ ነው። ስለዚህ በአገር የተገኘው ቀጣፊ ሁሉ ዛሬ በፕሮፓጋንዳው ሰፈር፣ በአራት ኪሎ ቤተ መንግስትና በየክልሎቹ አመራር አምባ የተሰባሰቡት የሥነ አእምሮ ጠቢባን (pathological liars) የሚሉአቸው የሚታዘንላቸው ሕመምተኞች፣ እውነትን የሚፈሩ፣ እውነት ሲነገር የሚደነግጡ፣ እውነት ሲወጣ የሚረበሹ ናቸው። ስለዚህ “አንድነት” በተፈተነበትና የአገር ሽያጭ በደራበት ሰዓት አንዱ ማወናበጃ ስልት ያው ምኒልክን በወንጀል መክሰስ ነው። “አምስት ሚሊዮን ኦሮሞ ገደለ” ነው አዲሱ አማርኛ። ለመሆኑ በምኒልክ ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር ከ5 ሚሊዮን ይበልጥ ነበር? ከዚህ ውስጥ የኦሮሞው ቁጥር ስንት ነበር? ለመሆኑ ምኒልክ ማነው? ምን ሰራ? ሕዝብን ከጫጫታው (ከዘመኑ) ለማዳን መሞከር አለብን ወይስ ታሪክ ነፃ ያወጣዋል በሚል አደብ እንግዛ?
“ ጥቁሩ ሰው” – እንደ ሰው

ታሪክ የበጐነት ምስክር – ወይም ለበጐነት የሚያደላ እማኝ ብቻ አይደለም። የአጥፊዎችን ጥፋት፣ የከሐዲዎችን አሳፋሪ ተግባር፣ የአምባገነኖችን ክፋትና ኢሰብአዊ አገዛዝ ጭምር ዘግቦ ለትውልድ ያስተላልፋል። ይሁንና ታሪክ የማያውቁ አዋቂዎች በመምሰል፣ አዳዲስ ድርሰት በመጻፍ ከሐቅ ግድግዳ ጋር የሚላተሙ፣ በባሕርያቸው ፀላዔ -ሰናይና የእውነት ጠላትነት ያላቸው ደካማ ፍጡራን መድረክ ሲደላደልላቸው የሚያዥጐደጉዱት ቅጥፈት መታለፍ እንደማይገባው እየተከሰተልን መጥቶአል። እስካሁን ግን “ለቅጥፈት ማስተባበያ” ወይም ማስተካከያ አያስፈልገውን በሚልና ውሎ አድሮ ሐቅ ይረታል በሚል እምነት ቅጥፈት ቅጥፈትን፣ ፈጠራና ድንፋታ ራሱን ሲፈጥርና እንደአሜባ ሲራባ በቸልታ ያለፍናቸው ጉዳዮች ሞልተዋል። ከሁሉም ከሁሉም አንድን ኅብረተሰብ የሚያቃጥለው የታሪኩና የጀግንነቱ መታወቂያ ሰነዶች፣ ግለሰብ ጀግኖችና ብሔራዊ መከበሪያ ሐውልቶቹና ቅሪቶቹ መደፈር ነው። በዚህ ረገድ ብዙ ተደፈርን። በዓለም አቀፍ ደረጃ የ”ታላቅ መሪነት”ን ደረጃ የተቀዳጁትን፣ ጠላት ሳይቀር የሰገደላቸውን መሪዎቻችንን ሳይቀር ዛሬ የራሳችን ልጆች በእነዚህ ላቅ ያሉ ሰዎች ላይ ሲያቅራሩ ስንሰማ እንቅልፍ መንሳቱ አልቀረም።

የወያኔ ቀዳሚ ሰልፍና ፍልስፍና ሕዝብን መከፋፈልና አገሪቱንም ማፍረስ መሆኑን ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠራጥረው ይከራከሩን የነበሩ ሰዎች ዛሬ ከግንዛቤ በመነሳት ራሳቸው “አገር እየጠፋ” መሆኑን እያረዱን ነው። በወያኔዎች በኩል ደግሞ የአገሪቱንም ሲሳይ እያፈሱ መልሰው አገሪቱን ለማጥፋት ማናቸውንም ሴራ እየፈፀሙ ናቸው። የትሮትስኪ ታሪክ መዝጋቢና የሩሲያን አብዮት ክሽን አድርጐ ያቀረበው አይዛክ ዶቸር ስለ ሩሲያ አብዮት መሪዎች ሲጽፍ “እነዚህ ሰዎች የማያውቁትንና ሊያውቁ ያልቻሉትን አገር ተረከቡ። ወይም በእጃቸው አስገቡ። ቀጥሎም የሚያምኑበትን አቃጠሉት። አቃጥለውም ሰገዱለት” ይለናል። አዎን ወያኔዎች ጥገትዋን አልበው እየጠጡ፣ አርደው ሊበሉአትም ፈለጉ” ለማለት ይቻላል። በተአምር በእጃቸው የገባችውን አገር ማዳን የብዝበዛቸውና የዘረፋቸው ዋስትና በሆነ ነበር። ይልቁን እዚህ ከደረሱ በኋላ እንኳ የዚህን አገር አንድነት ማዳን ቢሞክሩ ቢያንስ ልጆቻቸው አገር አለን እንዲሉ ባስቻላቸው ነበር። ይልቁንም ኦሮሞዎች ነን የሚሉ በዕድሜም፣ በግንዛቤና በአእምሮ ያልበሰሉ ልጆችን በመመልመል የሚያንጫጩብን እነዚሁ አገር በእጃቸው የወደቀ ሰዎች ናቸው። ምኒልክን ለመወንጀል የክሱን ነጥብ ሁሉ ከየት አገኙት?

እውን እነዚህ ጨርቋ ሕፃናት – የጨርቋ አእምሮ ውጤት የሆነ ፕሮፓጋንዳ በጩኸትና ሰላላ መላላ በሆነ ልሳን ሲያስተጋቡ የዚህ አገር ዋልታና ወጋግራ የሆነው ኦሮሞው ኅብረተሰብ ምንኛ እንደሚያፍርባቸው ትገነዘባላችሁ? ለመሆኑ ከኢትዮጵያ ታሪክ ባለቤትነትና ክብር ሊነጥለን የሚችል ማነው? ጃዋር? አያት ቅድመ አያቶቻችን ደምና አጥንት የሰጡአት አገርኮ ናት! የወያኔ የመስዋዕት ጠቦቶች ለሆኑት እነዚህ ኅፍረተ ቢሶሽስ የኦሮሞን ውክልና ማን ሰጣቸው? ስለማያውቁት፣ ስላላወቁትና ሊያውቁትም ስላልፈለጉት ሕዝብ በድፍረት መናገርን ከየት አመጡት? እነዚህ ልጆች “ወገኔ ነው” የሚሉትን ኦሮሞውን ኢትዮጵያዊ ከሌሎች (ለምሳሌም አማራው) ብሔሮች ጋር በማጋጨት ሊያመጡ የሚችሉትን ትርፍ ሊነግሩን ይችሉ ይሆን? ወይ ልክፍት!

ከሶቪየት ኀብረት ኤምፓየር መፍረስ በኋላ አንዳንድ የአሜሪካ የፖለቲካ ፈላስፎች እንደ ሶስተኛ አገር የሚታዩ የኅብረተሰብ ጽናትና ሰላም ያላቸው አገሮች በተቻለ መጠን ተሸንሽነው ብዙ አገሮች እንዲወጣቸው ሰፋፊ ጽሑፎችን በገበያ አውለዋል። ከእነዚህም መካከል መለስ ዶላር ያፈስስለት የነበረው የሐርቫርዱ ሳሙኤል ሐንቲንግተን ይገኛል። ከዚያም ሌላ አንዳንድ የሲአይኤ ቅጥረኞች ጽሑፎች በየጥናቱ መደብር አሉ። ዩጐዝላቪያ የዚህ ፍልስፍና “ጊኒፒግ” ናት። ከ1991 ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ የምትታመሰው በዚሁ ረቂቅ የጥፋት አውሎ ነፋስ መሆኑን አንዘንጋው። እነሆ እንደ ጃዋር ያሉ አለማወቃቸውን እንደ እውቀት፣ ጮኾ መናገርን እንደ ሐቅ፣ የፈለጉትን ጥጃ የአምልኮ ጸጋ በመቁጠር አየረ አየራቱን ሲያተረማምሱት ከእንግዲህስ “ተመከር! ተሳስተሃል! በአገር፣ በሕዝብና በታሪክ ላይ ያመጽህ ባለጌ ነህ” ማለት የሚገባ ይመስለኛል። ልድገመውና “በአባቴ ሙስሊምና ኦሮሞ፣ በእናቴ ክርስቲያንና አማራ ነኝ” በማለት ጅምሩን በማይጠቅመው መደምደሚያ ያበላሸዋል። ጃዋር መሐመድ። ሙስሊም፣ ክርስቲያን፣ አማራ፣ ኦሮሞ! ከኢትዮጵያዊነት ውጭ ምን ይሁን?

ጐበዝ በዚህ ዓይነቱ ጊዜ ከየጉድጓዱ ብዙ አይጦች ሊወጡ ይችላሉ። አትደነቁ። አንዳንዶቹ የመታወቅ አባዜ (የእንክብካቤ እጦት አባዜ…ወዘተ) የተከሰተባቸውና “እገሌ” ለመባል የሚጣባ ሕመም ተሸካሚዎች ናቸው። አንዳንዶቹ ቀጥታ ራሳቸውን ለማያውቁት ተልእኮ በመስዋዕትነት ለመሰጠት በምንዳ የተገዙ ናቸው። ለዚህ ዓይነቱ ተልእኮ የተመደበ በጀት ስላለ ሰው ከተገኘ ገዥ አለ። ሕሊና ለሌለው፣ ለሚሸጥ ወይም ለሚያከራይ ዘወትር ክፍት ቦታ አለ። እነ እንቶኔ በዚህ የሕመም ዘርፍ ላይ በመሆናቸው ሊታዘንላቸው እንጂ ሊታዘንባቸው አይገባም። ቀደም ሲል የተጠቀሰውን ጉብል አንድ ጊዜ በአንድ የቨርጂኒያ አዳራሽ ትልቅ ስብሰባ ላይ አይቼዋለሁ። እዚያ ስብሰባ ላይ ወደ ዘጠኝ መቶ የሚጠጉ ሰዎች ነበሩ። ይሁንና እስኪታወቅ ሳይሆን እስክንሰለቸው ድረስ የባጡንም የቆጡንም ሲናገር ቆይቶ “እዚህ ሥፍራ ኦሮሞና ሙስሊም ለምን አልተጋበዘም?” ይላል። መቸም “ከእናንተ መካከል ኦሮሞ የሆናችሁ ተነሱ! ሙስሊም የሆናችሁ ተነሱ!” አይባልም። ይኸ ደግሞ ከቅን አእምሮ የመነጨ ነው አይባልም። የሌሎቹንም “ዋልጌ ጭንቅላት” ባለዶላሩ ዋሐቢ፣ የሽብሩ ልጆች እነ…..በማናቸውም ሂሣብ ሊገዙአቸው አይፈልጉም አይባልም። ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን እስከ ተዋጉላቸው ድረስ።

አንዳንድ የዋሐን ወገኖቼ የእነዚህን በጥላቻ የተፀነሱ፣ በጥላቻ የተወለዱና የጥላቻን መርዝ በመካከላችን የሚዘሩ ሰዎችን ተጽእኖ እስከ መፍራት ደርሰዋል። ኦሮሞው ኅብረተሰብ እንዳይቀበላቸው ነው? ያፍርባቸዋል። ከአገር እድር ያስወጣቸዋል። ስለዚህ በሶሻል ኔትወርኩ ረገድ ኅላፊነት የወሰዱ ሁሉ ለኦሮሞ ወገኖቻችን የመናገር ዕድል (በሰፊው) መክፈት አለባቸው። በአንድ በኩል ደግሞ ታሪክ የሚያቆሽሹትና ወደ ኋላ እየተመለከቱ የሚናገሩት እነዚህ ወገኖች ርስበርሳችን ስለጀግንነት፣ ስለታሪክ፣ ስለታላቋ ኢትዮጵያ ማንነትና ምንነት….እንድንነጋገር ዕድል እያስገኙልን ይመስለኛል።

ጥቁሩ ሰው – ለጥቁር ሕዝቦች

ጀርመኖች በኦቶፎን ብዝማርክ፣ ጣልያኖች በጁሴፔ ጋሪባልዲ፣ ፈረንሳዮች በናፖሊዮን ቦናፓርቲ፣ በዣንዣክ ሩሶ፣ በዣን ደ አርህ፣ አሜሪካኖች በጆርጅ ዋሽንግተን፣ አብርሃም ሊንከን…..እንግሊዞች በዊልያም ዘኮንከረር፣ በዊንስተን ቸርችል፣..ይኰሩም ይኩራሩም ይሆናል። የእነዚህን ሰዎች ጀብዱ ስንሰማ፣ በትምህርት ቤቶች ዝናቸውን ስናወሳና ስናጠናቸው ስለኖርን የራሳችን ሰዎች እስኪመስሉን ድረስ በልባችን ጽላት ላይ ታትመዋል። ሰዎቹ በየዘመናቸው ለአገሮቻቸው ባበረከቱአቸው አስተዋጽዎችና የተለዩ አገልግሎቶች የየአገራቸው “አባቶች” እስከ መባል ደርሰዋል። በፖለቲካና በወታደራዊ መስክ ብቻ ሳይሆን እነዚህ አገሮች ብቻ ሳይሆኑ ሌሎችም አያሌ አገሮች ለአለም ጸጋ በሆኑ ልጆቻቸው አማካይነት በኪነ ጥበባት፣ በሳይንስ፣ በሥነ ጥበባትና በኬንያ (ቴክኖሎጂ) ባርከውናል። ልጆቻቸውን ተጋርተናል።

እንደገና ጀርመኖች በሒትለር፣ ጣልያኖች በሙሶሊኒ፣ ካምቦድያውያን በፓልፓት፣ ኡጋንዳውያን በኢዲአሚን፣ወዘተ እጅግ እንደሚያዝኑና እንደሚሸማቀቁ ይሰማኛል። እኛም የዚች አገር ጐስቋሎች ኢትዮጵያውያን በሃያ አንደኛው ምዕት ዓመት መለስ የሚሉት እኩይ ነፍስ ለኢትዮጵያ የዛሬው ትውልድ በመስጠታችን ጭብጥ ልናክል ነው። ሞተ ከተባለ ወዲህ እንኳ አገር እየሰጠ፣ አረብና ሕንድ እያነገሰብን፣ ምውት መንፈሱ እንዳሸበረን ነው። ሁላችንም የዓለም ዜጎች ይቺን የጋራ መሬት እኩል እንደምንባረክባት ሁሉ ጀግንነታቸው ያሞቀን የሃያኛው ክፍለ ዘመን ግዙፋን ባለታሪኮች ነበሩ። ጀኔራል ድዋይት አይዘንሐወርን፣ ጀኔራል ጆርጅ ፓተንን፣ ፊልድ ማርሻል ሞንትጐመሪን…እንደራሳችን እንጋራለን የሚል እምነት አለኝ። “እነዚህ ሰዎች ምነው ኢትዮጵያውያን ቢሆኑ ኑሮ” ብዬ በቁጭት አልናገርም። የአንዲት ምድር (ራችን) ልጆች በመሆናቸው ብቻ እንደራሳችን ጀግኖች- የሁላችንንም እምነት በተግባር ያዋሉ፣ የሁላችንንም ጦርነቶች ተዋግተው ያሸነፉ ስለሆኑ “የሁላችንም” እናደርጋቸዋለን። እንደ ምኒልክ ያሉ – እንደ ጐበና ያሉ- እንደ አሉላ ያሉ- እንደ አበበ አረጋይና በላይ ዘለቀ ያሉ ጀግኖች አባቶች ያሉት አገር ልጆች በመሆናችን እኛም ለዓለም ባበረከትናቸው ጀግኖቻችን ኩራት ይሰማናል። በምኒልክ የተመራው የኢትዮጵያ ሠራዊት በአንዲት ጀንበር የአንድ አውሮፓ ኅይል ካንኮታኰተ በኋላ በማግሥቱ የጠቅላይ ሚኒስትር ክሪስፒ መንግሥት (በኢጣክያ ሕዝብ እንደጐርፍ መውጣት ምክንያት) ከሥልጣን ከመወገዱም በላይ በናፖሊ ከተማ የነበረውን የንጉሡን (አምቤርቶ) አልጋ ወራሽ ሕዝቡ በትከሻው ተሸክሞ “ታላቁ ምኒልክና የአድዋ ጀግኖች ኢትዮጵያውያን ለዘላለም ይኑሩ ብለህ ጩኽ” በማለት ቀኑን በሙሉ በዚህ መልክ ሲያንባርቅ እንዲውል አድርገውታል። በማግሥቱ የወጡ የኢጣልያ ጋዜጦች ኢጣሊያ ራስዋ እንደተማረከች አድርገው ጽፈዋል። ምኒልክ!
አንዳንድ የጦርነት ዘገባዎችን፣ መጻሕፍትንና ታሪኮችን ለተከታተሉ ጀግኖች የሠራዊት አዛዦች ድል ካደረጉ በኋላ “ጠላት ነው” በማለት አይንቁትም። ወይም በእጄ ገብቶአል ብለው አይበቀሉትም። እንዲያውም በ”ተቃራኒ መስክ” የተሰለፈውን በክብር ያስተናግዱታል። በጦር መሪነታቸው እጅግ የተደነቁና በመሠረቱ በተቃራኒ ዐውድ ተሰልፈው ታሪክ የሰሩ ጄኔራል መኰንኖችን ላስታውስ እወዳለሁ። በአሜሪካ የሲቪል ጦርነት የኮንፌደሬሽኑ ጦር አዛዥ ሮበርት ሊ በአሜሪካ ሕዝብ ዘንድ ከሜጀር ጄኔራል ጆርጅ ማክሊላን የበለጠ ይታወቃል። በየከተማው መንገዶች ተሰይመውለታል። የጦር ምሽጐች በስሙ ተጠርተዋል። ከስለጠነው ዓለም ሌላም ማስረጃ ለማምጣት ይቻላል።

የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ከሚያውቃቸው ታላላቅ ጄኔራሎች መካከል ሒትለር በሰሜን አፍሪካ በዋና አዛዥነት ያሰለፈው ፊልድ ማርሻል አርዊን ሮሜል (የበረሃው ተኩላ) በምዕራብም ሆነ በምሥራቅ- በአክሲስ ፓወርስም ሆነ በአላይድ ፎርስስ እጅግ የተደነቀ ነው። በመሠረቱ ለጀግና ሠራዊት ባላንጣው የተከበረ ነው። በሬሳው አይጫወትም። ወይም ወያኔዎች በኢትዮጵያ ሠራዊት ሬሳና የደከመ አካል ላይ ቆመው እንደ ፈነደቁትና እንደሸለሉት ሳይሆን የሰብአዊነት ክብርና መገመቻ ጠላትን እንደአግባቡ ማድነቅ መቻልም ነው። ለተፋላሚ ክብር መስጠትና እንክብካቤ ማድረግ ነው። እነዚህ ሰነፎች ገዥዎቻችን ምንኛ ደካሞች እንደሆኑ አያችሁት?

ከአገራችንምኮ ለዚህ ክርስቲያናዊ አርአያነትና የሰለጠነ ወታደራዊ ባሕል ምሳሌ አንቸገርም። አድዋ ላይ በአንድ ጀምበር በርከት ያሉ ጄኔራል መኰንኖችን ድባቅ የመታውና ያንኑ ያህል የማረከው እምዬ ምኒልክ በእጃቸው የገቡትን ምርኮኞች ማለፊያ ምግብ እየሰሩ (ፓስታ፣ ሞኮሮኒ ወዘተ) በደንብ ከመመገብ ባሻገር ራሳቸውና ደገኛይቱ ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ እንደ ሐኪም ቁስል መጥረግ፣ ፋሻ ማሠርና የመሳሰሉትን የሕክምና አገልግሎቶች ጐንበስ በማለት ፈጽመዋል። ጦርነቱ እንዳለቀ ምሽት ላይ በየድንኳኑ እየተዘዋወሩ “ገደልን ብላችሁ እንዴት እንዲህ ያለ ፍከራና ሽለላ ታደርጋላችሁ?” በማለት ኅዘናቸውን እስከ መግለጥ ደረሰዋል። (አንቶኒ ሞክለር ኅይለስላሴስ ዋር በሚለው መጽሐፉ በመጀመሪያው እትም እንደ መግቢያ አድርጐ ገልጦታል።

በሌላው ታሪካቸው እንደ ተገለጠው አጤ ምኒልክ ከንጉስ ተክለሃይማኖት (ራስ አዳል ይባሉ ከነበሩት) ጋር እምባቦ ላይ ሲዋጉ የጐጃሙ ገዥ ቆስለው ሲማረኩ ራሳቸው ከመሬት ተቀምጠው ቆስሉን በጨውና በአልኮል እየጠረጉ እንዳስታመሙአቸው ይታወቃል። በኋላ ደግሞ አጤ ዮሐንስ ያለ የሌለ ጦራቸውን አስከትተው ጐጃምን ወርረው፣ ሥፍር ቁጥር የሌለውን ሕዝብ ዓይን በጋለ ብረት አቃጥለው፣ ሠራዊታቸው ቤት እየዘረፈ፣ በወንዱ ፊት ሚስቱን እየደፈረና ጐተራ እያራገፈ በጠቅላላው ንጉሰ ነገሥቱ እያዩ ሲያቃጥሉ አጤ ምኒልክ “እባክዎ ጃንሆይ ከንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ጋር ተጋጨሁ ብለው ሕዝብዎን አይጨርሱት” በማለት እንደተማጸኑአቸው የተጻፈ ታሪክ ሞልቶአል። እንዲያም ቢሆን የትናንት የአገሪቱን መሪዎች ለመወንጀል አልሻም።

ወደ ሃምሳ ዓመት የሚገመት ሙያዬ ከብዙ ሰዎች ጋር አገናኝቶኛል። እንደ ደጃች ኅይለ ሥላሴ ጉግሳ ካሉ ከሐዲዎች- እንደ ራስ መስፍን ካሉ አርበኞች- እንደ ጋዜጠኛ (ከንቲባ) ደስታ ምትኬ ካሉ በየአድዋው ጦርነት ላይ ከዋሉ የታሪክ ምስክሮች፣ እንደ ፊታውራሪ ተክለሃዋርያት ካሉ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ አንስቶ አገሪቱን ከፊውዳል ሥርዓት ለመጠራረግና የፖለቲካውን ሥርዓት ግልብጥብጡን ለማውጣት ከደከሙ ምሁራንና መሪዎች ጋር ትከሻ ለትከሻ ባልተሻሽም አጠገባቸው ተቀምጨ ያልነበርሁበትን ዘመን ልኖረው ሞክሬአለሁ። የሁሉም የጋራ ምስክርነት (የጀግናውም የባንዳውም) ኢትዮጵያ እንደ ምኒልክ ያለ መሪ ታድላ አታውቅም። እግዚአብሔር ይመስገን፤ ጻድቁ ዮሐንስ በጐ አእምሮ የወለደው ነው።

አዎን የዚህ መጣጥፍ አጀማመሬ አውሮፓውያንና አሜሪካውያን (ሌሎችም ሕዝቦች) የሚኮሩባቸው መሪዎችና በመሰረቱም የሚያፍሩባቸው አምባገነኖችም ሊኖሩባቸው እንደሚችል ላመለክት ሞክሬአለሁ። እንዲያውም አገር በችግር ማጥ ውስጥ ስትገባ ልባቸውን፣ ጭንቅላታቸውንና እጃቸውን አስተባብረው ሕዝብን በአንድ ጐራ አሰልፈው ከታላቅ ውጤት ላይ ያደረሱት እንዲህ ያሉ መሪዎች የየአገሮቻቸው አባቶች እስከ መባል ደርሰዋል። ጆርጅ ዋሽንግተንን አላነሣሁምን? የመቶዎች ባሪያዎች ባለቤት ቢሆን እንኳ ሁሉም አሜሪካዊ የአገሪቱ አባት ይለዋል። በዚሁ ልክ የኢትዮጵያን ታሪክ የመረመሩ የውጭ አገር የታሪክ ስዎችና ኢትዮጵያውያን ምሁራን ሁሉ አጤ ምኒልክንና አሳዳጊ አባታቸው አጤ ቴዎድሮስን የኢትዮጵያ አባቶች ይሉአቸዋል። ለከፈሉት የሞት ዋጋ፣ ለተሸከሙት የኢትዮጵያ ግዙፍ ተራራ፣…ይኸ የሚበዛባቸው ክብር አይደለም። ሁለቱ ሰዎች (ባይሆን ጣይቱን እንጨምራለን) ይህን ክብር ካልተቀዳጁ ማን ሊቀዳጅ ነው? ጣይቱን እናታችን ብንል ምንኛ ደስ ባለኝ!

ያለፈው ወር የእምዬ ምኒልክ መቶኛ ሙት ዓመት ነበር። አሸናፊዎች ሁሉንም እንደ ፈለጋቸው በሚያደርጉበት፣ በብር በወርቁ በሚያዙበት፣ ታሪክ ድርሰት ሆኖ በማረሻ በሚጻፍበት፣ የአገር ዳር ድንበር ያለ ጠባቂ በሚቀርበት፣ ጀግኖች የወደቁለት አንድነት መጫወቻ በሆነበት፣ ዜጐች እየተነቀሉ ነጩ፣ ብጫው፣ ጠይሙ…የባዕድ አገር ነጋዴ የሚምነሸነሽበት መሬት ጥንቡን በጣለበት ዘመን ላይ፣ መንግስት ሌባ፣ ሌባም መንግሥት በሆነበት ወቅት-እንደ መገኘታችን ብዙ ብዙ -የለም፤ ሁሉም በጐ አገራዊ ባሕል ትርጉም ባጣበት ሰዓት በሕዝብ ዘንድ ያለው ሐቅ ሁሉ ተጠቂ መሆኑ አንድና ሁለት የለውም። እነሆ ከሃያ ሦስት ዓመታት ወዲህ የኢትዮጵያ ታሪክ ተለውጦ ስለኢትዮጵያ አንድነትና ታሪክ የቆመው ሕዝብና ተቃዋሚ ኅይሎች ከሐዲ ሲባሉ…ወርቁም ሚዛኑም እንዳልነበረ ሆኖአል። ስለዚህ በምኒልክና በጣይቱ ላይ የሚወርደውን የፕሮፓጋንዳ መዓት፣ የፈጠራ ድርሰትና ልብ ወለድ ድርሳን ስታስቡት ለመሆኑ ከወያኔ አምባ የተጠበቀው ሌላ ንግርት ምን ነበር? በግልጽ የኢትዮጵያን አንድነት ተቋቁመው ከዚህ ደረጃ ያደረሱት ግለሰቦች በረከት፣ ስብሐት ነጋ፣ ዐባይ ጸሐይና ግልገል ወያኔዎችና እንደ ወያኔ የማሰብ በሽታ ከሸመቱ ግለሰቦች ምን ይጠበቅ ነበር? የኢትዮጵያን አንድነት አባቶችና ጠባቂዎች እንዲያወድሱ ነበር? ቀደም ሲል እንዳልሁት ታሪካችንን በጽሞና እንድንመረምር ዕድል የሰጡን ይመስለኛልና በበጐነት እንጠቀምበት።

ቀደም ሲል ስማቸውን ያነሣኋቸውን ጋሪባልዲንና ቢዝማርክን ለምክንያት ነበር የጠቀስሁአቸው። ጋሪባልዲ ኢጣልያንን ለማዋሐድ፣ ቢዝማርክ ተበታትና የቆየችውን ጀርመንን አሰባስቦ አንድ አገር (ኔሽን) ለማድረግ ሲወጡና ሲወርዱ የነበሩበት ሰዓት (በዘመነ ጓድነት) አንድ ነው። አፍሪካዊው መሪ (ጥቁር ሰው) ምኒልክ በተመሣሣይ ጥሪ በታሪክ መድረክ ላይ የታየውም በዚሁ የታሪክ ወቅት ነው። በዚህ ታሪካዊ ወቅት ምን ተፈጠረ? በዘመናት ውስጥ ተሸርሽራና ተበጣጥሳ የቆየችውን ኢትዮጵያ ዳር ድንበር አንድ አደረጉ። ሰበሰቡአቸው። በእነዚህ ተግባራት ብቻ ዓለም ካደነቃቸው ከነጋሪባልዲ ጋር ታሪክን ሊሻሙ የሚገባቸው ምኒልክ ዛሬ በወያኔና አንዳንድ አጫፋሪዎች ምን እየተባሉ ነው? አንዱና ጥሩ ውሸት መፍጠር ያልቻሉት ፀረ አንድነቶች የጡት ቆረጣ ወንጀል ነው። ይኸ ከየት የመጣ ነው? ለመሆኑ ወንጀሉስ የት ነው የተፈጠረው? ትክክለኛም ሆነ አልሆነ መልስ የመስጠቱን ዕዳ የሚሸከሙት ወያኔና ሁሉም ፀረ አንድነት የሚያቀነቅንበት ዜማ የሚጫወቱት ናቸው።

በሌላ በኩል ደግሞ የኦሮሞ ሴቶችን ጡት ስለማስቆረጥ የተፈጠረው አጉል ነጥብ ከአማራው (ማለትም ከክርስቲያን) ባሕልና እምነት ጋር ጨርሶ የሚሄድ አይደለም። በአንጻሩ ለጋብቻና ለመሳሰለው ዕድሜና እጆቹ እርፍ ለመጨበጥ የደረሰ ኦሮሞ ገበሬ ሚስት ሊያገባ የሚችለው አማራ በመስለብ መሆኑን እንኳ ለመስማት ፈልጌ አላውቅም። በእውነቱ ግን ወንጀሉ በየዘመኑ ለሚፈጠር ኦሮሞ ሁሉ እንዲቆየው አልሻም። በዚሁ ዓይነት አጤ ዮሐንስ ወሎንና ጐጃምን “ፈጅተውታል፣ አቃጥለውታል” በሚል የዛሬና የወደፊቱ ጐጃሜና ወሎየ ሁሉ ትግሬንና አጤ ዮሐንስን እንዲጠላ አላደፋፍርም። በውነቱ ደግሞ ዘወትር የምናወድሰው ታሪካችን አላስፈላጊና አሳፋሪ ጓዝም አለው። ቀደም ሲል ያነሳናቸው የኢጣልያንና የጀርመን የዛሬ ትውልዶች የየራሳቸው አንካሳ ታሪክ አላቸው። እኛ ላይ ሲደርስ ነው ከተደረገውና ከተፈጸመው ሁሉ በላይ የታሪክ ድሪቶና ቡትቶ ያየነው።

ኢትዮጵያዊነት አረጀ?

ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትንና የዚችን አገር ቁሳዊና መንፈሳዊ ሀብታት፣ ዜግነትንና እሴትን የሚጸየፍ አንድ ምስኪን ልጅ በአልጀዚራ ሲናገር ብዙ ኢትዮጵያውያን ሰምተውታል። የጋናው ኒክሩማህ፣ የኬንያው ኬኒያታ የኮትዲቮሩ ሑፌትቧኘ፣ የማላዊው ካሙዙባንዳ…በጆርጅ ፓድሞን መሪነት..ወደ አንድ የለንደን የስብሰባ አዳራሽ (በ1953 እ.አ.አ) የገቡበት ሁኔታ ትዝ ይለኛል። አዳራሹ በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አሸብርቆአል። እነዚህ በኋላ የአፍሪካ ታላላቅ መሪዎች የሆኑ የዚያን ዘመን የነፃነት ታጋዮች አረንጓዴ፣ ብጫና ቀይ የሆነውን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ እያውለበለቡ ወደ አዳራሹ ሲገቡ የነበረበትን የክብር ሰልፍ ሳስብ በቦታው ለመገኘት እንደ ታደለ ሰው ዛሬ የልቤ ኩራት ወደር ያጣል! የጃንሆይ አጤ ኅይለሥላሴን ምስል በኮታቸው ክሳድ ላይ ያደረጉት እነ ንክሩማህ ሁኔታ ወለል ብሎ ይታየኛል። አዳራሹ በአእምሮዬ ይመጣል። ኢትዮጵያዊነትና “ኢትዮጵያዊ ነኝ” የዓለም ጭቁን ሕዝቦችና በተለይም የጥቁር ሕዝብ ኩራት እንደሆነ እነ ጃዋር ሰምተው ያውቃሉ? ለጥቁር ሕዝቦች ሁሉ “ኢትዮጵያ” ምን ትርጉም እንደምትሰጥ ለመሆኑ እነዚህ ይቺን አገር ካላፈራረስን እንሞታለን የሚሉ ሰዎች በመጠኑስ ቢሆን ያውቁ ኖሮአልን? “ኢትዮጵያዊነት” ከተራ ስያሜና ከአንድ ተራ አገር መጠሪያ በላይ መሆኑን ያውቁ ኖሮአልን? ለእነዚህ ሕዝቦች ዞሮ መግቢያና መመኪያ …መንፈሳዊ ቤታቸውና ምስለ-ገነት የመሆንዋን ሐቅ ምን ያህል ሰምተዋል? የማርከስ ጋርቪን ፍልስፍና ያውቁታልን? ዛሬ ዛሬ ደግሞ እግዚአብሔር (ያህዌ ኤሎሒም) ለአዳምና ለሔዋን የፈጠረላቸው ገነት በአንደኛዋ የኢትዮጵያ ክፍል የመሆንዋ ግልጽነት አማራውን፣ ኦሮሞውን፣ ትግሬውን፣ ከምባታውን፣ ሐድያውን…ለሁሉም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት ተጨማሪ ኩራት በሆነ ነበር። (ከላይ የነካካኋቸውን ነጥቦች በይበልጥ ለማወቅ ማርከስ ገርቪንና ዱቢድ ሜሬዲትን ያነብቡአል።) በነገራችን ላይ ማርከስ ገርቪና ራስ መኮንን ይባል የነበረው ጃሜይካዊ ጓደናው በጃንሆይ ቅሬታ ያደረባቸው እነሱ ካሰናዱአቸው 3ሺ ዓለም አቀፍ ተጋዳዮች ይልቅ በእንግሊዝ ጦር በመጠቀማቸው መሆኑ ይነገራል።

በኢትዮጵያዊነት ማፈር እንደ አልጀዚራው ጉብል ባሉ የሐቅ ማይማን እየተነገረ ነው። ያ ጉብል – ጃዋር ደግሞ በሌላ ጊዜ በመቅለስለስ መልክ “ እኔ በአባቴ ኦሮሞና ሙስሊም፣ በእናቴ አማራና ክርስቲያን ነኝ።” ሲል አድምጨዋለሁ። የልጅነት ተማሪዬ ሌንጮ ለታ የደረሰበትን አጉል አጋጣሚ ያስታውሰኛል። የኦነጉ መሪ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ልብ ሲዘዋወር በነበረባቸው ወራት በጣም የተከበሩ አባቶች ወደ ነበሩበት ወደ ጅባትና ሜጫ ሄዶ ነበር። ያ አካባቢ እጅግ አስተዋይ የሆኑት ፊታውራሪ አባዶዮ ሠርገኛ ጤፍ አስመጥተው “ከዚህ መካከል ነጩንና ጥቁሩን ለይልኝ” ብለው ጥላቻንና ጠላትነትን ያወገሁበት አካባቢ ነው። ታዲያ ሌንጮ “አማሮች ያገኙን እንደእነዚህ እንስሳት ከብቶች አድርገውን ነው” ብሎ ሲጀምር “ልጆቻችንና ወንድሞቻችን..አንተ የምትላቸው አማሮች ናቸው። እኛም አማሮች፣ አማሮችም ኦሮሞዎች ናቸው።” ብለው በማስጠንቀቂያ ሸኝተውታል። የሮይተርን ቀጥታ ምስክርነት ለመጥራት እችላለሁ። ታዲያ ጃዋር እንደ ነገረን፣ ኦሮሞም ነው። አማራም ነው። ሙስሊምም ነው ክርስቲያንም ነው። ኢትዮጵያዊ ካልተባለ ምን ሊሆን ፈለገ? ቅጥ አምባሩ የጠፋበት አይደለም ትላላችሁ?

እነዚህን ሰዎች ሳስብ ኢሳይያስና መለስን አስባለሁ። የኦሮሞ ነፃነት ግንባር የሚለውን ድሪቶ የለጠፈባቸው ኢሳይያስ አፈወርቂ ነው። ወይም ኦነግን ጠፍጥፎ የሰራው እሱ ሲሆን “ኦሮሚያ” የሚለውን በታሪክም በተረትም የማይታወቅ የሕልም ዓለም ክልል ስያሜ ደግሞ በዳቦ ስምነት ያሸከማቸው አስመሮም ለገሰ የተባለው የእኛው ዩኒቨርሲቲ ውጤት ነው። በነገራችን ላይ የአስመሮም ለገሰ የገዳሥርዓት መጽሐፍ እስኪወጣ ድረስ ኦሮሚያ የሚባል ቃል አላውቅም ነበር። እንደ ነገሩ ደግሞ መጽሐፍ አገላባጭ ሰው ነኝ፥ እላለሁ።
የኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ-ይልቁንም መንግሥታዊው መድረክና አጀንዳ የፀረ አንድነቱ አቋም ማራገቢያ እንደ መሆኑ አገሪቱን ወደ ማፍረስ እየረሸጋገሩም ይመስላል። ለሱዳን፣ ለሳዑዲ፣ ለሕንድ፣ ለቻይና፣ ለፓኪስታንና ዶላር ላለው ሁሉ ተከፋፍሎ የተረፈውን ማለቴ ነው። ከዚህ መሠረትነት በመነሳት የሺህ ዘመናት ሥልጣኔ የነበረው የኦሮሚያ በአማሮች ተወርሮ “ኢትዮጵያ” የተፈጠረችው ከአንድ መቶ ዓመታት ወዲህ በዚያ መንግስት ፍራሽ ላይ ነው እየተባልን ነው። የዜጐች፣ የታሪክ ተመራማሪዎች ዝምታ ለተረትና ለቧልት መፈጠር፣ ለልብ ወለድ ታሪክ መፈብረክ አስተዋጽዖ አድርጐአል። ኦሮሞው ኅብረተሰብ (በብዙዎች አካባቢዎች- ለምሳሌ በወሎ ወዘተ ጋላ ማለት ስድብ ሳይሆን የተከበረና ትርጉሙም ትልቅ ማለት ነው) የዚህ አገር ታሪክ ተጋሪ፣ ፈጣሪና በግንባር ቀደምም እንደ አገሪቱ ዳር ድንበር ተከላካይና መከታ ሆኖ የቆየ ነው። አንዲት የምኒልክ ስንኝ በማስታወሻነት ከእናንተ ጋር ባቆይስ? እነሆ!

“ጐበና ጐበና ጐበና የኔ
የጦር ንጉሥ አንተ ያገር ንጉሥ እኔ” አዳዲሱ ድርሳናቸው ከዚህ ሐቅ ጋር የሚጋጭባቸው ደራስያን “አዳዲስ ታሪክ የመጻፍን የአሸናፊዎች አንበሶችን ሚና” ይዘዋል። እኛም ማፈሪያዎች እነሱም ማፈሪያዎች ነን። ይህን እንቀበል!

ስለ ጥቁሩ ሰው

ወደ ሌላ ከመሻገሬ በፊት ከምኒልክ የተለያዩ ጠቅላይ ገዢዎች መካከል ዋነኞቹ (ሦስቱ) ስለ አገርና ስለ ምኒልክ የነበራቸውን ቁምነገሮች ለማንሳት እወድዳለሁ፤
“ምኒልክ ትንሽዋን ወላይታ ወስዶ ትልቂቱ ኢትዮጵያን ሰጠኝ። በእውነት ምኒልክ የእኔም የኢትዮጵያም አባት ነው። – ካዎ ጦና ጋጋ – የመላው ወላይታ ርእሰ መሳፍንት ልጅ እያሱ ቀድሞ ኩምሳ ሞረዳ ይባሉ የነበሩትን የደጃች ገብረእግዚአብሔር ሞረዳን ልጅ ለማግባት ጥያቄ ሲያቀርቡላቸው – “ ምነው! ምነው ጌታዬ! እኔና እርስዎ ኮ ወንድማማች ነን። እኔ በመንፈስ ከአጤ ምኒልክ ተወልጃለሁ (አበልጅ) ስለዚህ እርስዎና እኔ ወንድማማች ነን። የእኔን ልጅ ሊያገቡ አይችሉም። ( አንዳንድ የወለጋ አረጋውያን በዚህ ላይ ሲጨምሩ ሰምቻለሁ። ተጨማሪው ቃል “ሲሆን ባል ሲመጣለት አባት ሆነው የሚለመኑ፣ ቆመው የሚድሩ መሆን ይገባዎታል”)
የደጃዝማች አባ ጅፋር አባ ጆብር (የከፋው ገዥ) ዘመድ የሆነ አንድ ሰው ዘወትር ይሹሙኝ እያለ ደጅ ይጠናቸው ነበር ይባላል። እንዲያውም አንድ ቀን እጅግ አምርሮ “ለመሆኑ እነዚህ ለሹመት ያበቁአቸው ሰዎች ከእኔ ይቀርቡዎታልን? ለእኔ አንድ የሹመት ቦታ አጥተው ነው?” ይላቸዋል።

አባ ጅፋር በተለመደው ስል አነጋገራቸው “የሕዝብ አደራን በተመለከተ ምኒልክ እጄን ይዞ ነው የነገረኝ። ያ ባይሆን ኖሮ እኔ እዚህ አልገኝም ነበር። ምኒልክ እጁን ይዞ “ሹመት የሕዝብ ነው- ሹመት ሺህ ሞት ነው” ብሎናል። ወንድሜ! ወደ ሥልጣን የገቡት እንዴት በነፃነት እንውጣ እያሉ ይጨነቃሉ። ይህንን የማያውቁ ደግሞ እየዘለሉ መግባት ይመኛሉ። እንድታውቅልኝ የምመኘው ከዓለም መንግስታት እኩል ያደረገን ምኒልክ አደራ ከባድ መሆኑን ነው።”
በነገራችን ላይ አጤ ምኒልክ ዘወትር ምሳና ራት ሲበሉ አብረዋቸው ማዕድ የሚቀርቡ (ሁል ጊዜ) ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ፣ ደጃዝማች ወልደሚካኤል ጉዲሳ (የአጤ ኅይለሥላሴ አያት)፣ ፊታውራሪ ቱሉ፣ አፈ ንጉሥ በዳኔና ብላታ አቲከም ነበሩ።

በአንድ ነጥብ እንለያይ። አጤ ምኒልክ በአንድነት አሰባሳቢነትና ተበታትና የቆየች አገራቸውን ወደ አንድ ኅብረት በማምጣት ረገድ የየአካባቢው መሪዎችን ትብብር በግድን በውድም ተቀዳጅተዋል። ስለዚህም በወለጋ ደጃዝማች ገብረ እግዚአብሔር፣ በከፋ ደጃዝማች አባጅፋር፣ በወላይታ ካዎ ጦና ጋጋ አካባቢያቸውን ይዘው፣ የውስጥ አስተዳደራቸውን አደራጅተው ሕዝቡን ይመሩ ነበር። ይሁንና በአርሲ በኩል ለጊዜው ሕዝብ የሚቀበለው ጐላ ያለ ተወላጅ በመታጣቱ አጐታቸው ራስ ዳርጌ ተመደቡ። ራስ ዳርጌ ደግሞ እጅግ ሃይማኖተኛ፣ ሕዝቡን በርኅራኄ የሚመለከቱ የአባትነት ተቀባይነት የነበራቸው ስለሆኑ አንዳች ዓይነት ግፍ ለመፈጸም ባሕርያቸው የማይፈቅድላቸው ሰው ነበሩ። እንግዲህ “አጤ ምኒልክ ጡት አስቆረጡ” የሚባለው አነጋገር አርሲ ውስጥ መሆኑ ነው። ማንም እንደሚገምተው ጡት የመቁረጥ የአረመኔ ተግባር የአማራ ባሕርይም የክርስቲያን ሕዝብም ተግባር አይደለም። በአንጻሩ እነ አባ ባሕርይና ሌሎችም ሥፍር ቁጥር የሌላቸው የታሪክ ጸሐፊዎችም ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ ኦሮሞ ጐልማሳ ከማግባቱ በፊት ብልት እስከ መስለብ፣ ጡት እስከ መቁረጥ የደረሰ “ጀብድ” መቁጠር መቻል አለበት፥ ይሉናል። ይኸም የትናንት ታሪክ ነው።

ለማንኛውም ተረት እየፈጠሩ ታሪክ፣ ድርሳን እየጻፉ በሕዝብ ዴሞክራሲ ስም ወደ ኋላ እየሄዱ የአገር ጊዜና ዕድሜ ከማባከን ይልቅ ጥላቻን ቀብረን፣ ፍቅርንና አንድነትን አንግበን ሰላም የተጠማችውን አገር ወደ ሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ማሸጋገር አይበጅም ኖሮአል? ዓለም እየታዘበን አይደለምን? ምን ይሁን ነው የምንለው?
በሕብረተሰብ ትክክለኛ አመራር ባሕርይ መንጸባረቅ ያለበት አንድ ክስተት “የነገው ከዛሬው” የተሻለ፣ ብሩሕ፣ አሰባሳቢ፣ እኩልነት የዳበረበት፣ ነፃነት የከበረበት መሆን አለበት። ያለፈው ጓዝና ጉዝጓዝ እንደ ጸሐይ ማብራት የሚገባውን “ነገ”ን በጨለማማ ገጽታው ሊያደበዝዘው አይገባም። ከትናንትና ከዛሬው ይልቅ “በነገው” ተስፋና አለኝታ መጣል ይገባናል። እንዲያም ቢባል ከትናንቱ ብሔራዊ ውርስና ቅርስ -ከትናንቱ የእድገትና የአንድነት መሠረት መካከል- ምኑም ማናምኑም በዛሬና በነገው ቀጣይ ታሪካችን ውስጥ ሥፍራ ሊኖረው አይገባም አይባልም። ታሪካችንም ሆነ የነገው “ጸጋችን” ምንም ዓይነት ተቀባይነት አይኖረውም አይባል። አያቱንና አባቱን የማያውቅ ትውልድ በፈንታው ለነገው ትውልድ አባትነትና አያትነት አይሰማውም። አዎን የምንኰራባቸው አባቶችና እናቶች አያቶችና ቅም አያቶች ያሉንን ያህል አሳፋሪዎች፣ ፈሪዎችና ደካሞች፣ መልቲዎችና ሰነፎች የሆኑ ዜጐችም ነበሩብን። አሉብንም።

እነዚህን ማወቁ-ታሪካችንን ጠንቅቀን መረዳቱ፣ ጀግንነትን ለማደስና ከቶውንም ያንን አዳብረን የዓለም “ጨው” እስከምንባል ድረስ ለመጓዝ ዓለማቀፋዊነት መሠረት ይሆነናል። አፍሪካውያን ብቻ ሳይሆን፣ ጥቁር ዓለምንም ብቻ ሳይሆን- የዓለምን ነፃነት ወዳጅና አክባሪ ሕዝቦች ሁሉ የሚያደንቁት “ምኒልክ” ከዚች አገር የጐን አጥንት የተከፈለ ነው። አንድን አገር ታላቅና ገናና፣ የተከበረችና የታፈረች የሚያደርጉአት ሕዝብዋ ሲሆኑ ለዚያ ሁሉ ታሪካዊ ሥፍራ ተቀዳጅነት የሚያስፈልጉ መሪዎች ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ በመሪነት የተነሡትን ልዩ ልዩ ነገሥታትና የዛሬዎችንም አምላክ ለቅጣት የሰጠንን ጨምሮ- ለኢትዮጵያ አንዳች ክብር ያመጣውን ዋነኛ ሰው ለማግኘት ብዙ ማሰስ አስፈላጊ አይደለም። የዶክተር ሥርግው ሀብለ ሥላሴን “አጤ ምኒልክ” ማንበብ የአሰሳው ፍጻሜ ሊሆን ይችላል። ደራሲው በዚህ መጽሐፍ ከሳባ ንግስት አንስቶ እስከ ቀዳማዊ ኅይለሥላሴ ድረስ ይዘልቃል። ለዚህ አገር ታዋቂነት- ይልቁንም ዳር ድንበርዋንና ነፃነትዋን በማስከበር ረገድ ድንቅ አስተዋጽዖ ያደረጉ፣ በመንፈሳዊና ቁሳዊ ሥልጣኔ ታስደመሙ መሪዎችን ታሪክ ለላንቲካ ያቀርባል። ከሙሉው- ከዚያ ሁሉ ጀግናም ሆነ ሰነፍ መሪ መሐል አንድ ሰው ነጥሮ ይወጣል። በፀረ አንድነት ኅይልነት ጸንቶ ያለው ወያኔ ይንጨርጨር እንጂ- ወያኔና ሻዕቢያ የፈጠሩአቸው ትንንሽ ጩዋሒዎች ይንጨርጨሩ እንጂ ሰውዬው ወጣቱ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን “ጥቁሩ ሰው” የሚለው ነው።

ይቺ አገር በነፃነት የተፀነሱ፣ በነፃነት ያደጉና ድሀም ቢሆኑ በነፃነት የሚራመዱ ዜጐች እናት ናት። ያቺ አገርና ሕዝብዋ ከምን ጊዜውም በላይ ያልተጠናቀቀ ብሔራዊ ዕዳ፣ ለትውልዶች የሚጠቅም ቅርስ ለማቆየት በጥድፊያ ላይ ያሉ ወገኖች እናት ናት። እዚህ መሬት ማሕፀን ውስጥ የተከበሩ ጀግኖች ተኝተዋል። በዚች ዛሬ የታሪክ መጫወቻ በሆነች አገር ማኅፀን ውስጥ ታላላቅ ጀብዱ ፈፅመው ያንቀላፉ፣ በልዩ ልዩ ሙያና በፍልስፍናም ጭምር ልቀው ያላቁን ታላላቅ ነፍሳት የእናት አገራቸው እቅፍ ሞቆአቸው ተኝተዋል። ዓምደ ጽዮን፣ ያሬድ፣ በካፋ፣ ቴዎድሮስ፣ ዮሐንስ፣ ምኒልክ፣ ሀብተ ጊዮርጊስ፣ አሉላ፣ አብዲሳ አጋ፣ በላይ ዘለቀ፣…የተኙባትና እረፍት ላይ ስላሉም መሬቲቱ በጥንቃቄ መረገጥ ያለባት ናት። እነሱን ያህል ለመሥራት ያልቻልን ሰነፎች እንደ መሆናችን ቆምብለን ራሳችንን መርገምም የሚገባን ነን። ይኽ ሁሉ የወያኔ ልዑካን ጫጫታ አያሳፍርም? ይኸ ድምፅ ከየት መጣ? ወሮበሎች አያሰኝንምን? ስድ አደግ ማለት- የእምነት ድህነት ማለት- የሕሊና ባዶነት ማለት- የአቋም ምስኪንነት ማለት ምን ማለት ነው? ይኸው በአደባባይ እየታየ ነው። (በዚህ ጉዳይ ላይ እመለስበታለሁ)

አሥራ አንድ ሰዓታት የፈጀው ክርክር –ክፍል አንድ –ሃብታሙ አያሌው (የአንድነት ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ)

$
0
0

ክፍል አንድ
በቀናት አቆጣጠር ሰባተኛው እረድፍ በምትይዘው በዕለተ ቅዳሜ ከዚህ ቀደም በጸረ ሽብር አዋጁ ዙሪያ ካደረግነው የተሟሟቀ ክርክር በኋላ ከገዥ ፓርቲ ጋር በሃሳብ ክርክር ለ11 ሰዓታት የተሟገትነው ቅዳሜ ጥር 17 ቀን 2006 ዓ.ም ባለፈው ሳምንት ነበር፡፡ ይህ መድረክ የተዘጋጀው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በጋዜጠኝነት እና ኮሚዩኒኬሽን የድህረ ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎች ከትምህርት ቤቱ ጋር በመተባበር እንደነበረ ከደረሰን የመጥሪያ ደብዳቤ ለመገንዘብ ችለናል፡፡

በዚህ ወቅት በዚህ ጉዳይ ሲምፖዚየም ማዘጋጀት ያስፈለገበት ምክንያት ምንድነው ? ለሚለው ጥያቄያችን የሲምፖዚየሙ ርዕስ ግልፅ ምላሽ ነበረው፡፡ ‹‹ የዴሚክራሲያዊ ልማታዊ መንግስት እና የመገናኛ ብዙኃን ግንኙነት›› (Nexus) ማጠንጠኛው ነበር፡፡
የኢህአዴግ መንግስት ‹‹በአቢዮታዊ ዴሞክራሲ ›› ፍልስፍና (ፍልስፍና ሊባል ከቻለ) እስከ 1991 ዓ.ም ከተንገዛገዘ በኋላ የባድሜውን ጦርነት እና የህወኃትን መሰንጠቅ ተከትሎ የፓርቲው የኃይል አሰላለፍ ሲቀየር ተቀጥላ ልማታዊ የሚለው ሥያሜ ጎላ ያለ ስፍራ እንዲያዝ መድጉ አይዘነጋም፡፡

ልማታዊ መንግስት ሲሉ አቢዮታዊ ዴሞክራሲ የሚለውን ስያሜ ለአንጃው ለመተው የፈለጉት አቶ መለስ ይህንን መጠሪያ የገነገነ ጥላታቸውን በመበታተን ተሸንፈው ከቆሙበት ጥግ ወደ መሃል ለመግባት ወሳኝ ብልሃት አድርገውት ነበር ማለት ይቻላል፡፡ አቶ መለስ ለኤርትራ መንግስት ያሰዳዩ የነበረው ከፍተኛ ወገንተኝነት ኢትዮጵያን ያለወደብ ከማስቀረት ተሸግሮ በኢትዮጵያ ምርቶች ኤርትራ በአለም የንግድ ገበያ ስሟ መጠራት መጀመሩ፤ በኢትዮጵያ ብር እየተገበያየች የዶላር ክምችቷን ከፍ ማድረጓ እና በወጪ እና ገቢ ሸቀጦች እረገድም በምንም ዓይነት የታክስ ሥርዓት አለማለፏ እና የመሳሰሉት አንደኛው የኩርፊያ መሰረት እንደነበረ ይታወቃል፡፡

ይሁን እንጂ የአንደኛው የሃሳብ የበላይነት ብዙ እርቀት ሳይሔድ በቀጭን ትዕዛዝ ጦርነቱን ያስቆሙት አቶ መለስ መንግስታቸው ልማታዊ መሆን ሲገባው ጦረኝነትን እንደመረጠ እና እንደበሰበሰ በመግለፅ የታይላንድ፤ ታይዋን እና ደቡብ ኮርያን መንግስታት ሥርእት በመተንተን ከአንጃው ካምፕ ብዙዎችን ማረኩ፡፡ ከዚያም ያልተደራጁ እና ስልት አልባ የነበሩ ተቃዋሚዎቻቸውን በታትነው ጥቂቶችን ዘብጥያ በመጣል አሸናፊ ሆነው ብቅ ያሉበት ነበር፡፡

‹ልማታዊ መንግስት›

አቶ መለስ ልማታዊ መንግስት ሲሉ መከራከሪያቸው ‹‹በውቅቱ የኤርትራ ወታደሮች የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ግዛት ድፍረው በገዛ ምድራችን ምሽግ ቆፍረው ሊወጉን እየተዘጋጁ እንደነበረ ብናውቀውም ወደ ጦርነት ያልሄድነው ልማት ይቀድማል ከሚል ትክክለኛ አስተሳሰብ ነው፡፡›› የሚል ነበር፡፡ ይህ ግን ጥሩ የማደናገሪያ ስልት እንኳ መምረጥ እንዳልቻሉ የሚያሳይ እንጂ የሃሳብ የበላይነት እንደነበራቸው የሚያመላክት አልነበረም፡፡ አንደኛ በወቅቱ ምንም አይነት የልማት አጀንዳ ያልነበራቸው መሆኑ፤ በሌላ በኩል የሀገር ሉዓላዊ ድንበር ተደፍሮ፤ የሌላበ ሀገር ሰራዊት ምሽግ እየቆፈረበት ልማት ስላሳሰበኝ ሀገር አልጠብቅም ማለት ጀነራል ሳሞራን እና እነአባዱላ ገመዳን ካልሆነ በቀር የኢትዮጵያን ህዝብ የሚያሳምን ሃሳብ አይደለም፡፡

የምንረዳው ቁምነገር ቢኖር እንደ ሀገር ለኢትዮጵያ ከነበራቸው የተንሸዋረረ አመለካከት እና ከያዙት የተሳሳተ አቋም በመነሳት በጫካ ውላቸው መሰረት ኤርትራ ራሷን የቻለች እና የበለጸገች ሀገር እንድትሆን እንደ አቶ ኢሳይያስ ምኞት ‹‹በ10 ዓመታት ውስጥ ኤርትራ አፍሪካዊዋ ሲንጋፖር ትሆናለች፡፡›› ከሚለው ቅዠት ጋር እየቃዡ የነበረ መሆኑን ነው፡፡
ለኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት፤ ለታሪክ እና ለብሔራዊ አንድነት ግድ የማይሰጣቸው አቶ መለስ ጦርነቱ ተጀምሮ በኤርትራ ላይ ጉዳት እንዳይደርስ የተከላከሉበት ‹‹የልማታዊ መንግስት የፖለቲካ ኢኮኖሚ ጉዳይ›› የሙት መንፈሳቸው እንደገና በያዝነው የ2006 ዓም የመጀመሪያ መንፈቅ አጀንዳ አድርጎታል፡፡ ይህ ወቅት በሙት መንፈሳቸው የሚመራው የኃይለማርያም መንግስት ታሪካዊ የሆኑ የኢትዮጵያ ግዛቶችን ሰቲት ሑመራን፤ ምዕራብ አርማጭሆን እና ቋራን ለሱዳን አሳልፈው በመስጠት ድነበር ለማካለል እያሴሩ ያሉበት ወቅት እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

የልማታዊ መንግስት አጀንዳ የባድሜን መሬት ለመስጠት በተሰላ ጊዜ ከገነነ በኋላ የፊት ሌቱን ገፅ ለቆ ቢቆይም የጎንደርን መሬት ለመስጠት ሲታሰብ እንደገና አብይ አጀንዳ ሆኖ ብቅ በሏል፡፡ ጥር 17 ቀን በኢንተር ኮንትኔንታል የተካሄደው ሲምፖዚየምም፤ የዚሁ የልማታዊ መንግስት አጀንዳ ማደናገርያ ክፍል አንድ ሊባል ይችላል፡፡

አሥራ አንድ ሰዓት የፈጀው ውይይት

ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ገደማ የጀመረው ውይይት የተጠናቀቅ ከምስቱ 1፡35 ደቂቃ ነበር፡፡ ከፍተኛ ምስጋን የሚገባቸው የድረህረ ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎች ካዘጋጁት መድረክ በስተጀርባ የተደገሰውን የፖለቲካ ዓላም ግን በግልፅ የተገነዘቡት አይመስልም፡፡ በፍጸም ገለልተኝነት የሃሳብ ክርክር እንዲደረግ የተቻላቸው ሁሉ ሲያደርጉ ተገንዝቤያለሁ፡፡
በውይይቱ ማጠናቀቂያም የጋበዟቸው የገዥው ፓርቲ ሰዎች አጀንዳውን ወደ ፖለቲካ ጎትተው ለፖሊሲ ስርጸት ለመጠቀም መሞከራቸው ተገቢ እንዳልነበረ በድፍረት አስተያየት ሰጥተውበታል፡፡ ከገዥው ፓርቲ፤ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ ከዩኒቨርስቲ መምህራን ከመገናኛ ብዜሃን አካላት እና ሌሎች ምሁራን መካከል ጥሪ ተደርጎላቸው እንደተገኙ በተገለጸው በዚህ መድረክ ከገዥው ፓርቲ አቶ ሽመልስ ከማል፤ አቶ ዛድቅ አብርሃ፤ አቦይ ስብሃትን እና በስም የማላውቃቸውን አስተውያለሁ፡፡ ከምሁራን መካከል ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ፤ ዶክተር ያዕቆብ ኃ/ማርያም ፤ ዶክትር ነጋሶ ጊዳዳ፤ ዶክተር በድሉ ዋቅጅራ ሲሆኑ በስም የማላውቃቸው ሊኖሩ እንደሚችሉ እገምታሉ፡፡

በእኔ ግምት በጋዜጠኝነት እና ኮሚዩኒኬሽን ድህረ ምረቃ ተማሪዎች ሲምፖዚየሙን አዘጋጀን ካሉበት አላማ አንጻር በዶክተር አብዲሳ ዘርዓይ {Media in Democratic Developmental State the Ethiopian Quandary } በአቶ ታምራት ኃ/ጊዮርጊስ The concept of democratic developmental state vis-a- vis The Ethiopian constitution እና በአቶ ሙሼ ሰሙ freedom of the press in the environment of a democratic developmental state የሚሉት ሞያዊ ዝንባሌ የታየባቸው academic discourse ከሚባሉት የሚመደቡ ነበሩ ማለት ይቻላል፡፡

በአንጻሩ በአቶ ወልዱ ይምሰል እና በአቶ ዛድቅ አብርሃ የቀረቡት ደግሞ ከተማሪዎቹ ሃሳብ በስተጀርባ የሙት መንፈስን ሃሳብ ለመጫን ያለሙ political discourse ነበሩ፡፡ በዚህ ሲምፖዚየም በልማታዊ መንግስት ፅንሰ ሃሳብ እና በሚድያ ነጻነት ዙሪያ ሰፊ ክርክ ተደርጓል፡፡ በአቶ ታምራት ኃይለጊዮርጊስ የቀረበው ጥናት በኢትዮጵያ የሚዲያ ነጻነት አለመኖሩ እና ይልቁንም በህገ መንግስት የተሰጡ የሚዲያ ነጻነቶችን ገዥው መንግስት በሌሎች ህጎች እንዳፈናቸው ዝርዝር ማብራሪያ ቀርቦበታል፡፡ እንደ አቶ ታምራት ገለጻ የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት የቡድን መብት ሲል ካስቀመጣቸው ጥቂት ተቀባይነት የሌላቸው አንቀጾች በቀር ጥሩ እና ሊበራል አስተሳሰብን ከፍ የሚያደርግ ነው ሲል መከራከሪያ አቅርበውታል፡፡ ይህ ሃሳብ ከገዥው ፓርቲ ተወካይ ከአቶ ዛድቅ ቁጣ የተቀላቀለበት ምላሽ የተሰጠበት ሲሆን አቶ ዛድቅ ሊበራል ሳይሆን ህገ መንግስታችን ካፒታሊስት ሥርዓት የሚገነባ ነው በማለት ካፒታሊዝም ለሊበራሊዝም ተቃርና እንደ ሆነ አድርገው ሲከራከሩ ተገርመን አስተውለናል፡፡ (እንደ አቶ ዛድቅ ገለጻ ከሆነ አዲሱን ልማታዊ መንግስት ለማነበር ካፒታሊስቱን ህገ መንግስት መሻር ግድ ሊለን ነው፡፡)

በዶክተር አብዲሳ ዘርዓይ ከተሰነዘሩ ሃሳቦች መካከል በ1980ዎቹ አካባቢ የታየው የሚድያ ነጻነት ክፉኛ እንደተመታ እና በአሁኑ ወቅት ያለው የሚድያ ነጻነት ደረጃ እጅግ አሳሳቢ እንደሆነ በጥናታቸው አስምረዋል፡፡ በዶክተሩ ጥናት ላይ መከራከሪያ የሚመስል ሃሳብ በማቅረብ አጸፋ ያሉትን ያቀረቡት የፋነው ስራስኪያጅ አቶ ወልዱ በበኩላቸው በ1980ዎቹ የነበረው የሚድያ ነጻነት መረን የለቀቀ እና በጦርነት የተሸነፈው የደርግ ኃይል በሚድያ ጦርነት የጀመረበት ወቅት ነበር ሲሉ ተከራክረዋል፡፡

በዚህ ወቅት ከፍተኛ ክርክር የተጀመረው በዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ እና በኢህአዴግ ተወካዮች መካከል ነበር፡፡ የተበተነው የደርግ ሰራዊት በእጁላይ በነበረው መሳሪያ በሀገር እና በህዝብ ላይ ጉዳት ሳያደርስ የኢትዮጵያን የመከላከያ ሰራዊት ጨዋነት ማስመስከሩ ሊያስመሰግነው እንደሚገባ፤ እዚህ ኢህአዴግ እንደሚከሰው ወደ ሚዲያ ጦርነት ሂደው ከነበረም መሳሪያ ጥለው በብዕር ክርክር ፍልሚያ መካፈላቸው ጠላት ሊያሰኛቸው አይገባም ነበር፡፡ ነገሩ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ‹‹ኢህአዴግ አንድን ጋዜጠኛ ከአንድ ባታሊዎን ጦር በላይ የፈራል›› እንዳለው ሆነ እንጂ ፡፡ በአንጻሩ የተበተነው ሰራዊት ወይም የኢሰፓ አመራሮች ሳይሆኑ በሚድያ ሃሳብ ይሰነዝሩ የነበሩት ምሁራን እና የ1960ዎቹ የሃሳብ እኩዮቻቸው እንደነበሩ መከራከሪያ ቀርቧል፡፡

በተለይም ከዚህ ክርክር የተረዳነው ቢኖር ገና በጠዋቱ ኢህአዴግ በሚዲያ ላይ የያዘው የተዛባ አመለካከት ከፍተኛ መሆኑን እና የተለየ አስተሳሰብን በሚድያ ማንጸባረቅ እንደ ወንጀል የሚቆጠጥር ነው፡፡ (በተሻሻለው የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እንደተከሰሰ ልብ ይሏል፡፡) በሲምፖዚየሙ ከፕሬስ ነጻነት አንጻር ክፉኛ የተተቸው የፕሬስ አዋጅ፤ የጸረሽብር አዋጅ፤ እንደተጠበቀ ሆኖ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ሲሻሻል የፕሬስን ጉዳይ በሚመለከት የተካተተው ህግ በሲምፖዚየሙ ትኩረት የሳበ ሆኖ ውሏል፡፡

በወንጀለኛ መቅጫ ህጉ ላይ የሰፈረው ፕሬስን የሚመለከት አንቀጽ ሆን ተብሎ ሚድያውን ለማፈን እና ጋዜጠኞችን ለማሳደድ የተካተተ በግልጽ በህገ መንግስቱ የተቀመጠውን የሚድያ ነጻነት የሚጥስ እና የሚደፈጥጥ ነው፡፡ በሚል መከራከሪያ ቀረበ፡፡ በዚህ ጊዜ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በአይኔ ላይ ውል አለ፡፡ በዚህ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ተወንጅሎ ፍርድ ቤት እየተመላለሰ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ጥያቄና አስተያየቱም ቁጡነት እና እልህኝነት ይታየበት የነበረውም በዚሁ ምክንያት እንደሆነ ይሰማኛል፡፡

ይህንን የወንጀለኛ መቅጫ ህግ አስመልክቶ የፎርችኑ አቶ ታምራት ህጉ በግልፅ ህገ መንግስቱን የጣሰ እና ተገቢ ያልሆነ ህግ እንደሆነ አስረግጦ ተከራክሯል፡፡ ከሁሉ የሚገርመው ግን ለዚህ ምላሽ የሰጡት የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚንስትር ድኤታ አቶ ሽመልስ ከማል ‹‹በእርግጥም የወንጀለኛ መቅጫ ህጉ ላይ ፕሬስን በተመለከተ የተቀመጠው አንቀጽ ከህገ መንግስቱ ጋር የሚቃረን እና ተገቢ ያልሆነ መሆኑን እንደ መንግስትም ተገንዝበናል፡፡ እንደ እኔ ግምት ይህንን ወንጀለኛ መቅጫ ህግ ያሻሻሉ ሰዎች በጭንቅላታቸው ቆመው የሰሩት ይመስለኛል፡፡›› ሲሉ በግርምት አድምጠናል፡፡

በዚህ ጊዜ አቶ ታምራት ኃ/ጊዮርጊስ እንዲህ በማለት ሃሳባቸውን አቅርበው ነበር፡፡ ‹‹ ክቡር ሚነንስትር ድኤታ በእርግጥ ስህተት ነው ባለው በግልዎም እንደ መንግስትም ማመንዎን አደንቃለሁ፡፡ ነገር ግን ይህ ስህተት በህግ አሻሻዮቹ አለማስተዋል እንደተሰራ ማስመሰል ተገቢ አይደለም፡፡ ይህ አንቀጽ ሆን ተብሎ ሚድያውን ለማፈን ዜጎች በህገ መንግስት ያገኙትን መብት ለመንፈግ የወጣ ነው፡፡ በእኔ ግምት ያሻሻሉት በጭንቅላታቸው ስለቆሙ አይመስለኝም፡፡ ዳኞች ይህንን አንቀጽ እየጠቀሱ ዜጎች ታስረዋል፤ ብዙዎች እንዲሰደዱ እንዲንገላቱ ምክንያት ሆኗል……››

በእርግጥ ወንጀለኛ መቅጫ ህጉን ያሻሻሉት በጭንቅላታቸው ስለቆሙ ነው ወይስ የፕሬስ ህግ፤ የጸረሽብር ህግ፤ የሲቪል ማህበራት ህግ ወዘተ…ጭምር ሲረቀቁ አቶ መለስ በአርቃቂዎች ጭንቅላት ላይ ስለቆሙ ? በቀሪዎቹ እና በአወንታዊ ነጥቦች ላይ እመለስበታለሁ፡:1609626_590403497711255_978655788_n

አስገራሚው የሳውዲው “ኮራጅ ”አባት ምክር እና የኢትዮጵያ ሰርከስ መስራች በሳውዲው ስደት ! –ነቢዩ ሲራክ / የካቲት 2006 ዓም

$
0
0

አስገራሚው የሳውዲው “ኮራጅ ” አባት ምክር

ነገሩ እንዲህ ነው …ከ20 ዓመት በፊት ሳውዲው ወጣት ራሱን ለሁለተኛ ደረጃ ፈተና ከማዘጋጀት ይልቅ በረቀቀ መንገድ ለፈተናው መልስ የሚሆነውን ማጭበርበሪያ የመልስ ወረቀት አዘጋጅቶ ለፈተና ይቀርባል። ፈተናውን በረቀቀ መንገድ አጭበረብሮ ሰርቶታልና ፈተናውን በተገቢ ውጤት አልፎ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ለማለፍ በቃ ! ከዚያም በታዋቂው ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ተከታትሎ ይመረቃል። ይህ ሁሉ አልፎ ስራ ይዞ እና ጎጆ ቀልሶ ለወግ ለማዕረግ በቃ ! ከጎጆም አልፎ የሰመረው ህይወቱ የልጆች አባት እስከ መሆን ታደለ !

በያዝነው ሳምንት የድሮው ተማሪና የዛሬው አባወራ ጆሮውን ያልተለመደና የማያውቀው ህመም ያሰቃየው ገባ ። ወደ ሃኪም ቤት ጎራ በማለት ምርመራ ሲያደርግ ለህምሙ ዋና ምክንያት በጀሮው ውስጥ ቁራጭ ወረቀት እንደሆነ የሚያስረዳው አስገራሚው ውጤት ተነገረው … አረጋዊው አባት በወጣትነት እድሜው ተግቶ በማጥናት ለፈተና ቀርቦ ማለፍ ሲገባው አስነዋሪ የማጭበርበር ድርጊት መፈጸሙን እያስታወሰ አልተደሰተም ፣ አዘነ እንጅ ! ዛሬ ለማጭበርበሩ የተጠቀመበትን ወረቀት በጀሮው እንዴት ሊያስገባው እንደቻለ ማመን ቢያዳግትም ከ20 አመታት በፊት ለኩረጃ እና ለማጭበርብር የተጠቀመበት ወረቀት በቀዶ ጥገና ከጀሮው እንዲወጣ መደረጉ አስገራሚውን ዜና እየተቀባበሉ እየዘገቡ ካሉት የአረብ መገናኛ ብዙሃን ለመረዳት ችያለሁ … ! ከሁሉም የሚያስገርም የሚያስደስተው በሰራው ስራ የሚያፍር እንጅ የማይኮራው አባት ልጆቹንና ወጣቶችን ሲመክር “ልጆቸ ሆይ ፈተና ለማለፍ አታጭበርብሩ! ” ማለቱ ተጠቅሷል ። የትናንቱ ተማሪ የዛሬው አባወራ ሳውዲው አባት በሰራው ስራ ተጸጽቶ ቀሪውን ለመምከር ወደ አደባባይ መውጣቱ ቢያስደስተኝ በዝንቅ መረጃየ ስር መረጃውን ላካፍላችሁ ፈቀድኩ !

ሳውዲውን አባት መልካም ምክር ካነሳሁ አይቀር ሰሞነኛ የማለዳ ወጌ እንግዳ ለማድረግ ስለፈቀድኩት አንድ ከ20 አመት በፊት በኢትዮጵያ ሰማይ ስር ባንድ ወቅት አንቱ የተባለ ስም ስለነበረው ብርቱ ወንድም ላጫውታችሁ … አብደላ አህመድ ኦመር ይባላል ። ቀዳሚው የኢትዮጵያን ሰርከስ መስራች ነው ። በስራው ቻይናን ጨምሮ በርካታ ሃገራትን ጎብኝቷል … ብርቱ ስፖርተኛ ከመሆን ባለፈ አንድን ሙያ ልያዝ ብሎ ከተነሳ በፍጥነት ክህሎትን የማዳበር ልዩ ተፈጥሮ ያለው ወንድም እንደሆነ ሰምቻለሁ ! ዛሬ በእርግጠኝነት መናገር የምችለው ነገር ቢኖር ብዙሃን ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ ሰርከስ መስራች ማን እንደሆነና የት እንዳለ የሚያውቁ አይመስለኝም ! … ብርቱው የቀድሞው ስፖርተኛ እና የሰርከሱ መስራች አብደላ ግን ሳውዲ አረቢያ ጅዳ ትዳር መስርቶ እና ልጆች ወላልዶ በስደት ህይዎትን በመግፋት ላይ ነው ።

አብደላን ሳላውቀው… ላውቀው!

መልከ መልካምና ደልዳላ ተክለ ቁመና ካለው ወንድም ጋር ለአመታት ልጆቸን በማስተምርበት በጅዳ የኢትዮጵያውያን አለም አቀፍ ትምህርት ቤት እንተያያለን ፣ ግን አንተዋወቅም ። በአንድ ወቅት ከአንድ ወዳጀ ጋር የትምህርት መለቀቂያ ሰአት ደርሶ ልጆቻችን ስንጠባበቅ አብደላ ሰላምታ አቅርቦልን አለፈ … አብደላን አንድ ወዳጀ ያውቀው ነበርና እንዲህ አለኝ … ” ለመሆኑ ይህን ሰው ማን እንደሆነ ታውቀዋለህ? ” ሲል ጠየቀኝ አረ አላውቀውም ስል መለስኩለት … ” አየህ ሳውዲ ያልያዘችው ፣ ያላቀፈችው ሃበሻ አይነት የለም፣ አንተ ደግሞ የሩቅ የሩቁን ፣ በበርሃ የምታገኘው ዘፋኝና ግፉዕ ተምር ለቃሚ ግመል ጠባቂ እህቶችን እንጅ እንዲህ በቅርብ ያለውን አየታይህም ” ሲል የመሰለውን አስተያየት ሲሰነዝር እንደ መቀለድ እያለ በፈገግታ ተሞልቶ ነበር እና እኔም እንደመሳቅ አልኩ ! ወዳጀ ወጉን ቀጠለ …

” አንደላን በትንሹ ከአስራ አምስት አመት በላይ አውቀዋለሁ። ስፖርተኛ ፣ አስማተኛ ፣ የስነ ጽሁፍ ክህሎትን የተካነ በሁሉም የሙያ መስክ የምታገኘው ሰው ነው። ዛሬ እንዲህ አንገቱን ደፍቶ ፣ ሰውነቱ ገዝፎ ስታየው የዋዛ አይምሰልህ (ፈገግ ብሎ) ፣ ከበርካታ አመታት በፊት ታዋቂው የአካል እንቅስቃሴ አሰልጣኝ ግርማ ቸሩ ለአመታት በአሰልጣኝነት ይሰራባቸው ከነበሩ በወቅቱ ታዋቂ ቱጃር በነበሩት የሸህ አልዙማን ስራ ተሰናብቶ ሳውዲን ሲለቅ የተተካው ፈርጣማው ጎልማሳ አብደላ ነበር ። ከዚያም የባለጸጎቹን ቤተሰቦች በአካል እንቅስቃሴ አሰልጣኝነት እና በልዩ ጥበቃ ለአመታት በመስራት ያልዞረበት ሃገር የለም ። በአዕምሮው በሳል ፣ በአካል ፈርጣማ ስፖርተኛ ነው ። አየህ ነቢዩ በሳውዲ ስደት የታቀፈው ግፉአን እህቶችና ወንድሞች ብቻ አይደሉም። እንዲህ አይነት ባለሙያም ሳውዲ ውስጥ ይኖራል። ታሪኩን ለመናገር ፈቃደኛ ከሆነ ለቀረው ትውልድ አስተማሪ ነውና አንድ ቀን አስተዋውቅህና እንዲያጫውትህ አደርጋለሁ! ” አለኝ ። … አብደላን ሊያገናኘኝ ከአንድ አመት በፊት እንዲህ ቃል የገባልኝ ቅን አሳቢ ወንድም ግን ዛሬ ከአካባቢው የለም … ኑሮው ቢከብደው ቤተሰቦቹን ይዞ እና ጥሪቱን አጠረቃቅሞ የአቅሙን ያህል ለመስራት ሃገር ቤት ገብቷል … ካንድም ሁለት ሶስት ጊዜ በፊስ ቡኩ መስመር ብንገናኝም ሃገር ገብቶ የሚይዝ የሚጨብጠው እንዳጣ መረጃ የሚያቀብለኝን ወንድም” አብደላን አገናኘኝ?” ብየ ማስቸገሩ ከብዶኝ መክረሙ እውነት ነው! መቸም ዘንድሮ መንገድና ፊስ ቡክ የማያገናኘው የለም ፣ የኢትዮጵያውን ሰርከስ መስራች በቀጭኑ የስልክ መስመር በሌላ ጉዳይ አግኝቸው ስናወጋ ማንነቱን ሲያጫውተኝ ማመን አልቻልኩም ። ፎቶዎችን ፣ ሰነዶችን በመረጃ ማስረጃነት ሲያጋራኝ ግን የማይታመነውን አጋጣሚ ለማመን ተገደድኩ ! ከወንድም አብደላ ጋር ልንገናኝ ቀጠሮ ይዘናል ። … በቀይ ባህር ዳርቻዎች ከቤተሰቦቻችን ጋር ተገናኝተን ፣ ልጆቻችን ሲጨዋወቱ ነፋሻውን የባህር አየር እየማግን የኢትዮጵያ ሰርከስ መስራቹን የአብደላን ዠንጉርጉር ህይወት እኔ እየጠየቅኩ እሱ በትዝታ እየነጎደ እስኪያወራኝ ቸኩያለሁ …

መልካም ቀን

ነቢዩ ሲራክ / የካቲት 2006 ዓም

ትግራዊ ማንነት ካለ ኢትዮጵያዊ ማንነትም አለ! በአብረሃ ደስታ

$
0
0

“ኢትዮጵያዊ ነኝ፤ ኢትዮጵያዊ ማንነት አለኝ” ብዬ ስል የራሴ (የግሌ) ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። የአከባቢ ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። የክልል (የብሄር) ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። ወይም እነዚህ የተለያየ ደረጃ ያላቸው ማንነቶቼ መጥፋት አለባቸው ማለት አይደለም። እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ ስል የራሴን ማንነት አልቀበልም ማለት አይደለም። የራሴ ማንነት ስላለኝ ነው ኢትዮጵያዊ ማንነት ሊኖረኝ የቻለው። እኔ የግል ማንነት ባይኖረኝ ኑሮ ኢትዮጵያዊ አልሆንም ነበር። ምክንያቱም የግል ማንነት ከሌለኝ የሀገር ማንነት ሊኖረኝ አይችልም። እያንዳንዱ ሰው የግሉ የሆነ ማንነት አለው። የግሉ ማንነት ስላለው ነው ኢትዮጵያዊ ማንነት ያለው። ኢትዮጵያዊ ማንነት ራሱ የቻለ የሁላችን የጋራ ማንነት ነው።

የትግራይ ማንነት ካለን የኢትዮጵያ ማንነት ለምን አይኖረንም? “ትግራዮች አንድ ነን” ካልን “ኢትዮጵያውያን አንድ ነን” ብንል ችግሩ ምንድነው? ኢትዮጵያዊነትኮ ከብሄር (ከክልል) ሰፋ ያለ ሀገራዊ ማንነት ነው። ሀገራዊ ማንነታችንን ብንቀበል ችግሩ ምንድነው?

ኢትዮጵያውያን አንድ አይደለንም አትበሉኝ። ምክንያቱም ኢትዮጵያውያን አንድ ካልሆንን ትግራዮችም አንድ አይደለንም፤ አማራዎችም አንድ አይደለንም፣ ኦሮሞዎችም አንድ አይደለንም። አንድ የሆነ አይኖርም።

“ኢትዮጵያውያን አንድ አይደለንም ምክንያቱም የተለያየ ታሪክና ባህል አለን” አትበሉኝ። ምክንያቱም እያንዳንዱ ግለሰብ፣ አውራጃ፣ ክልል (ብሄር) ወዘተ…ም የተለያየ ታሪክና ባህል ሊኖረው ይችላል። ኢትዮጵያውያን የተለያየ ባህልና ታሪክ ስላለን አንድ አይደለንም ካላችሁኝ ኦሮሞዎችም አንድ አይደሉም እላቸዋለሁ፤ ምክንያቱም የወለጋ ኦሮሞዎች፣ የሸዋ ኦሮሞዎችና የአርሲ ኦሮሞዎች የተለያየ ታሪክና ባህል አላቸው።

ኢትዮጵያውያን የተለያየ ባህልና ታሪክ ስላለን አንድ አይደለንም ካላችሁኝ አማራዎችም አንድ አይደሉም እላቸዋለሁ፤ ምክንያቱም ወለየዎች፣ ጎጃሞችና ጎንደሬዎችም የተለያየ ታሪክና ባህል አላቸው።

ኢትዮጵያውያን የተለያየ ባህልና ታሪክ ስላለን አንድ አይደለንም ካላችሁኝ ትግራዮችም አንድ አይደሉም እላቸዋለሁኝ፤ ምክንያቱም ተምቤኖች፣ ዓድዋዎች፣ ዓጋሜዎች፣ ራያዎች፣ ወልቃይቶች የተለያየ ታሪክና ባህል አላቸው።

“የተለያየነው በቋንቋ ነው” ካላችሁኝ። የተለያየ ቋንቋ የማንነት መለያ መስፈርት ከሆነና እኛ ኢትዮጵያውያን የተለያየ ቋንቋ ስለምንናገር የተለያየን ከሆንን ትግራዮችም አንድ አይደለንም። ምክንያቱም የትግራይ ህዝብ አንድ ቋንቋ ብቻ የሚናገር ህዝብ አይደለም፤ አንድ ዓይነት ባህል ያለው ህዝብ አይደለም። ምሳሌ ኢሮብ (ቋንቋ ሳሆ) የራሳቸው ቋንቋና ማንነት አላቸው። ግን በትግራይ ክልል ዉስጥ ናቸው። በትግራይ ኩናማዎች አሉ (ወልቃይቶች ጨምሮ)። የራሳቸው ባህል አላቸው። ራያዎች የራሳቸው የሚኮሩበት ባህል አላቸው። ስለዚህ በትግራይ ክልል የተለያዩ ባህሎችና ቋንቋዎች አሉ። ግን ትግራዮች (ተጋሩ) አንድ ነን። ተጋሩ አንድ ነን ስንል አንድ ቋንቋ፣ አንድ ባህል ብቻ አለን ማለታችን አይደለም፤ ተጋሩ አንድ ነን ስልን ሌላ ቋንቋ፣ ማንነት፣ ባህል ወዘተ ያላቸው ህዝቦች እውቅና አንሰጥም ማለት አይደለም። ማንነታቸው እንዲቀይሩ እናስገድዳቸዋለን ማለትም አይደለም። ተጋሩ አንድ ነን ስንል የግላችን ማንነት ጠብቀን የጋራ በሆነ የትግራይ ማንነት በአንድነትና በእኩልነት እንኖራለን ማለት ብቻ ነው።

ተጋሩ አንድ ነን። ኢትዮጵያውያንም አንድ ነን። የተለያየ ቋንቋ መናገራችን የተለያየን ስለመሆናችን ማረጋገጫ ሊሆን አይችልም። ስለ ኢትዮጵያዊ ማንነት ስናወራ ስለ ሌሎች ማንነቶች እውቅና እየሰጠን ነው። ምክንያቱም የያንዳንዳችን ማንነት ከሌለ የጋራ ማንነታችን አይኖርም። የያንዳንዱ ግለሰብ ማንነት ካከበርን የሁሉም ኢትዮጵያዊ ማንነት እናከብራለን። ምክንያቱም ኢትዮጵያዊ ማንነት ማለትኮ የኛ ማንነት ማለት ነው። “እኛ” ማን ነን? እኛ ሁላችን ነን።

ኢትዮጵያዊ ማንነት ከሌለ የክልል (ብሄር) ማንነትም አይኖርም። ኢትዮጵያዊ ማንነት አለ፤ ምክንያቱም የያንዳንዳችን ኢትዮጵያውያን የየግላችን ማንነት አለን።

ኢትዮጵያዊ ማንነትን ስናስቀድም ሁሉም ኢትዮጵያውያንን እናስቀድማለን። የዓድዋ ወይ የራያ ወይ የኢሮብ ማንነት ብናስቀድም እያስቀደምነው ያለነው ህዝብ የአንድ ወረዳ ወይ አከባቢ ብቻ ነው የሚሆነው። የትግራይ ማንነት ብናስቀድምም የምናስቀድመው የትግራይ ህዝብ ብቻ ነው የሚሆነው። ትንሽ ጠበብ ያለ ነው። ሌሎችስ ለምን እንተዋቸዋለን? ሌሎች (አማራዎች፣ ኦሮሞዎች፣ ሶማሌዎች፣ ደቡቦች፣ ዓፋሮች፣ ጋምቤላዎች፣ ቤኑሻንጉሎች፣ ጋምቤላዎች፣ ሃረሪዎች ወዘተ) ለምን በእኩል ዓይን አናስቀድማቸውም?

የትግራይን ማንነት የሚያስቀድም ሁሉ የኢትዮጵያ ማንነትም ማስቀደም አለበት። ምክንያቱም የትግራይን ማንነት ስታስቀድም የሌሎች ወገኖች ማንነት ትተወዋለህ። የኢትዮጵያ ማንነት ስታስቀድም ግን የሁሉም የኢትዮጵያ ህዝቦች (የትግራይ ጨምሮ) ማንነት ነው የምታስቀድመው።

በኢትዮጵያዊ ማንነት የማምነው ሁሉንም ኢትዮጵያውያን ማስቀደምና ማክበር ስላለብኝ ነው። በኢትዮጵያ ዉስጥ እየኖረ የራሱን ብሄር የሚያስቀድም ሰው በሁሉም ብሄሮች (ኢትዮጵያውያን) እኩልነት አያምንም ማለት ነው። በብሄሮች እኩልነት የማያምን ደግሞ የኢትዮጵያን አንድነት ማስጠበቅ አይችልም። ምክንያቱም እኩልነት ከሌለ አንድነት የለም። አንድነት ከሌለ ሀገር የለም። ሀገር ከሌለ ሉአላዊነት የለም። ሉአላዊነት ከሌለ የህዝብ ደህንነት አይጠበቅም። ስለዚህ ኢትዮጵያዊ ማንነት የማያስቀድም ለህዝብ አይበጅም።

አንድ የወረደ ሐሳብ ላንሳ።

የቡድን (የብሄር) መብትን የሚያስቀድመው የኢህአዴግ መንግስት የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች እኩልነት እንዳረጋገጠ ይተርክልናል። ግን በትክክል የኢህአዴግ መንግስት ሁሉንም ብሄሮች በእኩል ዓይን ያያል? ትንሽ እንውረድና …!

በፓርላመንታዊ ስርዓት (ኢህአዴግ የሚከተለው ዓይነት) የሀገር ከፍተኛው የፖለቲካ ስልጣን ጠቅላይ ሚኒስተርነት ነው። ሁሉም ብሄር፣ ብሄረሰቦች እኩል ናቸው ካልን ለዚህ ከፍተኛ የሀገር ፖለቲካዊ ስልጣን እኩል ዕድል አግኝተው መወዳድር አለባቸው።

ታድያ በኢህአዴግ ዘመነ ስልጣን አንድ የዓፋር ወይ የሶማሌ ወይ የቤኑሻንጉል ጉሙዝ ወይ የሃረሪ ወዘተ ተወላጅ የጠቅላይ ሚኒስተርነቱን ስልጣን ለመያዝ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በእኩልነት የመወዳደር ዕድል አለው? በኢህአዴግ ዘመን ዓፋር ወይ ሶማል ወይ ጋምቤላ ጠቅላይ ሚኒስተር ሊኖረን ይችላል? አይችልም። ለምን?

የሀገር ጠቅላይ ሚኒስተር ሁኖ መመረጥ የሚችለው የገዢው ፓርቲ አባል የሆነ ብቻ ነው። አባል መሆን ብቻ በቂ አይደለም። የፓርቲው ሊቀመንበር መሆን አለበት። የፓርቲ ሊቀመንበር የሚመረጠው ከፓርቲው አባል ፓርቲዎች ነው። የኢህአዴግ አባል ፓርቲዎች የደቡብ፣ ትግራይ፣ አማራና ኦሮምያ ብሄር ተወላጆች ብቻ ናቸው። ድርጅቶቹ ብሄር መሰረት ያደረጉ ናቸው። ስለዚህ በኢህአዴግኛ አሰራር አንድ የዓፋር ወይ የሶማል ወይ የቤኑሻንጉል ወይ የጋምቤላ ተወላጅ ጠቅላይ ሚኒስተር የመሆን ዕድል ወይ መብት የለውም። ይሄ ነው እኩልነት!?

በግለሰባዊ ኢትዮጵያዊ አስተሳሰብ ግን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለማንኛውም ስልጣን ወይ ሐላፊነት እኩል የመወዳደር ዕድል ይኖረዋል። አንድ ኢትዮጵያዊ የሚመዘነው እንደ ሰው (እንደ ዜጋ) እንጂ በመጣበት ብሄር ወይ አከባቢ ወይ በሚናገረው ቋንቋ መሰረት አይደለም። ስልጣን ለመያዝ ወይ ስራ ለማግኘት ኢትዮጵያዊ ዜጋ መሆኑ ብቻ በቂ ነው። ከሌላው ጋር በትምህርት ደረጃው፣ በብቃቱ ወዘተ ይወዳደራል። ምክንያቱም ሁላችን እኩል ነን። ለሁሉም ነገር እኩል ዕድል ይኖረናል።

ስለዚህ ኢትዮጵያዊ ማንነት ማስቀደም የምንፈልገው ሁሉም ዜጋ በእኩል ዓይን ማየት ስለምንፈልግና ጠንካራ ሀገር መመስረት ስላለብን ነው።

ትግራዊ ማንነት ካለ ኢትዮጵያዊ ማንነትም አለ!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር።

It is so!!!


የአቶ አለምነው መኮንን መኖሪያ ቤት በድንጋይ ተደበደበ (ፍኖተ)

$
0
0

የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የብአዴን ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን መኖሪያ ቤት በድንጋይ መደብደቡን የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ጠቆሙ፡፡ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች እንጠቆሙት ባሳለፍነው ሳምንት የካቲት 1 እና የካቲት 2 ቀን 2006 ዓ.ም(ቅዳሜና እሁድ) ለሊት በተደጋጋሚ ማንነታቸው ባልታወቀ ግለሰቦች መኖሪያ ቤታቸው በድንጋይ መደብደቡን ተከትሎ ቤታቸው ቀንና ለሊት በፖሊስ እየተጠበቀ ይገኛል፡፡

አቶ አለምነው መኮንን የአማራን ህዝብ የሚያዋርድና የሚዘልፍ ንግግር ሲያደርጉ የተቀዳ ድምፅ ለህዝብ ይፋ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ በብአዴን ውስጥ የንትርክ ምክንያት መሆናቸው አይዘነጋም፡፡

አቡጊዳ –የአንድነት ከፍተኛ አመራር አባል ወጣት ዳንኤል ተፈራ ታስሮ በዋስ ተለቀቀ

$
0
0

ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ እንደሚጠቁመው በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ ከሆኑት ወጣትና ከፍተኛ የአንድነት አመራር አባላት አንዱ የሆነው፣ ዳንኤል ተፈራ፣ ዛሬ ታስሮ ወደ ማእከላዊ እሥር ቤት ተወስዶ ለሰዓታት ከታሰረ በኋላ ፣ በመኪና ሊብሬ በዋስ መለቀቁን ለማረጋገጥ ችለናል።

አቶ ዳንኤል በደረሰው መጥሪይ መሰረት ትላንት ቀርቦ ከፖሊስ የቀረቡለትን ጥያቄ የመለሰ ሲሆን፣ በድጋሚ እንዲቀርብ በተጠየቀው መሰረት ዛሬ ወደ ፖሊሲ ሲሄድ ነዉ በቁጥጥር ሲል እንዲወል የተደረገዉ። ከዚያም በቀጥታ እስረኞችን ቶርቸር በማድረግ ወደ ሚታወቀዉ የማእከላዊ እሥር ቤት ተወስደ። ጥቂት ሰዓታ ካለፉ በኋላም ምክንያቱ በማይታወቅ ሁኔታ በዋስ ሊለቀቅ ተችሏል።፡

አቶ ዳንኤል በምን ክስ እንደተከሰሰ በገሃድ ባይታወቅም፣ «ከፓርላማ በስተጀርባ» በሚል ርእስ የአቶ ተመስገን ዘዉዴ ሕይወትና ፖለቲካ እንቅስቃሴ ያካተተ ጽሁፍ በመጻፉ ሊሆን እንደሚችል ምንጮች ይጠቁማሉ። «አቶ ተመስገን እና ዳንኤል ስማችንን አጥፍተዋል» በሚል እነ አየ ጫሚሶ ክስ እንዲመሰረቱ በማዘዝ፣ ኢሕአዴግ የዳንኤል ክስ እንዲቀናበር ማድረጉን የገለጹት ምንጮቻችን፣ ለጊዜዉ በአሜሪካን አገር የሚገኙት አቶ ተመስገን ዘዉዴም ወደ አገር ቤት ከተመለሱ ተመሳሳይ እድል እንደሚገጥማቸውም ይናገራሉ።

አቶ አየለ ጫሚሱ በምርጫ 97 የቅንጅት የአዲስ አበባ ምክር ቤት ተመራጭ የነበሩ ሲሆን፣ የቅንጅት መሪዎች ታስረው በነበረ ጊዜ ከአቶ ተመስገን ዘዉዴ፣ የቅንጅት መሪዎች እስኪፈቱ ድረስ ለመንቀሳቀስ በሚል፣ በቅንጅት ስም ሰርተፊኬት አዉጥተው የንቀሳቀሱ ነበር። የቅንጅት መሪዎች ሲፈቱ፣ እነ አቶ ተመስገን ዘዉዴ፣ «መሪዎቻችን ተፈተዋል። አሁን ስሙን ለነርሱ እናስረክብ» በሚሉበት ጊዜ አቶ አየለ ጫሚሶ ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ልዩነቶች ይፈጠራሉ። ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት እና ወደ ምርጫ ቦርድ ቢኬድም፣ እነዚህ ተቋማትን የሚቆጣጠረው ኢሕአዴግ በመሆኑ፣ የቅንጅት ስም ለአየለ ጫሚሶ ቡድን እንዲሰጥ ይደረጋል።
የቅንጅትን መንፈስ ለማጥፋት በሚል ገዢው ፓርቲ የቅንጅትን ስም፣ ለአየለ ጫሚሶ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ በመስጠቱ፣ ከቃሊቲ የተፈቱ የቅንጅት መሪዎች የሚንቀሳቀሱበት የድርጅት ማእቀፍ ያጣሉ። የነበራቸው አምራጭ የቅንጅት ስም እንዲመለስላቸው የሕጉን ሂደት መቀጠል፣ አሊያም በአዲስ ስም መደራጀት ነበር። የኢትዮጵያ ሕዝብ ያለዉን ሁኔታ እንደሚረዳ በማመን «አንድነት ለዲሞክራሲን ለፍትህ ፓርቲ» በሚል አዲስ ስም ለመንቀሳቀስ ወስነው መንቀሳቀስ ጀመሩ።

ገዥዊ ፓርቲ ኢሕአዴግ ፣ እነ አየለ ጫሚሶን፣ እንደ መሳሪያ በመጠቀም ላይ ላዩን ለመሸፋፈን ይሞክር እንጅ፣ ከነዳንኤል መታሰር በስተጀርባ ያለው ዋና ምክንይታ፣ የአንድነት ፓርቲ እያደረጋቸው ያለው ጠንካራ እንቅስቃሴ መሆኑን የፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ። «አቶ ዳንኤል የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ግብረ ኃይልን ሲመራ የነበረ ነዉ። በአዲሱ የፓርቲዉ አመራር ዉስጥም ቁልፍ የሆነው የድርጅት ጉዳይ ኮሚቴን በሃላፊነት የሚመራ ነዉ። እንደ እርሱ ያሉትን ጠንካራ አመራር አባላትን በማሰር ከወዲሁ ፓርቲዉን ለማዳከም ስለፈልጉ ነው ይህን አይነት ተግባር የሚፈጽሙት» ያሉት አንድ ተንታኝ ኢሕአዴግ በአንድነት ላይ ጦርነት እንዳወጀም ያናገራሉ።

በተመሳስይ ሁኔታ፣ የተለያዩ ፓርቲዎችን በማሰባሰብ ረገድ፣ ትልቅ ሥራ ሲሰሩ የነበሩ፣ የአንድነት ፓርቲ በዋና ጸሃፊነት ለበርካታ አመታት ያገለገሉት የተከበሩ አቱ አስራት ጣሴም በአሁኑ ወቅት በተራ ክስ ወደ ወህኒ መጣላቸው ይታወሳል።

አቶ አንዳርጌ መስፍን የተባሉ የፓርቲዉ ብሄራዊ ምክር ቤት አባላና የፍኖት ጋዜጣ ኤዲቶሪያ ቦርድ አባል ም እንደዚሁ በፖሊሲ ፊት እንዲቀርቡም ተደርጓል።

አንድነት እና መኢአድ ብአዴንን በመቃወም የተቃውሞ ሰልፍ ጠሩ

$
0
0

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ብአዴንን በመቃወም በባህርዳር ከተማ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ጠሩ፡፡ ፓርቲዎቹ ነገ በ4 ሰዓት በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት በጋራ መግለጫ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡ ለተቃውሞ ሰልፉ አስፈላጊው የማሳወቅ ተግባር መጠናቀቁ ታውቋል፡፡
አንድነትና መኢአድ እሁድ የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም የጠሩት የተቃውሞ ሰልፍ መነሻ ምክንያት እንዲያስረዱ በፍኖተ ነፃነት የተጠየቁት የአንድነት ፓርቲ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ሰለሞን ስዩም “አማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የብአዴን የጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን የአማራን ህዝብን ክብር የሚያዋርድና በለሌሎች ብሔረሰቦች በክፉ እንዲታይ የሚያደርግ የጥላቻ ንግግር በማድረጋቸውና ብአዴንም እንደ ፓርቲ ማስተባበያም ሆነ የማስተካከያ እርምጃ ባለመውሰዱ የግለሰቡን አቋም እንደሚጋራ ያመለክታል” ብለዋል፡፡ የመኢአድ ም/ፕሬዝደንት አቶ ተስፋዬ መላኩ በበኩላቸው “የአማራ ህዝብን እየመራሁ ነው እያለ እንደዚህ አይነት አስነዋሪ ንግግር ያደረገውን ባለስልጣና የሚወክለውን ፓርቲ ለማውገዝ እንዲሁም ለህግ እንዲቀርብ ለመጠየቅ ነው ሰልፉ የተጠራው” ብለዋል፡፡
የፓርቲዎቹ የባህርዳርና አካባቢዋ መዋቅሮች የተቃውሞ ሰልፉን ለማስተባበር ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ ሲሆን የባህርዳር ከተማና የአካባቢዋ ህዝብ በነቂስ በመውጣት በሰልፉ ተቃውሞውን እንዲገልፅም ጥሪ አቅርበዋል፡፡1625497_677782778947141_1570964459_n

አሥራ አንድ ሰዓታት የፈጀው ክርክር (ክፍል 2) – (አቶ ሃብታሙ አያለው –የአንድነት ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ)

$
0
0

እንደ መግቢያ
ቅጥፈት የስብዕና መሽርሽር ምልክት ነው፡፡ የግለሰቦች ስብሰብ በሚፈጠረው ማህበረሰብ ውስጥ የስብዕና መሸርሸር ሲበራከት ማህረሰበባዊ አደጋ ሰላማዊ አኗኗሩን ማነዋወጥ ይጀምራል ፡፡ ማህበራዊ ቀውስ በሰፈነበት ደግሞ ከግለሰቦቹ ውድቀት የሚነሳው ገፊ ምክንያት እንደ ማህበረሰብ የተገነቡ የጋራ እሴቶችን ይንዳል፡፡ ባህል ፤ ሃይማኖት ፣ታሪክ ፣ወግ እና ልማዶች ሁሉ መሰረታዊ ይዘታቸውን የላቁና የሰው ልጅ እንደ እንስሳ በቀላሉ ከእንቱ ነገሮች ጋር ሲወዳጅ ይስተዋላል፡፡

ቅድስ መጽሐፍ “በተቀደሰው ስፍራ የጥፋትነ ክርኩስት ባያችሁ ጊዜ አንባ ያስተውል” እንዳለ ለዘመናት የተገነባ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ተንዶ ግብረ ሰዶማዊነት፣ ሱሰኝነት ፣ሙሰኝነት ገዳይነት ከፍ ያለ ስፍራ ሲቸራቸው ሰብዓዊነት (የሞራል ልዕልና) ምን ትርጉም ይኖረዋል?
ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች እንደ ከዋክብት ሲበዙ ‹በድሪም ላይነሩ› በሰማይ በራሪ፤ በፈጣኑ ባቡር በምድር ተሸከርካሪ፤ ባህር ውቅያኖስ ተሻጋሪ፡ ለመሆን ሀገር ተገልብጣ ፈርሳ ብትሰራ ያለሰብዓዊ ልማት ትርጉም አልባ ናት

ሀገር ያለ ሰው ሰውስ ያለ ሀገር እንደምን ይሆናል? ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ ‹‹ሀገር ረቂቅ ነው ቃሉ፤ ሀገር ውስብሰብ ነው ውሉ›› እንዳለ፡፡ እንዲሁ ነው፡፡ የገዛ ዜጎቹን ለማምከን በሃሳብ በመለየታቸው እየወነጀለ፤ ዘብጥያ እየጣለ፤ ከሀገር እያሰደደ፤ በተከፈተ የሞተ ላንቃ ከወረወረ፤ በስነ ምግባር የታነፀ ብቁ እና ጤናማ የሰለጠነ ትውልድ እንዲፈጠር ከመጣር ይልቅ በተቃርኖ ጫፍ ከተሰለፈ፤ እንኳን መሬቱን ስማዩን ቢያለማው እንደምን መንግስት ብለን ልንጠራው እንችላል?

የአንድ ሀገር መንግስት ተነግሮት ካላደመጠ፤ ተናግሮ ካልተደመጠ ወንበሩ ለጥፋት እንጂ ለልማት አይጠቅመውም፡፡ መሪዎች በህዝባቸው ላይ ቅጥፈት ከጀመሩ ወገን ለይተው ከቦደኑ፤ ከዕውቀት እና ከጥበብ እርቀው የጉልበት አገዛዝ ካሰፈኑ፤ እመነኝ የመቃብራቸው ቀን ይረዝም ይሆናል እንጂ ሞታቸውን ለማወቅ መርዶ ነጋሪ አያሻህም፡፡

ባሳለፍነው ሳምንት (አሥራ አንድ ሰዓታት የፈጀው ክርክር) በሚል ለንባብ ያቀረብኩትን የውዝግብ ውሎ የመሪዎቻችንን ቅጥፈት በማስቀደም ያቀረብኩትን አጠቃላይ ቅኝት በዚህ ከፍል አጠናቅቃለሁ ፡፡

ከማለዳው የሻይ እረፍት በፊት (በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በጆርናሊዝምና ኮምኒኬሽን ት/ት ቤት መምህር) የሆኑት ዶ/ር አብዲሳ ዘርዓይ ያቀረቡት የጥናት ይዘት በመጠነኛ ፍርሃት የተወላከፉ ሃሳቦች ቢደመጡበትም አብዛኛው የጥናታቸው ክፍል ጥሩ ሊባል የሚችል (academic discourse) እንደ ነበር አመላክቻለሁ ፡፡

ነገር ግን ዶ/ር አብዲሳ በመክፈቻ ስነ- ስርዓቱ ሁለተኛ ተናገሪ ሆነው ካስሙት ወሳኝ ንግግር መካከል ጥቂቱን ሳይጠቅሱ ማለፍ የዕለቱ ዋና ተናጋሪ የነበሩት የአዲስ አበባ ዮኒቨርስቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር አድማሱ ፀጋዬ ካደረጉት ፍሬ አልባ ንግግር ጋር ወደ ቅርጫቱ ለመጣል የማሰብ ያህል ስለተሰማኝ ጥቂት እጠቅሳለሁ ፡፡
• ቁጥራቸው የበዛ ስብሰባ ብናደርግም ለውጥ አላመጣንም !
• ሁሉ ጊዜ የሚዲያ ተሳታፊዎቻችን ከአንድ ምንጭ የተቀዱ ናቸው፡፡
• የተለየ አስተሳስብ የሚያነሱትን ለማስወገድ ከመጣደፍ በቀር ሃሳብ ለመቀብል ዝግጁነት አይታይብንም፡፡
• እኛ ትክክል ነን እነሱ ትክክል አይደሉም ብሎ መነሳት ሃሳብ አፍላቂዎችን ስለሚያገልል የሚይጠቅም አመለካከት መሆኑን መገንዘብ ይገባናል፡፡
የሚሉ ነጥቦችን ከጠቃቀሱ በኋላ የጥናት ሰነዳቸውን ሲያብራሩ ደግሞ………
• ዶሞክራሲያዊ ልማታዊ መንግስት ለመሆን በአነድ አቅጣጫ የሚጓዝ ረጅም ጊዜ ሚወስድ ሥርዓት መዘርጋት ይጠይቃል፡፡ በኢትዮጵያ የመፃፍ፤ የመናገር፤ የነፃነት፤ የተለያየ የፖለቲካ አስተሳሰብ የማራመድ ጥያቄ እያለ፤ በየአምስት አመቱ የመንግስት ለውጥ ለማድረግ ምርጫ የሚደረግበት ሥርዓት ባለበት ሁኔታ ልማታዊ መንግስት ማለት በእጅጉ አዳጋች ነው፡፡
• የመንግስት እና ፓርቲ መዋቅር ስላልተለያየ ሁሉንም ኢህአዴግ ስለተቆጣጠረ አንጂ አንድ ሁለት ክልሎች ሌላ ፖርቲ ቢያሸንፍ ሥርዓቱ እንዴት ሊቀንጥል ይችላል? አንኳር በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች እንኳን መግባት ባልተፈጠረበት ሁኔታ፤ እኔ ከስልጣን ከወረድኩ ሌላው መጥቶ ያፈረሰዋል በሚል ስጋት ስልጣን የሞት ሽሪት ጉዳይ ስሚሆን ከአምባገነንነት ወጪ ሌላ አማራጭ ሊኖር አይችልም፡፡ ሲሉ ጥሬ ሃቁ ላይ ደፈር ሲሉ ተስተውለዋል

ሌላኛው ጽሁፍ አቅራቢ አቶ ሙሼ ሰሙ በበኩላቸው ባመዛኙ ከዶ/ር አብዲሳ ጋር የሃሳብ አንድነት ነበራቸው ማለት ይቻላል ፡፡ አቶ ሙሼ ጠንከር ባሉ ቃላት ‹‹ልማትዊ የሚለው የአህአዴግ አጀንዳ ከማደናገሪያነት የዘለለ ትርጉም የለውም›› ሲሉ ከደመደሙ በኋላ ‹‹በእኔ እምነት ልማታዊ ያልሆነ መንግስት የለም፤ የአንድ ሀገር መንግስት የዕለት ተዕለት ስራ ልማት ነው፡፡ መንግስታት ከዚህ ውጪ ምን ተልዕኮ አላቸው? የፖለቲካ ፍስፍና እና ስልት ነው ከተባለ ዴሞክራሲያዊነት የሚለውን ቀልድ ትቶ ዳቦ እንሰጣችኋለን መብትና ነፃነት አትጠይቁን ብሎ በግልፅ መምጣት ነው፡፡ ነፃነትን የዳቦ ተከታይ ማድረግ ደግሞ የአቶ መለስ አቋም ነበር ሲሉ ጠቅሰዋል፡፡

አቶ ሙሼ የልማታዊ መንግስት ፅንሰ ሃሰብ አፍኝ ባህሪ ምን እንደሚመስል ከዘረዘሩ በኋላ ትኩረታቸውን ወደ ዕለቱ ርዕስ በማድረግ
• ይህ የምትሉት የልማታዊ መንግስት ባህሪ አጠቃላይ የህዝብን አመለካከት በአንድ ፖለቲካ ፓርቲ ዕምነት ላይ በማጠር በዚያ ማለፍን አስገዳጅ አድርጎ ያመጣል፡፡ ልማታዊ ጋዜጠኛ፤ ልማታዊ ቄስ፤ ልማታዊ ሼክ ወ.ዘ.ተ… የሚባለውም ከዚህ ጠቅላይ ባህሪ በመነሳት ነው፡፡
• ገና በጠዋት ኢህዲግን በመንግስት ወንበር ሲቀመጥ ለሚድያው ነፃነት ስጥቶ ደርግና ከሱ የቀደሙትን ሊያስወግዝ ደፋ ቀና ሲል ሚድያው ፊቱን ወደራሱ አዙሮ ትችት እንደ ሃምሌ ዝናብ ሲያወርድበት መጠለያ መፈለግ ሳይሆን አማራጭ ያደረገው ከምንጩ ለማድረቅ ሚዲያዎችን ወደ ማፍን መሸጋገር ነበር፡፡
• በተለይ ከሚዲያ ነፃነት አንፃር ይህ ሥርዓት ስለ ልማት ብቻ ወይም ስለ አህአዴግ ብቻ ከሚናገር አዝማሪ ጋዜጠኛ በቀር ሌሎችን ወደ አንድ ጥግ የገፋ የተበላሸ ሥርዓት ነው፡፡ ሲሉ አጥበቀው ኮንነዋል፡፡ የፕሬስ አዋጅ፤ የፀረ ሽብር አዋጅ እና የመሳሰሉት አፍኝ ህጎችም ህግን ለማፈኛ ከመጠቀም የመነጩ ከኢህአዴግ ባህሪይ የተቆዱ ናቸው ሲሉ አውግዘዋል ፡፡
የፎርችኑ ታምራት ገ/ጊዮርጊስ መከራከሪያም በይዘቱ ከዚህ የተለየ አልነበረም፡፡
• የእኔ የአስተሳሰብ ልዕልና ከሁሉም ስለሚበልጥ ሌላውን ከውግዘህ ከኔጋር ተሰለፍ እንባላለን፡፡ እሱን አንቀበልም ስንል ተወግዘን እንለያለን፡፡ ችግር የሚዘንብብንም በዚያ ጊዜ ነው፡፡
• ችግሩ ህግ- መንግስቱ እንደዚያ ሆኖ እንዲጸድቅ ያደረጉ ሊበራል አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎች በሌሎች ተደፍቀው በተለያየ አስተሳሰብ ህግ- መንግስቱ መሸርሸሩ ነው፡፡ ከህግ በስተጀርባ መብት የሚጥሱ ሌሎች ህግች እንዲወጡ ተደርጎ የሚዲያ ነፃነት እየተገፈፈ ነው፡፡
• በእኔ ግምት ይህ ህግ- መንግስት የመሸርሸርና የመጣስ የሊበራል ኢለመንቶችን የማጥፋት ዘመቻ ሲጠናከር ልማታዊ መንግስት የሚል ሃሳብ በማምጣት አፈናው የቀጠለ ይመስልኛል ፡፡ ወ.ዘ.ተ የሚሉት ከታምራት ንግግሮች ጥቂቶቹ ነበሩ፡፡

ከዚህ በኋላ በዕለቱ መሪ ሃሳብ ይዘው በዋሉት በዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ እና በአቦይ ስብሃት፤ በአቶ ዛዲግ (የኢህአዴግ ተወካይ)፤ በዚህ ፅሁፍ አቅራቢ (የአንድነት ፓርቲ ተወካይ) እና በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በኩል ሰፊ የሃሳብ ንትርክ ተደርጓል፡፡

የኢህአዴግ መሪዎች የአደባባይ ቅጥፈት ጎልቶ የተስተዋለው በዚህ ክፍል ጊዜ ነበር፡፡ አቦይ ስብሃት ከዚያው ከኢአዴግ ባልደረቦቻቸው እንኳን ያልታርቀ የተለመደ አወዛጋቢ ሃስብ ሰነዘሩ፡፡ ”ልማታዊ መንግስት ዛሬ ያመጣነው ሃሳብ አይደለም ገና ጫካ ሳለን ሁለት የሚያጠና ቡድን ልከን ሊብራሊዝምና ሶሻሊዝምን አጥንተን ለኢትዮጵያ እንደማይበጅ ካረጋገጡልን በኋላ ልማታዊ መንግስት የሚለውን ፅንሰ ሃሳብ ይዘን መጣን፡፡”

ይህንን የአቦይን ንግግር ተከትሎ የልማታዊ መንግስት ከ1992 በኋላ የህወሃትን መሰንጠቅ ተከትሎ የመጣ ስለመሆኑ የራሳቸውን ሰነድ እየጠቀስን ተሟገትን፡፡ ዶክተር ዳኛቸው የስርዓቱ በተራ ውሸት ላይ መመስረት የደረስንበትን አሳፋሪ ሁኔታ ያሳያል ሲሉ ጀምረው ላደረጉት ረጅም ንንግር ቤቱ አጸፋውን በደማቅ ጭብጨባ መልሶላቸዋል፡፡ ይህን ጊዜ ዶ/ር ነጋሶ በ”ማንያርዳ የቀበረ ” አባባል የአቦይን ውሸት ተጋፈጡት፡፡ ”ለ10 ዓመታት በፕሬዝዳንትነትና በኦህዴድ አመራርነት ስቆይ ልማታዊ የሚል ነገር የሰማሁት የህወኃትን መሰንጠቅ ተከትሎ ነው፡፡ ከዚያ በፊት ከጫካ መጣ የሚባለው ውሸትነው፡፡ ደግሞስ ልማታዊ እንሁን ስንል የልማቱ ጸር የሆኑትን ተቃዋሚዎችን ልናጠፋ ይገባል ተብሎ ነበር የቀረበው፡፡ የአሁኑ ልማታዊነት በተቃዋሚዊ ፓርቲዎች ላይ ምን ለማድረግ አስቦ ነው ዴሞክራሲ እየተባለ ያለው፡፡” አሉና እርፍ አረጉን፡፡

የፋናው ስራአስኪያጅ አቶ ወልዱ፤ ከህዳሴው ግድብ ጽ/ቤት አቶ ዛድግ፤ ከኢትዮጵያ የሠላም ኢንስቲትዮት አቦይ ስብሃት፤ ከመንግስት ኮምኒኬሽን ሚንስትር ድኤታው አቶ ሽመልስ ከማል፡ በርካታ ጥረት ቢያደርጉም በሃሳብ የበላይነት ድርጅታቸውን በሃሳብ የበላይነት ከፍ አድርገው ለመውጣት አልተቻላቸውም፡፡ እንደ ተለመደው እያደገች፤ እየተመነደገች ያለች ሀገር፤ የሚድያ ነፃነት የተከበረባት፤ አንድም ዜጋ በአመለካከቱ ያልታሰረባት ሀገር ናት ሲሉን የውሽት ካብ መፈርሱ ባይቀርም ለጊዜው በገዛ መሬዎቻችን ስንዋሽ በሚፈጠር መጥፎ ስሜት ሳያበግኑን አልቀሩም፡፡

መውጫ
አቶ ሽመልስ የውይይቱን መጠናቀቅ የሚያበስር ንግግር ሲያደርጉ የሰነዘሩት ሃሳብ ስንወያይ ብቻ ሳይሆን ስንወጣም እንዲገርመን የፈለጉ ይመስል ነበር፡፡ ‹‹በዚህ ሀገር ብሔራዊ መግባባት ያስፈልጋል፡፡ ዩኒቨርስቲውም የመግባቢያ ፍሬም ወርክ እና ተደጋጋሚ የውይይት መድረክ ሊያዘጋጅ ይገባል፡፡›› ሲሉ ከወትሮ ቁጡነታቸው የተለየ የአነጋገር ዘዬ በመጠቀም ጭምር አጠናቅቀዋል፡፡ ወይ አቶ መለስ በስንቱ ጭንቅላት ላይ ቆመው ነበር ለዚህ አስከፊ ሆኔታ የዳረጉን?1609626_590403497711255_978655788_n

መኢአድና አንድነት ፓርቲ በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ፡፡

$
0
0

ከአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እና ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የተሰጠ መግለጫ !!!!

ብአዴን ኢህአዴግ የአማራን ህዝብ የመምራት የሞራል ልዕልና የለውም፤ ህዝብ ያዋረዱ አመራሮቹም ለፍርድ ሊቀርቡ ይገባል፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚገነዘበው በዚህች ታሪካዊት እና የጥቁር ህዝብ ድል ማዕከል፤ የነፃነት ተምሳሌትና የአፍሪካ ህዝብ ኩራት በሆነች ሀገር የኋላ ዘመን ውጣ ውረድ ውስጥ ሰፊው የአማራ ህዝብ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በአንድ ተሰልፎ ለሀገር ግንባታ ተኪ የሌለው ሚና ተጫውቷል፡፡ በዚህም የተነሳ በአምባገነኖች ጡጫ ተደቁሷል፡፡ ዛሬም እንደ ትላንቱ በገዢዎቹ እየተረገጠ ያለ ህዝብ ነው፡፡
ይህ ህዝብ እንደትላንቱ ሁሉ ዛሬም በየጋራው እና በየሸንተረሩ ተበታትኖ የኔ እንዳይላት እንኳን በተነፈገው ኩርማን መሬት አፈር እየገፋ ለመኖር መዳረጉ ሳያንስ የኢህአዴግ ፖለቲካ ሌላ ሰቀቀን ጨምሮ ‹‹ጨቋኝ ገዥ መደብ የነበረ፤ ትምክህተኛ›› በሚል ጎራ መድቦ ያልዘራውን ግፍ እንዲያጭድ እያደረገው እንደሆነ ይስተዋላል፡፡

የአማራ ህዝብ እንደሌላው ጭቁን የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ ዘመኑ ባነበራቸው የአገዛዝ ሥርዓቶች የጭቆና ቀንበር ተጭኖት፤ የግፍ ፅዋ የተጋተ መሆኑ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የተሰወረ አይደለም፡፡
ይሁን እንጂ ይህንን ህዝብ እወክላለሁ የሚለው የትላንቱ ኢህዴን የዛሬው ብአዴን ያፈራቸው አመራሮች ስልጣን በመቆናጠጥ የገዛ ህዝባቸውን ከመናቅና ከማዋረድ አልፈው ‹‹ትላንት ሽርጣም ያለህ ትምክህተኛ አንገቱን ይድፋ ዛሬ ተራው ያንተነው›› በማለት በግፍ እንዲገደል ማድረጋቸው ሰቆቃው ከህዝብ ህሊና ሳይወጣ አቶ መለስ ‹‹ጫካ መንጣሪ ሞፈር ዘመት›› ብለው እንደተሳለቁበት ሁሉ በሳቸው ራዕይ አስቀጣይ በዛሬዎቹ የብአዴን አመራሮችም ያው ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠሉ አገዛዙ የደረሰበትን አሳፋሪ ደረጃ በግልፅ ያሳያል፡፡

የክልሉ ምክትል ፕሬዘዳንት እና የብአዴን ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን በቅርቡ አደረጉት ተብሎ የተደመጠው አስነዋሪ ንግግርም የክልሉን ህዝብ ብቻ ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ የናቁ እና ያዋረደ፤ የሀገሪቷን ህገ- መንግስት በግልፅ የጣሰ የወንጀል ተግባር ነው፡፡ በተጨማሪም የአማራን ህዝብ ከሌሎች ወንድሞቹ ለመነጠልና አንገቱን ደፍቶ እንዲኖር የተደረገ ዘመቻ ነው፡፡
የኢህአዴግ አገዛዝ በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ከተጫነበት ጊዜ ጀምሮ በሁሉም ክልል ያለው ህዝብ በራሱ ቋንቋ ተናጋሪዎች በግፍ እየተገዛ፤ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቱ ተገፍፎ በድህነት አረንቋ ውስጥ እየኖረ ቢሆንም የአማራን ህዝብ እንወክላለን እንደሚሉት ብአዴኖች የሚመራውን ህዝብ በአደባባይ በተደጋጋሚ የዘለፈ፤ ያዋረደ እና አንገት ያስደፋ ድርጅት አለ ለማለት ይቸግራል፡፡

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የአማራን ህዝብ የመምራት የሞራል ልዕልና የሌለውን ብአዴን ኢህአዴግን ለመታገል መላውን አባላትና ደጋፊዎቻችንን ከጎናችን በማሰለፍ በፅናት እና በብቃት መታገል ያለብን ወሳኝ ጊዜ ላይ እንደሆንን እንገነዘባለን፡፡

መላውን ህዝብ ከዳር እስከ ዳር አንቀሳቅሰን ሰላማዊ ትግሉን ፍሬያማ በማድረግ አገዛዙ እንዲለወጥ እና የኢትዮጵያ ህዝብ ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤት እንዲሆን ለማድረግ የጀመርነውን ሰላማዊ ትግል አጠናክረን የምንቀጥል መሆኑን እያረጋገጥን የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ በስርዓቱ ላይ ያለንን ተቃውሞ እናሰማለን፡፡ ይህ ትግል ህዝብ ያዋረዱ አመራሮች በተገቢው ፍጥነት ለፍርድ እስኪቀርቡ በሌሎች የሀገራችን ክፍሎችም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡

የባህርዳር እና አካባቢው ነዋሪዎችም በነቂስ በመውጣት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተቃውሞውን እንዲገልፅ ሀገራዊ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ድል የህዝብ ነው !!!!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር !!!

የአንድነት አባል በመሆኔ ከስራ ልባረር ነው” መምህር አማኑኤል መንግስቱ

$
0
0

የአንድነት አባል በመሆኑ በሚያስተምርበት ትምህርት ቤት አስተዳደር የተለያዩ ዛቻዎችና ማስጠንቀቂያዎች እየደረሱበት እንደሆነ የሚናገረው መምህር አማኑኤል መንግስቱ “ከዚህ በፊትም ያለምንም ምክንያት ከማስተምርበት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንስተው ወደ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አውርደውኛል፡፡” በማለት በመንግስት ኃላፊዎች የደረሰበትን በደል ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ ተደጋጋሚ ዛቻ እየደረሰበት መሆኑንና በቅርቡም ከስራው ሊያፈናቅሉት እንዳቀዱ ጨምሮ አስረድቷል፡፡

መምህር አማኑኤል ላይ እየደረሰ ስላለው ዛቻ የተጠየቁት የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ሀብቶም “በስልክ መረጃ አልሰጥም” በማለት መምህር አማኑኤል ወንጀለኛ ነው የሚል ምላሽ ለፍኖተ ነፃነት ሰጥተዋል፡፡

ለመምህር አማኑኤል መንግስቱ በማዝገበ ብርሀን አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ተመስገን ወ/ጊዮርጊስ ፊርማ በተሰጠው የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ላይ እንደተጠቀሰው፡- የመንግስት ፖሊሲና ተግባሮች በተለያዩ አጋጣሚዎችና ድርጊት ማጥላላትና ሌሎችም እንዲያጥላሉ ተፅዕኖ ማሳደርና በተረጋጋና ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየሰራ ያለውን ሰራተኛመብት ተረግጧል መብትህን ለምንድነው የማታስከብረው በማለት ሽብር የመንዛት ሙከራዎችን ማድረግ የሚሉ ሀይለቃሎች ይገኙበታል፡፡

የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል የማዝገበ ብርሀን አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ትምህርት ቤት ሃላፊዎችን በስልክ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡1624404_273782822777376_963297502_n75520_315429845247207_539289201_n-125x150

አማኑኤል ዘሰላም –«ታላቁ መሪያችን» የመዘበሩት ቢመለስ በርካታ የባቡር ፕሮጀክቶችን ወጪ ይዘጋ ነበር

$
0
0

አቶ ወልደስላሴ በሕወሃት ተመድበው የጉምሩክ ምክትል ሃላፊ ነበሩ። ስራ ሲጀምሩ ደሞዛቸው 1600 ብር ነበር። በእድገት ደሞዛቸው ወደ 6000 ብር ይወጣል። እንዴት እንደሆነ በማይታወቅበት ሁኔታ ባለ 4 ፎቅ ህንጻ ባለቤት ሆነዋል። ወንድማቸው አቶ ዘርዓይ ወልደስላሴ፣ ደሞዛቸው 532 ብር ነበር። ነገር ግን በግል የባንክ አካዉንታቸው ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ ተገኝቷል። በአፋር ክልል ከ 1 ሚሊዮን አራት መቶ ሺህ በር በላይ በሆነ ወጭ የእርሻ ኢንቨስትመንትም አላቸው። ይሄ ሁሉ ሃብት ከየት ተገኘ ? አጭር መልስ ሌብነትና ሙስና !!!!
meles

አቶ ወልደስላሴ የጸረ-ሙስና ኮሚሽኑ በሙስና ወንጀል በቁጥጠር ስር አዉሏቸዋል። ይህ አይነቱን በስልጣን የመባለግና ሃብትን በማጭበርበር የማከማቸት እኩይ ተግባራት ላይ፣ የመንግስት የሕግ አካላት ሲነሱ ማየት በጣም የሚያስደስትና ጥሩ ጅማሬ ቢሆንም ዘልቆ ግን ሊሄድ አልቻለም። አቶ ወልደስላሴ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የመዘበሩት ግን ሌሎች ከፍተኛ የአገዝዙ ባለስልጣናት ጋር ሲወዳደር፣ እዚህ ግባ የማይባል ነዉ።እንግዲህ ሙስናን ከተዋጉ አይቀርም በአፍና ትናንሽ ጥንቸሎች ላይ ብቻ በመዝመት ሳይሆን ቱባ ቱባ መዝባሪዎችን በቁጥጥር ስር መዋል አለባቸው። በሕይወትም ከሌሎች በሕግ ከሕዝብ የሰረቁት ገንዘብ እንዲመለስ መድረግ አለበት።
አንድ ምሳሌ ላቀርብ። አንድ ገለልተኛ፣ «ዘ ሪቸስት» የሚባል፣ በአለም ያሉ ሃብታሞችን የሚዘረዝር ድርጅት አለ። ይህ ድርጅት በድህረ ገጹ ላይ፣ በሁሉ መስክ ያሉ የተላያዩ ሃብታሞችን ስም ፣ ምን ያህል የገንዘብ ሃብት እንዳላቸው ያስቀመጣል። በነገራችን ላይ ይህ ድህረ ገጽ ከኢትዮጵያዉያን ጋር ምንም ግንኙነት የሌለው፣ ከፖለቲክ ነጻ የሆነ ድርጅት ነዉ።

ያዉ እንደ ሚታወቀ ቢል ጌት አንደኛ ነዉ። 77.1 ቢሊዮን ዶላር አለው። በሁለተኛነት አምባገነኑ ቭላዲሚር ፑቲን ተቀምጧል (77 ቢሊዮን ዶላር)። ያዉ ስልጣኑን ተጥቅሞ ዘርፎ እንደሆነ ይታወቃል። የቀድሞ የኒዉዮርኩ ከንቲባ፣ ማይክል ብሉምበርግ 21ኛ ናቸው ( 31.2 ቢሊዮን) ። የቼልሲ እግር ኳስ ክለብ ባለቤት ሮማን አብራሞቪች 76ኛ ነዉ ( 13.6 ቢሊዮን)። የኛዉ ግማሽ ወሎዬው ሼክ ሞሃመድ አላ አሙዲ 85ኛነዉ። ( 12.5 ቢሊዮን)። የኤሲ ሚላን እግር ኳስ ክለብ ባለቤትና የቀድሞ የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስቴር ሲልቪዮ ቤሎርስኮኒ 195ኛ ናቸው። ( 6.2 ቢሊዮን) ። እንግዲህ የሃባታሞቹ ዝርዝር እንዲህ እያለ ይወርዳል።
የቀድሞ የአሜሪካን ፕሬዘዳነት ቢል ክሊንተር ፣ 80 ሚሊዮን (አስቡት ቢሊዮን አይደለም) ፣ የቀድሞ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቶኒ ብሌር 30 ሚሊዮን ፣ የአሁኑ የእንግሊዘ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዴቪድ ካሜሮን 6 ሚሊዮን፣ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የአዉስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስቴር የነበሩት ጁሊያ ጂላርድ 2 ሚሊዮን ፣ የካናዳዉ ጠቅላይ ሚኒስቴር ስቲቭን ሃርፐር 2 ሚሊዮን ፣ ዝነኛዉ የእግር ኳስ ተጫዋች ሊዮኔል ሜሶሲ 115 ሚሊዮን እና የራሷ የቴሌቭዥን ጣቢያ በአሜሪካ ያላት ኦፕራ ዊንፍሪ ደግሞ 2.9 ቢሊዮን የሚጠጋ ሃብት አላቸው።

የኛው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊ ከ1995 እስከ 2010 ያገኙት ደሞዝ 220 ዶላር በአመት፣ በጥቅሉ $2640 መሆኑን «ዘ ሪቸስት» በድህረ ገጹ ቢገልጽም፣ የአቶ መለስ ዜናዊ ሃብት ወደ 3 ቢሊዮን ዶላር እንደሆነ ግን ያስቀምጣል። የሃብታቸውም ምንጭ ሲገልጽ «ፖለቲካ»፡ እንደሆነ ይነግረናል።
ቁጭ ብዬ አስብኩ። ከቢል ክሊንተን፣ ቶኒ ብሌር፣ ዴቪድ ካሜሮን ፣ ጁሊያ ጂላርድ የመሳሰሉ የታላላቅ መንግስታት መሪዎች ከሰሩት የተለየ ፣ የፖለቲክ ቢዝነስ ምን ሊኖር ይችላል፣ አቶ መለስን እንደዚህ ቱጃር ያደረጋቸው ?

አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ፣ በቅርቡ ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ ለምን ቴሌኮሚኒኬሽንን ለግል ኩባንያዎች እንደማይሰጡ ሲገልጹ፣ «የባቡር ግንባታዉን እያደረግን ያለነው ከቴሌ በሚገኘው ገንዘብ ስለሆነ ፣ ቴሌን መልቀቀ አንፈልግም» የሚል እድምታ ያለው አስተያየት ነበር ያቀረቡት።
በአዲስ አበባ እየተሰራ ያለው የመለስተኛ ባቡር ፕሮጀክት አጣቃላይ ወጭዉ 475 ሚሊዮን ዶላር አካባቢ ነዉ። ከሰበታ -አዲስ አበባ – አዳማ የሚደርሰው ፣ ወደ መቶ ኪሎሜትር የሚሆን ድርብ የባቡር መስመር (ደብል ትራክ) ለመገንባት ፣ ከዚያም አዋሽን አልፎ እስከ ሚየሶ የሚደርሰዉን የባቡር መስመር በኤሌትሪክ እንዲሰራ ተደርጎ ለማደስ የሚያሰፍልገው ወጭ 1.1 ቢሊዮን ዶላር ነዉ። ከመዪሶ ፣ ድሬደዋን አልፎ ጅቡቲ ጠረፍ የሚደርሰዉን መስመር ለማደስ 1.5 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል። ለነዚህ ሶስት ፕሮጀክቶች የሚያስፈልገዉን ወጭዎች ብንደምራቸው፣ ሶስት ቢሊዮን ሰባ አምስት ሺህ ዶላር ይደርሳል።

«ታላቁ መሪያችን» አቶ መለስ ዜናዊ ከሕዝብ የዘረፉት ገንዘን ምንም አይነት ብድር ሳንወስድን እነዚህን ሶስት የባቡር ሃዲዶች ይገነባልን ነበር።
አቶ ኃይልማሪያም ደሳለኝ ፣ ባቡር ለመስራት በሚል ቴሌን ከሚገድሉ ፣ «ታላቁ መሪያችን» ሶስ ቢሊዮን የሚጠጋ ሃብት እንዴት እንዳገኙ ቢጠይቁ ጥሩ ሊሆን ይችል ነበር። እርሳቸው በየስብሰባዉና ቃለ መጠይቁ የሚክቧቸው አቶ መለስ፣ ላይበሉት፣ ከድሃዉ ሕዝብ የሰረቁት ገንዘብ እንደሆነ ይረዱ ነበር። ከሕዝብ የተመዘበረዉን ገንዘብ የማስመለስ ሥራ ቢሰሩ ለአገር የሚጠቅም ሥራ የሰሩ ነበር። «ታላቁ መሪያችን» አቶ መለስ ዜናዊ ከሕዝብ የዘረፉት ገንዘን ምንም አይነት ብድር ሳንወስድን እነዚህን ሶስት የባቡር ሃዲዶች ይገነባልን ነበር።

http://www.therichest.com/celebnetworth/politician/minister/meles-zenawi-net-worth/

http://www.railwaygazette.com/news/infrastructure/single-view/view/contract-awarded-for-ethiopian-electric-railway.html


ሪፖርተር –ከኢትዮጵያ ጋር መታረቅ ስለሚባለው ባልሰማውና ባላስበው እመርጣለሁ›› ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ

$
0
0

የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ የሥልጣን ዘመናቸውን ከጨረሱ በኋላ፣ የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግሥታትን ማስታረቅ እንደሚፈልጉ የመንግሥት የቴሌቪዥን ጣቢያ በሆነው ኢቴቪ በይፋ ገልጸው መስመር የያዘላቸው መሆኑንም አሳውቀው ነበር፡፡

በቅርቡ ከኤርትራ ቴሌቪዥን ጋር ሰፊ ቃለ ምልልስ ያደረጉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግን ምንም ዓይነት የዕርቅ ፍላጐት እንደሌላቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በፕሮፓጋንዳ ብልጫ እየተጠቀመበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ኢትዮጵያን በተመለከተ ለቀረቡላቸው ጥያቄ የሰጧቸው ምላሾች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

‹‹የሕዝብ ግንኙነት ብልጫ ለማግኘት ነው››

ሁለት የኤርትራ የመንግሥት ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች አንዳንድ የአገር ውስጥና የአካባቢ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ ጥያቄዎችን ለፕሬዚዳንት ኢሳያስ አንስተውላቸዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በኢትዮጵያና በኤርትራ ግንኙነት ላይ የሰጡት አስተያየት አነጋጋሪ ነው፡፡

በመግለጫው ከተገኙ የመንግሥት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ እንዲህ ብሎ ፕሬዚዳንቱን ይጠይቃቸዋል፤ ‹‹ኤርትራና ኢትዮጵያን ለማስታረቅ አንዳንድ ሙከራዎች እየተደረጉ እንደሆነ በሚዲያዎች እየተነገረ ነው፡፡ ይኼ የሚወራው ነገር እውነት ነው ወይ?›› ይላቸዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ለጥያቄው መልስ መስጠት ሲጀምሩ ፊታቸውን ጨለም አድርገዋል፡፡ የሆነ ከውስጥ የሚሰማ የቁጣ ስሜት እንዳለ ያሳብቅባቸዋል፡፡ መልስ መስጠት ቀጠሉ፡፡ ‹‹ከምኡ ዝበሃል ነገር የለን›› [እንደዚያ ብሎ ነገር የለም] በሚል በእምቢተኝነትና በእልኸኝነት ውስጥ ሆነው ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡

‹‹እንደዚያ ብሎ ነገር የለም፡፡ ወያኔ እስኪጠፋ ዕለት እንደዚህ ብሎ ማውራቱ ይቀጥላል፡፡ ዓላማውም የሕዝብ ግንኙነት (PR) ብልጫ ለማግኘት ብቻ ነው፡፡ እንደዚያ በማድረጉ የፕሮፓጋንዳ ትርፍ ያገኝ ይሆናል፡፡ ወያኔ ያላንኳኳው በር የለም፡፡ የልጆች ሥራ ነው የሚመስለው፣›› ኢሳያስ ምላሻቸው በዚህ አላበቃም፡፡

‹‹ምናልባት ቀደም ሲል እንዲህ ተባለ እንዲህ ሆነ እያሉ ሊያታልሉን ሞክረው ይሆናል፡፡ እኔ የሚገርመኝ ጊዜያቸውን በዚህ ለምን እንደሚያጠፉ ነው፡፡ የአዞ እምባ ነው፡፡ እኛን ሰይጠን እነሱን መልዓክ ለማስመሰል፡፡ ምንም ባልሰማውና ባላስበው እመርጣለሁ፡፡ በአገር ውስጥም በውጭም ያለው የኤርትራ ሕዝብ ፈጽሞ ስለዚህ ማሰብ የለበትም፤›› ብለዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ በዚሁ ምላሻቸው እየተባለ ያለው የዕርቅ ጥያቄ የውሸት መሆኑን፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የፈጠራ ወሬ መሆኑንና ኤርትራዊያንን ለማሞኘት መሆኑን ይናገራሉ፡፡

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በሰጡት መግለጫ የኢትዮጵያ መንግሥት ዕርቅ ለመፍጠር ‹‹ያላንኳኳው በር የለም›› ካሉ በኋላ ዓላማው እውነት ዕርቅ ፍለጋ ሳይሆን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሰላም ወዳድ መስሎ ለመታየት ነው የሚል አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ ከዚሁ ቀጥሎ የቀረበላቸው ተከታይ ጥያቄም ከዚሁ ጉዳይ ጋር ቅርበት ያለው ነው፡፡

‹‹ከዚህ ጋር በተያያዘ [የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳይ ምክትል ኃላፊ የነበሩት] ኸርማን ኮኸን የኢትዮጵያንና የኤርትራን ግንኙነት ወደነበረበት መመለስ አለበት በሚል የመፍትሔ ሐሳብ አቅርበዋል፡፡ ይኼና ሌሎች ጽሑፎች የአሜሪካ መንግሥት አቋም ናቸው ብሎ መውሰድ ይቻል ይሆን?›› የሚል ነበር፡፡ የፕሬዚዳንት ኢሳያስ ምላሾች በአብዛኛው በንቀት የተሞሉ የሚመስሉ ነበሩ፡፡ ‹‹አምባሳደሩ ኤርትራን ከብርድ እንታደጋታለን ነው የሚሉት፡፡ የምን ብርድ ነው እኛ ዘንድ ያለው? ኤርትራ ገዳም ወጥታለችና ወደ ቤቷ እንመልሳት ነው እኮ የሚሉት፤›› የሚል ምላሽ ፕሬዚዳንቱ ሲሰጡ የቁጭት ስሜት ይነበብባቸዋል፡፡

አምባሳደር ኸርማን ኮኸን የቀድሞ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ኃላፊ ሲሆኑ፣ በምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች የአሜሪካን መንግሥት በውጭ ፖሊሲ ከሚያማክሩ መካከል ናቸው፡፡ ‹‹ኤርትራን መታደግ አሁን ነው›› በሚል በቅርቡ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) በጻፉት የመፍትሔ ሐሳብ፤ ኢትዮጵያ አወዛጋቢውን የባድመ ግዛት ለኤርትራ እንድትሰጥ፣ በሁለቱም አገሮች መካከል ዕርቅ እንዲወርድ፣ ይኼም በአንድ ገለልተኛ የአውሮፓ አገር [ማን እንደሆነ ያልተገለጸ] አነሳሽነት እንዲጀመር የሚሉ ናቸው፡፡ የእሳቸው የዕርቅ ሐሳብ መነሻ ሁለቱም መንግሥታት (ኢትዮጵያና ኤርትራ) በድንበር አካባቢ ባለው ሰላምና ጦርነት አልባ ሁኔታ ተሰላችተዋል፡፡ ሁለቱም መንግሥታት የዕርቅ ፍላጎት አሳይተዋል የሚል ነው፡፡ ለዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያምና ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በተለያዩ ሚዲያዎች የሰጡዋቸው የተለሳለሱ አስተያየቶችን መታዘባቸውን መሠረት ያደረገ ነው፡፡

ኸርማን ኮኸን፣ በተጨማሪ ያነሱት ጉዳይ ኤርትራ በሶማሊያ በምታደርገው አፍራሽ እንቅስቃሴ ምክንያት በፀጥታው ምክር ቤት የተጣለው ማዕቀብ እንዲነሳ የሚል ነው፡፡ ለዚህም እ.ኤ.አ. ከ2009 ዓ.ም. ጀምሮ ኤርትራ አደብ መግዛቷንና አልሸባብን ስለመደገፏ አንድም ማስረጃ አልተገኘም የሚል ነበር፡፡ አምባሳደሩ ጽሑፋቸውን ባወጡበት ወቅት ይኼ አስተያየት ተመድና የአሜሪካ መንግሥት ካቀረቧቸው ሪፖርቶች ጋር የሚቃረን መሆኑ ተገልጿል፡፡

‹‹ከብርድ ሊገላግሉን ነው?›› በሚል ፌዝ መሰል ንግግር የጀመሩት ፕሬዚዳንቱ የአምባሳደሩን ሐሳብ አጣጥለዋል፡፡

‹‹በ[ሸባብ] ምክንያት በኤርትራ ሕዝብ ላይ ከሳሽ ራሳቸው ፈራጅ ራሳቸው ሆነው ቀጥተውናል፡፡ በፈጠራ ታሪክ ነበር ማዕቀብ ያስጣሉብን፡፡ አሁን ደግሞ ከ2009 ጀምሮ ምንም የሉበትም ይላሉ፤›› በማለት ቀደም ሲል ከ2009 በኋላ በኤርትራ ላይ የፀጥታው ምክር ቤት የጣለው ማዕቀብ ድሮም፣ በተፈበረከ ውንጀላ ነው የሚለውን ንግግራቸውን አምባሳደሩ ያረጋገጡላቸው በሚመስል ስሜት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

‹‹ፕሬዚዳንት ኢሳያስ የኤርትራ ዕጣ ፈንታ ከኢትዮጵያ ጋር የተያያዘ ነው ብሎኛል፤›› በማለት አምባሳደሩ ያቀረቡትን አስተያየት ያጣጣሉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ፣ ‹‹ቆይ ከየት የመጣ ነገር ነው? መቼ የት ነው እንዲህ ያልኩት?›› የሚሉ ጥያቄዎች አቅርበው፣ ‹‹ይኼ ማለት’ኮ ኤርትራ ያለ ኢትዮጵያ የለችም እንደማለት ነው፤›› ብለዋል፡፡

በአጠቃላይ የኸርማን ኮኸን የዕርቅ ሐሳብ በተመለከተ ግን ሌላ ቀደም ሲል የተገመተ መላምት ሰጥተዋል፡፡ የኤርትራና የአሜሪካ ግንኙነትን ለማዳስ ያለመ እንደሆነ በመግለጽ፡፡ ‹‹ሐሳቡ የቀረበበትን ጊዜ፣ ይዘቱን፣ ቋንቋውንና አቀራረቡን ስትመለከተው ይኼው ነው፡፡ ኤርትራ ግን አትፈልገውም፡፡ ከአሜሪካ ጋር የሚሻሻል ዝምድና ምንድን ነው? መጀመሪያ ራሳቸው በራሳቸው በፈጠሩት ውሸት የኤርትራን ሕዝብ ለመቅጣት ከጀሉ፡፡ ‹‹እናዳክማቸዋለን፣ እንቀጣቸዋለን፤›› በማለት ምላሻቸውን ይቀጥላሉ፡፡ አሜሪካውያን ስለኤርትራ ሕዝብ መወሰንም አለመወሰንም መብት እንደሌላቸው በማተኮር፡፡

የወያኔ ሴራ በሚለው ተደጋጋሚ አገላለጻቸው፣ ‹‹በኤርትራ ሕዝብ ላይ ከፍተኛ ጥፋት ከፈጸሙ በኋላ የኤርትራ ወጣቶች ከአገር እንዲኮበልሉ ካደረጉ በኋላ አሁን የምን ዕርቅ ነው?›› የሚል ሐሳብ አቅርበዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በቅርቡ በሱዳን ፕሬዚዳንት አማካይነት ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የዕርቅ ሐሳብ የያዘ ደብዳቤ መላካቸውን አንዳንድ ሚዲያዎች ዲፕሎማቶችን ዋቢ በማድረግ የዘገቡ ሲሆን፣ ፕሬዚዳንቱ ግን የዕርቅ ጥያቄው ከኢትዮጵያ መንግሥት የሚቀርብ መሆኑን፣ እሱም ቢሆን እውነትነት እንደሌለው ነው በዚሁ ቃለ ምልልሳቸው የተናገሩት፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ባለፈው ሰኞ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ በፕሬዚዳንት ኢሳያስ ቃለ ምልልስ ላይ አስተያየት የሰጡ ሲሆን፣ የተባለው ከእሳቸው የማይጠበቅ መሆኑንና በፕሬዚዳንት ኢሳያስ የሚመራው መንግሥት አስመራ እስካለ ድረስ ምንም አዲስ ነገር እንደማይጠብቁ ተናግረዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአሁኑ ንግግራቸው በመስከረም ወር አካባቢ የሰጡትን ቃለ ምልልስ ሙልጭ አድርገው የካዱት ይመስላሉ፡፡ ኤርትራ ውስጥ ያለው የልማት እንቅስቃሴና ሌሎች የመንግሥት አውታሮች በተለይ በኤሌክትሪክ ኃይል ዕጦት ምክንያት መቆሙን፣ እንዲሁም የአሰብ ወደብ ምንም ጥቅም እየሰጠ እንዳልሆነ ጠቅሰው፣ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት፣ ወደቡም ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ በማዘጋጀው ለኢትዮጵያ የማቅረብ ዕቅድ እንዳላቸው ተናግረው ነበር፡፡

ይህም በሁለቱም አገሮች መካከል ለሚዲያ ይፋ ያልሆነ የዕርቅ ጥረት ስለመኖሩ፣ እንዲሁም እንደ አምባሳደር ኸርማን ኮኸን የመሳሰሉ ሰዎች ፕሬዚዳንቱ ዕርቅ ማድረግ ይፈልጋሉ የሚል አመለካከት እንዲኖራቸው ሳያደርግ አልቀረም፡፡

የአሁኑ የኢሳያስ አስተያየት ግን የዚህ ተቃራኒ ነው፡፡ በአሁኑ ንግግራቸው ግን የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ በመግዛት ላይ ከምትገኘው ከሱዳን እንገዛለን ብለዋል፡፡ ይህ የብዙ ኢትዮጵያዊያንን ቀልብ የሳበ ቢሆንም፤ ምን ማለት እንደሆነ ለብዙዎች ጥያቄ ሆኗል፡፡ ቀደም ሲል በጂቡቲ በኩል ወደ ኤርትራ በሚገቡ የቡናና የጤፍ ምርቶች ምክንያት ኤርትራ በዓለም አቀፍ ደረጃ ካሉ ቡና አቅራቢዎች ግንባር ቀደም አድርጓት እንደነበር አንዳንዶች ያስታውሳሉ፡፡

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ከአገር ውስጥ ጉዳዮች በተጨማሪ በምሥራቅ አፍሪካ ፖለቲካ እ.ኤ.አ. በ2014 ምን ዕቅድ እንዳላቸው ጥያቄ የቀረበላቸው ሲሆን፣ ‹‹አሁን አላወራውም እንጂ በክልሉ ጉዳዮች ቀጥተኛ ተሳታፊ ለመሆን ዕቅድ አለን፤›› ብለዋል፡፡ በአካባቢው እየመጣ ያለው ለውጥ የኤርትራን ቀጥተኛ ተሳታፊነት እንደሚጠይቅ የገለጹት ኢሳያስ፣ በአካባቢው ፖለቲካዊ ጉዳዮች ከዚህ በፊት በተለየ ሁኔታ ለለውጦች ምላሽ መስጠት ሳይሆን፣ ቀድሞ ዕርምጃ በመውሰድ የለውጡ አካል ለመሆን የኤርትራ መንግሥት ዝግጅቱን አጠናቋል ብለዋል፡፡ የፕሬዚዳንቱ ንግግር ወዴት እንደሚያመራ ግን አመላካች የለም፡፡ ከዚህ በፊት ጎረቤት አገሮችን በመውረርና በመተንኮስ እንዲሁም በሶማሊያ ጣልቃ በመግባት የሚታወቁት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በተያዘው አዲሱ የአውሮፓውያን ዓመት ግን ሊገልጹ ያልፈለጉት ጉዳይ እንዳለ ጠቁመዋል፡፡

አዲስ አበባ የሚገኙ የዓረና ፓርቲ ወጣት አባላት በአሰብ ወደብ ዙሪያ ጥልቅ ፖለቲካዊ ውይይት አደረጉ

$
0
0

በአዲስ አበባ የሚገኙ የዓረና ፓርቲ አባል ወጣቶች የአሰብ የባህር በርን በተመለከተ በየካቲት 2/2006 ዓ.ም ፓርቲው በከፈተው አዲስ ጽ/ቤት ጥልቀት ያለው ፖለቲካዊ ውይይት አድርጓል፡፡

በእለቱ ሰፊ ትንተና ያቀረበው ደራሲ እና ፖለቲከኛ ወጣት አስራት አብረሃም ሲሆን በውይይቱ ጊዜም ወጣቶቹ የጦፈ ክርክር አካሄደዋል፡፡ ወጣት ፖለቲከኛው ስለ አሰብ ጉዳይ ሲያብራራ ንጉስ ሐይለሥላሴ በአንድ ወቅት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ) ወይይት ቀርበው መመለስ ያለበት የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኤርትራዊያን የዜግነት (የኢትዮጵያዊነት) ጥያቄም የአለም አቀፍ ተቋሙ በአግባቡ አጢኖ መመለስ እንዳለበት ሽንጣቸውን ገትረው በመከራከር የኢትዮጵያ አንድነት ሲያጸኑ በህወሀት የአገዛዝ ዘመን ግን የተገላቢጦሽ ድርጊት መፈጸሙ ምን ያህል ኃላፊነት በማይሰማው ግድየለሽ መንግስት እየተመራን መሆኑን ጠቅሶ፣ እኛ ኢትዮጵያዊያን እያልን ያለነው «አሰብ ይገባናል» ብቻ ሳይሆን “የኛ ነው” ሲል ሀሳቡን አንጸባርቆዋል፡፡
ቀጥሎም በውይይቱ ወቅት የአልጀርሱ ስምምነት በሁለቱም መንግስታት ስላልተከበረና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እንዲሁም ሉዓላዊነት የሚጻረር ስለሆነ መከበርም እንደሌለበት በመጥቀስ ኢትዮጵያና ኤርትራ አዲስ ድርድር አድርገው የኢትዮጵያ የተፈጥሮ የባህር በር ባለቤትነትም የሚያረጋግጥና ሉዓላዊነታችን የሚያከብር ስምምነት መደረግ እንዳለበት አንስቶዋል፡፡

ኤርትራ በሪፈረንደም (ሪፈረንደም ከሆነ -ምክንያቱም “ነጻነት ወይስ ባርነት” ተብሎ ሕዝባዊ መደረጉ እጅግ አከራካሪ ሆኖ ሳለ) ከእናት አገርዋ ስትገነጠል የኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር ከየት ወዴት እንደሆነ በውል ሳይካለል የተደረገ ችኩል ፍቺ መደረጉ ይታወቃል፡፡

ወጣቶቹ በውይይታቸው ኢትዮጵያ አለአግባብ (በኢህአዲግ ችኩል ውሳኔ የተነሳ) በአመት ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለጅቡቲ ወደብ ላይ ኪራይ በመክፈል ለከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ ከመዳረጓ ባሻገር የባህር በር አለመኖር ከብሔራዊ ጸጥታ እና ደህንነታችን በቀጥታ የተቆራኘ በመሆኑ የአጋራችን ሰላም አደጋ የተጋረጠበት መሆኑን በአጽንኦት ገልጾዋል፡፡

እናት አገር ኢትዮጵያ ልጇ ሳትክድ ከአፍንጫው አርቆ ማየት የተሳነው አምባገነኑ ኢሳያስ አፈወርቂ፣ እናት አገሩን በመክዳት አልፎ ተርፎም የሻእቢያ ሎሌ የሆኑት የህወሀት መሪዎች «ኤርትራ የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት ናት ፤ አሰብም የኤርትራዊያን ነው» በማለት ኤርትራ የማታውቀውንና የማይመለከታትን የባህር በር እንድታገኝ ማድረጋቸው፣ በኢህዲግ ዘመን ከተፈጸሙ ታሪክ ይቅር የማይላቸው ከባድ ስህተቶች ቀዳሚ መሆኑ ወጣቶቹ በክርክራቸው ጠቅሰዋል፡፡

እንዲሁም አጼ ዮሐንስ የባህር በር አስፈላጊነትን በተመለከተ “እንበለ ባህር በር መንግስት አይጸናም” በማለት ወደር የማይገኝለት የላቀ የአገር ፍቅር እንደነበራቸው፤ ጨፍጫፊው ኮሌኔል መንግስቱ ሀይለማርያምም ቢሆን በአገር አንድነት እና ሉዓላዊነት ጉዳይን በተመለከተ ድርድር እንደማያውቅ እና ጠንካራ አቋም እንደነበረው፣ በአንጻሩ ሁሌ ለኤርትራዊያን የሚያደላው መለስ ዜናዊ እና ፓርቲው «የባህር በር የኛ አይደለም። አመጣለሁ የሚል ካለም ብረት አንስተንም እንታገለዋለን» ማለቱ ከኢትዮጵያ መሪ የማይጠበቅ ንግግር መናገሩ በታሪክ ተዘግቧል፡፡

ዓረና ፓርቲም የአሰብ ወደብ የኢትዮጵያ የተፈጥሮ የባህር በር በመሆኑ እና የአለም አቀፍ ህጎችም (International Law) ስለሚደግፋት አገራችን ህጎችን ተንተርሳ ብሔራዊ ጥቅሟን እና ሉዓላዊነቷን ማስከበር እንዳለባት የሚያምን ፓርቲ መሆኑ ይህንኑ ለማስፈጸምም በጽናት እንደሚታገል በፕሮግራሙ አስፍሮት ይገኛል፡፡

በመጨረሻም ወጣቶቹም አሰብም ሆነ ቀይባህር በጠቅላላው ከኤርትራዊያን በፊት የትግራይ ነገስታት እንደሚያውቁት እና የባህር በሩን ላለማጣት አባቶቻችን ከባድ ተጋድሎ አድርገው ታሪካዊ ጠላቶቻችን ቀይ ባህርን የአረብ ባህር ለማድረግና አባይን ከምንጩ ለመቆጣጠር የነበራቸው ህልም በጽናት መክተው ያስረከቡን በመሆኑ፣ አዲሱ ትውልድ ድርብ አደራ እንደተጣለበት እና ይህንን ጥያቄ የመመለስ ታሪካዊ አደራም እንዳለበት በመጥቀስ ውይይቱ ተደምድሞዋል፡፡ ወይይቱ በተለያየ ርእሰ ጉዳዮች ዙሪያ እንደምንቀጥልም ተረጋግጦዋል፡፡

ኪዳነ አመነ

የፈረደበትስ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንጂ ግንቦት 7 እና የኤርትራ መንግስት አይደሉም! (ለአቶ ተክለሚካሄል አበበ፤ ጥያቄዎች ምላሽ ቢሆን) ያሬድ ኃይለማርያም

$
0
0

በመጀመሪያ በአቅርቡ በተከታታይ ለአንባቢያን ያቀረብኩዋቸውን ሁለት ጽሁፎች አንብበህና ጊዜህንም ወስደህ በዝርዝር ላቀረብከው የሙግት ሃሳብ ምስጋናዮ የላቀ ነው። ለነገሩ የጽሑፌም ዋና አላማ ጉዳዩን ሕዝብ እንዲያውቀው ብቻ ሳይሆን በተነሱት ነጥቦችም ዙሪያ በአንባቢዎች ዘንድ የውይይት ሃሳብንም በማጫር ጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኝም ጭምር ስለሆነ ያንተ ምላሽ እኔንም በዚሁ ጉዳይ ላይ በድጋሚ እንድመለስበት አድርጎኛል። ምንም እንኳን ባነሳሃቸው በርካታ ሃሳቦች ፍጹም የተለያየ አቋም ያለን ቢሆንም ከእንዲህ አይነቱ የውይይትና ሃሳብን ሥልጡን በሆነ መልኩ የማንሸራሸር ልምድ ከየኮምፒቱሩ ጀርባ ተደብቀው በፈረስ ስማቸው መረን የለቀቀ እና ድንቁርና የታከለበትን ስድባቸውን ለሚወረውሩት የሳይበር አርበኞች ትምህርት ሊሆን ይችላል ብዮ አምናለሁ፡፡ አንዳንዶቹ ከእኔም አልፈው የኢትዮጵያን ሕዝብ ጭምር ጸያፍ በሆነ መልኩ ለመዝለፍና ለማንቋሸሽ ሞክረዋል።

ለምሳሌ ያህል እጅግ ድንቁርና በሚታይበት መልኩ በቤልጂየም ከሚገኙ የግንቦት 7 ደጋፊዎች ወይም አባላት መካከል በአንዱ ECADForum በተሰኘው ድኅረ-ገጽ ላይ Anicent Ethiopia በሚል ቅጽል ስም እጅግ አሳፋሪ በሆነ መልኩ ከቀረቡት ሃሳቦች አንዱን ቃል በቃል ከነ አጻጻፍ ግድፈቶቹ ልጥቀስ፤ እንዲህ ይላል ‘… ethiopia’s hostory teaches us that when ethiopia’s unity and it’s children face such problems, not all ethiopians were ethiopia’s defenders, 80% of the population were bandas, only ethiopia’s brave children had resisted and won all the wars against ethiopia’s enemies. …’ ምንጭ http://ecadforum.com/Amharic/archives/10949/)። እንግዲህ እንዲህ የኢትዮጵያን ሕዝብና ታሪክ ፍጹም አሳፋሪ በሆነ መልኩ ጥላሸት የሚቀቡ የግንቦት 7 ደጋፊዎች እና አንዳንድ አባላቱ ህልማቸውም ሆነ ቅዠታቸው ምን እንደሆነ ግልጽ ስለሆነ በየድኅረ ገጹ ለሚጭሩት ነገር ሁሉ መልስ መስጠት ጊዜ ማጥፋት ነው። በነጻነት ትግል ስም ግን ቀጣዮቹ ወያኔዎች ለመሆን ማቆብቆባቸውን ግን መረዳት አያዳግትም። ለማንኛውም የሚማር አእምሮ ካላቸው ተቃውሟቸውንም ሆነ ነቀፌታቸውን ሥርዓት ባለው መልኩ ለማቅረብ ከአንተ የሙግት ሃሳብ አቀራረብ በመጠኑም ይማራሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። ለእነዚህ ሰዎች በዝርዝር ምላሽ መስጠቱ ጊዜ ማባከን ብቻ ሳይሆን ወደወረዱበት አዘቅትም አብሮ ማቆልቆል ስለሚሆን “ግንቦት 7 ሆይ በየመንደሩ ያፈራሃቸውን እንደ አባይ በሬ ያልተገሩ ተሳዳቢ ‘ነጻ አውጪዎቻችንን’ ከሕዝብ ጋር ሳያጣሉህ በፊት ቢያንስ በሥነ-ምግባር አንጽ” ብሎ ማለፉ ሳይሻል አይቀርም።

በዝርዝር ወዳቀረብካቸው ትችቶችና የሙግት ሃሳብህ ከመግባቴ በፊት ለጽሑፍህ ከሰጠኸው ርዕስ ልነሳ። ከዛም በአግባቡ መልስ ለመስጠት ያመቸኝ ዘንድና አንዱን ነጥብ አንስቼ ሌላውን እንዳልተው ልክ አንተ ባቀረብከው ቅደም ተከተል መሰረት እኔም ምላሼን እሰጣለሁ። “የፈረደበት ግንቦት 7፤ የፈረደባት ኤርትራ” የሚለው ርዕስህ ለነዚህ ሁለት አካላት ያለህን የረዥም ጊዜ ቅርበትም ይሁን አዎንታዊ ምልከታ ለሚያውቅ ሰው ብዙም አይደንቅም። ይሁንና እንደ እኔ እምነት የፈረደበትስ የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው እንጂ እነሱ አይደሉም። ከብዙ የአፈና እና የአገዛዝ ዘመን ቆይታም በኋላ ዛሬም ታሪክ እራሱን እየደገመ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሰላም፣ የፍትሕ፣ የዲሞክራሲና የነጻነት ምኞትና ተስፋው ቂምና ጥላቻን ባረገዙና በዘረኝነት መርዝ በተበከሉ ገዢዎች፣ ‘ነጻ አውጪዎች’ እና ከጀርባ ባሉ አናቋሪዎች ወይም አጫፋሪዎች እጅ መውደቁ እጅግ ያሳዝናል። ኢትዮጵያን የምታክል ታላቅ አገር፤ ልጆቿ ዛሬም እርስ በርስ መስማማትና የአገዛዝ ሥርዓትን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማስወገድ አቅቷቸው ከወያኔ እኩል ኢትዮጵያን ያደማና ለውርደትም የዳረጋት ሻቢያ ጉያ ስር መወሸቅንና ደጅ ጠኚዎች መሆንን እንደ አንድ አማራጭ ለመውሰድ የምንገደድበት ሁኔታ ውስጥ መሆናችን እጅግ ያሳፍራል። ስለዚህ እንደኔ እንደኔ ሊታዘንለት የሚገባውም ሆኑ የፈረደበት አገሩን፣ ክብሩን፣ የባህር በሩን እና ተስፋውንም ጭምር በጎጠኞችና በጽንፈኛ ‘ታጋዮች’ የተነጠቀው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንጂ ከወያኔ ጋር በፍቅር በቆየበት ዘመን ለብዙ ኢትዮጵያዊያን ሕይወት መጥፋትና ታፍኖ መሰወር በግንባር ቀደምነት ሊጠየቅ የሚጋባው እና ‘ለኢትዮጵያ የመቶ አመት የቤት ሥራ ሰጥቻታለው’ እያለ ሲያቅራራ ለነበረው ለሻቢያ ወይም በሱ ጉያ ስር የህዝብን ትግል ወስደው ለቀረቀሩት እንደ ግንቦት 7 ላሉ ኃይሎች አይደለም።

ይህን ካልኩኝ ዘንዳ በዝርዝር ወዳስቀመጥካቸው የሙግት ነጥቦችህ ልመለስ። የጽሑፍህን ይዘት በጥቅሉ እንዳየሁት ብዙ የአስተሳሰብ ግድፈት ብቻ ሳይሆን ጭብጦችንም (ሆነ ብለህ ባይሆንም እንኳን) አጣሞና አዛብቶ የመተርጎም አዝማሚያም አይቼበታለሁ። ለማንኛውም ወደ ዝርዝር ጉዳዮቹ ልግባ።

1. ‘ለሰብአዊ መብት መሟገት አመል ሆኖበት’ በሚል ስላቅ በሚመስል መልኩ ነገር ግን አዎንታዊ ብለህ በምታስበው መንገድ ያቀረብከው መደርደሪያ የጽሑፍህን ጠቅላላ ይዘትም ሆነ እስከ ማጠቃለያህ ድረስ ለዘለቅክበት ትችትና ደጋግመህ ለጠቃቀስካቸው አመለካከቶችህም ጭምር መነሻ መስሎ ስለታየኝ በእሱ ላይ አጠር ያለ ነገር ልበል። ይህ አገላለጽ ምንም እንኳን አንተ በአዎንታዊ መልኩ ብታቀርበውም ለእኔም ሆነ ለአንባቢዎች የሚሰጠው ትርጉም ተቃራኒውን ነው። ብዙ ጊዜ እንደ ወያኔ እና ሻቢያ ያሉ አንባገነናዊ ሥርዓቶች በሰብአዊ መብቶች አያያዛቸው ላይ ለሚቀርብባቸው ትችትና ወቀሳ ምላሽ የሚሰጡት በዚሁ መልኩ ነው። እነሱም አንተ በገለጽከው መልኩ፤ ነገር ግን አሉታዉ በሆነ ጎኑ የመብት ተሟጋች ድርጅቶችን ወይም ግለሰቦችን በሆነ ባልሆነው የመጮህ ‘አመል’ ወይም ‘ሱስ’ የተጠናወታቸው አድርገው በመግለጽ ያንቋሽሿቸዋል። መልዕክታቸውም ባደባባይ እየገደሉም እኛ የፈጸምነው አንዳችም በደል ወይም የመብት ረገጣ ሳይኖር ነው ተሟጋቾቹ በባዶ ሜዳ የሚጮሁት የሚል የአይነ ደረቅ መከላከያ ነው። ኢሰመጉ የዚህ አይነቱ ዘለፋ አንዱ ሰለባ ነው። ይህ አይነቱን ነቀፌታ በእኔ ጽሑፎች ላይ ሃሳብ በሰጡት የግንቦት 7 ደጋፊዎችም ተንጸባርቋል። የእነዚህን ሰዎች ትችት ‘አወይ መመሳሰል’ (ከገዢዎቻችን ጋር ማለቴ ነው) በሚል ትዝብት አልፌዋለው። ይሁንና የአንተን ከገዢዎቻችን አገላለጽ ለየት የሚያደርገውና ምናልባትም የከፋ የሆነው ግንቦት 7ም ሆነ የኤርትራ መንግሥት የሚነቀፉበትን ተግባር አልተፈጸሙም ከሚል መነሻ ሳይሆን ድርጊቱን ቢፈጽሙም ትክክል ናቸው፤ ትክክል ባይሆኑም እንኳን ሊጠየቁ አይገባም ወይም በገለጽካቸው ምክንያቶች በዝምታ ልናልፈው እንጂ ልንወቅሳቸው አይገባም የሚል ነው። ባጭሩ ‘አመል’ ሆኖብኽ ነው በማይጮኽበት ጉዳይ ለሙግት የቆምከው የሚለው ምልከታህ መሰረታዊ የሆነ የአስተሳሰብ ግድፈት የሚታይበት ሆኖ ነው ያገኘሁት። ‘አመል ሆኖብህ’ የሚለውም አገላለጽ በጽሑፌ ላይ ደረሱ ያልኳቸውን በደሎች ለማቃለልና የተበዳዮቹንም አቤቱታ ለማጣጣል ሆነ ብለህ የተጠቀምክበት መንገድም ሆኖ ነው ያገኘሁት። ለአመል ተብሎ የሚደረግ የሰብአዊ መብቶች ሙግት ቧልት ስለሆነ አሉታዊ ነገርም የለውም። የሰብአዊ መብት ጥሰት አቤቱታ በማስረጃና በእውነት ላይ እስከተመረኮዘ ድረስ ከልብ የመነጨ ሙግት እንጂ አንድን ወገን ለመጉዳት ወይም ለመጥቀም ወይም ለአመል ሲባል የሚፈጸም አይደለም። ተበድለናል የሚሉት ወገኖች ለቅሶ የበለጠ እውነቱን እንዳረጋግጥና በቂ ማስረጃዎችንም እንዳሰባስብ በጎ እልህ ውስጥ ይከተኛል እንጂ አንተ እንዳልከው እውነታውን በጥሞና እንዳልመረምርና ግራ ቀኙንም እንዳላይ አይጋርደኝም።

2. እውነት ነው እኔና ተክሌ ከ1990ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ እንተዋወቃለን። ጽሑፌን ያነበቡ የግንቦት 7 ደጋፊዎች ከሥነ-ምግባርም ጭምር በራቀ መልኩ ለሰጡዋቸው ነቀፌታዎች ለያንዳንዱ ምላሽ አለሰጠሁም። በእንዲህ ያሉ ፍሬ ከርስኪ ጎዳዮችም ጊዜዬን አላጠፋም። ሆኖም ስለኔ ማንነት ለሰጠኸው ምስክርነት አመሰግናለሁ።

3. ኦሬንጅና አፕልን የመደባለቅ ያህል አብረው የማይነጻጸሩ ነገሮችን በማነጻጸር የመገናኛ ብዙሃንን፣ ግንቦት 7ን፣ ኢሳትን እና የኤርትራ መንግሥትን ተችተሃል፤ ይህም ስህተት ነው በሚል ወዳቀረብከው ዝርዝር ጉድያ ልምጣ። የምንወያይበት ትልቁ ፍሬ ጉዳይም እሱ ቢሆንም በመካከላችን ያለው የሃሳብ ልዩነት ግን እጅግ ሰፊ ነው። በዚህ ዙሪያ ያነሳሃቸው ፍሬ ነገሮች ባጭሩ ሦስት ናቸው። የመጀመሪያው ለነጻነት ትግል ብሎ ወዶና ፈቅዶ ጫካ በገባ ሰውና ኑሮን ለማሸነፍ በየአረብ አገሩ ከባርነት ባልተናነሰ መልኩ ተሰዶ እየተሰቃየ ባለው የህብረተሰብ ክፍል መካከል ያለው ልዩነት አልገባህም የሚል ነው። ሁለተኛው ደግሞ የሽምቅ ውጊያ ለማካሄድ በፈቃዳቸው ወደ ጫካ የገቡ ሰዎች ሰብአዊ መብቶቻቸውን ለአላማዎቻቸው ሲሉ ትተው የሸፈቱ ሰዎች ስለሆኑና የዘመቱትም ለመግደል ወይም ለመሞት በመቁረጥ ስለሆነ እነዚህ ሰዎች በየትኛውም አስከፊ ሁኔታ ውስጥ ቢገኙ እኳን የሰብአዊ መብት ጥያቄ ሊነሳ አይችልምና ያለቦታው ነው ሙግት የገጠምከው የሚል ነው። ሦስተኛው ነጥብህ ግንቦት 7 በትጥቅ ትግል የሚያምን እና በተግባር ላይ ያለ ድርጅት በመሆኑ፤ እንዲሁም የኤርትራ መንግስ ለኢትዮጵያ ታጣቂ ኃይሎች ጥላ ከለላ በመሆኑ ሊመሰገኑ እንጂ ሊወቀሱ አይገባም የሚል ነው። ካልተሳሳትኩ የጽሁፍህ መልዕክት ከነዚህ ሦስት ነጥቦች የዘለለ አይደለም። እያንዳንዱን በየተራ ልመልስ።

4. እርግጥ ነው ወደ ኤርትራ ለትግል በሄዱትና ወደ አረብ አገሮች በተሰደዱት ወገኖቻችን መካክል ያለው ልዩነት አንተም እንዳስቀመጥከው ግልጽ ነው። ይሁንና ሁሉም አገራቸውን ለቀው የወጡበት ምክንያት ግን ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ነው። ሁሉም በአገራቸው እንደ ሰው ልጅ ተከብረው ሊኖሩበት የሚያስችል የፖለቲካም ሆነ የኢኮኖሚ ነጻነትና መፈናፈኛ መታጣት ነው። ሁሉም የወያኔ የአፈና ሥርዓት ሰለባዎች ናቸው። የኢኮኖሚና የፖለቲካ ነጻነት ቢኖርና ሁሉም በሃገሩ እንደልቡ ሰርቶና ሃብት አፍርቶ የሚኖርበት አመቺ ሁኔታ ቢኖር ኖሮ በአስከፊ ሁኔታ ውስጥ ወዳለችው ኤርትራም ሆነ ወደሌሎች አረብ አገሮች ኢትዮጵያዊያን ነፍጥም ሊያነሱ ይሁን በባርነት ሊያገለግሉ አይሰደዱም ነበር። እኔ እና አንተም ብንሆን ኑሮዋችንን በአውሮፓና ካናዳ ባላደረግን ነበር። የእዚህ ሁሉ ችግር ምንጩ አገሪቷ ያለችበት አስከፊ የሆነ ሁኔታ ነው። በመጀመሪያ እራሳቸውንም ሆነ አገራቸውን ነጻ ለማውጣት በመወሰን ሕይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለው ‘ዱር ቤተ’ ብለው ለዘመቱት ወገኖቼ የሄዱበትን መንገድ ፈጽሞ ባልደግፈውም እንኳን ነፃነታቸውን ለማግኘት ያላቸውን ቁርጠኝነት አደንቃለሁ። ዋናው ቁምነገር ግን ኢትዮጵያዊያን በማናቸውም ምክንያት ይሰደዱ፣ በየትኛውም አገር ይገኙ፣ ለየትኛውም አገራዊ ተልዕኮ ይሰማሩ ሕይወታቸው በአስከፊ ሁኔታ ውስጥ ወድቆና ቀን ጨልሞባቸው ለወገን የድረሱልን ጥሪ ሲያቀርቡ ‘አይ እናንተ ወዳችውና ፈቅዳችው ለነጻነት ትግል የሄዳችው ሰዎች ስለሆናቸው ሻቢያም ሆኑ ግንቦት 7 ያሻችውን ቢያደርጉዋችሁ መብታቸው ነውና የበላችሁ’ የሚል ምላሽ ኃላፊነት ከሚሰማው ወገን የሚጠበቅ አይደለም። እንኳን መደብደብ ቢገሉዋቸውም እንኳን ልናዝንላቸው አይገባም የሚል ጭካኔ የተሞላበት አቋምህ አስገርሞኛል፤ አሳዝኖኛልም። እነዚህ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖቻችንም ሆነ አንዳንዶቹ የሞቱት ከወያኔ ጋር ፍልሚያ ሲያደርጉና በጦር አውድማ ላይ ቢሆን ኖሮ አንድ ወታደር በጦርነት ውስጥ ለምን ተገደለ ብሎ የሚጠይቅ ቂል ሰው ያለ አይመስለኝም። እኔ ያነሳሁት ጭብጥና የእነዚኽ ወገኖቻችንም ጥያቄ ከዚህ አንተ አጣመህ ካቀረብከው ታሪክ ጋር እጅግ የተለየ ነው። ጉዳዩንም ለማጣጣል በማሰብ አንተ እንዳቀረብከው ለቅንጦት የቀረቡ የመብቶች ይሟሉልን ጥያቄዎች አይደሉም። እኔ የሳኡዲና የኤርትራውን ክስተቶች ያነጻጸርኩበት እና አንተ የተረዳህበት ወይም ልትረዳ የፈለክበት መንገድ ፍጹም ለየቅል ነው። ትልቁ የአስተሳሰብ ስህተትህም የሚጀምረው ከዛ ላይ ነው።

5. በጽሑፌ በየትኛውም ክፍል በኤርትራ ውስጥ በእስር የሚገኙት የነጻነት ታጋዮች ሳኡዲ እንዳሉት ኢትዮጵያዊያን ሠርቶ የመኖር፣ ሃብት የማፍራት፣ ሃሳባቸውን ባደባባይ የመግለጽ፣ እንደፈለጉ የመንቀሳቀስና ሌሎች ላንተ የቅንጦት የሚመስሉህ መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸው ሊከበሩላቸው ይገባል የሚል ሃሳብም ሆነ ክርክር አላቀረብኩም። እኔ እየተሟገትኩ ያለሁት በግፍ ታስረው የግፍ ተግባር እየተፈጸመባቸ ስላሉ ሰዎች ነው። የመብት ጥያቄ የሚነሳው እንደ ጉዳዩ ባህሪ እና እንደምትገኝበትም ስፍራ ነው። አንድን የሕግ እስረኛም ብትወስድ በመታሰሩ ብቻ አብዛኛዎቹን መብቶቹንና ነጻነቶቹን ይነፈጋል። ያ የቅጣቱ ዋነኛ አላማም ነው። ይህ ማለት ግን ለሰው ልጆች የሚገቡ መሠረታዊ መብቶችን ሁሉ ተነፍጎ ከሰው ተራ እንዲወጣ ይደረጋል ማለት አይደልም። በቂ ምግብ፣ ህክምና፣ መጠለያ እና ሌሎች መሰረታዊ የሆኑ ነገሮችን የማግኘት መብት አለው። ይህ መብት በቃሊትም ላሉ ይሁን በአስመራ ማጎሪያ ቤቶች አመታትን እያስቆጠሩ ላሉት ጋዜጠኞችና የመብት ተሟጋቾችም ባልተከበረብት ሁኔታ በጦርነት ላይ ላለ ወታደር ወይም ሽምቅ ተዋጊ ይከበር ብሎ መጠየቅ ላንተ፤ ይገደሉ ብለህ ለፈረድክባቸው ሰዎች ቅንጦት መስሎ ሊታይህ ይችላል። የእነዚህ መብቶች አለመከብር በአዲስ አበባና በአስመራ ያሉትን ግፈኛና አንባገነናዊ ሥርዓቶች የባህሪ አንድነትና መጥፎነት ያሳያል እንጂ ከልቡ ለሰዎች መብት ለሚጨነቅ ሰው የቅንጦት ጥያቄዎች አይደሉም።

6. ለነገሩ ለእዚህ አይነቱ ጭካኔ የተሞላበት ፍርድ የዳረገህ በአዋጅ በታወቀ የጦርነት ጊዜም ይሁን በሽምቅ ውጊያ ወቅት የመንግስትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ኃይሎች (Non-state actors) (አማጺያን፣ የተደራጁ ሽፍቶች ወይም ሽምቅ ተዋጊዎች) በአለም አቀፍ ሕጎች ስለተጣለባቸው ኃላፊነትም ሆነ የተጠያቂነት ግዴታ ያለህ ግንዛቤ ወይ የተሳሳተ ነው ወይም በኤትራና በግንቦት 7 ፍቅር ታውሯል። ይህ ካልሆን ግን እንዳንተ ሕግ የተማረ ሰው ይህን ማንም ሊስተው የማይችለውን እውነታ ይገድፋል ብሎ ማሰብ ይቸግራል። ለነገሩ በጽሑፍህ ተ.ቁ. 6 ላይ የሄግንና የጄኒቫን ስምምነቶችና በዚያ ዙሪያ የተጻፉ ትንታኔዎችን ባነብ እንደሚጠቅመኝ መክረኸኛል። እንዲህ ያለ ምክር የሚሰጥ ሰው ከላይ የተጠቀስትን ያፈጠጡ ግድፈት ይፈጽማል ብሎ ማሰብ ይከብዳል። እንደው በግርድፉ ከጠቀስካቸው አለም አቀፍ ድንጋጌዎች ውስጥ Protocol I additional to the Geneva Conventions, 1977
(http://www.icrc.org/applic/ihl/ihl.nsf/Treaty.xsp?action=openDocument&documentId=AA0C5BCBAB5C4A85C12563CD002D6D09) እንዲሁም አራቱንም የ1949 የጄኒቫ ስምምነቶች (http://www.icrc.org/eng/war-and-law/treaties-customary-law/geneva-conventions/) ብንመለከት በየትኛውም ሁኔታ መሳሪያቸውን አስረክበው በቁጥጥር ስር በዋሉ እስረኞች ላይ ድብደባና ማሰቃየት፣ ያለ ፍርድ (በወታደራዊ ፍርድ ቤት) ግድያ፣ የሕክምና እና የምግብ አቅርቦትን መንፈግን፣ እንዲሁም በባርነት የጉልበት ሥራን ማሰራትና ሌሎች ለሰው ልጅ የማይገቡ አያያዞች እንዲፈጸምቻቸው የሚፈቅድ አንድም የሕግ ማእቀፍ የለም።

7. ብዙ ጊዜ በአንተም ተደጋግሞ እንደገለጽውና የግንቦት 7 ደጋፊዎችም እንደሚሉት የሽምቅ ውጊያ ውስጥ የገባን አማጺ ኃይል የሚዳኝ ወይም በሰብአዊ ጉዳዮች ተጠያቂ የሚያደርግ ሕግ የለም፤ ያሻውን ማድረግ ይችላል የሚለው መከራከሪያ ከወዴት እንደመጣ ሊገባኝ አይችልም። እንደዛማ ቢሆን የአለም አቀፉን የወንጀል ፍርድ ቤት የአፍሪቃ አማጺያን መሪዎች ባልሞሉት ነበር። እነዚህ ሕጎች በመንግሥታት ስምምነቶች የጸደቁ ቢሆንም ተፈጻሚነታቸው ግን በመንግሥታት ላይ ብቻ ሳይሆን ነፍጥ አንግበው በተደራጁና በአማጺነት እውቅና ባገኙ ኃይሎች ላይ ሁሉ እንደየአግባቡ ተፈጻሚ ይሆናሉ። በተለይም መሳሪያቸውን ጥለው በቁጥጥር ስር የዋሉ ምርኮኞችና ወታደራዊ እስረኞች ስለሚደረግላቸው የሕግ ጥበቃና እንክብካቤ በግልጽ ተደንግጓል (http://www.icrc.org/eng/war-and-law/protected-persons/prisoners-war/overview-detainees-protected-persons.htm) ። መንግሥትም ይሁን አማጺ ቡድን እንኳን የራሱን ሠራዊት አባላት ይቅርና የጠላት ወታደሮችንም በማረከ ጊዜ አንተ እንዳልከው ቢሻው ሊረሽን፣ ቢሻው አስሮ እንዲያሰቃይ፣ ቢሻው በባርነት እንዲያቆያቸው የሚፈቅድ አለም አቀፋዊ ድንጋጌ የለም። በሰላም ጊዜም ይሁን በጦርነት ወቅት ለነዚህ እስረኞችና ምርኮኞች የተሰጡት የሕግ ጥበቃዎች አንተ ባስቀመጥከው መልኩ የሚሸራረፉ ወይም እንደ ሁኔታው የሚቀያየሩ አይደሉም። በማናቸውም ሁኔታ ውስጥ እነዚህ ታሳሪዎች ከላይ የጠቀስኳቸው መብቶች አሏቸው። ወንድሜ ተክሌ ከጋርዮሽ ዘመን ከወጣን ብዙ እርቀናልና እንዲህ ያለው ነፍጥ ያነገቡ ብድኖችን ከሕግ በላይ አድርጎ የማንገሱ አዝማሚያ መዘዙ ብዙ እንደሆነ ልትረዳው ይገባል። ከዚህ ደግሞ ለመማር ሕጉን ትተነው ያለፉ ታሪኮቻችንን እንኳን በቅጥ ማጤን በቂ ነው።

8. ከላይ ከተነሳው የታጠቁ ቡድኖች የሕግ ኃላፊነት አንጻር ግንቦት 7 ያለበትን አቋም በመጠኑ መቃኘት ተገቢ ይመስለኛል። በእኔ እይታ ግንቦት 7 አንተም ሆንክ ደጋፊዎቹና አባላቱ እንደሚሉት እንደ አንድ በትጥቅ ትግል ውስጥ እንደተሰማራ አማጺ ኃይል ተደርጎ መውሰዱ የድርጅቱን አቋም የማይመጥን የተጋነነ ገለጻ ነው። ግንቦት 7 አማጺ ለመሆን ምኞቱ ነው እንጂ ያለው በዛ አቋም ላይ ያለ ድርጅት አይደለም። የግንቦት ሰባት ምሽግ አስመራና ኢሳት ቢሆኑም፤ ‘ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው’ የሚለውን አገራዊ አባባል በደንብ አጢኖ ይመስላል ከአስመራ ይልቅ ግዳጅ እየጣለ ያለው የድርጅቱ ልሳን በሆነው ኢሳት ነው። ኢሳት ግንቦት 7ን በሚገልጽበት አኳኋን ቢሆን ድርጅቱ ያለው ቀጣዩን ምርጫ ከወያኔ ጋር ሳይሆን ከግንቦት 7 ጋር ነበር የምናሳልፈው። ወያኔ የሚሰራቸው የአኬል ዳማ እና ጂሃዳዊ አረካት ፊልሞች አልበቃ ብሎ ከዚህ ክሽፈት ልምድ የወሰደው ኢሳት በቅርቡ በብዙ ክፍሉች እየደጋገመ በኢሳት ያቀረበው የ’ሚሊኒየም ኦፕሬሽን’ የግድያ ሙከራ ፊልም ጥሩ ማጣቀሻ ነው። እንኳን ለፍልሚያ ለልምምድም እንኳ ጥይት ተኩሰው የሚያውቁ የማይመስሉት የግንቦት 7ን ኃይሎች ከሌሎች የአፍሪቃም ሆኑ የላቲን አሜሪካ አገሮች አማጺ ታጣቂዎች እኩል ማስቀመጡ አጉል መንጠራራት ነው የሚሆነው። ከዚህ ግንቦት 7ን ከካብክበት ማማ ላይ ሆነህ የሰጠኽው አስተያየትም በእኔ እይታ ፈር የሳተ ነው። ይህውም ግንቦት 7ን የተደራጅና የራሱ ውታደራዊ የዳኝነት ሕግና ስልት እንዳለው አድርገህ በማስቀመጥ ተበዳዮቹ በዛ እንደሚዳኙና ፍትሕ እንደሚያገኙ አድርገህ ያስቀመጥከውን ሃሳብ የሳምንቱ ምርጥ ቀልድ አድርጌ ወስጄዋለሁ። ያም ሆኖ ግን ግንቦት 7ም ሆኑ የኤርትራ መንግሥት መሬት ላይ በሌለ የነጻነት ትግል ስም የኢትዮጵያን ወጣቶች እየመለመሉ ወስደው የሻቢያ ቂም መወጣጫ ማድረጋቸው በታሪክም ይሁን በሕግ ከመጠየቅ አያድንም።

9. ሌላው አስገራሚውና አስቂኝ ጉዳይ ሆኖ ያገኘሁት የሻቢያንና የወያኔን የድል ጉዞ የቃኘህበት መንገድ ነው። እነዚህ ኃይሎች በትግላቸው ወቅት በራሳቸው አባላትም ላይ ሆነ በሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የፈጸሙት ግፍና በደል በታሪክም ሆነ በሕግ ይቅር የማያስብል ነው። የትግሉ መሥራቾች የሆኑትና ድርጅቶቹን በጊዜ ጥለው የወጡት አባላቶቻቸው ሳይቀሩ ድርጅቶቹ ከጦር ውድማ ውጪ በሰበብ አስባቡ ያጠፉት የሰው ሕይወት በመቶ ሺዎች የሚቆጠር እንደሆነ እየመሰከሩ ነው። ይሁንና የአለማችን መጥፎ የፖለቲካ አቅጣጫ እድል ሰጥቷቸው ለፈጸሙት በሰው ዘር ላይ የተነጣጠረ ወንጀል (crime against humanity) ሊጠየቁና በአለም አቀፍ ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ሲገባ በለስ ቀንቷቸው በእነ አሜሪካና እንግሊዝ አጃቢነት መንግስታት ለመሆን በቅተዋል። ተጋዳላይ እያሉ የጀመሩትንም የወንጀል ተግባራት ‘ያዲያቆነ ሴጣን ሳያቀስ አይለቅም’ አይነት መንግስታት ሆነውም ቀጥለዋል። እንግዲህ ፍርደ ገምድል የሆነው የአለማችን ፖለቲካ ከወያኔ እና ከሻቢያ ያነሰ ወንጀል የፈጸሙ ሌሎች የአፍሪቃ አማጺያንን ከገቡበት ጉድጓድ እያወጣ ከፍርድ አደባባይ ሲያቆም የእኛዎቹን ደግሞ ‘ተራማጅ መሪዎች’ በሚል እያሞካሸ ከነተሸከሙት ወንጀል እና ሃጢያት በላያችን ላይ አንግሷቸዋል። ዛሬም ባደባባይ ሕዝባቸውን እየረሸኑና እያሰቃዩም እንዲቀጥሉ ሁኔታዎች ተመቻችቶላቸዋል። እንግዲህ ወንድሜ ተክሌ ወያኔና ሻቢያ የገዛ ሕዝባቸውን እየረሸኑና እያስወገዱ የመጡበት መንገድ ወደ ሥልጣን ለመወጣጣት አዋጪ መንገድ ስለሆነ ‘የመረሸንና የማስወገድ’ ሕጋዊ ወይም ፖለቲካዊ ፈቃድ ለግቦት 7 እና ለኤርትራ መንግስት ይሰጥ የሚል ሙግት ነው እያቀረብክ ያለኸው። አትታዘበኝና እውነት እውነት እልሃለው እጅግ የወረደ እና በብዙ ሰዎች ዘንድም ትዝብት ውስጥ የሚከትህን ሃሳብ ነው፤ አውቀኸው ይሁን ሳታውቅ የገለጽከውና እስኪ ቁጭ ብለህ በጥሞና የተናገርከውን እንደገና መርምረው። አንድ ሰው ሲገደል እኮ እንደው እንደ ልጆች የቃቃ ጨዋታ ወይም እንደ ሆሊውድ ፊልፎች አይደልም። አንድ ሰው ያለ አግባብ በግፍ ሲገደል አብሮት የሚሞተው ፍትህ ነው። አንድ ሰው ያለ አግባብ ሲገደል የሚያዝነውና የሚጎዳው አገርና ህዝብ ነው። የሚበተን ቤተሰብ፣ ልቡ በሃዘን የሚሰበር ወገን እና በተለይም በግፍ ፈጻሚዎቹ ላይ ቂም የሚቋጥር ቀሪ ወገን አለ። ለማንኛውም አንድ በአንተና በእኔ እድሜ ያለ፣ ዘመናዊ ትምህርትን የዋጀና በተለይም የሕግ ትምህርትን የቀሰመ፣ የወያኔን እና ላንተ ባይዋጥልህም የሻቢያን ክፉ ተግባራት ለመታዘብ የቻለ ሰው እንዲህ ያለ ፍርደ ገምድል አስተሳሰብ ይይዛል ብሎ ማሰብ ይቸግራል።

10. በዝርዝር ካነሳሃቸው ሌሎች ሃሳቦች መካከል መልስ በሚያሻቸው አንድ፤ ሁለት ነጥቦች ላይ ሃሳብ ልሰንዝርና ጽሑፌን ልቋጭ። በግንቦት 7 ተበደልን ያሉት ሰዎችን በተመለከተ ቁርጠኝነት የሌላቸው እና በቅጡ ስልጠና ያላገኙ ደካማ ሰዎች አድርገኽ ከዝልፊያ ባልተናነሰ የሰነዘርከውም ሃሳብ ለትዝብት የሚዳርግህ ነው። በመጀመሪያ እኔም ሆንኩ አንተ የአገዛዝ ሥርዓቱን በትር ፈርተን ከመሸግንበት አውሮፓና ካናዳ ሆነን የነኝኽህን ወገኖች ጥንካሬና ቁርጠኝነት ለመፈተሽ አቅም አለን ብዮ አላስብም። ያሉበትንም መከራ እነሱ ስለሆኑ የሚያውቁት ልፍስፍሶች ናችሁ እያሉ ማንጓጠጡ ተገቢ አይመስለኝም። የእነዚህ ሰዎች ቁርጠኝነት የታየው ወደ አስመራ ግንቦት 7ን አምነው ለመሄድ የወሰኑ ዕለት ነው። ይሁንና እነዚህ ሰዎች በአካል ተገኝተው ያዩትና የታዘቡት ግንቦት 7 በኢሳትና በሌሎች ሚዲያዎች እራሱን አገዝፎና አሳብጦ ያቀረበበት መንገድ በተጨባጭ ድርጅቱ ካለበት ሁኔታ ጋር የማይጣጣም መሆኑ አስደንጋጭ እንደሆነባቸው ነው። ከንግግራቸው የምንረዳውም፤ እውነታውም ይኼው ነው። በድርጅቱና በበጎ ፈቃድ ዘማቾቹም መካከል የተፈጠረው አለመግባበት መንስዔው ይኼው ነው። ወንድሜ ተክሌ፤ ታዲያ ግንቦት 7ን በጥሩ ሁኔታ እንደተደራጀና እንደሚወራለትም በጥሩ የትግል አቋም ላይ እንዳለ አስመስለህ በማቅረብ የእነዚህን ወገኖች ጥያቄ ልፍስፍስና አቋመ ቢስነት እንደሆነ አድርገህ ማቅረብህ አጀብ የሚያሰኝ ነው።

11. ለነገሩ በኢሳትና በሌሎች ሚዲያዎች ስለግንቦት 7 ፍጹም የተሳሳተ ገጽታ በኢትዮጵያዊያን ዘንድ ለመፍጠር የተሰራውን ፕሮፓጋንዳ ያህል ወያኔም በአገሪቱ ውስጥ ያሉና ስጋት የሚሆኑበትን ግለሰቦችና ቡድኖች በቀላሉ ለማስወገድ ሲል ግንቦት 7ን እና ሌሎች ታጣቂ ኃይሎችን ሽብርተኛ ብሎ መሰየሙ ሌላው ድርጅቱ እራሱን በአየር እንደተሞላ ፊኛ እንዲያሳብጥና አየር ላይ እንዲንሳፈፍ ትልቅ ድርሻ ተጫውቷል። ይችን ‘ሽብርተኛ’ ተብሎ የመሰያየሟን ካርድ ሁለቱም (ወያኔ እና ግንቦት 7) ሊያተርፉባት ሞክረዋል። ወያኔ ሰላማዊ ተቀናቃኞቹን በቀላሉ ሽብርተኞች እያለ ለማጥመድና ለማስወገድ (በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞችና ሌሎች ወገኖችም ጉዳይ ሊጠቀስ ይችላል)፤ ግንቦት 7 ደግሞ ጠንካራ ተቀናቃኝ እና የወያኔ ስጋት ስለሆንኩ ነው ሽብርተኛ የተባልኩት፣ ወያኔ በእኔ መኖር ተርበርብዷል፣ እንቅልፍ አጥቷል ስለዚህ የአርበኝነት ቦድ (እንደ አባይ ቦንድ መሆኑ ነው) እየገዛችሁ ብትደግፉኝ ወያኔን በስድስት ወር ጉሮሮውን አንቄ አወርዳለሁ እያለ የአመታት እድሜን ለማግኘት ችሏል። በእንዲህ ያለው የፖለቲካ ቁማር የሚከስረውም ሆነ ተጎጂው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነውና ወያኔም ሆኑ ግንቦት 7ዎችን ‘ሃይ’ ሊላቸው ይገባል።
ማጠቃለያ
የአቶ ተክለሚካሄልን ሙግት ሳይውል ሳያድር ነጥብ በነጥብ ለመመልስ ብዮ ጽሑፌን አንዛዝቼዋለሁና በትእግስት ላነበባችሁት ሁሉ ምስጋናዬ ይድረስ። በግፈኞች እጅ ተይዘውና በስውር ታስረው ለሚማቅቁ ወገኖቻችን ድምጻችንን ለማሰማት ሰዋዊ ብቻ ሳይሆን ወገናዊ ኃላፊነትም አለብን። የግፍን ተግባር ለመቃወም የፈጻሚዎቹ ማንነትም ሆነ የተፈጸመባቸው ሰዎች ምንነት መደራደሪያ ሊሆን አይችልም። የግፍና የጭካኔ ተግባር በማንም የፈጸማ በማን፣ በየትም ስፍራ የፈጸም ያው ግፍ ነው። ወያኔ ስፈጽመው ወንጀልና ግፍ፤ ሻቢያና ግንቦት 7 ሲፈጽሙት ሕጋዊ ወይም ቅዱስ ተግባር የሆነ የመብት እረገጣ የለም። ሁሉም ግፈኞች ነው የሚሆኑት የሚሆኑት።

ግፈኞችን በማውገዝ ለግፉዋን መብት መከበር በጋራ እንቁም!

በቸር እንሰንብት።

http://humanrightsinethiopia.wordpress.com/

አቡጊዳ –ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በባህር ዳር ከተማ –የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም

$
0
0

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ፣ በባህር ዳር ከተማ የካቲት 16 ቀን ፣ ከመኢአድ ጋር በመሆን በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ፣ የባህር ዳር እና የአካባቢዉ ሕዝብ፣ በነቂስ እንዲወጣ፣ ከፍተኛ የቅስቀሳ ዘመቻ እንደተጀመረ የሚገልጹ ዘገባዎች እየደረሱን ነዉ።

bahir_dar

«አንድነታችን ከልዩነቻትን በላይ ነው» ፣ «የአማራዉን ሕዝብ ያዋረዱ የብአዴን/ኢሕአዴግ ባለስልጣናት ለፍርድ ይቅረቡ» «ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በባህር ዳር ከተማ የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም፣ ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ» የሚሉ አባባሎችን የያዙ ፣ በኮከብ የለሽ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ ያሸበረቁ፣ ፖስተሮች ተዘግጅተዉ እየተበተኑ ሲሆን፣ በሶሻል ሜዲያዎችም ዘመቻው የተጧጧፈ ይመስላል።

የባህር ዳር ከተማ፣ ከአዲስ አበባ ቀጥላ አለች የምትባል፣ ትልቅ ከተማ እንደመሆኗ፣ በዚያም ደግሞ የሚገኘዉ የብአዴን ኢአሕዴግ አፈናና ጫና በጣም ከባድ በመሆኑ፣ የስለፍ አስተባባሪዎች ትልቅ መስዋእትነት እየከፈሉ በቆራጥነትና በድፍረት ሥራ እየሰሩ እንደሆነ የሚናገሩት ያነጋገርናቸው አንድ የፓርቲው አመርር አባል፣ በተቀረዉ የኢትዮጵያ ግዛት፣ እንዲሁም በዉጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮዮጵያዊያን፣ ከባህር ዳር ሕዝብ ጎን እንዲሰለፉ ጥሪ አቀርበዋል።

በአካል እንኳ መገኘት ባይቻልም፣ በጸሎት፣ በምክር፣ በሶሻል ሜዲያ በሚደረጉ ቅስቀሳዎች፣ እንዲሁም በገንዘብ መደገፍ እንደሚያስፈልግ የገለጹት የአመራር አባሉ፣ «ይህ አይነቱ እንቅስቅቅሴ ዉጤት ሊያመጣ የሚችለዉ ሁሉም ሳይፈራና ሳይሸማቀቅ፣ የድርሻዉን ሲያበረክት ብቻ ነዉ» ሲሉ ጠንከር ያለ አስተያየት ሰጠዋል።

አቡጊዳ –የአንድነት ፖርቲ ሕዝብን የናቁ መሪ፣ ለፍርድ እንዲቀርቡ የሚጠየቅ ፔትሽን አዘጋጀ

Viewing all 1809 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>