Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all 1809 articles
Browse latest View live

የኦህደድ እና ኦነግ ፖለቲካ «ኦሮሞዉን» ጎድቷል –አማኑኤል ዘሰላም

$
0
0

የኢትዮጵያ ፈዴራል ሕገ መንግስት አንቀጽ 46 «ክልሎች የሚዋቀሩት በሕዝብ አሰፋፈር፣ ቋንቋ፣ የማንነት እና ፈቃድ ላይ በመመስረት ነዉ» ይላል። አንቀጽ 47 ደግሞ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሩፑብሊክ አባላት የሆኑቱን ክልሎች ይዘረዝራቸዋል። እነርሱም የትግራይ፣ የአፋር ፣ የአማራ፣ የሱማሌ፣ የቤኔሻንጉል/ጉሙዝ፣ የደቡብ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ፣ የጋምቤላ ሕዝቦች እና የሃረሪ ሕዝብ ክልሎች ናቸው።

የዚህን የፌደራል ክልልን በተመለከተ በክልሎች እየታዩ ያሉትን አንዳንድ ሁኔታዎች ለማሳየት እንሞክራለን። ከትልቁ ክልል ኦሮሚያ እንጀምር።

ኦሮምኛ የማይናገሩትን የማግለል ዘረኛ አሰራር

ኦሮሚያ ክልል ዉስጥ ሃያ ዞኖች አሉ። ሶስቱ «ልዩ ዞኖች» ይባላሉ። ናዝሬት/አዳማን ያካተተ፣ የአዳም ልዩ ዞን፣ ጂማን ያካተተው፣ የጂማ ልዩ ዞን እና የቡራዮ ልዩ ዞን ናቸው። በነዚህ ዞኖች የመጀመሪያ ቋንቋቸው አፋን ኦሮሞ የሆኑቱ ቁጥራቸው ከ45 በመቶ በታች ነዉ። በአዳማ 26%፣ በጂማ 39% እና በቡራዮ 44% ናቸው።

በአሥራ ሶስቱ ሌሎች የኦሮሚያ ዞኖች አፋን ኦሮሞ የመጀመሪያ ቋንቋቸው የሆኑ ከ90 % በታች ናቸው። እነዚህም ምስራቅ ሸዋ ( 69%)፣ ጉጂ (77%) ፣ አርሲ ( 81%)፣ ሰሜን ሸዋ ( 82%)፣ ደቡብ ምስራቅ ሸዋ (84%)፣ ሆሮ ጉድሩ ወለጋ (85%) ፣ ምእራብ አርሲ (87%)፣ ምስራቅ ወለጋ ( 88%) ፣ ምእራብ ሃረርጌ (89 %)፣ ኢሊባቡር (90%) ፣ ጂማ – የጅማ ከተማ አካባቢ ( 90%)፣ ባሌ (90%)፣ ቦረና (90%) ናቸው። እንግዲህ ከሃያ የኦሮሚያ ዞኖች፣ በአሥራ ስድስቱ፣ ምን ያህል አፋን ኦሮሞ የመጀመሪያ ቋንቋቸው ያልሆኑ ኢትዮጵያዉያን በስፋት እንዳሉ እያየን ነዉ። በአራት የኦሮሚያ ዞኖች፣ በአፋን ኦሮሞ አፋቸዉን የፈቱ፣ ከዘጣና ሶስት በመቶ በላይ ናቸው። እነርሱም ምእራብ ወለጋ (97%) ፣ ምእራብ ሸዋ (93%)፣ ምስራቅ ሃረርጌ፣ (94%)፣ ቀለም ወለጋ ( 94%) ናቸው።

አሁን በሥራ ላይ እየተተገበረ ያለው የኦሮሚያ ክልል ሕገ መንግስት አንቀጽ 33 «በክልሉ ዉስጥ ነዋሪ የሆኑና የክልሉን የሥራ ቋንቋ የሚያውቅ ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ በማንኛዉም የክልሉ መንግስታዊ ወይም ሕዝባዊ ሥራ ተመርጦ ወይም ተቀጥሮ የመስራት መብት አለዉ።» ይላል። አንቀጽ 5 ደግሞ « ኦሮምኛ የክልሉ መንግስት የሥራ ቋንቋ ይሆናል። የሚጻፈዉም በላቲን ፊደል ነው» ይላል።

74% የአዳማ፣ 61% የጂማ ከተማ ፣ 56% የቡራዩ ዞን፣ 31% የምስራቅ ሸዋ ዞን፣ 23% የጉጂ ዞን ፣ 25% የሆሮ ጉድሮ ወለጋ ዞን፣ 23% የምእራብ አርሲ ዞን … ነዋሪዎች የመጀመሪያ ቋንቋቸው አፋን ኦሮሞ ባላመሆኑ፣ አፋን ኦሮሞ ካልተማሩ በቀር፣ የመመረጥ፣ በኦሮሚያ ክልል የመስራት መብት የላቸውም። ይህም አማርኛና ሌሎች ቋንቋዎች የሚናገሩ፣ በኦሮምያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንን እንደ ሁለተኛና ሶስተኛ ዜጋ እንዲቆጠሩ የሚያደርግ ነዉ። በብሄረሰብ መብት ስም የግልሰበ መብት እየተረገጠ ነዉ።

«ኦሮሚያ ፈርስት» የሚል እንቅስቃሴን የሚመራው ጃዋር ሞሃመድ፣ አንድ ወቅት «Ethiopians Out from Oromia» የሚል መፈክር ያሰማበትን ቪዲዮ ተመልክቻለሁ። ጃዋር በአጭሩ አነጋገር፣ ኦሮሚያ የኦሮሞዎች ብቻ እንደሆነችና ሌሎች «ኦሮሞ» ያልሆኑ፣ በኦሮሚያ ዉስጥ እንግዶች፣ ኦሮሞዎች ሲፈቅዱላቸው ብቻ ሊኖሩ የሚችሉ እንደሆኑ ነው የነገረን። ይህ የጃዋር አባባል፣ ብዙዎችን እንዳስገረመ ተመልክቻለሁ። ነገር ግን አንድ የዘነጋነው ነገር ቢኖር፣ ይህ የጃዋር አባባል ፣ ጃዋር የፈጠረዉ ሳይሆን በኦሮሚያ በአሁኑ ሕግ መንግስት፣ በሰነድ የተቀመጠ እንደሆነ ነዉ።ይህ አይነቱን ዘረኛ የጃዋር አባባል፣ የኦሮሚያ ክልል «ሕግ» ይደግፈዋል። ስለዚህ ትኩረታችንን ከጃዋር አዙረን ወደ ኦሕደድ/ኢሕአዴግ እንዲሁም ኦነግ ማዞር አለብን።

የኦሮሚያ ክልል ሕገ መንግስት አንቀጽ ስምንት «የኦሮሞ ሕዝብ የክልሉ የበላይ ስልጣን ባለቤት ሲሆን ..» ሲል የኦሮሚያ ባለቤት «ኦሮሞው» ብቻ እንደሆነ ነው ያስቀመጠው።

ኦሮምኛ ተናጋሪው በኢኮኖሚ እንዲጎዳ ያደረገ ጎጂ ፖለቲካ

የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ፖሊሲን ካየን ደግሞ፣ አዲስ አበባ አካባቢ ያሉ እንደ አዳማ/ናዝሬት ያሉ ቦታዎች ሕዝቡ ተቃዉሞ ስላስነሳ፣ በዚያ ተማሪዎች አማርኛም ከአፋን አፋን ኦሮሞ ጎን ለጎን እንዲማሩ ከመደረጉ በስተቀር፣ በኦሮሚያ የሚኖሩ ተማሪዎች አማርኛ እንዲማሩ አይደረግም። አማርኛ ማንበብና መጻፍ አይችሉም።

አንድ የግል ባለሃብት ከአዲስ አበባ ሄዶ አንድ ኩባንያ በአንድ የኦሮሚያ ከተማ ይመሰርታል። ሰራተኞች ቀጥሮ ያሰራል። ሰራተኞቹ ስራቸዉን በተመለከተ፣ ሪፖርት ማቅርብ ሲጠበቅባቸው ሪፖርት ሳያቀርቡ ይቀራሉ። አለቃቸው ያስጠራቸዉና ይጠይቃቸዋል። ሪፖርታቸውን በቃል ያቀርቡለታል። «እሺ በፋይል እንዲቀመጥ በጽሁፍ አምጡልኝ» ሲላቸው፣ ማንገራገር ጀመሩ። «ጌታዬ እኛ አማርኛ መጻፍ አንችልም። በቁቤ እንጻፈዉና ከፈለጉ ያስተርጉሙት፤ ወይም እኛ አስተርጉመን እንመጣለን» ይሉታል። ሰዎዬዉ ባንድ በኩል ቢናደድም፣ በሌላ በኩል አዘነ። ቢዝነስ ነዉና፣ ለስራው ብቃት ከሌላቸው ሰራተኞቹ ማባረር ግድ ሆነበት።

አማርኛን የመጥላት የኦህደድ እና ኦነግ ፖለቲካ ፣ ዜጎች አፋን ኦሮሞን ያዉም በቁቤ ብቻ እንዲማሩ በማድረግ፣ ትልቅ የኢኮኖሚ ጉዳት በ«ኦሮሞዎች» ላይ አድርሷል። እዚህ ላይ «ብቻ» የሚለውን ቃል እናስምርበት። በትግራይ ከአንደኛ ክፍል ጀመሮ ከትግሪኛ ጎን አማርኛ እንዲማሩ ይደረጋል። የኦሕደድ ባለስልጣናት እነ አባ ዱላ ገመዳ፣ ኩማ ደመቅሳ የመሳሰሉት ልጆቻቸዉን የሚያስተምሩት በአዲስ አበባ ሃሪፍ ትምህርት ቤቶች ነዉ። ሃብታም የሆኑና አቅሙ ያላቸው ልጆቻቸውን ወደ አዲስ አበባ እየላኩ ያስተምራሉ። ለምን ቁቤ ብቻ ተምረው ልጆቻቸው የትም እንደማይደርሱ ስለሚያወቁ።

የግል ኢንቨስተሮች የሥራ ቋንቋቸው በኦሮሚያም ሳይቀር በብዛት አማርኛ ነዉ። በናዝሬት፣ በጂማ በመሳሰሉት ቦታዎች ሂዱ፣ የንግድ ተቋማት፣ የግል መስሪያ ቤቶች .. የሚጠቀሙት አማርኛን ነዉ። ከክልል መንግስት ጋር አንዳንድ ደብዳቤዎች መላላክ ካስፈለገ ፣ የክልሉን የአፋን ኦሮሞ ብቻ ፖሊስ ሕግን ለማክበር ፣ ተርጓሚ ይቀጥራሉ።
በኢትዮጵያ ካሉ 9 ክልሎች በአራቱ (አማራዉ፣ ደቡብ፣ ጋምቤላና ቤኔሻንጉል ጉሙዝ) ክልሎች፣ እንዲሁም በአገሪቷ መዲና አዲስ አበባ፣ በድሬደዋ የሥራ ቋንቋ አማርኛ ነው። የፌደራልም ቋንቋ አማርኛ ነዉ።

በመሆኑም ኦሮሚያ ያለው የቁቤ ትዉልድ፣ በፌደራል መንግስት ዉስጥ ተቀጥሮ የመስራት አቅሙ ዜሮ ነዉ። እንደ ባህር ዳር፣ አዋሳ፣ ድሬደዋ፣ አዲስ አበባ በመሳሰሉ ታላላቅ ከተሞች ለመኖርና ለመስራት፣ ለመቀጠር በጣም ይቸገራል። በአጭሩ፣ ይህ የኦሮሚያ ክልል አሰራር፣ የኦሮሚያ ተማሪዎች፣ በኢኮኖሚ እንያድጉና እንዳይሻሻሉ ትልቅ ማነቆ ነው እየሆነባቸው ያለዉ። በሌሎቹ ክልል ካሉ ጋር ሲወዳደሩ ወደኋላ ቀርተዋል። ከላይ ለመጥቀስ እንደሞከርኩት የኦነግ መሪዎች ልጆቻቸው በበርሊን፣ ሚኒሶታ …በመሳሰሉ ቦታዎች እያስተማሩ ነዉ። አማርኛም ባያወቁ፣ እንግሊዘኛ እስካወቁ ድረስ ችግር አያጋጥማቸዉም። የኦህደድ መሪዎች ልጆቻቸውን ሃሪፍ ትምህርት ቤቶች ነዉ በአዲስ አበባ የሚያተምሩት። ድሃዉና ምስኪኑ የኦርሚያ ተማሪ ግን፣ አጥር ታጥሮበት፣ በአጉል የኦሮሞ ብሄረተኘንት ስም እንዲተበተብ ተደርጎ ጉዳት እየደረሰበት ነዉ።

ይህ በኦሮሚያ የሚኖሩት ወገናችን በኢኮኖሚ፣ በትምህርት ፖሊሲ ረገድ እየደረሰባቸው ካለው ግፍ በተጨማሪም፣ ኦነግ እየተባሉ በሺሆች የሚቆጠሩ እየታሰሩና እየተሰቃዩ ናቸው። ሕወሃት/ኢሃዴግ በአንድ በኩል እነሌንጮን፣ ቀንደኛ ኦነጎችን፣ እያባበለና እያቀፈ፣ በሌላ በኩል የነሌንጮ ደጋፊ ናችሁ እያለ ሰላማዊ ዜጎችን ያስራል።

ታዲያ መፍትሄዊ ምንድን ነዉ ? አራት ነጥቦች ላስቀምጥ፡

1. ኢትዮጵያዉያን አፋቸዉን በየትኛው ቋንቋ ነዉ የፈቱት የሚለዉን ጥያቄ ብንጠይቅ ፣ በአንደኝነት የሚቀመጠዉ ኦሮምኛ ነዉ። በበርካታ ዞኖች ከዘጠና በመቶ በላይ ኦሮምኛ የሚነገርባቸው ቦታዎች አሉ። 33.8 % የሚሆነው ሕዝባችን አንደኛ ቋንቋዉ አፋን ኦሮሞ ነዉ። 29.36% የሚሆነው ህዝብ አማርኛ አንደኛ ቋንቋዉ እንደመሆኑ፣ አማርኛን ወይንም ኦሮምኛን እንደ አንደኛ ቋንቋ የሚናገሩ 63.2% ይደርሳሉ። በመሆኑም ኦሮሞኛ ከአማርኛ ጎን የፌደራል ቋንቋ ቢሆን ትልቅ ጥቅም ይኖረዋል። ቢያንስ አማርኛ ፊደል የማያነበው፣ የጠፋው አንዱ የቁቤ ትዉልድ በፌደራል መሥሪያ ቤቶች የመስራት እድል ያጋጥመዋል።

2. በሁሉም ክልሎችና ወረዳዎች፣ በአካባቢዉ ከሚነገረው ቋንቋ ጎን ለጎን፣ ተማሪዎች አማርኛ እንዲማሩ መደረግ አለበት። አማርኛ እንደ አንደኛ ቋንቋ 29.3% የሚሆነው ሕዝብ ይናገረዋል። እንደ ሁለተኛ ቋንቋ ደግሞ፣ ከ30፣ 40 በመቶ በላይ የሚሆነው ሕዝብ ሊናገረው ይችላል ብዬ አስባለሁ።በመሆኑም አማርኛ ማወቅ ጥቅም አለው። ቋንቋ በአጠቃላይ ይጠቅማል እንጂ አይጎዳም። አማርኛን መማር ኦሮሞኛን አይጎዳም። የኦሮሞ መሪ ነን የሚሉ ፖለቲከኞች፣ ለራሳቸው ልጆች እንዳሰቡት፣ ለተቀረዉም የኦሮሞ ልጅ ሊያስቡ ይገባል ባይ ነኝ።

እነርሱ አቀላጥፈው አማርኛ መናገር፣ ማንበብ መጻፍ እንደሚችሉትም ሌላዉን እነርሱ ታገኙትን እድል ማሳጣት የለባቸውም። እስቲ አስቡት አሁን አባ ዱላ አማርኛ መጻፍና ማንበብ ባይችል ኖሮ የፓርላማ አፈጉባኤ ይሆን ነበር ? ዶር ነጋሶ ፕሬዘዳነት መሆን ይችሉ ነበር ? እያልን ያለነዉ እኮ የኦሮሞ ወጣት፣ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ፣ አቶ ኩማ ደመቅሳ፣ ዶር ዲማ ነግዎ፣ ጀነራል ከማል ገልቹ ፣ ዶር መራራ ጉዲና ያገኙት እድል ያግኙ ነዉ። አፋን ኦሮሞም ይማሩ፤ አማርኛም ይማሩ።

3. የኦሮሚያ ክልል መንግስት አማርኛን ከኦሮሞኛ ጎን የሥራ ቋንቋ ማድረግ አለበት። ኦሮሞኛ የማይናገር በክልሉ አስተዳደር ዉስጥ የመስራት መብቱ ሊጠበቅለት ይገባል። በኦሮሚያ 95% ነዋሪዉ ኦሮሞኛ የሚናገር ቢሆን፣ እሺ አንድ ነገር ነዉ። ግን ከ 15% በመቶ በላይ ሕዝብ አንደኛ ቋንቋም ኦሮሞኛ ባልሆነበት፣ «አፋን ኦሮሞ ብቻ ወይንም ሞት» ማለት ትልቅ ስህተት ነዉ። ዘረኝነትም ነዉ። በክልሉ ዋና ከተማ አዳማ/ናዝሬት እንኳን ፣ አንድ አራተኛ ሕዝብ ብቻ ነው ኦሮሞኛ የሚናገረው።

4. ናዝሬት/አዳም እና ጂማ የመሳሰሉ እንደ አዲስ አበባና ድሬደዋ፣ ለጊዜዉ ቻርተር ከተማ ቢሆኑ መልካም ነዉ። (ለዘለኬታዉ፣ ለሁሉም በሚበጅ፣ የተለያዩ ሁኔታዎችን ከግምት ባስገባና በተጠና መልኩ ፣ፌደራል አወቃቀሩ እንደገና በአዲስ የሚዋቀርበትን ሁኔታ በመፈለግ ለብዙ ችግሮች መፍቴሄ ማግኘት ይቻላል)

ከላይ የዘረዘርኳቸዉ አሃዞች በኦፊሴል ከተመዘገበዉ የኢትይጵፕያ ሕዝብ ቆጠራ ሪፖርት ነዉ። በሚቀጥለው ጊዜ የቤኔሻንጉል ጉምዝ እና ሃረሪ ክልሎችን እንመለከታለን።


ኢ.ኤም.ኤፍ –የግንቦት 7 የግፍ ተግባር እና የመገናኛ ብዙሃን ዝምታ – ያሬድ ኃይለማርያም

አቡጊዳ –አመራር አባልና የቀድሞ ዋና ጸሃፊ አቶ አስራት ጣሤ ታሰሩ

$
0
0

የአንድነት ፓርቲ ለበርካታ አመታት በዋና ጸሃፊነት ያገለገሉት አቶ አስራት ጣሴ መታሰራቸዉን የአንድነት ፓርቲ ሚሊየም ድምጽ፡ለነጻነት ፌስቡ ገጽ ዘገበ።

«የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ አስራት ጣሴ፣ በክስ ሂደት ላይ የነበረው የአኬልዳማ ዶክመንተሪ በድጋሚ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን መታየቱን ተከትሎ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ ከፃፉት አስተያየት ጋር በተያያዘ “ዘለፋ አዘል ጽሑፍ” ጽፈዋል በሚል ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲያስረዱ ትዕዛዝ በተላለፈባቸው መሰረት በዛሬው እለት በፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የተገኙ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ለ7 ቀን ታስረው በቀጣዩ ሳምንት እንዲቀርቡ በማለት የእስር ትዕዛዝ ወስኖባቸዋል » በሚል ነበር ዘገባው የቀረበዉ።

በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶ ነጻነት እንደሌላዉ የሚታእቅ ሲሆን፣ በአቶ አሥራት ጣሴ ላይም ሆነ በሌሎች የተቃዋሚ አመራር አባላት ላይ እየታዩ ያሉ ጥቃቶች፣ፍርድ ቤት ወለድ ሳይሆኑ፣ ሆን ተብሎ አንድነትን ለማዳከም ከኢሕአዴግ ጽ/ቤት በመጣ መመሪያ መሰረት መሆኑን ብዙዎች ይናገራሉ።

በሦስት የመንግስት ተቋማት ላይ አንድነት ፓርቲ ክስ መሰረተ –በአሸናፊ ደምሴ

$
0
0

ሕገ-መንግሥቱ የሚፈቅድልኝን ሰላማዊ ሰልፍ እንዳላካሂድ ከልክለውኛል፤ አባላቶቼን ያለአግባብ በማንገላታት አስረውብኛል፤ ቅስቀሳ እንዳላካሂድ አግደውኛልና ድምፅ ማጉያዎቼን ቀምተውኛል ሲል አንድነት ለዴሞክራሲ ለፍትህና ፓርቲ (አንድነት) በሶስት የመንግስት ተቋማት ላይ ክስ መሰረተ። ፓርቲው በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ፍትሃ ብሔር ችሎት ላይ ክስ የመሰረተባቸው ተቋማት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መሆናቸውን በክስ መዝገቡ ተገልጿል።

ፓርቲው የዘወትር ፖለቲካዊ ስራዎቹን እንዳላያካሂድ መስተጓጉል ተፈጥሮብኛል በማለቱ ክሱ መዘጋጀቱን ለሰንደቅ ያስረዱት የሕግ ባለሙያው አቶ ተማም አባቡልጉ፤ በክስ ዝርዝሩ ውስጥ ፓርቲው በመስቀል አደባባይ የጠራው ሰልፍ እንዳይካሄድ ከመደረጉም በተጨማሪ የቅስቀሳ እገዳ፣ የአባላት መታሰርና የቁሳቁስ መነጠቅ ሁሉ ስለማጋጠሙ በክሱ ውስጥ በዝርዝር ተካቷል ብለዋል።

በከተማዋ ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ከፈቃድ ሰጪ አካላት ፈቃድ መገኘት አለበት ቢባል እንኳን ተቋማት የተከተሉት አካሄድ አግባብነት የሌለውና ከሕግም ውጪ በመሆኑ ይህን ለመጠየቅ ክስ መስርተናል ብለዋል። የመንግሥት አካላቱን የሰልፍ እገዳ ተከትሎ አንድነት ፓርቲ ዘጠኝ የሚደርሱ አማራጭ የሰልፍ ቦታዎች ቢያቀርብም አንዱንም ሳይቀበሉ በራሳቸው ምርጫ ጃንሜዳ ላይ ሰልፍ እንዲካሄድ መፍቀዳቸው በሕጉ ላይ ከሰፈረውና ማንኛውም ዓይነት ሰላማዊ ሰልፍ ከጦር ካምፕ በ50 ሜትር ርቀት ላይ መካሄድ አለበት ከሚለው መመሪያ ጋር የማይጣጣም ነው ብለዋል።

ይህም በመሆኑ አንድነት ፓርቲ የመንግስት ተቋማት በጣምራ በመሆን ሕዝብን ለመቀስቀስ የሚደረገውን ጥረት ስልታዊ በሆነ መንገድ አስተጓጉለውብኛል ይላል።

በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የተመሰረተባቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የተመሰረተባቸውን ክስ አስመልክተው በችሎት በመገኘት የሚሰጡትን መልስ ለማድመጥ ለየካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

አቶ በቀለ ገርባ የእሥር ጊዜያቸውን ቢጨርሱም ሊፈቱ አልቻሉም

$
0
0

በእስር ላይ የሚገኙት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ም/ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ የእስር ጊዜያቸውን ቢጨርሱም ኣመክሮ መከልከላቸው ተሰማ። ህክምናም እያገኙ ኣይደለም ተብሏል። የኮንግረሱ ዋ/ጸኃፊ ለዶቸቬሌ እንደ ነገሩት ከሆነ አቶ በቀለ ገርባ የ 3 ዓመት ከ 7 ወር የእስር ጊዜያቸውን ኣጠናቀው መለቀቅ የነበረባቸው ባለፈው ጥር 11 ቀን ነበር::

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሺን በበኩሉ የዚህ ኣይነት ቅሬታ እስከኣሁን እንዳልደረሰው ኣስታውቋል።
ቀድሞ በዶ/ር መረራ ጉዲና ይመራ የነበረው የኦሮሞ ህዝብ ኮንግረስ (ኦህኮ) እና ያኔ በአቶ ቡልቻ ደመቅሳ ይመራ የነበረው የኦሮሞ ፌደራሊስት ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፈዲን) ተዋህደው የፈጠሩት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር ነበሩ፤ አቶ በቀለ ገርባ። በያዙት ኃላፊነትም ያለ ኣግባብ የታሰሩ ኦሮሞዎችን ጉዳይ እየተከታተሉ ለዓለም ዓቀፍ የመብት ተሟጋቾች እና ለሚመለከታቸው ሁሉ ያሳውቁም ነበር። ይኸው ተግባራቸው ያላስደሰተው የኢትዮጵያ መንግስት ታዲያ የኮንግረሱ ዋ/ጸኃፊ አቶ በቀለ ነጋ እንደሚሉት ኣሸባሪ በሚለው ድርጅት ስም ወንጅሎ ኣስፈረደባቸው። የተፈረደባቸው ስምንት ዓመት ሲሆን በይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት ወደ 3 ዓመት ከ 7 ወር ተሻሽሎላቸው ነበር ዝዋይ እስር ቤት የከረሙት።

አቶ በቀለ ገርባ ከዝዋይ እስር ቤት ጀምሮ ኣሁን በሚገኙበት የቃሊቲ ወ/ቤትም ታመው ህክምና እንዳላገኙም ነው እየተነገረ ያለው። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሺን ሊቀመንበር የሆኑት አምባሳደር ጥሩነህ ዜና ግን የዚህ ኣይነት አቤቶታ እስከ ኣሁን ኣልደረሰንም ባይ ናቸው።
ከኢትዮጵያ መንግስት ወከባና እስራት ሸሽተን በጎረቤት ኣገር እንገኛለን ከሚሉት የኦሮሞ ተወላጆች መካከል ኣንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ ስደተኛ በበኩላቸው ከአቶ በቀለ ገርባ በባሰ ሁኔታ ህክምና ተነፍገው የሞቱ የኦሮሞ እስረኞችም ኣሉ ሲሉ ኣንዳንዶቹን ጠቃቅሷል። ከዚሁ በመነሳ የኢትዮጵያ እስር ቤቶች የስራ ቐንቐ ኦሮምኛ ሆኗል እስከማለትም ተደርሷል። የሰብዓዊ መብት ኮሚሺን ሊቀመንበሩ አምባሳደር ጥሩነህ ዜና ግን ሊደንቀን ኣይገባም ይላሉ።
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ም/ሊቀመንበሩ፤ አቶ በቀለ ገርባ፤ በተፈረደባቸው ዕለት የፍርድ ማቅለያ ኣስተያየት ይሰጡ ዘንድ እድል ቢሰጣቸውም «ሳላጠፋ የፈረደብኝን ፍ/ቤት ይቅርታ ኣልጠይቅም። ይቅርታ መጠየቅ ካለብኝ የሚጠበቅብኝን ያህል ካልሰራሁለት የኦሮሞን ህዝብ ነው ይቅርታ እምጠይቀው» ሲሉ ችሎቱ ፊት ቆመው መናገራቸው አይዘነጋም።
ጃፈር ዓሊ
ተክሌ የኋላ

አቡጊዳ –ኢሕአዴግ የአንድነት መሪዎች ለማሰር እየተዘጋጀ እንደሆነ ተዘገበ

$
0
0

የአንድነት ልሳ የሆነዉ ፍኖት ነጻነት፣ ሰበር ዜና ብሎ እንደዘገበዉ፣ ኢሕአዴግ አቶ ዳን ኤል ተፈራን ጨምሮ በርካታ የአመራር አባላትን ለማሰር እየትዘጋጀ እንደሆነ፣ በፍትህ ሚኒስቴር ያሉትን ምንጮች በመግለጽ ዘግቧል።

« አቶ ዳንኤል ተፈራን ጨምሮ አራት የአንድነት አመራሮችን ለማሰር መዘጋጀቱን የፍትህ ሚ/ር ምንጮች አጋለጡ፡፡ ምንጮቹ ለፍኖተ ነፃነት እንዳስታወቁት በኢህአዴግ ጽ/ቤት ትዕዛዝ ክስ እንዲከፈትባቸውና እንዲታሰሩ የተወሰኑት የአንድነት አባላት በርካታ ናቸው፡፡ ሆኖም የመጀመሪያው ዙር ክስና እስር በ4 አመራሮችና አባላት ላይ ያነጣጠረ ነው፡፡» ሲል የዘገበው ፍኖት፣ የክስ ቅድመሁኔታዎች በፍርድ ቤት መጠናቀቃቸውን ገልጿል።

አንድነት መግለጫ – የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ የማድረግ ትግላችን ተጠናክሮ ይቀጥላል!!!

ለግንቦት 7ም ሆነ ለሌሎች ተቃዋሚዎች ያለመተቸትን ከለላ ማን ሰጠ? የእነ “…ወይም ሞት” ፖለቲካ ያሬድ ኃይለማሪያም

$
0
0

ከ1960ዎቹ የተማሪዎች ንቅናቄ ጀምሮ የአገራችንን ፖለቲካ የተጠናወተው የ“…. ወይም ሞት” አስተሳሰብ ከአስርት አመታት በኋላም አለቅ ብሎን ዛሬም እኔ ከምደግፈው ፓርቲ ወይም የፖለቲካ ቡድን ወይም አስተሳሰብ ውጭ ያለው መንገድ ወይም አማራጭ ሁሉ ገደልና ሞት ነው ብለው የሚያስቡ ፖለቲከኞችና ዓጃቢዎችን ቁጥር በብዙ እጥፍ አባዝቶ ቀጥሏል። በ‘ደርግ ወይም ሞት’ የጀመረው የኼው የተወላገደ እና ጸረ-ዲሞክራቲክ የሆነው አስተሳሰብ ሳንወጣ ዛሬም ‘ወያኔ ወይም ሞት’፣ ‘ግንቦት 7 ወይም ሞት’፣ ‘ኦነግ ወይም ሞት’፣ ‘… ወይም ሞት’ በሚሉ ካድሬዎችና ስሜታዊ የድርጅት አምላኪዎች ተተክቶ እያደናበረን ይገኛል። ለአንድ የፖለቲካ ማኀበረሰብ በዲሞክራሲያዊ ጎዳና ለማቅናትም ሆነ እራሱን ከፍ ወዳለ የሥልጣኔ ባህል ለማደግ ትልቁ መሣሪያ ነጻ አስተሳሰብ እና ግልጽ ውይይት ነው። ባጭሩ በነጻነት የማሰብ (freedom of thought)እና ያሰቡትን በነጻነት የመግለጽ (freedom of expression) በዚያ ማኅበረሰብ ውስጥ በአግባቡ ሲተረጎሙ ነው ያ ማኅበረሰብ ወደ ጤናማ የፖለቲካ ባህል የሚሸጋገረው። ይህ ማለት ግን አንድ ሰው ያሻውን የማሰብ ነጻነት ቢኖረውም ሃሳቡን በተለይም አገራዊና ሕዝባዊ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ አውጥቶ ከሌሎች ጋር ሲወያይ ሊያከብራቸው የሚገቡ የሥነ-ምግባር እና የሕግ ገደቦች አይኖሩም ማለት አይደለም። ለጋራ ጥቅም ተብለው ከተቀመጡት የሕግና የሞራል ወሰኖች መለስ ግን ፍጹም ስልጡን በሆነ መልኩ ሃሳብን ማፍለቅ እና መወያየት የጭዋነት መለኪያ ብቻ ሳይሆን ሊሚናገሩትም ነገር ኃላፊነት የመውሰድን ግዴታንም አብሮ የያዘ የእያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነት ስለሆነ ሰዎች ባደባባይ ወጥተው ያሰቡትን ከመናገራቸው በፊት በቅጡ እንዲያስቡ ያደርጋል። ያለመታደል ሆኖ ከሃገር መሪዎች አንስቶ የፖለቲካ ተሿሚዎች፣ ካድሬዎችና ደጋፊዎች ለዚህ አይነቱ ኃላፊተት ብዙም ሳይጨነቁ ባደባባይ ያሻቸውን ይናገራሉ፣ የዘላብዳሉ፣ ይሳደባሉ፤ የሚጠይቃቸውም የለም።

ብዙ ጊዜ በእንዲህ ያለው ማኅበረስብ ውስጥ ኅብረተሰቡን በማንቃት፤ እንዲሁም ፖለቲከኞችን በማረቅና ለሚናገሩትም ሆነ ለሚሰሩት ነገር ተጠያቂ በማድረግ የፖለቲካው ባቡር ሃዲዱን ስቶ ሕዝቡንም ይዞ ቁልቁል መቀመቅ እንዳይወርድ ትልቁን ድርሻ የሚጫወቱት ነጻ የመገናኛ ብዙሃን እና ገለልተኛና ደፋር የአደባባይ ምሁራን ናቸው። ነጻ ሚዲያ በሌለበት ወይም በተዳከመበት እና የከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና ምሁራን ነጻ ባልሆኑበትና በማይከበሩበት አገር ሁሉ ጨለምተኝነት፣ አክራሪነት፣ ጽንፈኝነት፣ ጎጠኝነት እና አንባገነናዊነት ይነግሳሉ። በእንዲህ አይነቱ ማኅበረሰብ ውስጥ በጠመኝጃ አፈሙዝ ሥልጣን የተቆናጠጠ የወያኔ አይነት አምባገን ብቻ ሳይሆኑ ሌሎች ትናንሽ አምባገነን ድርጅቶችና ግለሰቦችም እንደ አሸን ይፈላሉ። ምክንያቱም የሚፈሩት ሕዝብ የለማ። ትንሹ አምባገነን ትልቁን፤ ትልቁም ትንሹን ይፈራል እንጂ ሕዝብን አይፈሩም። የሰሉና የተደራጁ ነጻ የመገናኛ መድረኮችና ብቃት ያላቸውና ለሕሊናቸው ያደሩ ጋዜጠኞች ባሉበት አገር አንድ ግለሰብ በሕዝብና በአገር አናት ላይ ቆሞ ያሻውን መናገርና መዘባረቅ ይቅርና ገና የፖለቲካ ጎራውን ሲቀላቀል ከልጅነት እስከ አዋቂነት የሄደበትን ጉዞና የሕይወት ታሪኩን በማጥናት ያ ሰው በሕዝብና በአገር ጉዳይ እጁን የማስገባት ሞራላዊም ሆነ ፖለቲካዊ ብቃት ያለው መሆኑን ሕዝቡ እንዲመዝን ያደርጋሉ። ይህ የፖለቲከኞቻችንን ሥነ-ልቦናዊም መሰረትም ሆነ ምሁራዊ ብቃት እንድናውቅ ከማገዙም ባሻገር የተጠያቂነትንም ባህል ያጎለብታል።

በአንድ ወቅት በሕዝብና በአገር ጥቅም ላይ ጉዳት ያደረሰ፣ ወይም በመጥፎ ሥነ-ምግባር ውስጥ ያለፈ፣ ወይም ከቤተሰቡ አንስቶ በሚኖርበት አካባቢ በመልካም ተግባሩ የማይታወቅ ሰው በምንም መንገድ አገራዊ ኃላፊነት እንዳይጣልበት ያደርገዋል። እስኪ ዛሬ አገሪቷን ተቆጣጥረው የኢትዮጵያን ሕዝብ ደም እንባ እያስለቀሱ ካሉት የወያኔ ባለሥልጣናት እና በተቃዋሚ ጎራ ተሰልፈው ካሉት የፖለቲካ ተዋናዮች መካከል ስንቶችን በቅጡ እናውቃቸዋለን? በሁሉም ጎራ ስለተሰለፉት ፖለቲከኞቻችን ያለን መረጃ ምን ያህል ነው? እንዴነ እጅግ ውሱን ነው፤ ስም፣ የትምህርት ድረጃ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ፣ የአንዳንዱን እድሜና ጥቂት ነገሮች። የእያንዳንዳቸውን ጀርባ እናጥና ከተባለ ጉዱ ብዙ ነው። በቅርቡ እንኳን ከሟቹ መለስ ዜናዊ እኩል ወይም በተወሰነ ደረጃ ባላፉት ሃያ መታት ውስጥ በኢትዮጵያ ውስጥ የወያኔ አገዛዝ ሥርዓት ለፈጸማቸው አስከፊ የሰብአዊ መብቶች እረገጣዎች በሕግ ተጠያቂ ሊሆኑ የሚገባቸው እንደ እነ አቶ ስዮ አብረሃ (የጦር ሚኒስትር እና የሥርዓቱ ቁልፍ ሰው የነበሩ) አይነት ሰዎች ከወያኔ ጋር ስለጠጣሉ ብቻ በሕግ ይቅርና በፖለቲካ መድረክ እንኳን ያለመጠየቅ ከለላ ተሰጥቷቸውና ወቃሽ ሳያገኙ የዲሞክራሲ ኃይሉ አካል ተደርገው ትግሉን እንዲቀላቀሉ ተደርጓል።

ባጭሩ ያጎለበትነው የፖለቲካ ባህል ቁጥራቸው ቀላል ለማይባሉ እጃቸው በንጹሃን ደም ለጨቀየ፣ በርሃብና በድህነት በሚሰቃየው ሕዝባችን ውድቀት ሞስነው ለጠበደሉ፣ በግል ህይወታቸውም ሆነ በሙያቸው ላልተሳካላቸው አዳዲስ እና ነባር ፖለቲከኞች መደበቂያ ጫካ ሆኗል። በቅርቡ “የፍርሃት ባህልን እያነገሰ ያለው የኢትዮጵያ ፖለቲካ” (http://humanrightsinethiopia.wordpress.com/) በሚል ርዕስ ባቀረብኩት ጽሑፍ ላይ እንደገለጽኩትም የገዢዎቹንም ሆነ የነጻ አውጪዎቹን፤ በጥቅሉ የፖለቲካ መዘውሩ ዙሪያ ያሉ ግለሰቦችን ማንነትና ጀርባ በቅጥ ማወቅ አለመቻል አንዱ ኅብረተሰብን ለፍርሃትና ከፖለቲካ ተሳትፎ እንዲቆጠቡ የሚዳርግ ምክንያት ነው። እነዚህን መሰረታዊ ነገሮች ከግምት በማስገባት ከዋናው ርዕስ ጋር የተያያዙ አንዳንድ ነጥቦችን ላንሳ።

በዚህ ርዕስ እንድጽፍ ምክንያት የሆነኝ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ፤ የወያኔ ሳያንስ የነፃ አውጪዎቻችን (የግንቦት 7) የግፍ ተግባር እና የመገናኛ ብዙሃን ዝምታ” በሚል ርዕስ ከአንባቢዎች የተሰነዘሩ አስተያየቶች ናቸው። ሦስት አይነት ነቀፌታ አዘል አስተያየቶች ጽሑፌን አትመው ባወጡ ድኅረ-ገጾችና በማኅበረሰብ የመወያያ መድረኮች ላይ ተነበዋል። ለእያንዳንዱ አስተያየት ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ለኔም አመቺ ሆኖ ስላገኘሁት በሦስቱ ጎራ ላሉት አስተያየቶች ምላሽ ልስጥ። የመጀመሪያው አስተያየት ባነሳሁት ፍሬ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ሳይሆን ብስጭትና ንዴት በተቀላቀለበት ስሜት ዝልፊያና ‘ዋናው የአገር ጠላት ወያኔ እያለ እንዴት ግንቦት 7ን ትተቻለ’፣ ግንቦት 7ን የነቀፈ ሁሉ ‘ወያኔ’ ነው፣ ተቃዋሚዎችን መተቸት ‘ትግሉን’ ያዳክማል፣ ተቃዋሚዎች ከነሃጢያታቸው መደገፍ ብቻ ነው ያለባቸው፣ ገፋ ብሎም ወንጀልም ቢሰሩ እንኳን ሊጠየቁ አይገባም ወያኔን እስከታገሉልን ድረስ የሚሉ ሃሳቦች የታጨቁበት ነው። እውነት ለመናገር ከእንደነዚህ አይነት ግራ ከተጋቡ ሰዎች ጋር ለመወያየት ያስቸግራል። ስለፖለቲካም ያላቸው ግንዛቤ ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል። ከዚህ በፊት በሌሎች ጽሑፎቼም እንዳልኩት እነኚህ ሰዎች ገሚሱ በቅን ልቦና ለውጥን ብቻ ከመናፈቅ፣ ገሚሱም አዕምሯቸው በቂምና በበቀል ስሜት ተወጥሮ ፖለቲካውን መሳሪያ ያደረጉ፣ ገሚሶቹም ስለ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ባህል ያላቸው ግንዛቤ ውሱን ወይም የተዛባ በመሆኑ መፈክራቸው ሁሉ ‘ግንቦት 7 ወይም ሞት’፣ ‘ኢሳት ወይም ሞት’፣ ወዘተ የሚል ነው። እነዚህ ሰዎች አዕምሮዋቸውን ከፈት አድርገው በፃነት እንዲያስቡ እና ከካድሬነትና ጭፍን ድጋፍ ወደ ሰላና በእውቀት ላይ ወደተመሰረተ የፖለቲካ ደጋፊነት እራሳቸውን እንዲያሳድጉ እመክራለሁ።

ሁለተኛው አስተያየት ሰጪዎች “ከግንቦት 7 ወይም ሞት’ የወጡ ቢሆንም አሁንም በተነሳው ፍሬ ነገር ላይ ያተኮሩ ሳይሆኑ በጸሃፊው (በእኔ) ማንነትና በአስረጂነት በጽሁፌ ላይ ባጣቀስኩት ድኅረ-ገጽ ባለቤቶች ማንነት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ይህም አስተያየት ቢሆን ያው ‘ፍሬውን ትቶ ገለባውን’ የመውቀጥና ከአስተሳሰብ መዛነፍ የመነጨ ነው። ገሚሶቹ ድብቅ ተልዕኮ ከሌለህ ግንቦት 7ን በአደባባይ መተቸት አልነበረብህም፣ ችግሩ ተከስቶም ቢሆን ባደባባይ ሳይሆን ውስጥ ለውስጥ ነው ጉዳዩን መግለጽ ያለብህ የሚል ነው (ወያኔ እንዳይሰማ መሆኑ ነው)። ሌሎቹ ደግሞ ‘የወያኔ’ መልዕክተኛ ነህ በሚል ፈርጀውኛል። እኔን ብቻ ሳይሆን የመረጃው ምንጭ ተደርገው የተጠቀሱትንም አካላት ወያኔዎች ናቸው ብለው ደምድመዋል። ለነገሩ እንዲህ ያለው ፍረጃ በተሰነካከለው የፖለቲካ ባህላችን ውስጥ ትችቶችን ለማፈን፤ ለማስቆምና የሰላ ትችት የሚሰነዝሩ ሰዎችን ዝም ለማስባል እንደ ስልት ገዢው ወያኔም ሆነ አንዳንድ ተቃዋሚዎች የሚጠቀሙበት ስልት ስለሆነ አያስገርምም። በፖለቲካችንም ውስጥ ይህ አካሄድ የቆየ እድሜ አለው። ይሁንና እኔንም ዝም አያሰኘኝም፤ እውነታውንም የመሸፈንም ሆን የመቀየር አቅም የለውም። እውነት ደግሞ ጊዜን እየጠበቀች የምትፈካና ከተገለጠችበት የምትወጣበት አንዳች ተፈጥሯዊ ኃይል ያላት ስለሆነች እንዲህ ያሉ ፍረጃም ሆነ ማደናገሪያ ጭርሱኑ አያጠፏትም። ይልቅ እንደ ሰለጠነ ማኅበረሰብ ችግሩን መመርመረሃ ምፍትሄ መሻት ይበጃል፤ ለአገርም ለድርጅቶቹም ቢሆን።
ሦስተኛው አስተያየት ኃላፊነት ከሚሰማቸውና የጉዳዩን ክብደት በቅጡ ከተረዱ ወገኖች የተሰነዘረ ነው። ይህውም ጉዳዩ የሰብአዊ መብትን የሚለለከት ስለሆነ በተበዳዮቹ ላይ ደረሱ ለተባሉት ጥቃቶች በቂ ማስረጃ አለህ ወይ? የሚል ነው። በመጀመሪያ እንኳን ለፍትሕ፣ ለዲሞክራሲና ለነጻነት እንታገላለን ያሉትን የፖለቲካ ኃይሎች ይቅርና አለም በሰብአዊ መብቶች እረጋጭነት ያወቀወን አንባገነናዊ የወያኔ ሥርዓት ለመተቸትም ሆነ ለመንቀፍ የሁል ጊዜ መነሻዬ ማስረጃዎች ናቸው። እንደ አንድ የሰብአዊ መብት ተሟጋች መረጃና ማስረጃዎች ያላቸውን ልዩነትም ሆነ ጠቀሜታ ጠንቅቄ ስለማውቅ ያለመረጃም ሆን ያለ ማስረጃ ማንንም ባደባባይ ለመውቀስም ሆነ ለመተቸት አልደፍርም። በተነሳው ጉዳይ ላይም በቂ ብቻ ሳይሆን ከበቂ በላይም ማስረጃዎችን መዘርዘር ይቻላል።

ጽሑፌን ለመደምደም በመጀመሪያ ወደ እዚህ ውይይት ያመራንን ጽሑፍ በማተም የጋዜጠኝነትና የመረጃ መድረክነታችውን ባግባቡ ለተወጣችሁ ድኅረ-ገጾችና የመወያያ መድረኮች ምስጋናዬ የላቀ ነው። የኔን ጽሑፍ በማስተናገዳችሁ የተነሳ ‘ወያኔ’ ተብላቸሁ የተሰደባችሁም ለእውነት መቆም የሚያስከፍለውን ዋጋ ነው እና እየከፈላችው ያላችሁት ግፉበት። ጽሑፌን አሉ ለተባሉት ድኅረ-ገጾች ሁሉ ነው የላኩት፤ መልእክቱም የደረሳቸው መሆኑን ከራሳቸው በተላከ ኢሜል አረጋግጫለሁ ይሁንና በሥራ ብዛት ይሁን በሌላ ያላስተናገዳችሁንት ወደፊት እንደምታትሙት እየጠበኩኝ የፍረጃ ፖለቲካውን ፈርታችሁ ወይም እናንተም የ’… ወይም ሞት’ የፖለቲካ አዙሪት ውስጥ ገብታችሁ አቋም ለያዛችሁትም ሁሉ እግዚያብሄር ለእውነት የምትቆሙበትን ልቦና እና መንፈሳዊ ወኔ ይስጣቸሁ በሚል ልሰናበት።

እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል።
በቸር እንሰንብት።
www.humanrightsinethiopia.wordpress.com


የአንድነት መሪዎች መታሰርን አይፈሩም –ግርማ ካሳ

$
0
0

አዲሱ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸዉ ሽፈራዉ፣ ለገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ የሰላምና የእርቅ ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል። «ኢሕአዴግ እኛን እንደ ጠላት እና ሽብርተኛ ማየቱን ማቆም አለበት። እኛም ደግሞ ኢሕአዴግን እንደ አዉሬ ማየት ማቆም አለብን። ከጥላቻ ፖለቲካ በመዉጣት ችግሮቻችንን በሰላም መፍታት መማር አለብን» ሲሉ ነበር፣ ለአገር በሚጠቅሙ በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ ከኢሕአዴግ ጋር ለመስራት፣ ያሉትን ልዩነቶችን በዉይይት ለመፍታት አንድነት ፍላጎት እንዳለው የገለጹት።

ይህ የአንድነት ዘመናዊ፣ የሰለጠነ፣ የፍቅርና የመግባባት ፖለቲካ፣ በኢህአዴግ ዉስጥ ያሉ ሞደሬቶችን ሳይቀር፣ አብዛኛዉን ኢትዮጵያዊ ያስደሰተ ቢሆንም፣ ስልጣኑን በያዙ በኢሕአዴግ አክራሪዎች ዘንድ ግን የተገኘዉ የአጸፋ ምላሽ የሚያስደስት አይደለም። ገዥዊ ፓርቲ ኢሕአዴግ ፣ አሁንም የአንድነት ፓርቲን እንደ ጠላት በማየት ፣ አንድነትን ለማዳከም አሳዛኝና አሳፋሪ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ነዉ። ወደ መሃል መጥተዉ፣ ለዉይይት ይዘጋጃሉ ብለን ስንጠብቅ፣ ጭራሹኑ እያከረሩ ነዉ። የታሰሩ የሕሊና እስረኞቹን ይፈታሉ ብለን ስንጠብቅ፣ ጭራሽ የጊዜ ገደባቸው የጨረሱ እንደ አቶ በቀለ ገርባ ያሉ እስረኞችን አንፈታም እያሉ ነዉ። ጭራሽ ሌሎች ሰላማዊ የፖለቲካ ታጋዮችን በተለይም ከአንድነት ፓርቲ እያሰሩና ለማሰርም እየተዘጋጁ ነዉ።

ለረዥም ጊዜ የአንድነት ፓርቲ ዋና ጸሃፊ ሆነው ያገለገሉትና፣ አሁን ደግሞ የብሄራዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት፣ አቶ አስራት ጣሴ በአሁኑ ጊዜ ታስረዋል። የታሰሩት በአንድ ጋዜጣ ላይ፣ «በፍርድ ቤቶች ፍርድ ማግኘት አይቻልም» በማለታቸው ነዉ። እዉነትን በመናገራቸው።

የአንድነት ልሳን ፍኖት ጋዜጣም፣ በፍትህ ሚኒስቴር ዉስጥ ያሉትን ምንጮች በመጥቀስ፣ በኢሕአዴግ ጽ/ቤት ትእዛዝ፣ አቶ ዳንኤል ተፈራ እንዲሁም ሌሎች የአንድነት አመራር አባላትን ለማሰር የክስ ሰነድ እንደተዘጋጀም ዘግቧል።

ይህ የአንድነት አመራር አባላትን ለማሰርና ለማዋከብ የሚደረገዉ ጥረት፣ ምክንያቱ አንድና አንድ ነዉ። ኢሕአዴግ፣ የአንድነት ፓርቲ አሰላለፍ በጣም ስላሰጋዉ፣ መሪዎችን በማሰርና የፓርቲዉን አባላትና ደጋፊዎች በማስፈራራት፣ ፓርቲዉን ከወዲሁ ለማዳከም ነዉ።

የአንድነት ፓርቲ በአሁኑ ወቅት፡

1) ከሰማያዊና ከኤዴፓ በስተቀር፣ ከበርካታ ደርጅቶች ጋር ለመዋሃድ ትልቅ ሥራ እየሰራ ነዉ። በተለይም ከመኢአድ እና ከአራና ጋር ዉይይቱ ሥር የሰደደ ይመስላል።

2) በአድዋ ከተማና በአዲስ አበባ፣ የአድዋን ድል በአል ለማክበር፣ እንዲሁም፣ በአማራዉ ክልል የሚኖረዉን ሕዝብ የተሳደቡ የብአዴን አመራር አባል ለፍርድ እንዲቀርቡ የሚጠይቅ፣ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በባህር ዳር ለማድረግ አቅዷል።

3) የሚሊየነም ድምጽ ለነጻነት ክፍል ሁለት ዘመቻ በቅርብ ጊዜ ዉስጥ ይፋ ለማድረግ በዝግጅት እንዳለ ይነገራል።

እነዚህና የመሳሰሉት የአንድነት እንቅስቃሴዎች፣ የፖለቲካዉን አስተላለፍ በእጅጉ የሚቀየሩ እንደመሆናቸው፣ በገዢው ፓርቲ ዉስጥ ያሉ ፖሊሲ አዉጭዎችን ማሳሰቡ አያስገርምም። አንድነት፣ የኢሕአዴግ ስርዓት ለመቀየር ና ለዉጥ ለማምጣት ሰላማዊና ሕግን በተከተለ መንገድ ስራዉን ሲሰራ፣ ኢሕአዴጎችም በስልጣናቸው ለመቆየት የራሳቸዉን ሥራ መስራት የሚጠበቅ ነዉ። የሚያወቁትና የለመደባቸው ደግሞ ዜጎችን ማሰርና ማዋረድ ስለሆነ ይኸዉ እያሰሩ ነዉ።

ይህ በኢሕአዴግ፣ አመራር አባላቱን በማሰር አንድነቶች ለማስፈራራት የሚደረገዉ እንቅስቃሴ የሚሰራ ግን አይመስለኝም። የአንድነት ፓርቲ መሪዎች፣ ትግሉን ሲቀላቀሉ፣ እንደሚታሰሩ፣ ሊገደሉ እንደሚችሉ በማወቅ ነዉ። በብርቱካን ሚደቅሳ፣ በአንዱዋለም፣ በእስክንደር ነጋ …የሆነዉን ያውቃሉ። ነገር ግን ከምቾታቸዉና ከጥቅማቸው ይልቅ አገራቸውን ያስቀደሙ በመሆናቸው ፣ ለእስራቱም ሆነ ሊመጣ ለሚችለው መከራ የተዘጋጁ ይመስላል።

እንግዲህ መልእክቴ ይሄ ነው። ኢሕአዴግ በአንድነት ፓርቲ ላይ በአንድ በኩል የያዘዉን ጠመንጃ ተጠቅሞ ጫና ሲያሳደር፣ አገር ቤት ያሉ ታጋዮች ሕይወታቸውን መስመር ላይ አድርገዉ ዋጋ ለመክፈል ሲዘጋጁ፣ እኛ ደግሞ የአንድነት ፓርቲን ከመቼዉም ጊዜ በበለጠ በመርዳትና በመደገፍ ማጠናከር አለብን። የአራት ኪሎ ባለስልጣናት በያዙት ዱላ ይተማመናሉ። አንድነት፣ በኔ እና በ እናንት፣ በኛ ፣ አገር ቤት ባለነውም ሆነ በዉጭ በምንኖር ፣ በኢትዮጵያ ህዝብ ጉልበት ይተመመናል።

እንግዲህ ጨዋታዉ ተጀምሯል። ፊሽካዉ ተነፍቷል። ተስፋ ቆርጠን፣ «አይቻልም» ብለን ሜዳዉን ለቀን ከወጣን በፎርፌ ዜሮ ገባን ማለት ነዉ። ነገር ግን ዝምታ፣ ተስፋ መቁረጥ አይሁን። ሁላችንም የድርሻችንን እንወጣ።

ለኢሕአዴጎች ይህንን እላለሁ። «ጸሃይ ሳትጠልቅ ቀናዉን ነገር ማድረግ ተማሩ። ትንሽ እንኳ የሰላም ነገር ልባችሁ ይግባ። ይህ በሌሎች ላይ የመዘዛችሁት ሰይፍ መልሶ እናንተኑ ነዉ ስለሚበላችሁ ሰይፋችሁን ወደ ሰገባው መለሱና ለሰላም እጆቻችሁን ዘርጉ»

ኢትዮጵያዊነት –”የለህም ይሉኛል፤ እውነት የለሁም ወይ?” –መስፍን ነጋሽ

$
0
0

ከማንነት ጋራ የተያያዙ ጥያቄዎች፣ ሙግቶች፣ በተቃራኒውም አስቀያሚ ሐሳብ አልባ ስድድቦች ሰሞኑን በርከትከት ብለዋል። ጥያቄዎቹና ሙግቶቹ መኖራቸውን አጥብቄ እደግፈዋለሁ። በእኔ እይታ አብዛኞቹ ምልልሶች ወይም ሙግቶች በመሠረቱ አዲስ ጭብጥም ሆነ መከራከሪያ አላቀረቡም። ቢሆንም የነበረውንም ቢሆን በአግባቡ በተደጋጋሚ እያነሱ ሐሳብ መለዋወጡ ጠቃሚ ነው፤ ሙከራው ቢያንስ እርስ በርስ መተዋወቅን ይጨምራል፤ አልፎም አዲስ ሐሳቦችን ለማፍለቅ እድል ይሰጣል።

የማነ ናግሽ ኢትዮጵያዊ የሚባል ማንነት የለም፤ ያለው በብሔረሰብ ላይ የተመሰረተ ማንነት ብቻ ነው የሚለውን ሐሳብ በትግሪኛ ጽፎት ተመልክቼ ነበር። ኃላም ራሱ ወደ አማርኛ እንደመለሰው ይህን ጽሑፍ ወደማጠናቀቁ ስቃረብ ተመልክቻለሁ። በመሠረቱ ሐሳቡ አዲስ አይደለም። በየማነ አስተያየት መነሻነት ሌሎችም አመለካከታቸውን አካፍለዋል፤ ጥቂቶቹን በሚገባ አንብቤያለሁ። በሒደቱ የታየው ጉዳዩን ከመመርመር ይልቅ ተናጋሪውን የማጥቃት ስልት ጠቃሚ ስላልሆነ ወደዚያ አንመለሰም። በሐሳቡ ላይ ግን አስተያየቴን ላካፍል።

1. ስለማንነት እንደመነሻ
ሁልጊዜም ከጥንቱና ከስሩ መጀመር ጠቃሚ ቢሆንም ጽሑፌን ወደ መጽሐፍ ምእራፍነት እንዳይቀይረው በመስጋት፣ ከዚያ በላይ ደግሞ አንባቢዎቼ ስለማንነት እና ስለፖለቲካው መሠረታዊ ጉዳዮች ያውቃሉ ከሚል እምነት ስለማንነት ወደመዘርዘር አልገባም። በምትኩ ለክርክሬ የሚሆኑኝን መነሻዎች ብቻ እጠቅሳለሁ። አምስት ጭብጦች ላስይዝ፤
1.1. አንድ ሰው ብዙ አይነት ማንነቶች ሊኖሩት ይችላሉ፤ ይኖሩታልም። አንድ ማንነት በጉልህ የሚታየው ከሌላው ጋራ ሲነጻጸር እንደመሆኑ መጠን፣ አንድ ሰው ማንነቱን የሚገልጽበት መንገድ እንደሁኔታው ይለያያል። ጥያቄው ሃይማኖትን ሲከተል፣ ሃይማኖታዊ ማንነቱን ያስቀድማል እንደማለት። እዚህ የምናነሰው ግን ቋንቋን ጨምሮ ከተመሳሳይ ባህል፣ ታሪክ እና ስነልቦና ጋራ ስለተቆራኘው ማንነት ነው። የማንነት ፖለቲካ በአገራችን በዋናነት የሚወከለውም በዚሁ ነው። ለውይይታችን እንዲረዳ በብሔረሰባዊ እና በአገራዊ ማንነት ላይ ብቻ እናተኩር።
1.2.ማንነት (ብሔረሰባዊም ይሁን አገራዊ) ማኅበረሰብ ሠራሽ ነው፤ ተፈጥሯዊ አይደለም። ማንነት ከቤተሰብ፣ ከማኅበረሰብና ከትምህርት ቤት የምንማረው ነው። ስለዚህም ባለበት አይረጋም፤ መጠነኑና ፍጥነቱ ቢለያየም ይለወጣል።
1.3.ማንነት በአጋጣሚ በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ በመወለድ እና/ወይም በማደግ፣ አለዚያም በተጽእኖ ሊገኝ ወይም ሊለወጥ ይችላል። ይህ ብቻ ግን አይደለም። ማንነት በምርጫም ሊገኝ ይችላል፤ አንድ ሰው በፍላጎቱ የአንድ ማንነት አካል ሊሆን ይችላል፤ ምን ያህል ይሳካለታል የሚለውን የሚወስኑ ብዙ ከእርሱ ውጭ የሆኑ ሁኔታዎች ቢኖሩም። አንዳንድ ማኅበረሰቦችና ማንነቶች ከሌላው የበለጠ አዲስ መጤን የመቀበልና የማዋሐድ ጠባይ አላቸውና።
1.4. አንድ ማንነት ከቀላል ጀምሮ ወደ ውስብስብና ብዙ እንደሚያድግ ሁሉ፣ ማንነቶች ሊወራረሱ፣ አልፎም ማንነቶች ተደባልቀው/ተዋሕደው ”አዲስ/የተለየ” ማንነት ሊፈጥሩም ይችላሉ።
1.5. በማንኛውም መንገድ መስተጋብር የመፍጠር እድል ያገኙ ማንነቶች የተለያዩ እሴቶቻቸውን ይለዋወጣሉ፣ ይዋዋሳሉ፣ ያዳቅላሉ። እንዳለ የሚያስጠብቁት የማንነታቸው አካል መኖሩ እንደማይቀርም እሙን ነው። ስለዚህም ንጹህ የሚባል ማንነት አይኖርም። ንጹሕ የሚባል ማንነት ካለ ያ ማንነት በላቦራቶር የተፈጠረና እስካሁንም ወደምንኖርባት የሰው ዓለም ያልመጣ ማንነት ነው።

ከዚህ የሚከተለው ክርክሬ ቢያንስ በእነዚህ አምስት መንደርደሪያዎች ላይ የተመሠረተ ይሆናል። እነዚህን መነሻዎች ይዘን ወደ ጥያቄው እንመለስ። እውነት ኢትዮጵያዊ ማንነት የለም?

በአገራችን የብሔረሰብ ማንነት አለ፤ ራሱን የዚህ ወይም የዚያኛው ብሔረሰብ አባል አድርጎ የሚመለከት ሰውም አለ። ይሄ ለክርክር የሚቀርብ፣ ያልተረጋገጠ ጉዳይ አይደለም። ይህኛው ቡድን ”ብሔርሰብ ነው ወይስ ዘውጌ ወይስ ጎሳ?” የሚለው ጥያቄ ላነሳነው ክርክር አስፈላጊ አይደለም። ለአሁኑ፣ ቁም ነገሩ፣ የራሳችን ባህላዊና ታሪካዊ ማንነት አለን የሚሉና ያላቸው ብድኖች መኖራቸው ነው። ስለዚህ ”እኔ የእገሌ ብሔረሰብ አባል ነኝ፤ የዚያኛው አይደለሁም፤ ማንነቴም አገው፣ ትግራዋይ፣ ጉሙዝ፣ ኦሮሞ፣ አማራ…ነው” የሚሉ ሰዎች አሉ። መኖራቸው እውነት ነው፤ በአግባቡ ከተያዘም ጸጋ ነው። አሁን የቀረበው ጥያቄ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት እነዚህ ብሔረሰባዊ ማንነቶች ብቻ ናቸውን የሚል ነው። ወይም፣ ኢትዮጵያዊ ማንነት የለምን? እርግጥ የአንድ ማንነት ታጋሪዎች ነን የሚሉ ሰዎች እስካሉ ድረስ ስለማንነቱ ለማረጋገጥ ሌላ ምርመራ ማድረግ የግድ አይደለም ብሎ የሚከራከር ይኖር ይሆናል። በዚህ ስሌት፣ ”ኢትዮጵያዊ ማንነት አለን” የሚሉ ሰዎች መኖራቸው ብቻውን በቂ ማስረጃ በሆነ ነበር። ቢሆንም ተጨማሪ ሐሳቦችን መለዋወጡ አይጎዳም።

2. ኢትዮጵያዊ/አገራዊ ማንነት የለም የሚሉ ሰዎች ቢያንስ አራት ስሕቶችን ይፈጽማሉ።
2.1. ከፍ ሲል የጠቀስኩትን የማንነቶችን መወራረስ፣ አልፎም የአዲስ ማንነቶች መፈጠር አይቀበሉም። ይህ ማለት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙት ብሔረሰቦች (የፖለቲካ ማኅበረሰቡ አባል የሆኑት ወደውም ይሁን ተገደው) በታሪክ ባካሔዱት መስተጋብር የሁሉም ”ቅልቅል” የሆነ (ምናልባትም የሆኑ) አዲስ ማንነቶች ሊፈጠሩ እንደሚችሉ አይቀበሉም ማለት ነው። አዳዲስ ማንነቶች ሊፈጠሩ ይችላሉ ብለው ካመኑ ክርክራችን በአገራችን አዲስ ማንነቶች ስለመፈጠራቸው እና ስለተፈጠረው/ስለተፈጠሩት አዲስ ማንነቶች ስያሜ ይሆናል ማለት ነው። በእኔ እምነት፣ በረጅሙና በውስብስቡ የአገረ ኢትዮጵያ መስተጋብር አዳዲስ ማንነቶች ተፈጥረዋል። (ይህ ማለት የብሔረሰብ ማንነቶች ጠፍተዋል ማለት አይደለም፤ እርግጥ ባሉበት አንዳችም ሳይለወጡ ቀጥለዋል – ንጽሕ የሚለው ቁልምጫ ትርጉሙ እርሱ ይመስላል- ማለትም ቢያንስ ፖለቲካዊ የዋህነት ይሆናል።) ከተፈጠሩት ”አዲስ/የተለዩ” ማንነቶች አንዱና ዋናው ብዙዎቻችን ”ኢትዮጵዊነት” የምንለው ማንነት ነው። ስለዚህ ማንነት አይነቶች ወይም አረዳዶች ወደ ኋላ አነሳለሁ፤ የችግሩ መነሻ ”ኢትዮጵያዊነት” የሚለው ስያሜ ለተለያዩ ሰዎች የተለያየ ትርጉም መስጠቱ ሊሆን ይችላልና።

2.2. ተከታዩ ስህተት አንድ ሰው ከአንድ በላይ ማንነት ሊኖረው አይችልም፣ አንዱን ማንነት ሲቀበል ሌላውን መተው አለበት፣ ወይም የቀደመ ማንነቱን ከአዲስ ማንነት ጋራ ማዳበል ወይም ማዋሐድ አይችልም ከሚል የተሳሳተ አመለካከት የሚመነጭ ነው። ይህ በንድፈ ሐሳብም ሆነ በተግባር የተሳሳተ ነው። አሁን ያለችውን ኢትዮጵያ ተጨባጭ እውነታም መረዳት ይጎድለዋል። ዛሬ፣ ራሳቸውን በብሔረሰባዊም በአገራዊ ማንነታቸውም የሚገልጹ በሚልዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው ሰዎች አሉ። ልብ በሉ፣ ለእነዚህ ሰዎች ኢትጵያዊነት ዜግነት ብቻ አይደለም፣ ማንነትም ጭምር ነው። ራስን በብሔረሰብ ማንነት ብቻ ሳይሆን በሃይማኖት ማንነትም ደርቦ መግልጽ እንደሚቻለው፣ ኢትዮጵያዊነትን ተጨማሪ ማንነት ማድረግ እውነት የማይሆንበት ምክንያት አይታየኝም። ብሔረሰባዊም አገራዊም ማንነት ያለቸው ሰዎች ስለመኖራቸው ማረጋገጥ ከባድ አልመሰለኝም። አገራዊ ማንነት የለንም የሚሉ ሰዎችን የግድ ይኑራችሁ ብዬ አልከራከርም። ዝርዝሩ ሌላ ውይይት ይፈልጋልና ልተወው።

2.3. ኢትዮጵያዊ ማንነት የለም የሚሉት ሰዎች የሚሰሩት ሌላው ስሕተት ከፍትሕ ጋራ የተያያዘ ነው። እነርሱ ታሪካዊቷ ኢትዮጵያ ”ማንነታችንን ሳታከብር ኖራለች፣ እውቅና ተነፍገን ኖረናል፣ ይህም ሊለወጥ ይገባል” ብለው ይከራከራሉ። ተገቢና እውነት ያለው የፍትሕ ጥያቄ ነውና ከልቤ እደግፈዋለሁ። ይህን እነርሱ የሚጠይቁትን ፍትሕ ግን ለሌሎች፣ ዛሬ ኢትዮጵያዊ የሚባል ማንነት አለን ለሚሉትን ወገኖቻቸው እየከለከሉ ነው። አሁንም ስለዚህ ኢትዮጵያዊ ማንነት ወደ ኋላ አነሳለሁ።

2.4. እነዚህ ሰዎች ከሚሰጡት ማብራሪያ የምንረዳው ሌላው ጭብጥ እውነተኛው/ደንበኛው ማንነት በብሔረሰብ ላይ የተመሰረተው ነው የሚል ነው። እነርሱ ባወጡት የማንነቶች ደረጃ መሠረት፣ ከብሔረሰባዊ ማንነት ውጭ ያሉት ማንነቶች አንድም ውሸት ናቸው አለዚያም ጠንካራ አይደሉም። ብሔረሳባዊ ማንነት ከሌሎቹ ማንነቶች ቀዳሚነት እንዳለው ይሰብካሉ። ይህንን ለፖለቲካ መቀስቀሻነት የሚጠቀሙት ሰዎች ዓላማ የተሰወረ አይደለም። ሐሳቡ ግን በግማሽ እውነት ላይ የተመሰረተ ስንኩል መከራከሪያ ነው። ግለሰቦችና ቡድኖች የሚያስቀድሙት የማንነት መለያ የሚወሰነው በኖሩበትና ባሉበት ታሪካዊ ሁኔታ እንጂ አስቀድሞ በወጣ የማንነቶች ደረጃ አይደለም። ከሌላው ማንነቱ በፊት በሃይማኖታዊ ማንነቱ ራሱን የሚገልጽ ሰው/ቡድን ይኖራል፤ ለሌላው ደግሞ ብሔረሰባዊ አለዚያም አገራዊ ማንነቱን ቀድሞ ይሰማው ይሆናል። ሁሉም የማኀበረሰባቸው ታሪክ ውጤቶች ናቸው። አንዱ ከሌላው የበለጠ ትክክል አይደለም፤ እንደ ግለሰቡ እና ቡድኑ ሊለያይና ሊለዋወጥ የሚችልም ነው። ይህ አመለካከት አንዳንድ ጊዜ ብሔረሰባዊ ማንነታቸውን የማያስቀድሙ ሰዎችን ”የማንነት ችግር” እንዳለባቸው ወይም እየዋሹ እንደሆነ የመክሰስ ድፍረት ተላብሶ የሚታይበት ጊዜም አለ።

3. ኢትዮጵያዊነቶች?
እንደማንኛውም ማንነት ኢትዮጵያዊነትም ብዙ ገጽታዎች አሉት። በታራካዊ ሂደቶችም ብዙ ተለውጧል፤ ገና ይለወጣልም። ኢትዮጵያዊ ማንነት ብዙ ገጽታዎች አሉት ወይም ብዙ አይነት ኢትዮጵያዊ ማንነቶች አሉ ብሎ መነሳት ይቻላል። ለዚህ ጽሑፍ አግባብነት አላቸው ያልኳቸውን ሦስት የኢትዮጵያዊ ማንነት አረዳዶች ብቻ ላስቀምጥ።፡ይህን የማደርገው፣ ኢትዮጵያዊ የምንለው ማንነት ለተለያዩ ሰዎች የተለያየ ትርጉም እየሰጠ አለመግባባት ፈርሮ እንደሆነ በሚል መነሻ ነው። ለመግባባት ሲባል ለማንነቶቹ ሌላ ስያሜም መስጠት እንችል ነበር፣ ለጊዜው ይቆየን።

3.1. አንደኛው ኢትዮጵያዊ ማንነት ራሱን የሁሉም የአገራችን ብሔረሰቦች አካል አድርጎ ይመለከታል፤ ለአንዱ የተለየ ቅርበት አይሰማውም። እነዚህ ሰዎች ምክንያቱ ምንም ይሁን፣ ራሳቸውን የዚህ ወይም የዚያኛው አንድ ብሔረሰብ አባል አድርገው አይቆጥሩም። የዚህ ማንነት ባለቤት የሆነው ኢትዮጵያዊ፣ በአገሪቱ ውስጥ የሚገኝ ማንኛውም ነገር እኩል ተጋሪ ባለቤት እንደሆነ ያምናል። ብሔረሰባዊ ማንነትን ያከብራል። ብሔረሰባዊ ማንነትን ተገዳዳሪው አድርጎ አይፈራውም። ይህ ማንነት ድንገት ከሰማይ ወርዶ የሁሉም አካል ነኝ የሚል፣ ባለቤት አልባ ማንነት አይደለም። በአብዛኛው በተለይ በከተሞች አካባቢ ያደጉ (ለረጅም ጊዜ የኖሩ) ሰዎች የዚህ ማንነት ተጋሪዎች ናቸው። ባህላዊና ስነልቦናዊ ማንነታቸውን የቀረጸው ያለፉበት ታሪክ ነው፤ ፖለቲካው፣ ጦርነቱ፣ የሕዝብ እንቅስቃሴውና መስተጋብሩ፣ ትምህርቱ፣ የከተሜ ኑሮ…። ለእነዚህ ሰዎች ኢትዮጵያዊነት ዜግነት ብቻ ሳይሆን ማንነትም ጭምር ነው። ቁጥር የበለጠ ትርጉም የሚሰጣቸው ሰዎች ካሉ፣ የዚህ ማንነት ባለቤቶች ቢያንስ በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ስለመሆናቸው አልጠራጠርም። (እኔም ራሴን ያገኘሁት እና መሆንም የመረጥኩት እዚህ ውስጥ ነው።)

3.2. ሁለተኛው ኢትዮጵዊነት የአንድ ብሔረሰብ ማንነት ያለው፣ ነገር ግን በተጨማሪም ኢትዮጵያዊ ማንነት ያለው ነው። በብሔረሰብ ማንነቱ የብሔረሰቡ የሆነውን ሁሉ ይጋራል፤ እዚያ ግን አያቆምም፤ በኢትዮጵያዊ ማንነቱ ከሎሎች ኢትዮጵያዊ ማንነት ካላቸው ጋራ የሚጋራው ሌላም ብዙ ነገር አለ። ይህ ሰው የሚረዳው ኢትዮጵያዊ ማንነቱ፣ ብሔረሰባዊ ማንነቱን እንዲተው የሚጠይቅ አይደለም። ይህ ማንነት፣ ከከተሞች መስፋፋት፣ ከትምህርትና ከመንግሥት ቢሮክራሲ ዝርጋታ ጋራ እያደገ እንደመጣ እገምታለሁ። አሁንም የዚህ ቡድን አባላት ቁጥር ከአገሪቱ ሕዝብ ከግማሽ በላይ እንደሚሆን አልጠረጥርም። ይህ ባይሆን አገሪቱ ህልውናዋ ባከተመ ነበር ከሚል መነሻ።

3.3. ሦስተኛው ኢትዮጵያዊነት፣ ብሔረሰባዊ ማንነትን የሚክድ ወይም ለማጥፋት የሚፈልግ ተጻራሪ ማንነት አድርጎ የሚመለከት አረዳድ ነው። ከታሪክ አንጻር በከፊል እውነት ነው። ለዚህ አረዳድ፣ ኢትዮጵያዊነት ማለት የክርስቲያን ሰሜን ኢትዮጵያ ባህልና ማንነት ነው። እንደ ጉዳዩ አቅራቢ ይህ ኢትዮጵያዊነት የአማራ ባህልና ማንነት ብቻ ተደርጎ የሚቀርብበት አጋጣሚም አይጠፋም። ለዚህ አመለካከት አስፈላጊው ጭብጥ ግን፣ ”ኢትዮጵያዊ” ማንነት ቀድሞም ይሁን አሁን ሌሎች ባህላዊ ማንነቶችን ለመደፍጠጥ ያሰፈሰፈ ማንነት ተደርጎ መታየቱ ነው። ይህ መሠረተ ቢስ ስጋት ነው ብዬ እንዳልደመድም እነርሱ ”ኢትዮጵያዊነት” ከሚሉት ውጭ ያለ አገራዊም ሆነ ብሔረሰባዊ ማንነት እንዲጠፋ አዋጅ ማወጅ የሚቃጣቸው ሰዎች አሉ። ማለት የምችለው፣ የእኔ ኢትዮጵያዊነት ከዚህ ይለያል። ይህ የኢትዮጵያዊ ማንነት አረዳድ የብሔረሰብ ማንነቶችን የማያከብር፣ ስለመኖራቸውም ሙሉ እውቅና የማይሰጥ ነው። ይህ ኢትዮጵያዊነት ብሔረሳባዊ ማንነቶችን በጥርጣሬ ይመለከታል፣ የአገራዊ መተሳሰር ጠላቶች አድርጎ ይፈርጃል፣ ማንነቶቹን ማዳከምም ይፈልጋል። የዚህ ማንነት አቀንቃኞች በአብዛኛው በአማራ ልሒቃን መካከል የሚገኙ ጥቂቶች ናቸው። እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያዊ ማንነት በዚህ ገጽታው ብቻ ሲወከል ይስተዋላል።

ህወሓት/ኢሕአዴግ በስልጣን ዘመኑ የመጀመሪያ አስር ዓመታት ሆን ብሎ ሁሉንም ኢትዮጵያዊነቶች በጅምላ እንዲጠሉ ብዙ ሰርቷል። ሌሎቹ ብሔረሰብ ተኮር ፓርቲዎችም ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ስትራቴጂ ተከትለዋል። ስጋታቸው ግልጽ ነው፤ የብሔረሰባቸው አባላት ኢትዮጵያዊ ማንነትን ከደረቡ የደጋፊ መጠናቸው ሊቀንስ ይችላል። በውጤቱም፣ ዛሬ፣ ”ኢትዮጵያዊ ማንነት” ሲባል በብዙ የአደባባይ ሰዎች ዘንድ አስቀድሞ የሚጠቀሰው ይህ ሦስተኛው አመለካከት ብቻ ሆኗል። የፖለቲካ ልሒቃኑ ኢትዮጵያዊነትን በቀዳሚዎቹ ሁለት መልኮቹ የሌለ በማስመሰልም፣ ሦስተኛውን ግን በማጉላት፣ የማንነቱን ባለቤቶች በጅምላ ጥፋተኞችና ተጠርጣሪዎች አስመስለው ያቀርቧቸዋል። ይህ ስህተት ብቻ ሳይሆን ሸፍጥም ነው። የሸፍጥነቱ ስላቅ ወደዜኒቱ የደረሰው፣ እነመለስ ደርሶ የሁለተኛው ዓይነት/አረዳድ ኢትዮጵያዊነት (3.2) አራማጆች ሆነው፣ ባንዲራ መስቀልና ስለሺህ ዓመት የኢትዮጵያ ታሪክ መስበክ ሲጀምሩ ነበር። ሌላው በጣም የሚገርመኝ ነገር፣ የመጀመሪያው ዓይነት ኢትዮጵያዊ ማንነት ያላቸው ዜጎች መኖራቸውን ገዢው ፓርቲ ጭምር ዛሬም ድረስ እውቅና ለመስጠት መፍራታቸው ነው።

ብሔረሰባዊ ማንነትን የፖለቲካቸው ማቀጣጠያ አድርገው መጠቀም የሚፈልጉ ልሒቃን፣ እንዲሁም ከማንነት ፖለቲካና የውድድር ስሜት የሚመጣው ስሜተ-ስሱነት የሚያስከትለውን ሚዛን የመሳት አደጋ ቀድመው ያልጠረጠሩ ሰዎች፣ በአገራችን ውስጥ ያሉት ብሔረሰባዊ ማንነቶች ብቻ ናቸው ይላሉ። ይግረማችሁ በማለትም፣ ኢትዮጵያዊ ማንነት የለም ይላሉ።

ማንኛውም ማንነት እና ከእርሱ ጋራ ተያይዘው የሚመጡ ስሜቶች (የኩራት-ሃፍረት፣ የበላይ-የበታችነት፣ የአሸናፊ-ተሸናፊነት፣ የጊዜው የእኛ ነው-አይደለም፣ የተስፋ-ስጋት ወዘተ) መኖራቸውን ማስቀረት ባይቻልም መጠናቸውን ሲያልፉ ከፍተኛ አደጋን ይጋብዛሉ። አደጋው ሐልዮታዊ ብቻ ሳይሆን ማኅበረሰባዊም ነው። በሐልዮት ደረጃ፣ አሁን እንደምናየው፣ ”ያለሁት እኔ ነኝ እንጂ አንተ አይደለም” እስካማስባል ያደርሳል። አገራችንም ሆነች ዓለማችን በዚህ መሰሉ ሚዛኑን የሳተ የማንነት ስሜት ብዙ ዋጋ ስለመክፈላቸው ታሪክ ብዙ ያስነብበናል። አገራዊ ማንነት ሲጦዝ ሌላውን አገር በእብሪት ወደ መውረር ስካር ያመራል፤ በቆዳ ቀለም መኩራት (የሚያኮራ ከሆነ) ከዚያ አልፎ የበላይነት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ሆኖ ሲወሰድ ወደ አፓርታይድ ያደርሳል፤ በብሔረሰባዊ ማንነት ኮርቶ ራስን ማስተዳደርና ባህልን ማዳበር ከዚያ አልፎ የሌላውን (በተለይ ተፎካካሪ ተደርጎ የሚቆጠረውን) ማንነት መኖርና አለመኖር (በሐልዮትም ይሁን በአካል) ለመወሰን ወደሚያስችል ስልጣንነት ሲቀየር የመጠፋፋት በር ማንኳኳቱን ልብ እላለሁ፤ እሰጋለሁም።

ማንኛውም ብሔረተኝነት በጋራ ታሪክና መጻኢ እጣ ሚዛን መገደብ አለበት። ይህ ካልሆነ፣ ገደብ አልባ በራስ የመተማመን እና የእርግጠኝነት ስሜት ይፈጥራል። ትህትናንና መተሳሰብን ከግለሰብ ልብ፣ ከቡድን የጋራ ስነልቦና ያጠፋል። ይህ ስሜት በግለሰብም በቡድንም ደረጃ ሊንጸባረቅ ይችላል።

ኢትዮጵያዊ ማንነት አለ። ኢትዮጵያዊ ማንነት የሚለው አገላለጽ የሚወክለው መጥፎ የታሪክ አሻራም አለ። የመጥፎው አሻራ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያዊነት አረዳድ በሒደት እየተዳከመ መሔዱ ግልጽ ነው። ምኞቴም ነው። ሌሎቹ ሁለቱ አይነት ኢትዮጵያዊ ማንነቶች ግን የታሪካችን ተጨባጭና በጎ ውጤቶች አድርጌ አያቸዋለሁ። ምንልባትም መጻኢው የኢትዮጵያ መልካም እጣም ያለእነርሱ እውን የሚሆን አይመስለኝም። ራሴንና መሰሎቼን እንዴት ከነገው መልካም ቀን አውጤቼ ልመለከት እችላለሁ? እንዴትስ፣ ”እንኳን የነገው አካል ልትሆን፣ ዛሬም የለህም” ስባልስ ዝም እላለሁ?! ኢትዮጵያዊነት አለ። የለም ስለተባለም አይጠፋም። እኔ አለሁ።

ማንነት ውበት ነው። የማንነት ፖለቲካ ግን አስቀያሚ ገጽታው ይበዛል። እንዳለመታደል ሆኖ እርሱን መዝለል፣ መካድ፣ ንቆ መተው አይቻልም፤ አይገባምም። ስለዚህ በመከባበርና በመረዳዳት መንፈስ መነጋገሩ ይጠቅመናል።

አቡጊዳ –ኦፌኮ የወጣቶች ሊግ አቋቋመ

$
0
0

በዶር መራራ ጉዱና የሚመራዉ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ፣ የወጣቶችን ሊግ ማቋቋሙ የዶር መራራ እና አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ፌስቡክ ዘገበ። ሊጉ የኦሮሞዎች መብት በኢትዮጵያ እንዲከበር ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ በኦሮሚያ ዞኖች ይንቀሳቀሳል ተብሎ ይጠበቃል።

ofc1

አዲስ አበባን ጨምሮ ሃያ አንድ የኦሮሞያ ዞኖች ሲኖሩ፣ አዲስ ለተቋቋመዉ የወጣቶች ሊግ፣ ተወካዮች ከአሥራ ሁለት ዞኖች እንደመጡም ለማወቅ ተችሏል። ወጣት ተወካዮች የመጡት፣ ከሰሜን ሸዋ ዞን፣ ከምእራብ ሸዋ ዞን፣ ከኢሊባቡር ዞን፣ ከቀለም ወለጋ ዞን፣ ከምስራቅ ሃረርጌ ዞን፣ ከጉጂ ዞን፣ ከምእራብ ወለጋ ዞን፣ ከምስራቅ አርሲ ዞን እና ከፊንፊኔ/አዲስ አበባ ሲሆን፣ ከደቡብ ምስራቅ ሸዋ ዞን፣ ከምስራቅ ሸዋ ዞን፣ ከአርሲ ዞን፣ ከባሌ ዞን፣ ከምእራብ ሃረርጌ ዞን፣ ከቦረና ዞን፣ ከጂማ ዙሪያ ዞን፣ ከጅማ ከተማ ልዩ ዞን ፣ ከቡራዩ ልዩ ዞን እና ከአዳማ/ናዝሬት ልዩ ዞን ተወካዮች አልተገኙም።

የወጣቱ ሊግ 50 ወጣቶች ያሉበት አመራር ያሉት ሲሆን፣ 11 አባላት ያሉበትም የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እንዲኖረው ተደርጓል።

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ የመድረክ አባል ድርጅት ሲሆን ከአምስት አመታት በላይ ከአረና ትግራይ፣ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከመሳሰሉ ጋር ጠንካራ የሥራ ግንኙነት የፈጠረ፣ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ ጠንካራ አቋም ያለው ድርጅት ነዉ። ሊቀመንበሩ ዶር መራራ ጉዳና፣ ኦሮሞዉ የኢትዮጵያ ግንድ እንደሆነ በመገልጽ፣ «እንዴት ግንድ ከቅርንጫፍ ይገነጠላል ?» በማለት የአንዳንድ ጽንፈኛ የኦነግ ዘረኛ የመገነጠል ፖለቲካን በይፋ ማጣጣላቸው ይታወቃል።

አንዳንድ የመድረኩ አባል ድርጅቶች፣ በመድረኩ ያሉ የፖለቲካ ልዩነቶችን ሰጥቶ በመቀበል መርህ አጣቦ ፣ ወደ ዉህደት የመምጣት ፍላጎት የነበራቸው ቢሆንም፣ በኦፌኮ ዘንድ ብዙ ተቀባይነት እንዳላገኝ ዉስጥ አዋቂዎች ይናገራሉ። ከአገር አቀፍ ድርጅቶች ጋር አብሮ መስራት እንጂ የሚፈልጉት፣ የ«ኦሮሞ» ድርጅትነታቸውን እና ኦሮሞ ለሚሉት ብቻ የመቆም አላማቸውን ማከሰሙ እንደማይመቻቸው፣ ያከሉት የዉስጥ አዋቂዎች፣ «የኦሮሞ ስማችንን ከቀየርን ፣ ከአክራሪ የኦሮሞ ብሄረተኞች ጥቃት ይደርስብናል» የሚል ስጋት እንዳላቸው ይናገራሉ።

ኦፌኮ በመድረክ ዉስጥ ዉህደትን ከመፍጠር ፣ በቅርቡ «ወደ አገር ቤት ገብቼ እታገላለሁ» የሚል አቋም የያዘው፣ በቀድሞ ነባር የኦነግ አመራር አባላት በነበሩ፣ በነአቶ ሌንጮ ለታ፣ አቶ ዲማ ነግዎ በመሳሰሉ በተቋቋመው ፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ጋር ዉህደት መመስረቱን እንደሚመርጥ የሚናገሩት ዉስጥ አዋቂዎች፣ «ሁለቱም አሁን ያለውን በቋንቋ ላይ ያለው ፌደራል አወቃቀር እንዲቀጥል ይፈልጋሉ። ሁለቱም የሚታገሉት ለኦሮሞዉ ነዉ። ሁለቱም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ነው ለመታገል የሚፈልጉት። ሁለቱም በምርጫ ለመወዳደር ፍላጎት አላቸዉ» ሲሉ፣ በኦፌኮ እና በኦዴግ መካከል በፖለቲካ ፕሮግራሞቻቸው ሆነ በትግል ስትራቴጂዎች አኳያ ምንም ልዩነት እንደሌላቸው ያስረዳሉ።

አቡጊዳ –ህወሓት ፀረ ዴሞክራሲ (ፀረ የወላጆቻችን ትግል) መሆኑ በተግባር አስመስክሯል አሉ አቶ አብርሃ ደስታ

$
0
0

አረና በሁመራ ለማድረግ ያቀደው ህዝባዊ ስብስበ በአዲግራት እንደተደረገው ሁሉ በሕወሃት አምባገነንነት ሳይሳካ ቀርቷል። የአረና አመራር አባል አቶ አብርሃ ደስታ በፌስቡክ ብሎጋቸው :

«ዓረና መድረክ በሑመራ ከተማ ህዝባዊ ስብሰባ ለማድረግ ለዓርብ ጥር ሰለሳ ቀጠሮ ይዞ፣ አስተዳዳሪዎችን አሳውቆ፣ የማዘጋጃቤት አዳራሽ ተፈቅዶለት ያለ ምንም የፀጥታ ችግር የተሳካ ቅስቀሳ ቢያደርግም የሑመራ (እንዲሁም የወልቃይት) ህዝብ ጥሩ አቀባበል ያስደነገጣቸው የከተማው አስተዳዳሪዎች ቃላቸው በማጠፍ የጠራነው ስብሰባ ሕገ ወጥ መሆኑና ማካሄድ እንደማንችል ዛሬ ሐሙስ ጥር ሃያ ዘጠኝ ትእዛዝ ሰጥተውናል። ለስብሰባው የሁለት ቀናት ሙሉ ቅስቀሳ ተደርጓል። ከ አስር ሺ በላይ በራሪ የጥሪ ወረቀት በሑመራና ሌሎች ስምንት የአከባቢው ከተሞች ታድሏል። ስልሳ አራት የፓርቲው አባላት በቅስቀሳው ተሳትፈዋል። ሁለት የድምፅ ማጉልያ በመጠቀም አውጀናል። ህዝቡ በስብሰባው ለመሳተፍ ያሳየው ተነሳሽነት በመገንዘብ ካድሬዎቹ ስብሰባው አግደውታል። ማስፈራርያም ተሰጥቷል» ሲሉ የነበርየወልቃይት ሑመራ ህዝብ ላደረገልን መልካም አቀባበል እናመሰግናለን»

ሲሉ፣ የነበረዉን ሁኔታ ያብራሩ አብራርተዋል። የወልቃይጥ ጠገዴ ሕዝብም ላደረገላቸው ትብብርና ድጋፍ ምስጋናቸዉንም አቅርበዋል።

የትግራይ ህዝብ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ የከፈለው ትልቅ ዋጋ ሃይጃክ እንደተደረገ ያስረዱት አቶ አብርሃ፣ የሕወሃት፣ ሕዝብን የማፈን ተግባራትን፣ የጭካኔ ተገባራት ብልዉታል።

«ህወሓት በትክክል ጨካኝ ነው። “ጨካኝ” የሚል ቃልም አይገልፀውም። ትናንት ማታ ካድሬዎች በሑመራ ከተማ አልጋ እንዳናገኝ ባለ ሆቴሎችን ያስፈራሩ ነበር (አልጋ እንዳያካራዩን)። እራት ለመብላት ስንንቀሳቀስ እየተከታተሉ የምግብቤት ባለቤቶችን እራት እንዳያቀርቡልን ያስጠነቅቁ ነበር። እራት ካቀረቡልን ግን (ነገ ጠዋት) የንግድ ፍቃዳቸው እንደሚሰረዝ ይነግሯቸው ነበር። ይህ የተደረገው ሐሙስ ማታ ነበር። ከሐሙስ በፊት ግን አስተዳዳሪዎቹን ሳይቀሩ ጥሩ አቀባበል አድርገውልን ነበር። ህወሓቶች ግን ለቂም በቀል ባትጋብዙን ምን አለበት? ለምን ህዝብ ፊት በሐሳብ ተከራክረን አሸናፊው በህዝብ ድምፅ አይለይም? ለነፃነትና ዴሞክራሲ ብለው ህይወታቸው የሰዉ ወላጆቻችንን አሳዘኑኝ። የወላጆቻችን ትግል ዉጤቱ እንዲህ ዓፈና ከሆኑ አባቶቻችን ባደረጉት ትግል ከስረዋል ማለት ነው። ምክንያቱም እነሱ የህይወት መስዋእት ቢከፍሉም የታለመው የልጆቻቸው ነፃነትና ዴሞክራሲ ግን ከሽፏል። እኛ ልጆቻቸው እንደገና መስዋእት ልንከፍል ነው። ወላጆቻችን ጭቆናን መታገል እንጂ መቀበል አላስተማሩንም። ስለዚህ ወላጆቻችን የጀመሩት የነፃነት ትግል እንጨርሰዋለን። ዴሞክራሲ በተግባር እስኪረጋገጥ ድረስ እንታገላለን። ህወሓት ፀረ ዴሞክራሲ (ፀረ የወላጆቻችን ትግል) መሆኑ በተግባር አስመስክሯል። በጨቋኞች አንምበረከክም። ከባርነት ነፃነት ይሻላል። ወላጆቻችን ለስልጣን አልታገሉም። ህወሓት ግን የወላጆቻችን ትግል የስልጣን ኮረቻ ለመጨበጥ ተጠቀመበት። የነፃነት መንገድ ትግል ነው» ሲሉም ትግላቸዉን በምንም ሁኔታ እንደማያቋርጡም አረጋግጠዋል።

በሁመራ ስለነበረዉ ሁኔታ ሲዘረዝሩ «የዓረና ፓርቲ የድርጅቶች ጉዳዮች ሐላፊ አቶ ስልጣኑ ሕሸና የፓርቲው አመራር አባል የሆነው አቶ ሃይለኪሮስ ታፈረ ትናንት ምሽት በሑመራ ከተማ በፖሊስ ታስረዋል። ዛሬ ዓርብ ተለቀዋል። በስብሰባው ለመሳተፍ የመጣ ህዝብ በአስተዳዳሪዎች ተበትኗል። ዛሬ በሑመራ ከተማ ከ አምስት ሰው በላይ ተሰባስቦ መንቀሳቀስ ወይ መቀጠም ወይ ሻይ መጠጣት አይፈቀድም ነበር። የፀጥታ ሃይሎች እየተዘዋወሩ ይበትኑም ያስሩም ነበር። ባጠቃላይ ዛሬ በሑመራ ከተማ ‘State of Emergency’ ታውጆ ነበር። ከአባሎቻችን ጋርም መሰብሰብ አልቻልንም። ህወሓት የሰለማዊ ትግል በር እያጨለመው ይገኛል። የወልቃይት ህዝብ ለውጥ ይፈልጋል። ስርዓቱ ለመቀየር ከሚታገል ማንኛውም ሃይል ጋር ለመተባበር ዝግጁ መሆኑ አረጋግጦልናል» ነበር ያሉት።

ብዙ ውህደትና ተጨማሪ ትብብር ለኢትዮጵያ ፓርቲዎች (አንድነት እያደረገ ስላለው የዉህደት ጥረት) –ዳዊት ሰለሞን

$
0
0

የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎቻቸው እንዲወዳደሩ ወይም ስልጣን እንዲይዙ ለማድረግ የሚያገለግሉ መሳሪያዎች ናቸው፡፡የውክልና ዴሞክራሲ እንዲጠነክርና እንዲጎለብት ፓርቲዎች የሚጫወቱት ሚናም ቁልፍ ነው፡፡

በሰለጠነው አለም የፖለቲካው ልቀት የሚለካው በፓርቲዎች ብዛት ነው፡፡የፖለቲካ ስልጣንን ለማግኘት የሚፎካከሩ ፓርቲዎች ቁጥር ሁለት ቢበዛ ሶስት ነው፡፡ለምሳሌ በአሜሪካ ኋይት ሃውስ ለመግባት የሚፎካከሩት ፓርቲዎች ሁለት ናቸው፡፡ዴሞክራቶችና ሪፐብሊካኖች፡፡ በእንግሊዝ ዋነኞቹ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሶስት ናቸው፡፡ወግ አጥባቂዎቹ (ኮንሰርቫቲቭ)የሰራተኛው(ሌበር ፓርቲ)እና ሊበራሎች፡፡

የአሜሪካና የእንግሊዝ ፓርቲዎች ጥርት ባለ የፖለቲካ አይዶሎጂ (Clear Ideologies) ላይ የተመሰረቱና ህዝቡን በፖለቲካ፣በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዩች በማንቃት ምርጫው እንዲያደርጋቸው የሚታገሉ ናቸው፡፡ ፓርቲዎቹ ጥርት ያለ አደረጃጀት ያላቸው በመሆናቸው በመሪዎቻቸው መለዋወጥ የሚለዋወጡ አይደሉም፡፡

ወደ አገራችን ስንመለስ መሬት ላይ የምናገኛቸው ፓርቲዎች ቁጥር ከ73 ይልቃል፡፡ፓርቲዎቹ በአብዛኛው በመሪዎቻቸው የፖለቲካ ቁመና የሚመዘኑ ስፖንሰሮቻቸው በማዕበል እንደተመታች መርከብ ከወዲያ ወዲህ የሚያላጓቸው ናቸው፡፡የፓርቲዎቹ ጥንካሬ የመሪዎቻቸው የፖለቲካ ቁመና ብቻ ነው፡፡

የአገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር የፓርቲዎችን ፕሮግራም አንብቦና አማርጦ ተከታያቸው ለመሆን የሚያስችል ባለመሆኑም የየፓርቲዎቹ አመራሮች ጭምር ፓርቲያቸው ስለሚከተለው የፖለቲካ ፕሮግራም እውቀት ያላቸው ስለመሆኑ አፍን ሞልቶ ለመናገር ያስቸግራል፡፡

የሊበራል የፖለቲካ ፍልስፍናን በሚያራምድ ፓርቲ ውስጥ በሶሻሊስት አይዶሎጂ የተጠመቀ መሪ ቢያገኙ መደነቅ አይኖርብዎትም፡፡ምክንያቱም በኢትዮጵያ የፖለቲካ ተሳትፎ ማድረግ የፕሮግራም ጉዳይ ሳይሆን የህልውና በመሆኑ ነው፡፡
የምርጫ ቦርድን መዝገብ ያጣበቡት የሚበዙት ፓርቲዎች በአይዶሎጂ የተፈበረኩ ሳይሆኑ ዘውግ ተኮር በመሆናቸውም አንደኛቸው ከሌላኛቸው የሚለዩት ‹‹የእኛ›› ‹‹የእነርሱ›› በሚለው የዘውግ አጥር ነው፡፡በእነዚህ ፓርቲዎች ሐሳብ፣ፕሮግራምና የፖለቲካ ፍልስፍና ቦታ የላቸውም፡፡ምርጫ ሲቀርቡ የዘውጌያቸው ተወላጅ የሆነ እንዲመርጣቸው ከመጠየቅ ባለፈ ከዘውጌያቸው ውጪ ያለ ሊመርጣቸው የሚችልበት መንገድ አይኖርም፡፡ስለዚህ እነዚህ ፓርቲዎች የፖለቲካ ስልጣን መዘውሩን የመጨበጥ እድላቸው በዜሮ የሚባዛ ይሆናል፡፡

ዘውግ ተኮር ፓርቲዎች የስርዓቱ ስጋት ተደርገው የሚታዩ ባለመሆናቸውም የምርጫው አድባር ኦዲት ተደረጉም አልተደረጉ አልያም ጠቅላላ ጉባኤ ባያደርጉም ይፈልጋቸዋል፡፡

ተቃዋሚዎች በቁጥር በዝተው በምርጫ ገበያው ራሳቸውን ማቅረባቸው ሁልግዜም የሚጠቅመው ስልጣን ላይ የሚገኘውን አካል ብቻ ነው፡፡የገዢውን ፓርቲ የፖለቲካ ሃይል ለመቀናቀን ፓርቲዎች ቁጥራቸውን ለመቀነስ የሚያስችላቸውን ብስለት የተሞላበት ውሳኔ ማሳለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡ያለፈው የህብረት፣የውህደት፣የትብብርና የግንባር ልምድ ጥሩ ባለመሆኑ ብቻ ውህደት ፣ቅንጅት፣ህብረትና ትብብር አያስፈለግም ማለት የገዢውን ፓርቲ እድሜ ለማራዘም ከመወሰን ተለይቶ መታየት አይኖርበትም፡፡

የከዚህ በፊቶቹ ውህደቶች፣ቅንጅቶች፣ህብረቶች ያልሰሩበትን ምክንያት በማየት የተሻለ ሆኖ ለመውጣት መስራት ይገባል እንጂ የከሸፉ ታሪኮችን በማስታወስ ማላዘን የትም አያደርስም ደግሞስ ‹‹Those who do not learn from past mistakes are doomed to repeat it››ይባል የለምን፡፡ትምህርት ቀስሞ የሚሰራ ውህደት፣ትብብር ወይም ቅንጅት ለመፍጠር መስራት ከሁሉም ዴሞክራሲያዊ ሃይሎች ይጠበቃል፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከመኢአድ ጋር የጀመረውን የውህደት ድርድር ከዳር በማድረሱ ሁለቱ ፓርቲዎች በቅርቡ አንድ እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡አረና ከአንድነት ለመዋሐድ እያደረገ የሚገኘው ድርድርም በአስተማማኝ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ መረጃ አለኝ፡፡አንድነት ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር የጀመረው ትብብር ከፍተኛ ስኬት በማስመዝገቡ ፓርቲዎቹ በውህደት ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ለመፈራረም መብቃታቸው አይዘነጋም፡፡እናም ብዙ ውህደትና ተጨማሪ ትብብር ለኢትዮጵያ ፓርቲዎች !!

አቡጊዳ –አረናዎችን ለመገድል ህወሃት እያሴረ ነዉ ተባለ

$
0
0

ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ለመዋሃድ ንግግር እያደረገ ያለው የአረና ፓርቲ፣ ከሕወሃት ጋር ከፍተኛ የሰላማዊ ትግል ትንቅንቅ ላይ እንደሆነ በስፋት እየተነገረ ነዉ። በቅርቡ በአዲግራት ሊደረግ ታስቦ በነበረዉ ሕዝባዊ ስብስባ ከሌላ አኡራጃዎች የመጡ የሕወሃት ካድሬዎችና ዱርዬዉን ድንጋይ እየወረወሪ ሲበጠብጡ፣ የአመራር አባላትን ሲደበድቡ እንደነበረ የሚታወስ ነዉ። ህወሃት እነዚህ ዱርዮዎችን አሰማርቶ የሽብር ተግባራትን በመፈጸሙ ምክንያት፣ ስብሰባዉን ማድረግ ካለመቻሉ የተነሳ፣ የአዲግራት ሕዝብ አማራጮችን እንዳይሰማ ተደርጓል።

በተመሳሳይ ሁኔታ በሁመራ ሕወሃት በሕግ ተፈቅዶ የተጠራን የአረና ስብሰባ በኋይል ለማጨናገድ ችሏል። አረናዎች ሳይታክቱ በየከተሞቹ የሚያደርጉት ሰላማዊ እንቅስቃሴዎች ፣ በሌላ ብኩል ደግሞ ህወሃት እያሳያቸው ያለው ፍጹም ጸረ-ሰለማ እና ጸረ-ዲሞርካሲ ተግብራት አብዛኛዉን የህወሃት ደጋፊ የነበሩትን ሁሉ እያስገረመና እያስቆጣ ሲሆን፣ በርካታ ሕወሃቶች ወደ አረና እየተጎረፉ እንደሆነ ምንጮች ይጠቁማሉ።

ከዚህም የተነሳ ሕወሃት የአረናን ግለት መግታት ስላልቻሉ የአመራር አባላቱን የመግደል ሴራ አያሴሩ መሆናቸውን የሚገልጹ ዘገባዎች እየተነበቡ ናቸው።

የአረና ከፍተኛ አመራር አባል የሆኑት አቶ አብርሃ ደሳታ በዚህ ጉዳይ ላይ በፌስቡክ የጻፉትን እንደሚከተለዉ አቅርበናል፡

=========================
ሑመራ (ዳንሻ) በነበርኩበት ግዜ ከተወሰኑ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች ጋር ተገናኝቼ ነበር። ሁለት ታጋዮችን የነገሩኝ ላካፍላቹ። “ለምንድነው የትግራይን ህዝብ ፈሪ የሆነው?” አንድ ጓደኛዬ የጠየቀው ነበር። ታጋይ አንድ (ወንድ ነው) ሲመልስ “የትግራይን ህዝብ ፈሪ የሆነው ከድሮ ጀምሮ የህወሓትን ጭካኔ ስለሚያውቅ ነው። ህወሓት ሰው በሊታ መሆኗ የትግራይ ህዝብ በደንብ ያውቃል” አለ። “እሺ የትግራይ ህዝብስ ይፍራ እናንተ ታጋዮችስ ለምን ትፈራላቹ?” ብዬ ጠየቅኩ። ታጋይ ሁለት (ሴት ናት) “እኛ ታጋዮችምኮ የህወሓትን ጭካኔ በደንብ እንረዳለን። ከህዝብ በላይ ህወሓትን የምናውቃት እኛ ነን። አብዛኞቹ የህወሓት ታጋዮችኮ በህወሓት የተረሸኑ ናቸው። በደርግ ከተገደሉብን ብፆት (ጓዶች) በራሷ በህወሓት የተገደሉ ይበዛሉ። በህወሓት እንደተረሸኑ እያወቅንም ‘በጦርነት ተሰውተዋል’ ብለን ነው የምንናገረው። አብዛኞቻችን እናውቀዋለን። ግን እንፈራለን። አሁን ግን ማንን እንደምንፈራ አላውቅም” አለች። “ፍርሓት ፍርሓት … መጨረሻ ድፍረት ይሆናል” ብዬ ተሰናበትኳቸው።

የህወሓት መሪዎች ተስፋ ከመቁረጣቸው የተነሳ የዓረናን መሪዎች እስከመግደል ሊደርሱ እንደሚችሉ አንድ የህወሓት የደህንነት ሐላፊ ዛሬ አጫውቶኛል። ተስፋ የቆረጡበት ምክንያት … የራሳቸው (የህወሓት) አባላትም ዓረናዎች የሚያነሷቸው ሐሳቦች እያነሱ ስለሚጠይቁና በብዛት ከህወሓት አባልነት እየለቀቁ በመሆናቸው ነው። ባሁኑ ግዜ በትግራይ ክልል የሚገኙ የህወሓት አመራር አባላት በየዞኗቸው ተሰብሰበው የሚገኙ ሲሆን ከሚያነሷቸው ሐሳቦች በመነሳት የህወሓት መሪዎች በአባሎቻቸውም እምነት የላቸውም። እስካሁን ድረስ በሰሩት ወንጀል ምክንያት ተጨናንቀዋል። (ሁሉም አመራር አባላት በየዞን ከተሞች የተሰበሰቡ ሲሆን የተምቤኖች ግን ለየት ይላል። ተምቤኖች ጠንከር ያለ ተቃውሞ ያነሳሉ በሚል ስጋት ለብቻቸው በዓድዋ ከተማ እንዲሰበሰቡ ተደርጓል። ሌሎች የማእከላዊ ዞን አባላት ግን በአክሱም ይገኛሉ)። የህወሓት የ አባላት ለስብሰባ ሲገቡ ሞባይላቸው እንዲዘጉ በጥብቅ ይታዘዛሉ። የመሪዎች ንግ ግር መቅረፅ በጥብቅ የተከለከለ ነው። ህወሓት እንኳንስ ህዝብ የራሱ አባላትም አይመርጡትም። የሰሩት ወንጀል ራስ ምታት ሁኖባቸዋል። ስልጣን መልቀቅ የሞትን ያህል አስፈርቷቸዋል። በዚሁ አካሄዳቸው ደግሞ በስልጣን ሊቆዩ እንደማይችሉ በሚገባ ተረድተዋል።

ህወሓት ፍፁም አምባገነንነቱን እያጠናከረ ነው። ትናንት ዓርብ በሑመራ ከተማ ሰዓት እላፊ ማወጁ ይታወሳል። በዓረና እንቅስቃሴ በጣም የሰጋ ህወሓት ዛሬ የዓረና አባላትን ሲያስፈራራ ዉሏል። አቶ መሰለ ገብረሚካኤል የተባሉ የዓረና ስራ አስፈፃሚ አባልና የምዕራባዊ ዞን የዓረና አባላት አስተባባሪ ዛሬ ታስረው እየተገረፉ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል። የዓረና ፓርቲ ቢሮ (በሑመራ) በህወሓት ካድሬዎች ዛሬ ተዘርፏል፤ ኮምፒተሮች ተወስደዋል (የአቶ መሰለ የግል ላፕቶፕም ጭምር በባለስልጣናቱ ተዘርፋለች)። የመንግስት ስልጣን የያዘ አካል እንዲህ የተራ ሽፍታ ስራ ሲሰራ ይደንቃል። ለአምባገነናዊ ስርዓት አንምበረከክም። ማሸነፋችን አይቀርም።

ሕወሓት ከመለስ ጋር ተቀብሮአል ክፍል ሁለት ከነፃነት አድማሱ


ሰበር ዜና –ፍኖተ ነፃነት፤ ዳንኤል ተፈራ ቃል እንዲሰጥ በፌደራል ፖሊስ ታዘዘ

$
0
0

የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ የሆነው ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ ዳንኤል ተፈራ ማዓከላዊ ወንጀል ምርመራ በመቅረብ ቃሉን እንዲሰጥ በፌደራል ፖሊስ ታዘዘ፡፡ ፍኖተ ነፃነት ምንጮችን ዋቢ በማድረግ አቶ ዳንኤል ተፈራን ጨምሮ በአራት የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት ላይ ክስ ለመመስረት ጥረት እየተደረገ መሆኑን መዘገቧ ይታወሳል፡፡
በቅርቡ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ አስራት ጣሴ፣ በክስ ሂደት ላይ የነበረው የአኬልዳማ ዶክመንተሪ በድጋሚ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን መታየቱን ተከትሎ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ ከፃፉት አስተያየት ጋር በተያያዘ “ዘለፋ አዘል ጽሑፍ” ጽፈዋል በሚል ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲያስረዱ ትዕዛዝ በተላለፈባቸው መሰረት በፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የተገኙ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ለ7 ቀን ታስረው በቀጣዩ ሳምንት እንዲቀርቡ በማለት የእስር ትዕዛዝ ወስኖባቸዋል ፡፡ በማሰር እና በማንገላታት ስልጣን ለመቆየት የሚደረገው አፈና ቀጥሏል ዜጎችን በማሰርና በማስፈራራት የትጀመረውን ትግል ማፈን እንድማይቻል መቼ ይሆን የሚገንዘቡት? ትግሉ ይቀጥላል! የአምባገነኑ ዘረኛ አገዛዝ ያከትማል!!1610073_10152193473611870_527946694_n

የአቶ አሥራት ጣሴ እስር የኢህአዴግ የጉልበት ፖለቲካ ማሳያ ነው! –ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ የተሠጠ መግለጫ

$
0
0

ፓርቲያችን አንድነት በተደጋጋሚ ከገዥው ፓርቲ ህግን ከለላ በማድረግ እና የመንግስትን ሥልጣን በመጠቀም የሚደርስበትን ከፍተኛ አፈና ተቋቁሞ የኢትዮጵያን ህዝብ ሉዓላዊ የስልጣን የበላይነት ለማረጋገጥ ትግሉን አጠናክሮ መቀጠሉ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡

በተለይም ፓርቲያችን በመላው የሀገራችን ክፍል የዘረጋውን መዋቅር በህዝባዊ አቅም ወደ ተሻለ ደረጃ በማሸጋገር በአምስት ዓመት ስትራተጂክ ዕቅዱ መሰረት እያከናወነ ያለው ህዝባዊ ንቅናቄ እና በተሳካ ሁኔታ ጠቅላላ ጉባዔ አካሂዶ ዴሞክራሲያዊ የአመራር ሽግግር ማድረጉ በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ ትልቅ ተስፋ ያሳደረ ቢሆንም ገዥውን ፓርቲ በአንጻሩ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንደከተተው ይስተዋላል፡፡

ኢህአዴግ ቀደም ሲል የፓርቲያችንን እንቅስቃሴ በመከታተል ከከፍተኛ አመራሮች መካከል አቶ አንዱዓለም አራጌ፤ ናትናዔል መኮንን እና ሌሎች በርካታ አባላትን የተለያየ ምክንያት ፈጥሮ እየወነጀለ ለእስር መዳረጉ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህም በድንገት የተደረገ ሳይሆን የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር እና የኢህአዴግ ሊቀመንበር አቶ መለስ ዜናዊ በግልጽ በፓርላማ ተገኝተው ‹‹አንድነት ፓርቲ እግር ሲያወጣ እግሩን እንቆርጣለን›› ባሉት መሰረት የፈጸሙት ነበር፡፡

አሁንም የራዕያቸው አስቀጣይ ነን የሚሉ የገዥው ኃይሎች ፈለጋቸውን ተከትለው የአውራ ፓርቲ (የአንድ ፓርቲ ስርዓት) ለመገንባት አንድነትን በጉልበት ፖለቲካ ማጥፋት እንደ ብቸኛ መንገድ ወስደው እየተረባረቡ ይገኛሉ፡፡ በመላው የሀገራችን ክፍል በርካታ አባሎቻችን ከስራ ተፈናቅለዋል፤ በግፍ ከሀገራቸው እንዲሰደዱ ተደርገዋል፤ ታስረዋል፤ ተደብድበዋል፡፡ ይህም በየጊዜው በፓርቲያችን ልሳን በመረጃ ተደግፎ ለህዝብ ይፋ የተደረገ ሲሆን፤ በአጠቃላይ በፓርቲያችን አመራር እና አባላት ላይ የተፈጸመውን የሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰት ባመላከትንበት ሪፖርትም ተካተቶ ለህዝብ ይፋ ተደርጓል፡፡

በተለይም የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል የተካሄደውን ህዝባዊ ንቅናቄ ተከትሎ ፓርቲያችን በተንቀሳቀሰባቸው አሥራ አንድ የሀገራችን ከተሞች ጉልህ ሚና የተጫወቱ እና በህዝብ ተቀባይነት ያላቸውን አባላት ምክንያት እየፈጠሩ እና የፍትህ ስርዓቱን የፖለቲካ መሳሪያ እያደረጉ ለእስር እና ለእንግልት መዳረጉን አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡

ኢህአዴግ ገና በጊዜ የጀመረው የ2007 ዓ.ም የምርጫ ዘመቻ የተለመደውን የጉልበት ፖለቲካ የተከተለ ሲሆን በቅርቡ በምዕራብ ሸዋ ዞን ለንሴቦ ወረዳ አቶ አለማየሁ ለሬቦ የተባሉ የሲተዳማ ዞን የአንድነት ስራ አስፈጻሚ በአዲስ አበባ ተገኝተው የፓርቲ ጉባኤ ተሳትፈው ሲመለሱ በቁጥጥር ስር ውለው ለ22 ቀናት ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ በእስር ቤት ከተሰቃዩ በኋላ መንግስትን ሰድበዋል የሚል ክስ ተመስርቶባቸው በዋስ ተለቀዋል፡፡ ይህንን ተከትሎ በየካቲት 30 ቀን የፓርቲያችን ከፍተኛ አመራር (የብሄራዊ ምክር ቤት አባል) የሆኑት አቶ አስራት ጣሴ ፍርድ ቤትን ዘልፈዋል ተብለው ለእስር የተዳረጉ ሲሆን ሌሎች አራት ከፍተኛ የፓርቲ አመራሮች ሊታሰሩ ሴራ እየተሸረበባቸው መሆኑን ምንጮች ለፓርቲያችን እያረጋገጡ ይገኛሉ፡፡

የፍትህ ስርዓቱን ዋነኛ የፖለቲካ መሳሪያ ያደረገው የኢህአዴግ መንግስት አቶ አስራት ጣሴን ለማሰር እንደ ምክንያት የተጠቀመው በአዲስ ጉዳይ መጽሄት 197 ቅፅ 7 ያወጡትን ጽሑፍ ሲሆን አጠቃላይ መልዕክቱም በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ የሌለ መሆኑን፤ ህጎች አፋኝ መሆናቸውን፤ ኢ.ቲቪ የሰራቸው አኬልዳማ፤ ጀሃዳዊ ሃረካትና ሌሎች ለፖለቲካ ጥቃት ማድረሻ የተቀነባበሩ ድራማዎች ህገ ወጥ መሆናቸውን የሚገልጽ ነው፡፡ ይህ የፍትህ ጥያቄ ደግሞ አቶ አስራት ጣሴ ገና በጠዋት ለትግል የወጡበት፤ ከመሰሎቻቸው ጋር ሆነው አንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍት ፓርቲ እንዲመሰረት በርካታ መስዋዕትነት የከፈሉበት የፖለቲካ አላማቸው እና የፓርቲ አቋም መሆኑ ይታወቃል፡፡

‹‹የኢህአዴግ መንግስት ከሚመራቸው ፍርድ ቤቶች ፍትህ ይገኛል ብለን ሳይሆን ለታሪክ እንዲመዘገብ ወደ ፍርድ ቤት እንሄዳለን›› ሲሉም የግል ሃሳባቸው ብቻ ሳይሆን በብዙ አንቀጽ የተጠቀሰ የፓርቲያቸው አቋም ስለመሆኑም ማሳያ ነው፡፡ ከዚህም በላይ ኪሊማንጃሮ የተባለው ድርጅት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር በመንግስት ተቋማት ላይ ያደረገው ጥናት እንደሚያሳየው በህዝብ ከማይታመኑ ተቋማት መካከል ፍርድ ቤቶች በአንደኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡ ናቸው፡፡

ከነዚህ በህዝብ ከማይታመኑ ተቋማት ፍትህ አይገኝም ብሎ ማመን እና እምነትን መንገርም ሆነ መጻፍ ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑ እየታወቀ በአካል ባልተገኙበት ችሎት በአካል ተገኝቶ ችሎትን ያወከ ወይም የዘለፈ በሚቀጣበት ፍታብሔር አንቀጽ 480 ቀርበው እንዲያስረዱ ከተጠሩ በኋላ ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ይሁን እንጂ የተጠሩበት የፍታብሔር አንቀጽ የሚያዘው ጥፋታኛ ሆነው የተገኙ ቢሆን እንኳ በአነስተኛ የገንዘብ መቀጮ የሚቀጣ እንጂ ለእስር የሚያበቃ አልነበረም፡፡

ኢህአዴግ ይህንን እያደረገ ያለው ቀናቶች ወደ 2007 ዓ.ም ምርጫ እየገሰገሱ እና ፓርቲያችንም በህዝባዊ አቅሙ እየጎለበተ በመምጣቱ ካለቃቸው እንደተማሩት እግር ያወጣ ፓርቲያችንን እግር በመቁረጥ፤ አመራሩን ህግን ከለላ አድርገው ለእስር በመዳረግ፤ እንዳይጽፍ፤ እንዳይነገር እና በፍርሃት ቆፈን ተይዞ አንገቱን እንዲደፋ በማድረግ በምርጫ ሜዳው ከጀሌዎቻቸው ጋር ሩጠው አሸንፈናል ብሎ ለማወጅ የሚደረግ አስነዋሪ ዘመቻ ነው፡፡

ነገር ግን እንዲህ ያለው አምባገነናዊ ተግባር ትግላችንን የበለጠ አጠናክረን በመግፋት ሰላማዊ ትግሉ የሚጠይቀንን መስዋዕትነት ለመክፈል የሚያበረታን እንጂ ወደኋላ የማይመልሰን መሆኑን ዛሬም እንደ ትላንቱ ለመላው ህዝባችን እናረጋግጣለን፡፡

የፍትህ ስርዓቱም ከአንድ ፓርቲ ወገንተኝነት እንዲወጣ እና በግፍ የታሰሩ አመራሮቻችንንም በነጻ እንዲያሰናብት እንጠይቃለን !!!!

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!
የካቲት 1 ቀን 2006ዓ.ምUDJ

“እግዚአብሔርና ፋሺሽቶቹ” ቫቲካን ከሙሶሊኒ ጋር ስለ ነበራት ሕብረት ስለ ዴሽነር መጽሐፍ፤ በኪዳኔ ዓለማየሁ

$
0
0

ይህ ጽሑፍ የሚያተኩረው ዋናው ምንጩ በሆነው፤ እ.አ.አ በ2013 (2006 ዓ/ም) ታትሞ ለንባብ በደረሰው፤ ካርልሔንዝ ዴሽነር (Karlheinz Deschner) “እግዚአብሔርና ፋሺሽቶቹ – የቫቲካን ሕብረት ከሙሶሊኒ፤ ፍራንኮ፤ ሒትለርና ከፓቬሊች ጋር” “God and The Fascists – The Vatican Alliance with Mussolini, Franco, Hitler, and Pavelic” በተሰኘው መጽሐፍ በተካተተው ማስረጃ ላይ ነው። የጽሑፌ ዓላማም በፋሺሽቶች ኢትዮጵያ ላይ ስለ ተፈጸመው እጅግ መራር የጦር ወንጀል፤ የቫቲካንና የሙሶሊኒ ግንኙነት ምን ይመስል እንደ ነበር ደራሲው ተመራምሮ ያቀረበው ማስረጃ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ሰፊ ግንዛቤ እንዲያገኝ ለማድረግ ነው። ስለዚህ፤ ደራሲው ቫቲካን ከሒትለር፤ ከፍራንኮና ከፓቬሊች ጋር ስለ ነበራት ግንኙነት ያቀረበውን ማስረጃ በዚህ ጽሑፌ አላካተትኩትም።
እንደሚታወቀው፤ በሙሶሊኒ ትመራ የነበረችው ፋሺሽት ኢጣልያ፤ በቫቲካን ያልተቆጠበ ድጋፍ፤ ኢትዮጵያ ላይ በፈጸመችው የጦር ወንጀል አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ከመጨፍጨፋቸው በላይ 2 000 ቤተ ክርስቲያኖችና 525 000 ቤቶች ወድመዋል። ሌላም እጅግ አስከፊ ግፍ ተፈጽሟል።

በዓለም-አቀፍ ሕግ በተከለከለ የመርዝ ጋዝ ጭምር በመጠቀም ፋሺሽቶች በፈጸሙት የጦር ወንጀል፤ ቫቲካን ስለ ነበራት ሚና በተለይም መሪዋ ስለ ነበሩት ፖፕ ፓየስ 11ኛና ፋሺሽቱ ሙሶሊኒ ሕብረት በብዙ ማስረጃ ተረጋግጧል። በበኩሌ ከዚህ ቀደም ባቀረብኳቸው መጣጥፎች፤ እነአልቤርቶ ስባኪ (Alberto Sbacchi, “Ethiopia Under Mussolini”) አቭሮ ማንሐታን (Avro Manhattan: “The Vatican in World Politics”), ሥዩም ገብረእግዚአብሔር (“The Symphony of My Life”) ወዘተ. መጽሐፎች እንዲሁም ታዋቂ በሆኑ ጋዜጦች (New York Times) እና (Manchester Guardian) የቀረቡትን አስተማማኝ ማስረጃዎች አካፍያለሁ። በተገኙት ማስረጃዎች ሁሉ ፖፕ ፓየስ 11ኛ ከሙሶሊኒ ጋር በነበራቸው ፖለቲካዊ ቅርበትና የመጠቃቀም ሥልት፤ “ላተራን” (Lateran) የተሰኘ ውል ተፈራርመው ሲደጋገፉ እንደ ነበር፤ ፖፑ ራሳቸው የኢጣልያን ንጉሥ፤ ኡምቤርቶን “የኢጣልያ ንጉሥና የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት” ብለው የባረኳቸው መሆኑን፤ የቫቲካን መሪዎችና ካሕናት የፋሺሽቱን ጦር መባረካቸውን በተጨባጭ ማስረጃ ፍንትው ብሎ ቀርቧል።

ፖፕ ፓየስ 11ኛና ሙሶሊኒ እጅና ጓንት ሆነው እንዲተባበሩ ያመቻቸላቸው ዋናው መሠረታዊ ምክንያት ሁለቱም መሪዎች ለዲሞክራሲ፤ ለሕብረተ-ሰብዓዊነትና ለኮሙኒዝም ይጋሩት የነበረው ጥላቻ ነበር። በአበው አነጋገር፤ “የጠላቴ ጠላት፤ ወዳጄ ነው” በሚለው ሰንካላ መርሆ ይመሩ ነበር ማለት ነው።

የ”እግዚአብሔርና የፋሺሽቶቹ” ደራሲ፤ ካርልሄንዝ ዴሽነርስ ምን ብሏል?

1ኛ/ እ.አ.አ ከ1922 በፊት፤ ቫቲካንና የኢጣልያ ፖለቲካ ፓርቲዎች ተጻራሪዎች ነበሩ። ቫቲካን ባንድ በኩል ስትሆን በሌላ በኩል፤ የሶሺያሊስትና የኮሚዩኒስት ፓርቲዎች ሐገሪቱን ለመቆጣጠር ይፎካከሩ ነበር። በተለይ ሙሶሊኒን በተመለከተ፤ በጊዜው እሱ በእግዚአብሔር የማያምን፤ እንዲያውም ስለ ክርስቶስ ተገቢ ያልሆኑ ቃላት በጽሑፍ ያቀርብ እንደ ነበረና ይህንን ሁኔታ የተገነዘቡ ሌሎች ጸሐፊዎች በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንና በፋሺሽቶቹ መሀል ምሕረት የሌለው ግጭት ሊከሰት እንደሚችል ይተነብዩ ነበር። (ገጽ 28-29)
“Mussolini was certainly an atheist. His first essay, published in 1904 and titled “There is No
God.” was about the nonexistence of God…..” (p 28) (ትርጉም፤ ሙሶሊኒ በእርግጥ በእግዚአብሔር የማያምን ሰው ነበር። (እ.አ.አ.) በ1904 ያሳተመው “እግዚአብሔር የለም” የተሰኘው የመጀመሪያ ጽሑፉ ስለ አምላክ አለመኖር ነበር።)(ገጽ 28)
2ኛ/ እ.አ.አ በ1921 ግን ሊከሰት የሚችለው ግጭት ቀርቶ ፋሺሽቶቹ ባወጡት መግለጫ፤
“…the Fascist leader announced “that the only universal idea that exists in Rome today is
the one that emanates from the Vatican.” (p. 29) (ትርጉም፤ የፋሺሽቱ መሪ (ሙሶሊኒ)፤
“ባሁኑ ጊዜ በሮም የሚገኘው ዓለም-አቀፋዊ አስተሳሰብ ከቫቲካን የሚመነጨው ነው።” በማለት
አስታውቋል። (ገጽ 29)

ስለዚህ፤ አኪሌ ራቲ (Achille Ratti) በመባል ይታወቁ የነበሩት የካቶሊክ ካርዲናል እ.አ.አ የካቲት 5 ቀን 1922 (February 5, 1922) ፖፕ ፓየስ 11ኛ (Pope Pius XI) ተሰኝተው እንደ ተመረጡ ሙሶሊኒ ከሁለት ጓደኞቹ ጋር በእለቱ ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ የቫቲካን አደባባይ በመሔድ የተሰማውን ጥልቅ ስሜት አንጸባርቆ ነበር። ከጥቂት ጊዜ በኋላም ሙሶሊኒ በጻፈው ደብዳቤ ለፖፕ ፓየስ የነበረውን አድናቆት እንዲሁም በፖፑና በኢጣልያ መሀል የነበረው ግንኙነት እንደሚሻሻል አስተያየቱን ገልጾ ነበር። (ገጽ 29፤ ምንጭ (Neisser Zeitung, March 12, 1929)

የሙሶሊኒ ድርጊት ግን ሃይማኖተኛ ወይም ካቶሊካዊ በመሆኑ አልነበረም። እንዲያውም፤ ሃይማኖት ንጉሦችና ጨቋኞች ለሥልጣናቸው የሚጠቀሙበት መሣሪያ መሆኑን ያምን ነበር።
“But on the other hand, Mussolini knew that religion, as he had himself stated in his
first atheist piece of writing, is “a trick of kings and oppressors to keep their subjects
and slaves under control” (p. 30) (ትርጉም፤ በሌላ በኩል፤ በሙሶሊኒ እውቀት፤
በመጀመሪያው የኢአማኝ ጽሑፉ፤ “ሃይማኖት ንጉሦችና ጨቋኞች ሕዝቦቻቸውንና
ባሪያዎቻቸውን በቁጥጥራቸው ስር ለማድረግ የሚጠቀሙበት ማታለያ” መሆኑን አትቶ ነበር።)(ገጽ 30)

3ኛ/ ካርዲናል አኪሌ ራቲ፤ ለፖፕነት ከመመረጣቸው በፊት እ.አ.አ. በ1921 ስለ ሙሶሊኒ የነበራቸውን ከፍ ያለ አድናቆት እንደሚከተለው ገልጸው ነበር፤
“ Mussolini is making quick progress and will crush everything that gets in his way with
elemental force. Mussolini is a wonderful man. Did you hear? A wonderful man!…..
The future belongs to him.” (p 30)
(ትርጉም፤ ሙሶሊኒ በፍጥነት እየገሰገሰ ነው፤ የሚጋረጥበትንም ማንኛውንም ነገር በኃይል ያወድመዋል።
ሙሶሊኒ ግሩም ሰው ነው። ሰማችሁኝ? ግሩም ሰው!…..መጪው ዘመን የሱ ነው።” (ገጽ 30) (ምንጭ፤ Paris,
The Vatican, 69)

4ኛ/ አኪሌ ራቲ፤ ፖፕ ፓየስ 11ኛ በመባል ከተመረጡ በኋላ ከፈጸሟቸው ለሙሶሊኒ እጅግ ጠቃሚ ተግባሮች አንደኛው እ.አ.አ. ጥር 20 ቀን 1923 (January 20, 1923) የቫቲካን ዋና ደጋፊ የነበረውን “ፓርቲቶ ፖፑላሬ” (Partito Populare) የተሰኘውን የካቶሊክ ፓርቲ ማውደም ነበር። የዚህም ዋናው ምክንያት ለቫቲካን የፋሺሽቱ ፓርቲ የተሻለ ጥቅም የሚያስገኝ መሆኑን በማመን ነበር።

5ኛ/ ሙሶሊኒ ለቫቲካን ያበረከተው የመጀመሪያው አገልግሎት 1.5 ቢሊዮን ሊሬ በማበርከት ነበር፤
“The first service the ex-socialist rendered to the Holy See was a financial one. He saved the
“Banco di Roma” to which the curia and many of its prelates had entrusted large amounts of
money, from bankruptcy by stepping in with approximately 1.5 billion lire at the expense of the
Italian state.” (p31-32) (ትርጉም፤ የቀድሞው ሶሺያሊስት (ሙሶሊኒ) ለቫቲካን ያበረከተው የመጀመሪያው
አገልግሎት የገንዘብ እርዳታ ነበር። በኢጣልያ መንግሥት ወጪ፤ 1.5 ቢሊዮን ሊሬ በማበርከት ቫቲካንና
መንፈሳዊ መሪዎቿ ብዙ ገንዘብ ያስቀምጡ የነበረበትን “ባንኮ ዲ ሮማ”ን ከክስረት አዳነው። (ገጽ 31-32፤ ምንጭ፤
Manhattan, 112)

በሙሶሊኒና በፖፕ ፓየስ 11ኛ መሀል የነበረው ግንኙነትና ሕብረት እጅግ የተጠናከረ ስለ ነበረ፤ ፋሺሽቶች ተቃዋሚ ካቶሊኮችን ሲያሰቃዩና ሲገድሉ ፖፑ ምንም ተቃውሞ አላሰሙም ነበር። እንዲያውም፤ የካቶሊክ ካሕናት በሙሉ ከካቶሊክ ፓርቲ ራሳቸውን እንዲያገልሉ በማዘዝ ለፋሺሽት ፓርቲ ከፍተኛ እንቅፋት የነበረውን ሁኔታ አስወገዱለት። ከዚህ በተጨማሪ፤ ከዚህ በታች ያለውን መግለጫ ለዓለም አስታወቁ፤
“Mussolini has been sent to us by Providence.” (p. 33) (ትርጉም፤ ሙሶሊኒ በፀጋ (በአምላክ) የተላከልን
ነው።) (ገጽ 33፤ ምንጭ፤ Manhattan, 115)

6ኛ/ ሌላው ሙሶሊኒና ፖፕ ፓየስ 11ኛ የተጠቃቀሙበት እጅግ ከፍተኛ ጉዳይ፤ “ላተራን” (Lateran) የተሰኘውን ውል በመዋዋል ነበር። በዚህ ውል መሠረት፤ ቫቲካን መንግሥታዊ ልዑላዊነት እንዲኖራት ከመደረጉ በላይ የኢጣልያዊ ብሔራዊ ሃይማኖት ካቶሊካዊነት እንዲሆን ተደረገ። ቫቲካንም የፋሺሽቶቹ ዋና ደጋፊ፤ አጋር ሆነች፤
“The church rejoiced. On February 13, 1929, the pope once again praised Mussolini as the man
“who was sent to us by Providence” and shortly after ordered the clergy to say prayer “for the
King and the Duce” (“Pro Rege et Duce”) at the end of daily mass.” (p. 36) (ትርጉም፤ ቤተ
ክርስቲያኗ (ቫቲካን) ፈነደቀች። እ.አ.አ. የካቲት 13 ቀን 1929 ፖፑ (ፖፕ ፓየስ 11ኛ) ሙሶሊኒን አመሥግነው
“በፀጋ የተላከ ሰው” መሆኑን እንደ ገና ገልጸው፤ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ካሕናቱ ለንጉሡና ለዱቼ (ለሙሶሊኒ) በየእለቱ
ሥርዓት እንዲጸልዩ አዘዙ።) (ገጽ 36፤ ምንጭ፤ Tondi, Die geheime Machr [The Secret Power], 34,
and Die Jesuiten [The Jesuits], 73, Manhattan, 118)

7ኛ/ የሙሶሊኒና የፖፕ ፓየስ 11ኛ ጠንካራ ሕብረት የተንጸባረቀበት ከባድ ክስተት በኢትዮጵያ ላይ የተፈጸመው የጦር ወንጀል ነበር። በቫቲካን በኩል፤ እነካርዲናል ኢልዲፎንሶ ሹስተር (ሚላን) (Cardinal Ildefonso Schuster of Milan) ኢትዮጵያን የካቶሊክ ሃይማኖት ተከታይ ለማድረግና የኢጣልያን ግዛት ለማስፋፋት ወረራውን በይፋ ሲደግፉ በፋሺሽቶቹ በኩል ደግሞ ቁጥሩ እየጨመረ ለሔደው ለኢጣልያ ሕዝብ የቅኝ ግዛት ማስፈለጉን እንደ በቂ ምክንያት በማቅረብ ጦርነቱ እንዲከናወን ገፉበት። ፖፕ ፓየስ 11ኛ የፋሺሽቱን ወረራ በሚቀጥለው ቋንቋ ደገፉት፤

“On August 27 (1935), when the Italian war preparations were running at full speed, the
Pope announced-interwoven in many calls for reason and peace-that a defensive war (!) for
the purposes of the expansion (!) of a growing population could be just and right.”
(ትርጉም፤ እ.አ.አ. ነሐሴ 27 (1935) የኢጣልያ የጦርነት ዝግጅት እየተጧጧፈ ሳለ፤ ፖፑ (ፖፕ ፓየስ 11ኛ)-
ከተገቢነትና ከሰላም ጥያቄዎች ጋር እያወሳሰቡ፤ ታዳጊ ለሆነው የሕዝብ ብዛት ግዛትን ለማስፋፋት (!) የመከላከያ
ጦርነት (!) ማከናወን ተገቢና ትክክል መሆኑን ገለጹ።” (ገጽ 43፤ ምንጭ፤ Manhattan, 121 ff. The speech is
Printed in Reichspost, Vienna, August 30, 1935)
ፖፕ ፓየስ 11ኛ የፋሺሽቱን የኢትዮጵያ ወረራ የደገፉት ከላይ በተጠቀሰው መግለጫ ብቻ አልነበረም። ብዙ ሌሎች ተጨባጭ እርምጃዎች ወስደው ነበር። ከነዚህ ውስጥ፤ (ገጽ 41-49)

(ሀ) ጳጳሶቹ የወርቅ መስቀሎቻቸውንና የአንገት ሰንሰሎቻቸውን እንዲያስረክቡ አዘዙ። በተጨማሪም፤ ጳጳሶቹና
ካሕኖቹም የካቶሊክ ምእመናን ወርቆቻቸውንና ጌጦቻቸውን ለፋሺሽቱ መንግሥት ጦርነት እንዲያበረክቱ
አደረጉ።
“According to Professor Salvemini from Harvard University, at least seven Italian
cardinals, twenty-nine archbishops, and sixty-one bishops supported the Fascist
raid (on Ethiopia) immediately,….) (p. 46) (ትርጉም፤ የሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲው ፕሮፌሰር
ሳልቬሚኒ (እንዳቀረቡት) ቢያንስ 7 (የካቶሊክ) ካርዲናሎች፣ 29 ሊቀ-ጳጳሶች እና 61 ጳጳሶች ወረራውን
(በኢትዮጵያ ላይ) ወዲያውኑ ደገፉ።” (ገጽ 46፤ ምንጭ Manhattan, 123)
(ለ) ጀርመን ሐገር የነበረው የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ንብረት ለሙሶሊኒ እንዲዛወርና ለጦርነቱ የሚያስፈልገው
እንዲገዛበት አደረጉ፤
(ሐ) ሌሎች ሐገሮች የሚገኙ ካቶሊኮች የኢጣልያን ወረራ እንዲደግፉ አደረጉ፤
(መ) የካቶሊክ ካሕናትና ሰባኪዎች ለኢጣልያ ጦር ድል እንዲጸልዩ ተደረገ፤
(ሠ) የፋሺሽት ወታደሮች፤ መድፍና የመርዝ ጋዝ በተጋዘበት መርከብ የቅድስት ማርያም ምስሎችም አብረው
እንዲጓዙ ተደረገ፤

“…..Abyssinians, who had neither gas masks nor shelters, unsuspectingly fell victim to the
dangers of Catholic culture. After the so-called Battle of Amba Aradam, an Italian
captain counted more than sixteen thousand butchered “enemies” (Ethiopians). They lay
there, dead or half-dead, where the skin-burning, lung-tearing gas that was sprayed
from the air had reached them, and they were all eliminated in the most hygienic
possible way – that is, by flamethrowers. (p. 49) (ትርጉም፤ ጭንብልና መጠለያ
የሌላቸው ያልጠረጠሩ ሐበሾች (ኢትዮጵያውያን) የካቶሊክ ባህል ሰለባ ሆኑ። አምባ አራዶም
ከተሰኘው ጦርነት በኋላ አንድ የኢጣልያ ካፕቴን በቆጠረው መሠረት ከ16 000 “ጠላቶች”
(ኢትዮጵያውያን) በላይ ከአየር በተነሰነሰባቸው የመርዝ ጋዝ ቆዳቸው ተቃጥሎ፤ ሳምባቸው ተበጣጥሶ
የሞቱ ወይም በመሞት ላይ የሚገኙ ነበሩ። ሁሉም በተወረወረባቸው የእሳት ቃጠሎ በቅልጥፍና
ተወገዱ። (ገጽ 49፤ ምንጭ፤ Borgese, 400)

(ረ) የፋሺሽቱ ጦር ኢትዮጵያን 90% ሲቆጣጠር፤ ፖፕ ፓየስ 11ኛ የደስታ መግለጫ አሰምተው ነበር፤
“And the Pope also shared in the “triumphant joy of the truly great and good people
about the peace, which,” he said on May 12, 1936, “as one may hope and agree, will be
an effective contribution, a prelude to true peace in Europe and the whole world”. (p 49)
(ትርጉም፤ እ.አ.አ. ግንቦት 12 ቀን 1936 ፖፑ (ፖፕ ፓየስ 11ኛ) የደስታ ተካፋይነታቸውን ሲገልጹ፤
“ለአውሮፓና ለመላው ዓለም እውነተኛ ሰላም አስተዋጽኦ የሚኖረው ለታላቅና ግሩም ሕዝብ (የኢጣልያ)
ታላቅ ድል መሆኑ እንደሚታወቅ ተስፋ ይደረጋል።” (ገጽ 49፤ ምንጭ፤ Manhattan, German edition,
116)
8ኛ/ ፖፕ ፓየስ 11ኛን የበታቾቻቸው ከሆኑት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን መሪዎች ተግባሮች ነጻ ለማድረግ የሚደረገው ሙከራ ሁሉ መሠረተ ቢስ ነው።
“….But all attempts to exculpate the pope are in vain because his own words are a testament
to the contrary. Quite apart from the fact that the bishops can do only what he wants. Or
should they collect gold, bless weapons, and give martial speeches to Italy, of all places, if
the pope has banned it? If he really desires peace? (p. 44) (ትርጉም፤ የራሳቸው ቃላት
ተቃራኒውን ስለሚያረጋግጡ፤ ፖፑን ከኃላፊነት ለማዳን የሚደረገው ሙከራ ዋጋ ቢስ ነው። ተጨባጩ ጉዳይ
ጳጳሶቹ ሊያከናውኑ የሚችሉት ፖፑ የፈቀዱትን ብቻ ነው። ፖፑ ከልክለው ቢሆን ኖሮ (ጳጳሶቹ) ወርቅ
መሰብሰቡን፤ የጦር መሣሪያ መባረኩንና ቀስቃሽ የሚሊታሪ ንግግሮችን፤ ሌላ ሐገር ሳይሆን በኢጣልያ ማከናወን

ይችሉ ነበር?(ፖፑ) ሰላም ቢፈልጉ ኖሮ? (ገጽ፤ 44)

መደምደሚያ፤

በኢትዮጵያ ላይ ለተፈጸመው አሰቃቂ ግፍና የጦር ወንጀል፤ በሙሶሊኒና በፖፕ ፓየስ 11ኛ መሀል ስለ ነበረው የጠበቀ ግንኙነትና ሕብረት፤ ብዙ አስተማማኝ ማስረጃ በማቅረብ ግንዛቤያችንን ስላጠናከረልን፤ ደራሲውን ዴሽነርን አመሠግናለሁ። ስለዚህ ጉዳይ፤ ተቃራኒውን በመጻፍ የማያስፈልግ ውዥንብር የፈጠሩ ጸሐፊዎችም፤ በተለይ ኢትዮጵያውያን፤ ተገቢውን እርምት በማከናወን ለውድ ሐገራችን ለኢትዮጵያ የሚገባትን ፍትሕና ክብር ለማስገኘት እንዲተባበሩ በዚህ አጋጣሚ አደራ እላለሁ።
በተጨማሪም፤ ዓለም-አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ – የኢትዮጵያ ጉዳይ (Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause) የተሰኘው ድርጅት በኢትዮጵያ ለደረሰው የፋሺሽት ግፍ ተገቢው ፍትሕ እንዲገኝ ለሚከተሉት ዓላማዎች እየጣረ ነው፤

(ሀ) ቫቲካን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ፤
(ለ) የኢጣልያ መንግሥት ተገቢውን ካሣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲከፍል፤
(ሐ) ቫቲካንና የኢጣልያ መንግሥት ከኢትዮጵያ የተዘረፉትን ንብረቶች እንዲመልሱ፤
(መ) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፤የፋሺሽቱን ጦር ወንጀል በመዝገቡ እንዲያውል፤ እና
(ሠ) በቅርቡ፤ የቫቲካን ተወካይ በተገኙበት፤ አፊሌ (ኢጣልያ) ለፋሺሽቱ ወንጀለኛ የተመረቀው ኃውልት
እንዲወገድ።

ባሁኑ ጊዜ፤ ከላይ የተጠቀሰው ድርጅትና ደጋፊዎቹ በመተባበር፤ የዚህ ዓመት የካቲት 12 የሰማእታት ቀን በዓለም ዙሪያ በ30 ከተሞች እንዲከበር ጥረት እየተደረገ ነው።
ለበለጠ ዝርዝር የድርጅቱን ድረገጽ፤ www.globalallianceforethiopia.org መመልከት ይቻላል። በዚያውም፤ ኢጣልያኖች ጭምር የፈረሙት አንድ ዓለም-አቀፍ አቤቱታ ስለሚገኝ አንባቢዎች በፊርማችሁ ድጋፋችሁን እንድትገልጹ በትሕትና ተጋብዛችኋል።

ለኢትዮጵያ ክብርና ፍትሕ እንታገል!

ባረጀ ባፈጀ የጭቆና መሳሪያ የግፍ ስረአትን ጠጋግኖ ለማቆየት አይቻልም ሸንጎ

በብአዴን ማን ይወክላል? (ከጉራማይሌ ፖለቲካ ክፍል 2) –ተመስገን ደሳለኝ

$
0
0

በዘመነ ኢህአዴግ ከታሪክ ተጠያቂነት በፍፁም ሊያመልጡ ከማይችሉ የፖለቲካ ድርጅቶች መካከል ብአዴን እና ኦህዴድ በግንባር ቀደምትነት ይሰለፋሉ፡፡ ሁለቱም ‹እንወክለዋለን› በሚሉት ሕዝብ ላይ ተደጋጋሚ ክህደት ለመፈፀማቸው፣ ደርዘን ያለፉ ድርሳናትን ማዘጋጀት እንደሚቻል እናውቃለን፡፡ አልፎ ተርፎም ህወሓትን ከመሰለ የማፍያ ቡድን ጋር ግንባር ፈጥረው ‹‹ወከልነው›› የሚሉትን የማህብረሰብ ክፍል ህልውና ማድቀቃቸው እውነት ነው፡፡ በርግጥ ምንም እንኳ የሀገር አንድነትን አደጋ ላይ የጣለ ከፋፋይ ፖለቲካን ጨምሮ ሕዝብ እና ትውልድ የሚሉ ነገሮችን ቅርጫት ውስጥ የመጣል አባዜ ቢጠናወተውም፣ ህወሓት ከቅጥረኞቹ ይልቅ የራሱ የሆነ የፖለቲካ ቁመና እና መሬት የወረደ አጀንዳ ይዞ የተነሳ መሆኑ የማይካድ እውነታ ነው፡፡

በዚህ ቁጣ እንድናገር ያደረገኝ ሰሞነኛ ምክንያት ከአንድ የብአዴን ከፍተኛ ካድሬ ነውረኛነት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ይህ ሰው የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አለምነው መኮንን ሲሆን፣ ኢህአዴግን የተቀላቀለው በተወለደበት ሰሜን ወሎ በ1982 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ነበር፡፡ ከመንግስት ለውጥ በኋላም ረዝም ላለ ጊዜ በዛው በሰሜን ወሎ ከገዱ አንዳርጋቸው ጋር በኢህዴን /ብአዴን/ ተጠሪነት ሰርቷል፤ ከሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ የመጀመሪያ ዲግሪውን ማግኘቱን ተከትሎም በክልሉ አስተዳደር ስር ባለው በምፃረ ቃል ‹‹SRAR›› ተብሎ በሚጠራው (በእርሻና መልሶ ማቋቋም ላይ በሚያተኩር) ተቋም በአንድ ክፍል ኃላፊነት አገልግሏል፡፡ በምርጫ 97 ዋዜማ ደግሞ የክልሉ የማስታወቂያ ቢሮ ኃላፊ እንደነበር ይታወሳል፤ ቀጥሎም የአማራ ዲዛይንና ቁጥጥር ስራ አስኪያጅ ሆኖ ሰርቷል፤ ከ2004 ዓ.ም
መጨረሻ ጀምሮ ደግሞ የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የብአዴን ቢሮ ኃላፊ ነው (በነገራችን ላይ በአማራ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንቶች ሶስት ናቸው፤ ከአለምነው በተጨማሪ ብናልፍ አንዱአለም እና ዶ/ር አምባቸው የተባሉ ተሿሚዎችም አሉ) የሆነው ሆኖ ይህ ሰው ባለፈው ሳምንት በባህር ዳር በተዘጋጀ አንድ ስብሰባ ላይ የተናገረውን አስነዋሪ ነገር፣ ረዥም ዕድሜ ለኢሳት ይሁንና ጭው ባለ ድንጋጤ ተውጬ አድምጬዋለሁ፤ ግና ተሳዳቢው የክልሉ አስተዳዳሪ ይሆናል ብዬ አላሰብኩም ነበር፤ የንግግሩ ይዘት ከሞላ ጎደል እንደሚከተለው ይጠቃለላል፡-

‹‹….የአማራው ህዝብ በቅድሚያ እንዳይሰደድ ለማድረግ ስራ እየተሰራ ነው፣ ነገር ግን ከተሰደደ በሁዋላም ቢሆንም ሰንፋጭ የሆነውን ትምክህተኝነቱን በመተው፣ ከሌላው ጋር መኖርን መልመድ አለበት፡፡ …የአማራው ህዝብ ሰንፋጭ የሆነ ትምክህተኝነት የተጠናወተው በመሆኑ፣ በቤንሻንጉልና በሌሎችም ቦታዎች ለመሰደድ ምክንያት ሆኖታል። ….በባዶ እግሩ እየሄደ የሚናገረው ንግግር ግን መርዝ ነው። ይሄ መርዝ ንግግሩ አንድ የሚያደርግ አይደለም፡፡ …ከኢትዮጵያውያን ጋር አብሮ ለመኖር አማራው የትምክህት ለሃጩን ማራገፍ አለበት። ይሄ ለሃጭ ሳይራገፍ በጋራ መኖር አይቻልም። …ማንኛውም ስም ያወጣ ሙትቻ ፓርቲ ሁሉ መንገሻው አማራ ክልል ነው። ትምክህትን እንደ ምግብ ስለሚመገበው ነው። ያንን ምግብ እየተመገበ ያቅራራል።››

በእውነቱ ይህንን የተናገረው ፋሽስቱ ዱቼ ሞሶሎኒ አሊያም ሶማሊያዊው መሀመድ ዜያድባሬ ቢሆን ኖሮ፣ ቅኝ-ግዛት ያማለለው የፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ አድርጎ ማለፍ ይቻል ነበር፤ ግን የዚህ ልብ ሰባሪ ቃላት ባለቤት የክልሉ አስተዳደሪ አለምነው መኮንን ነው፡፡ ዳሩ እርሱስ ቢሆን ማንን እየሰማ አደገና ነው! ምክንያቱም የቀደሙት የብአዴን ሰዎች የወከሉትን ዘውግ ሲረግሙና ሲያንቋሽሹ መታዘባችን የትላንት ክስተት ነው፡፡ የታምራት ላይኔን ‹ሽርጣም ሲልህ የኖረውን ይሄን ነፍጠኛ አሁን ጊዜው ያንተ ነውና በለው› የሚለውን ሐረር ላይ የተሰማ እልቅቲ ነጋሪ አዋጅ ጨምሮ፤ የተፈራ ዋልዋ ‹አማራው በባዶ እግሩ እየሄደ፣ ስንዴ በሩ ላይ አስጥቶ በባዶ ሆዱ የሚፉልል ትምክህተኛ ነው› እስከሚለው ድረስ ያሉ በአደባባይ የተሰሙ ስድቦችን መጥቀስ ይቻላል፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ምሳሌ ለማድረግ፣ እዚህ ሳምንት ድረስ በሬዲዮ ፋና እየተተረከ ያለ አንድ የጥላቻና ዘረኝነት አቀንቃኝ የሆነ መፅሀፍን ልጠቀስ (በነገራችን ላይ እንዲህ አይነቱን ለእርስ በእርስ ግጭት መነሾ የሚሆን፣ በክፋት፣ በተንኮል፣ በክበረ-ነክ ጭብጥ የተሞላን መፅሀፍ ርዕስ እዚህ ጋ ማንሳቱ አስፈላጊ ነው ብዬ አላምንምና አልፈዋለሁ)፡፡ ይህንን መፅሀፍ ደረሲው ዳንኤል ግዛው በእንግሊዘኛ ቋንቋ ያዘጋጀው ሲሆን፣ ወደ አማርኛ የመለሰው የብአዴን ታጋይና የበረከት ስምኦን ባለቤት ወንድም የሆነው መዝሙር ፈንቴ ነው፡፡

በርግጥ በምስጋና ገፁ ላይ እንደተጠቀሰው፣ እንዲተረጉመው ያዘዘውና መፀሀፉን የሰጠው ለአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ነፃነትና ክብር በዱር-በገደል ታግያለሁ የሚለን ራሱ በረከት ስሞኦን ነው፤ ውለታውንም እንዲህ ሲል ገልፆለታል፡-

‹‹…የምተረጉማቸውን እያንዳንዳቸውን ገፆች ከስር ከስር እየተከታተለ ያነባቸውና ያበረታታኝ ነበር፡፡ ያስጀመረኝ እሱ፣ ያስጨረሰኝም እሱ ነበርና ለአቶ በረከት ስምኦን ያለኝ ምስጋና እጅግ ከፍ ያለ ነው፡፡››

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝም ‹‹አስተማሪ፣ አስገራሚና መሳጭ›› ሲል በፃፈው የጀርባ ገፅ አስተያየት፤ ይህንን እንቶ ፈንቶ እና አንድ ብሔርን ለይቶ የሚያጠቃ ውጉዝ ድርሳን ከፍቅር እስከ መቃብር ጋር በአቻነት አስከማስመሰል ታብዮአል፡፡ ህላዊ ዮሴፍም ረቂቁን በማንበብና በማረም ከፍተኛ አስተዋፆ እንዳደረገ ተርጓሚው ተናግሯል፤ በአናቱም መዝሙር ፈንቴ መፅሀፉን ከመተርጎሙ በፊት በ‹‹ደርባ ሚድሮክ ሲሚንቶ›› ፋብሪካ ውጪው ተሸፍኖለት (የማሳተሚያ ዋጋውንም የቻለው ሼክ መሀመድ አላሙዲ ነው) አደረኩት በሚለው ጉዞ፣ አማራ ረግጦ፣ ቀጥቅጦ፣ ከሰው በታች ዝቅ አድርጎ፣ መሬታቸውን በመንጠቅ አሽከር አድረጎ… እንደገዛቸው የተተረከላቸው የማንጃ እና ማኛ ብሔረሰብ አባላት ወደ ሚገኙበት ደቡብ ኢትዮጵያ ሄዶ ሰፊ ጥናትና ምርምር ማድረጉን ከነገረን አኳያ (የእንግሊዘኛውን ቅጂ ማግኘት አልቻልኩም) መፀሀፉ ቃል በቃል የተተረጎመ ነው ብሎ መቀበሉ ይቸግራል፡፡ ራሱም ቢሆን የፃሀፊው ተደራሲያኖች አሜሪካውያን መሆናቸውን ጠቅሶ ‹‹አቀራረቡን ኢትዮጵያዊ ለማድረግ ብዙ ጥረት አድርጌያለሁ›› ማለቱን ስናስተውል ከተርጓሚነትም ወሰን ተሻግሮ ተጉዟል ብለን እንድናምን ከመገፋታችንም በላይ፣ እነበረከት ስምኦን በአማራው ላይ ያላቸውን ያደረ ጥላቻ ለማንፀባረቅ የተጠቀሙበት ሊሆን ይችላል ብለን ለመጠርጠር እንገደዳለን፡፡

እንግዲህ ብአዴን ማለት፣ ከጉምቱ መሪዎቹ ጀምሮ የክልሉን ነዋሪ ‹‹ቀጣይ ነፃ አውጪያችሁ ነኝ›› የሚለውን ነውረኛውን አለምነው መኮንን ጨምሮ፣ ይህን መሰል በተዋረደ ስብዕና የሚበየኑ ምስኪን ፍጥረቶች የተሰባሰቡበት ድርጅት ነው፡፡ መሰረታዊው ጥያቄ ታዲያ፤ ለዚህ ሁሉ ሰቅጣጭ ሁኔታ፣ የክልሉ ነዋሪ የሆነው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ዝምታ ምን ድረስ ይሆን? የሚለው ይመስለኛል፡፡

Viewing all 1809 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>