Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all articles
Browse latest Browse all 1809

ኢትዮጵያውያን”ዲያስፖራዎች”ሆይ!!! ቢጫውን መተት፣በደም-ድግምት ተቋጥሮ፤ በዐይኔ፣በብሌኗ: አየሁት። አቢይ ኢትዮጵያዊ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ

$
0
0

“ድግምት” ሲባል እየትደገመ ዐዚምን ለማድረግ:-በሐረጎች የሚገለጥ፣በቃላት የሚበላ፣በፊደላት የሚቋጠር፣በሰዋስው የሚታኘክ፣የሚዋጥ፣የሚሰለቀጥ፣ተመልሶም የሚተፋ፤ሲበዛም በማስታወክ የሚፈፀም ወደትፋቱ የሚያስመልስ ርኩስ ተግባር ነው፤ግብሩም ዐዘመ ይባላል።

ዐዚምን በሰው ላይ የሚያደርጉ ሰዎች እንደድንገት በአንድ ሰበብ ይጀምሩትና ለመተዳደሪያቸው ሲቀጥሉበት እንደጀመሩት ግን በቀላሉ አይላቀቁትም።እንደውም ቋሚ የገቢ ምንጫቸው እንዲሆንላቸው ሲሉ የማይቻላቸውን የሞት ቁማር ለመጀመር በግድ ሞትን ሲያስጎነጩ በመጨረሻው ሰዓታት መራራዋን ሞት ራሳቸው ድንገት በክፉ መናፍስት ተገደው ይጎነጯታል።ለእኛ የሰው ልጆች ሞት የማይቀር ዕዳችን ቢሆንም የ”ኅጢያት ድሞዝ ሞት ነውና”እንደየግፋችን አፈጻጸም እና እንደየክፍያችንም ዓይነት በምሬቱ ይለያያሉ። ይህም ልዩነት በግልጽ በአሟሟታችን(ሬሳ አሸኛኘቱ ሳይሆን)ሁኔታ ይታያል።ለዚህም ነው ኑሯችን የተጎሳቆለ ቢሆንም በማይቀረው ሞት ፊት እንኳ “እባክህ ጌታዬ አሟሟቴን አሳምርልኝ::” የሚባለው።ብታምኑም ባታምኑም በሕይወት ያለነውን እነዚያ የሞቱት ግፈኞች ዘመዶቻችን ሞተውም በቁማችን እየፈለጉን:-በመጀመሪያ ጣረ መናፍስት ሆነው በሚያገኙት አጋጣሚ ተሻምተው፣በሕይወት ያለነውን ሊገድሉን ያሳድዱናል።ይህ የፈረንጅ ልብ ወለድ አይደለም፤ባጋጣሚ ታውቋቸው የነበሩትንና ዛሬ በሕይወት የሌሉትን ሰዎች እስኪ ለአንድ አፍታ አስታውሷቸው።በነገራችን ላይ ስለሞት በጥልቀት ለማወቅ መንፈሳዊም ሆነ ሥጋዊ ዕውቀት የነበራቸውን የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እና እንግሊዞች አግበስብሰው የወሰዱትን የደብተራ ዘነብ ኢትዮጵያዊ(ብርቲሽ ሙዚየም ዩኬ)መጽሐፍትን ማንበቡ ይረዳል።ይህ ክስተት በያንዳንዱ የግፈኛ ቤት ያለ የደም ዕዳ ታሪክ ነው።ለዚህ በምሳሌነት የሚወሱት እስራኤላውያን ናቸው፤የማይደርስ መስሏቸው “እኔ ይሄ ሰው ጥፋተኛ ሆኖ አላገኘሁበትም”ብሎ ጲላጦስ ከደሙ ንጹህ ነኝ ብሎ እጁን ሲታጠብ”እኛ ላይ እስከዘር ምንዘራችን ይተላለፍብን”ያሉት ቃል ዛሬም ድረስ እንዳስለቀሳቸውና በዓለም ላይ የቁም-ሞት እየኖሩ ይገኛሉ።

ወደ ተነሳንበት ዋና ጉዳይ ስንመጣ፣የኛዎቹ የዘመኑ ገዥዎች እረ በቅድስቲቱ የተባረከች አገራችን:-<< በኢትዮጵያ ሕዝቦች መካከል ዕርቅ ያስፈልጋል፤ካለፉት ሁለት የወደቁ መንግሥታት ታሪክ እንማር፣በቃችሁ ይበለን፤ >>ሲባሉ ማንና ማን ተጣላና፣ዕርቅ በኛ መቃብር ላይ፣እስከመጨረሻው እንጋደላለን እንጂ፤ዕርቅ አይታሰብም ብለዋል።መዘዙ ለዘር ማንዘራችን ይተላለፍ እንጂ አናደርገውም:- ሲሉ በአሁኑ ያለው ትውልድ ከገዥው ቡድን ከሰማ ሃያ አምስት አመታት አስቆጠርን።እኛ በውጭ አገር ተበታትነን የምንኖር ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች በጥንቃቄ እንመልከት።የወያኔ ቡድን ወይም ጉጅሌው ፈረንጆቹ ላይ የሚያደርገውን የሃያ አምስት አመታት ማጭበርበር ልምድ ድርጊት በግልፅ አናውቀውምን???? ድርጊቱ የማጭበርበር መሆኑ የተረጋገጠው ጉጅሌው ለግልጽ ውይይት ፈቃደኛ አለመሆኑ እና “በጉልበት ያሸነፈኝ ይቀማኝ”ብቻ የማለቱ ውሳኔ ከሕዝብ ጋር መለያየቱን እና በጣም መራራቁን አረጋግጧል።የሚያሳዝነው:-”ከሰደበኝ የነገረኝ አሳመመኝ”ሆነና የኢትዮጵያውያን ነገር:- የእነሱ እና የእኛ ተብሎ ተከፈለ፤ዕውነቱ ግን የሁላችንም የኢትዮጵያውያን መሆኑ የማይታበል ሐቅ ነው።ለዚህም ነው ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች በጉልበት ያለውን በመንቀፍበ፤ሕግ እና በፍትህ የሚለውን ወገን በመደገፍ፤ለዕውነት እና ለግልፅነት መቆም ያለብን።

ከዚህ አንፃር የራሳችንን ጥቅም ካላስቀደምን፤እጅግ አሳፋሪ አስተዋፅዖ ማድረጋችንን በደምብ እንረዳለን።እስኪ ራሳችንን እንመርምር፣በሚሊዮኖች የምንቆጠር በተለያዩ ምክንያቶች ወጥተን:-ቢያንስ በነጻነት ስለአገራችን ለመምከር የሚያስችል የመናገር እና የመወያየት ነጻነት አለን።የየራሳችን አኗኗር ይኑረን እንጂ አብዛኝዎቻችን ግን የሩጫ ኑሮ እንግፋለን።በጣም ጥቂቶች ብቻ ናቸው የተደላደል ኑሮ የሚኖሩት፤እናም ይህ ሩጫችን ተራ በተራ ስንሰበርና ሬሳ ተብለን በመዋጮ እስክንቆጠር ድረስ ነው:-እናም አያበቃምሳ?ይህን የቁም ሞት ቁስላችንን መሸፋፈን አለብን ወይስ በጋራ ከፍተነው ተወያይተን በሰለጠነ አዕምሮ ማከም አለብን???…ተራራቅንና አቅመቢስ ሆንን እንጂ፤ብንቀራረብ ከመውደቃችን በፊት ክንዳችንን ምን ያህል ኢትዮጵያዊ ጠንካራ የማይበገር እንደሆነ ማሳየት እንችላለን።ትልቁ እና አቢይ ቁምነገሩ ጭምብል አድርገው እኛ ይህን መልካም ነገር ተገንዝበን ለማድረግ ስንቀሳቀስ:-እጃቸውን አጣጥፈው የማይቀመጡ፣የጥቅም ተገዥዎች መኖራቸውን ለአፍታም ሆነ ለሰከንድም ቢሆን አለመዘንጋት ነው።

የመጣንበትን የታሪክ ጎዳና አድቅቀን በተጨባጭ እንመልከተው እስኪ።አሁን ባለው መንግሥት ተፈናቀሉ!!!!ታሰሩ!!!!ተረሸኑ!!!!ተገደሉ!!!!ኡ!!!ኡ!!!!ኡ!!!ሲባል፤አልፎ ተርፎም በሌሎች አገሮች፣በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችሟ እና የመንግስታት ያልሆኑ ድርጅቶች፣በተንቀሳቃሽ ምስል አስደግፈው እያሳዩን፤እየተነገረን፤እየታወቀን፤በዝምታ ፈዘን በምን አለብኝነት እናያለን።ምንም እንዳልተፈጸመ:-ምንም ላለማድረግ ሕሊናችንን በግል ጥቅም ቆልፈን፣በምን አገባኝ ሐጢያት ተቋጥረናል።እኔ ከመጀመሪያው የስደት ዘመኔ ጀምሮ ለሦስት የሰላማዊ ሰልፎች ግዜ ወጥቼ እንደ አገር ቤቱ የድጋፍም ሆነ የተቃውሞ ሰልፍ የራሴ መፈክር፣የራሴ ጥሩምባ፣የራሴ አለባበስ ከሰንደቅ ዓላማዬ ጋር ውሃና የብርድ መከላከያዎቼን ይዤ በነፃነት ያለፍርሃት በፓርላማው አካባቢ ተገኘሁ።በዚያን ጊዜ ያየሁት ሁኔታ ተስፋ አስቆራጭ ከመሆኑም በላይ እኔን እያጮለቁ የሚያዩኝ መብዛት ከቁጥራችን አናሳነት ጋር ተደምሮ ጥያቄዎችን በልቦናዬ ውስጥ አሳዝሎኝ መገኘቱንም ተውኩት፤እርግጥ አልፎ አልፎ በቤተክርስቲያን ጉዳይ፣በገዳማት መበተን በጅምላ ግድያም ሆነ በእስር ተቃውሞ ላይ አልቀረሁም።ይሁንና አልተዋጠልኝም:-ከዚህ ከ72,250 በለንደን ከተማ ብቻ የሚኖርባት ኢትዮጵያውያን:-ከዚህ ውስጥ ጉጅሌን ደጋፊ 3324 ባለኢንቨስተር1897 ባንዳ 2340 ቅጥር ነፍሰ ገዳይ 1097 ሕጻናት 5076 በፈረቃ ሥራ ምክንያ ት ሊገኙ የማይችሉ 3220 ሕመምተኞች 2454 ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት 1750 = 20158 ከወጪ ቀሪ 51092 ሰዎች በሦስት መደብ ተከፍለው በየፈረቃቸው 17030 በየትኛውም ሰልፍ ላይ (በሚንከባለል ስሌት) በትክክል መገኘት ይኖርባቸው ነበር።አሁን ባለው ተጨባጭ መረጃ ግን በአገር ጉዳይ ላይ የሚገኙት ብዛት 100-500 ሰዎች ብቻ ናቸው።መሆን ግን አለበት???…በፍጹም የለበትም!አልነበረበትም !!!…… በዚህም መሠረት ሌላ ዓይነት ስሌት መከተል አለብን፤ይኸውም ቢጫውን የተመተተ ደብተር የያዙ ሰዎች ከፓስፖርታቸው ጋር በተጨማሪ የሚጠቀሙበት ነው።በዚህም ሁኔታ ዐዚም አዙረውባቸዋልና ሒሳባችንን ያዛንፈዋል።ለመሆኑ ስንቶቻችን ነን ፓውንዶችም ሆኑ ዶላሮች አሊያም የኛይቱ ብር እንኳ ሳትቀር በዐይን የማይታይ የሚሥጥር ምልክት እንዳላቸው የምናውቅ???…በአንጻሩም በእርኩስ መንፈስ የሚያምኑ ደግሞ ርኩስ ነገር ላለማድረግ ምን ይከለክላችቸዋል???መልሱን ለአንባብያን ትቼዋለሁ።

“ዝ-ሆነ ሆይኑ” አሉ ኣቦይ ጛጕ:- በትግርኛ የሆነው ሆነና ወደ ሆነው ነገር ልመልሳችሁ።ይህንንም ሁኔታ ለማጣራት ምክንያት እና ሰበቡን በጥልቀት ሳጠና ድንገት እግዚኣብሔር ሲያድለኝ ቢጫውን መተት በደም ድግምት ተቋጥሮ በባለ አምስት ኮከብ ቅርጽ የጦር ስግስግ ማህተም ተለብጦበት አየሁ።በስደት በነጻነት አገር እየኖርን አንድቀንም እንኳ ከሰባ ሁለት ሺህ ሕዝብ መካከል ቢያንስ በሺህ የሚቆጠሩ የድጋፍም ሆነ የተቃዋሚ ሰልፈኞች አግኝተን አናውቅም::ዕውነት የለንም ማለት ነው???…ጉጅሌ ነው ትክክል???በፍጹም አይደለም።ጉጅሌ:-ገዳይ፤አጭበርባሪ፤ውሸታም፤አታላይ፤አወናባጅ፤ዘራፊ፤ዘረኛ፤ደደብ፤መሆኑን ራሳቸው የጉጅሌው አባላት በግልጽ ይመሰክራሉ።ታዲያ ለምንድነው ጒደኛዬ “ሰለሞን በቀለ”የጉጅሌ ቡድንን ነቅፎ እና መልሶ የሚደግፈው?ወይም ምንም የማይቃወምበት?ምክንያት ሊገባኝ አልቻለም ነበር።አሁንማ በሚገባ አወቅኩት።ለዚህም ጥናቴ የረዳኝ የወዳጅ ጠላቴ ጒደኛዬ ሁኔታ ነው።በጣም ርቄው ሳይሆን ቀርቤው፣ተጠግቼውና መርምሬው አየሁት።እዚያ የተቀመጠውን በልጃ ስክፍተው ለብቻው የተቀመጠ ቢጫ መታወቂያ ደብተር አየሁ።ይህ ደብተር የጒደኛዬን ሙሉ ሥም፣ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን አድራሻ፣መቼ እነደተዘጋጀና መቼ አገልግሎቱ እንደሚያበቃ፤የት እንደተዘጋጀ ይገልጻል።የሚገርመው ከመጨረሻው ላይ ያለው ባዶ ገፅ ነው።ከኮከብ ማህተብ በስተቀር ሌላ ሲታይ በፍጹም አንድም ነገር የሌለበት ነው። ምንም የሚነበብ የለውም፤ሚሥጥሩም እሱ ላይ ነው።የማይነበብ ጽሁፍ ያለበት ባዶው ገፅ በስውር ነባቢት እንዲህ የሚል ባለሁለት አንቀጾችን ይዟል፥

“ይህ ግለሰብ ልዩ የኮከባችን አባል ነው።ወዳጆቻችን የሆናችሁ ሁሉ፣በፎቶግራፉ ላይ የምትመለከቱት ግለሰብ ወደኢትዮጵያ ገብቶ የፈለገውን ለማድረግ ይችላል።መሬት ለመግዛት ወይም ለመሸጥ፣የግል ንግዱን ለማስፈጸም ለመለውጥ ወይም ለመለገስ፣የፈለገውን ንብረት ይዞ ለመግባትም ሆነ ይዞ ለመውጣት፣በፈልገውም ጊዜ ለመመላለስ ሙሉ ቡሙሉ ተፈቅዶለታል።ይህን መረጃ ማገድም ሆነ መከልከል አሊያም መሰረዝ የሚችለው በየአህጉራቱ ባሉት ኤምባሲዎች የተደራጁ አካላት ብቻ ናቸው።ማሕተም ባለ አምሥት ኮከብ ማዕዘናት ቅርፅ፣የጦር ዘንግ የተሰገሰገበት፤ፊርማ የማይነበብ።”ይላል።

በእርግጥ ስለቢጫው የፓስፖርት ደብተር ስነግራት ወዲያው “አውቀዋለው!” አልችኝና “ብዙ ሰዎች’ኮ አላቸው:-” አለችኝ።”የኢሕአድግ የሚሥጥር አባልነት መታወቂያ” ተብሎ በደም የተጻፈውን’ስ አንበሺዋል???ብዬ ደግሜ ጠየቅኳት።በፍጹም አልተጻፈም አለችኝ።እንግዲያውስ አርባ አምስት ድግሪ ዘቅዝቀሽ በሰያፍ ወደላይ አድርጊና ተመልከቺው፣ኮከቡ መሓል በደቃቅ ተጽፚል አልኳት።እስኪ ቤት ስገባ የማውቃትን ልጅ ደብተር ጠይቄ እመረምረዋለሁ አለችኝ።እኔም ምን መመርመር ያስፈልጋል:- የራሷ ተግባር ይናገር የለም፣እስኪ ተመልከቻት አገር ቤት ትመላለሳለች?ወያኔ ገደለ፣አሰረ፣ረሸነ፣ገነጠለ፣ሲባል ግድ ይሰጣታል????…ፍጹም::እናም ከዚህ የበለጠ ድግምት እንዴት ሊኖር ይችላል።አዎ አለችኝ።አየሽ አፈር ድሜ ግጣ፤ጽዳትም ሆነ ሸክም ሥራ ሠርታ፤አገር ቤት ነው።አዎ አገር ቤት ይናፍቃል፤ዳሩግን እንዳትዘነጋ ድሮ ትዝ ይልሃል??አቶ ከበደ መኮንን ሲናገሩ:-”ደሞዝ ተቀብዬ ሩጥ የሚለኝ እንትናሆቴል፣ቤትና ጠጅ ቤት ነው” ሲሉ።የዛሬውን የጉጅሌን ርኩስ ካርድ ከእነሱ በምን ይለየዋል???በምንም።የተደገመብትን ቢጫ የዓለም አቀፍ ሕገወጥ መታወቂያ ጉዳይ ለጓደኛዬ አስረድቻት ግደየለም ቀዳደሽ ጣይው ብያት:-አደርገችውም፤ቢያንስ የሞራል ግዴታዋን ተወጣች።በድብቅ አገር ቤት ለመሄድ ብላ ሰልፍ አልወጣም የሚለውን አቁማ በድፍረት:-አዎ “አስራ ሥምንት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ሕዝብ መራቡን ላለማሳወቅ ረሃባችንን በመደበቅ:-” “ዕድገት ሞልቷልii” በማለት አንዋሽም:-በማለት በጋራ ድምጻችንን ስናሰማዋለን።ለመሆኑ ስንቶቻችን ነን “ቢጫው የመተት መታወቂያ” እንዳለን ያለሕፍረት የምንናገር???…እኛዎቹ ዕውነተኛ የሕዝብ ልጆች ነን።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 1809

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>