Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all articles
Browse latest Browse all 1809

በመቱ ዞን የአንድነት ፓርቲ የድ/ጉዳይ ኃላፊ 2 ዓመት ተፈረደባቸው

$
0
0

በኦሮሚያ ክልል መቱ ዞን የአንድነት ፓርቲ የድ/ጉ/ኃላፊ የሆኑት አቶ ታመነ መንገሻ ጳጉሜ 4 ቀን ታስረው እንደነበረና ጳጉሜ 5 ቀን 2006 ዓ.ም በዋስ እንደተለቀቁ በመለቃቸውም በአካባቢው ያሉ የመንግስት ካድሬዎች ለምን ተለቀቁ መታሰር አለባቸው በማለታቸው በድጋሚ መታሰራቸውን ፍኖተ ነፃነት መዘገቧ አይዘነጋም፡፡ አቶ ታመነ መንገሻ የታሰሩት አማራ ይውጣ ብለሃል በሚል ሰበብ እንደሆነ ይህን ተናገሩ በተባለበት ወቅትም ታመው አልጋ ላይ እንደነበሩ፣ ፖሊስ በሳቸው ላይ እንዲመሰክር በፖሊስ ጣቢያ ለምስክርነት ያቀረበው ግለሰብም እሳቸው ሁልጊዜ ሲናገሩ የምሰማው “ዓላማችን መለያየት ሳይሆን ኢትዮጵያዊነት እንዲቀጥል ነው” ብለው በማለታቸው መስካሪውም እንዲታሰሩ ተደርገው በዋስ ተለቀዋል፡፡ አማራ ይውጣ ብለሃል በተባሉበት ቀን ታመው በህክምና ላይ እንደነበሩ በህክምና ማስረጃ ፍርድ ቤት ቀርበው ቢረጋገጥም መስከረም 21 ቀን 2007 ዓ.ም በዋለው ችሎት ፖሊስ ሀሰተኛ ምስክሮች አስመስክሮ 2 ዓመት እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ፈርዶባቸዋል፡፡10646903_531661860302107_777911837412960542_n


Viewing all articles
Browse latest Browse all 1809

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>