Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all 1809 articles
Browse latest View live

ተልእኮና የፋሲል የኔአለም ጫፍ የቆመ እይታ –የአንድነት አመራር አቶ ዳንኤል ተፈራ

$
0
0

አንድነት ፓርቲ በተሳካ ሁኔታ ጠቅላላ ጉባኤውን ፈጽሞ በበርካታ ወጣቶች የተገነባውን ካቢኔ ይፋ ካደረገ ጥቂት ሳምንታት አለፉ፡፡ በነዚህ ጥቂት ቀናትም የምንታገልለትን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን ለማድረግ ቀን ከሌሊት መስራት ይገባል የሚል እቅድ አንግቦ ደፋ ቀና በማለት ላይ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለን ግን፣ የግል አስተያየት በማለት የኢሳቱ ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም «የአንድነት ፓርቲ የመጭው ጊዜ ፈተና» በሚል የፃፈዉን ያልታሰበበት ጽሁፍ አነበብኩ፡፡

በቅድሚያ ለጽሁፉ ለምን መልስ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ እንዳገኘሁት መግለጽ ይገባኛል፡፡ ፋሲል ማስተላለፍ የፈለገው «አንድ ጫፍ ብቻ» የረገጠ መልእክት የተዛነፉ ሃሳቦች የተላለፈበት፣ ከግለሰብ ጥላቻ በመነሳት ፓርቲውን ፈተና ውስጥ፣ ያለ በማስመሰልና ዋጋ እየከፈሉ ያሉትን ውድ አባሎቻችንን በግብአትነት በመጠቀም ክፍፍል ለመፍጠር የፈለገ በመሆኑ ነው፡፡ ወይም ፀሀፊው «ሁለት የከረሩ ጫፎች ብቻ ያስፈልጋሉ» ከሚል አይነት አመለካከት ላይ ቆሞ ከመፃፍ የመነጨ ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያቴ፣ በአምባገነኑ ስርዓት ተጠፍንገው ከተያዙ የብሮድካስት ሚዲያዎች ውጭ፣ አማራጭ አልባ ለሆነው ህዝብ በአማራጭነት ለቀረበው ኢሳት፣ ካለኝ አክብሮት ነው፡፡ ምክንያቱም ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም የኢሳት ባልደረባ እና ኃላፊነት የያለበት ሰው በመሆኑ፡፡

ፋሲል በጠቅላላ ጉባኤው በከፍተኛ ድምጽ የአንድነት ፓርቲ ፕሬዚደንት ሆነው የተመረጡት ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው ከሪፖተር ጋር ቃለ-ምልልስ ካደረጉት ውስጥ «ከኢህአዴግ ጋር ገንቢ ግንኙነት (Contractive engagement) እንዲኖረን እፈልጋለሁ. . .» የሚለው ለሱ ሃሳብ የሚመቸውን ቆንጥሮ በማውጣት ከልደቱ አያሌው «ሦስተኛ መንገድ» ካለው ወይም «መሀል ላይ መቆም» ብሎ ከተረጎመው ሃሳብ ጋር ለማያያዝ ሞክሯል፡፡ ስህተቱ እዚህ ላይ ይጀምራል፡፡ አንድነት በሊበራል አስተሳሰብ የሚያራምድ በመሆኑ የግለሰቦች መብት በቅድሚያ መረጋገጥ አለበት ብሎ ያምናል፤ በስትራቴጂው እንዳስቀመጠውም የኢህአዴግ አይነት የብሔር (የቡድን) መብትን ማክበር ወይም የዚህ ተቃራኒ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔርተኝነት ላይ ብቻ ቆሞ ሌሎችን አለማዳመጥ ዴሞክራሲያዊ አይደለም ይላል፡፡ ሁሉም ባልተሸራረፈ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ ያለምንም ጣልቃ ገብነት የመደራጀት መብታቸው መከበር አለት፡፡ ስለዚህ ጥያቄው ጫፍ የመቆም ሳይሆን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመፍጠር ነው፡፡

ስለዚህ አንድነት እንደ ሊበራል ፓርቲ ከገዢው ፓርቲ ጋር መደራደር ይገባዋል፡፡ መደራደር፣ ሰጥቶ መቀበል እንደነውር መታየት የለበትም ብሎ አስቀምጧል፡፡ ኢ/ር ግዛቸውም በቃለ ምልልሱ ያስቀመጡት ይህንን ነው መደራደር የፖለቲካ ፓርቲዎች አንዱ ሥራ ነው፡፡ መደራደር ዘመናዊ አስተሳሰብም ነው፡፡ አሁንም እየታገልን ያለው ያለው ችግራችንን በጠረጴዛ ዙሪያ እንፍታ፣ ሆደ ሰፊ እንሁን፣ ጠርዝ ከያዘና ከፍረጃ ፖለቲካ እንላቀቅ ማለት ነው፡፡ ጋዜጠኛ ፋሲል «መሀል ላይ መቆም» ያለው እንደዚህ አይነቱን ሃሳብ ነው እንጅ ራሱ ፀሀፊው አንድነትም ሆነ አመራሩ ተንበርክኮ እንዳልሆነ፣ እንደ አንድነት ዋጋ የከፈለና እየከፈለ ያለ ፓርቲ እንደሌለ የሚያውቅ ይመስለኛል፡፡

ጋዜጠኛ ፋሲል በተሳሳተ ዕይታ የኢ/ር ግዛቸውን ንግግር ቆንጥሮ «ፍርሃት ነው» ለማለት ይሞክራል፡፡ በውጭ ሀገር እየኖሩ መታገል፣ ትግሉን መደገፍ እንደሚችል አምናለሁ፡፡ ለፋሲል ግን አንድ ጥያቄ መጠየቅ እፈልጋለሁ፡፡ የሚፈራ ሰው መቀመጫው የት ነው? እንደሚመስለኝ ወይ የኢኮኖሚ ጥያቄ ካልሆነ በስተቀር ፀሀፊው ከሀገር የወጣው ሀገሩን ስለሚጠላ ሳይሆን ሥርዓቱን ስለፈራ ነው፡፡ ሥርዓቱን ፈርቶ በተሰደደ ሰውና ከሥርዓቱ ጋር ፊት ለፊት ግብግብ እየፈጠረ ያለ ሰው መካከል ትልቅ የሞራል ልዩነት አለ፡፡ ስለዚህ ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ፍርሃትን የተረጎመበት መንገድ ድንጋዩ ተመልሶ ወደ እርሱ እንዲያርፍ የሚያደርግ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ከሀገር ወጥቶ ትግሉን መደገፍ ትክክል ቢሆንም ፖለቲካውን ለመምራት መሞከርም ሌላ ትልቅ ስህተት ይሆናል፡፡ እንዲህ ሲባል እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ ለማምጣት የአቅማችንን እያደረግን ያለን ሰዎች መተቸት የለብንም ብዬ አላምንም፡፡ በመሳደበና በመተቸት መካከል ግን ትልቅ ልዩነት እንዳለ ሊሰመርበት ይገባል፡፡

ሌላው ማንሳት የምፈልገው ጋዜጠኛ ፋሲል የአንዱዓለምንና ናትናኤልን ስም በመጥቀስ ጫፍ ላይ የቆመ ሃሳብ የሚያራምዱ አድርጎ መግለፁም ስህተት ነው፡፡ አንዱዓለምም ሆነ ናትናኤል ፋሲል የጠቀሰውን አይነት ሃሳብ የሚያራምዱ አይደሉም፡፡ ሆነውም አያውቁም፡፡ በተለይም የአንዱዓለምን ሃሳብ ለመረዳት መጽሀፉን ማንበብ ተገቢ ነው፡፡ ወጣቱ ፖለቲከኛ በሆደ ሠፊነት «ኧረ የመቻቻል ያለህ፣ ኧረ የድርድር ያለህ፣ ኧረ የመደማመጥ ያለህ . . .» በማለት አንድ ጫፍ ላይ ቆሞ ማክረር እንደማይጠቅም ገልጿል፡፡ ለአዲሱ አመራርም እውቅናና ድጋፍ ሰጥቷል፣ ደስተኛም ነው፡፡ ይሄን የምለው አንዱዓለም ለገና በዓል በአካል አግኝቼ ሃሳቡን የማዳመጥ እድል ስለገጠመኝ ነው፡፡

በመጨረሻ ግን ስለ ኢሳት ማንሳት እፈልጋለሁ፡፡ ኢሳት ለኢትዮጵያውያን በአማራጭነት ብቅ ያለ ትልቅ ሚዲያ ነው፡፡ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ያለውን አበርክትቷል ማድነቅ እፈልጋለሁ፡፡ እኔም በተለያየ ጊዜ በዚሁ ሚዲያ ላይ የተለያዩ ሃሳቦችን ሰጥቼ አውቃለሁ ወደ ፊትም እድሉን ባገኘሁ ቁጥር እሰጣለሁ፡፡ የተለያዩ አማራጭ ሃሳቦችን በተደራጀ ነፃ ሚዲያ ማግኘት የተራበው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዳያዝን የኢሳት ጋዜጠኞችን የኢዲቶሪያል ቦርድ አባላት በእጅጉ ሊያስቡበት ይገባል፡፡ ማንኛውም ሚዲያ ከአድሎ አሠራር ነፃ መሆን አለበት፡፡ በዚህ ሚዲያ ላይ የሚሰሩ ጋዜጠኞቹ ግን የግል አመለካከታቸውንና እምነታቸውን በማስቀደም አንድን ድርጅት ለማጥቃት የሚሄዱበትን መንገድ መፈተሽ ጠቃሚ ነው፡፡ ጋዜጠኛ ፋሲል በአንድነትና አመራሩ ላይ የሰነዘረው የተዛባ አስተሳሰብ በሚል አስተያየት ስም የቀረበ ቢሆንም ግለሰብ አንድ ትልቅ ፓርቲ ላይ ሲጽፍ መውሰድ የሚገባውን ጥንቃቄ አላደረገም፡፡ ስለዚህ ብዙ ተሳሳተ፡፡ ለማንኛውም ሁሌም ከጥላቻ የሚነሳ ሃሳብ ለህዝብም አይጠቅምም፡፡ አበቃሁ፡፡


የማለዳ ወግ …የመረጃዎች እውነት ፣ እውሸት ፍልሚያ ጅማሮ ነቢዩ ሲራክ

$
0
0

በርካታ ከሳውዲ ወደ ሃገር ቤት የተመለሱ ዜጎችን በሚመለከት የጀርመንና የአሜሪካ ራዲዮን ጨምሮ በርካታ የመገናኛ ብዙሃን አንድ አይነት የሚመስል መረጃ ግፉአን ተመላሾችን እማኝ እያደረጉ መረጃ አቀብለውናል ።http://www.rappler.com/world/regions/africa/45783-ethiopia-s-colossal-human-airlift-from-saudi-arabia ” ራፕለር ” በታዝነው ሳምንት ባቀበለን መረጃ ሻንጣቸው ጠፍቷቸው በአንድ የሻንጣ ማጠራቀሚያ ግቢ ሻንጣቸውን ሲፈትሹ የሚያሳየውን ፎቶ አስደግፎ የተመላሾችን አስተያየት አካቶበታል። ዜጎች ወደ ሳውዲ ሲሰደዱ ከቤተሰብ ፣ ከዘመድ አዘመድ አዝማድና ከተለያዩ ቦታወች የወሰዱትን የብድር ገንዘብ ስላልመለሱ ኑሯቸው የሰመረ እንዳልሆነ እየተናገሩ ነው ። ሃገር ቤት ገብተው የስራ ማጣት እና እሳት የሆነው የኑሮ ውድነት ግራ ያጋባቸው በርካቶችም አሁንም መልሰው ለስደት እንደቋመጡ እኛ የምንቀርበው መረጃ ባይስማማ የፈረንጆቹ መገናኛ ብዙሃን የሚያቀርቡት የገሃዱን እውነት አንድምታ ያሳያል ።

በግል ሃገር ግብተው የማገኛቸውን በርካቶች ሃገር ቤት ተመልሰው የጋጠማቸው የኑሮ ውድነት አማሯቸዋል። መልሶ ማቋቋሙ ደግሞ ከወሬ ባለፈ አለመጀመሩን እየሰማን ነው ። ባሳለፍነው እሁድ በጀርመን ራዲዮ እንዎያይ ፕሮግራም የቀረበው ተመላሽ ወንድምም ተመላሾችን በማደራጀቱና መልሶ በማቋቋሙ ረገድ የተጀመረ ነገር እንደ ሌለ መረጃውን አካፍሎናል። በአንጻሩ በመንግስት ኢቲቪና የቀሩት በስሩ የሚተዳደሩት መገናኛ ብዙሃን የሚናገሩት የሚታመን ከሆነ “ተመላሾቹ በየክልሉ ተደራጅተው እራሳቸውን የሚያቋቁሙበት ስራ ተጀመሯል!” የሚል መልካም መረጃ እያስተላለፉ ይገኛሉ …ከዚህ ጋር ያያዝኩት አዲስ ዘመን ጋዜጣ ” ከስደት ተመላሾች ሥልጠና ጀምረዋል !” በሚል ሁላችንም ሳውዲን ለቀን ወደ ሃገር እንገባ ዘንድ የሚያበረታታ መልካም የብስራት ዜና አሰራጭቷል። … እውነት ከሆነ ማለቴ ነው ! ይህንን አሻግሮ ተቀምጦ “እውንት እውሸት “ማለት አይቻልምና ሊናገሩ የሚገባቸው ባለቤቶቹ ብቻ ናቸው ። ተመላሾች ሆይ ምን ትላላችሁ ? http://www.ethpress.gov.et/addiszemen/index.php/addiszemen/news/7374-2014-01-13-08-07-09

አለም አቀፉ የስደተኞች ተጠሪ IOM መስሪያ ቤት ተመላሾችን መልሶ ለማቋቋም $13.1 ሚሊዮን ዶላር ወይም 9.5 ዩሮ እንደሚያስፈልግ ይፋ አድርጓል ። የስደተኞች ንብረት በተለይ የሻንጣ ጌጣጌጡን መጥፋት ጉዳይ አሳሳቢነት ግን ከፍተኛ ሃላፊዎችን ሳይቀር ያስደመመ እንደሆነ በሚሰራጩት መረጃዎች ለመረዳት አልገደደንም ።

“ወደ ሃገር ግቡ አንገባም ፣ እንግባ አትገቡም …”

ከአሰሪያቸው ጋር የማይሰሩና በህገ ወጥነት የተፈረጁ ዜጎች ወደ ሃገር እንዲመለሱ የሚጠይቀው የሳውዲ መንግስትን ጨምሮ የኢትዮጵያ ኢንባሲና የቆንስል መስሪያ ቤቶች ጥሪ ነው ። ጥሪው በቀጥታ የሚመለከታቸው ሰነዳቸውን ያላሟሉ የሚባሉት በባህር በኡምራና ሃጅ ብቻ ሳይሆን በስራ ኮንትራት መጥተው ከአሰሪዎቻቸው ጋር የማይሰሩ “ህገ ወጥ ” የተባሉ ዜጎች ግን “ሳውዲን ለቃችሁ ውጡ! ” የሚለውን ጥሪ ችላ በማለት ዘና ብለው የተለመደ ኑሯቸውን መኖር ጀምረዋል። ፍርሃትና ጭንቀቱ የት እንደገባ ባይታወቅም የሳውዲ መንግስት ባሳለፍነው ሳምንት ጉዳያቸውን ጀምረው ላልጨረሱ የሰጠው የሁለት ወር ማስተካከያ ጊዜ ገደብ ነዋሪውን ያዘናጋው ይመስላል። ያን ሰሞን በስጋት እቃቸውን ሲጠራርፉ የነበሩት ዛሬ እቃቸውን ወደ ነበረበት መልሰው የለመዱትን የመዘናጋት ኑሮ መግፋት ይዘዋል። አንዳንዶቹን ጠይቄያቸው “ዛሬም የሳውዲ መንግስት አይጨክንም ህጉን ያሻሽለዋል !” በማለት ሲመልሱልኝ አንዳንዶቹ ደግሞ “ሃገር ቤት የሄዱት የኑሮ ውድነት እያማረራቸው እየሰማን መሄዱ ማበድ ነው “ሲሉ መልሰውልኛል ። እስርና ቅጣቱስ አልኳቸው እንዴት ትቋቋሙት አላችሁ? አልኳቸው ” የፈለገው ቢሆን እዚሁ ሁኔ መቋቋም እና መቀበሉ ይቀላል !” ሲሉ ክችም ያለ መልስ ሰጥተውኛል ! እኒህ ለእኔ ቀቢጸ ተስፈኞች ናቸው ..

የሳውዲን መንግስት ወደፊት ጠንከር ብሎ ይወስደዋል ተብሎ የሚጠበቀውን እርምጃ የፈሩ ጥቂቶች አሁንም ወደ መጠለያ በመግባት እና ለመግባት በዝግጅት ላይ ናቸው። ያም ሆኖ በጅዳ የሽሜሲ መጠለያ ሰነዳቸው ይሰራላቸው ዘንድ በመጠባበቅ ላይ እንዳሉ በስልክ እየደወሉ “ተቸገርን! ።የምግቡ ችግር ቢቻልም ፣ በመጓጓዙ ላይ ዘገየን፣ መላ ወደሚገኝበት ቦታ ጩኸልን !” እያሉ ተማጽነውኛል ። ትናንት ሰኞ ከቀትር በኋላ ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት መረጃ ያቀበሉኝ “ከመዲናና ከጅዳና ከተለያዩ ቦታወች ከቀናትና ከሳምንታት እና ከወር በፊት ወደ ሽሜሲ ገባን!” ያሉኝ ወገኖች ” ጉዟችን ለማፋጠን በቆንስላችን ክትትልና ትብብር ስለማይደረግልን እየተጉላላን ነው !” ሲሉ ጭንቀታቸውን ገልጸውልኛል። በኮንትራት ስራ የመጡትን ወደ ሃገር ቤት ለመመለስ ችግሩ መቋጫ አግኝቷል ቢባልም አሁን ድረስ ችግሩ አለመፈቱን ነዋሪዎች ከሽሜሲ መጠለያ በምሬት ገልጸውልኛል ። “ካለፉት ሶስት ቀናት ወዲህ ወደ መጠለያ ለመግባት ፈልገን ወደ መጠለያ የሚወስደን የሚቀበልን አጣን! ውጡ ብለውን እንውጣ ስንል የሚያስወጣን አጣን !” ያሉኝ በርካቶችም በጅዳ ሸረፍያ እንደሚገኙ አጫውተውኛል ። ህግን ተጋፍተው በሳውዲ ለመኖር ተስፋቸው የተሟጠጠ እንህኞች የሚደግፋቸው ይሻሉ … !

የጀዛን …እውነት

በጅዛን በተደጋጋሚ የሚደርሰኝ መረጃ በማቅረቤ ያን ሰሞን የወገን ለወገን ደራሽ ኮሚቴን የጠለፉት የመንግስት ፖለቲካ ድርጅት አንዳንድ ካድሬዎች እዚህ ጅዳ ከጎኔ ተቀምጠው አዲስ የማጥላላት ዘመቻ ጀምረዋል። የወገንን ሳይሆን ለመንግስት ሃላፊዎች በማደገግደግ እንደፈለጉ በሚፈነጩበት የህዘብ ግንኙነት የፊስ ቡክ ገጽ ” እውነቱ ይሄ ነው ” በሚል ባስነበቡን መረጃ የእኔን ሳይሆን የተበዳዮችን እውንት ጥላሸት ሊቀቡት ከጅለው ሳይ አዝኛለሁ። “በሉ !” ትዕዛዙን ይፈጽሙ ዘንድ አንደተባሉት በማስተጋባት እውነቱን ” ውሸት !” ብለውታል። ሳያፍሩ ፣ ሳይፈሩ !

የተሳሳተ መረጃ ደረወሶኝ ይሆን ስል አጠራጠሩኝ ። ግን እንዲያ አልነበረም ። መረጃውን ለማጣራት ጅዛኖችን ደጋግሜ “ሃሎ” ብያቸው ነበር … ያገኘኋቸው አስገራሚና አሳዛኝ መረጃዎች ” አሳ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል !” አስብሎኛል ። ከህግ ታሳሪዎቹ ጋር በነበረኝ ቆይታ “የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች የእናንተን ጉዳይ እየሰሩ እንደሆነ ተነግሮኛል ፣ እውነት ነውን? !”ያልኳቸው ወንድሞች የተባለው መረጃ ትክክል አለመሆን ተበሳጭተው የሚጠይቅላቸው ስላጡትነና በሚሰራው ስራ ዙሪያ ብዙ አጫውተውኛል ። በአሳዛኝ እና በአስገራሚው የስደት ህይወት እጁ የተቆረጠውን ወንድም ፣ ታናሽ ወንድሙን እና እሱ በርሃ ላይ ሲጓዙ ተይዘው ዛፍ ላይ ታስረው ተንጠልጥለው ሲውሉ አቅም አንሶት ከፊቱ ላይ ደክሞ ተዝለፍልፎ የሞተ ታናሽ ወንድሙን ታሪክ ወንድሙ ራሱ ይነግረናል … ይህ ወንድሙን በበርሃ ላይ ያጣ ወንድም ስድስት ወር እንዲታሰር ቢፈረድበትም ከአመት በላይ ጠያቂ አጥቶ መንገላታቱን መስማት ያማል ! ይህንንም በድምጽ ይዠዋለሁ ! ትሰሙታላችሁ … እናም በጀዛን ፍርዳቸውን የጨረሱ የህግ ታራሚዎች ድምጽ “ወደ ሃገር እንድንገባ ድጋፍ የሚያደርግልን የመንግስታችን ሃላፊዎችን አጣን ! ” የሚል ነው ! የጅዛን እውነቱ ይህ ነው !

መንግስት ሆይ ስማን … ወገን ሆይ ስማን !

ሰነድ የሌላቸው ዜጎች ” ህግን ተላልፋችኋል !” ተብለው ” ከሃገር ይውጡ !” ተብሏል ! ዜጎች ከሃገር ውጡ ሲባሉ መንገዱን በማመቻቸቱ ረገድ ከኢትዮጵያ መንግስት የኢንባሲና ቆንስል መስሪያ ቤቶች ከመረጃ ጀምሮ ብዙ ይጠበቃል ! ቢያንስ ሁሌ እንደምለው “መውጣት አልፈልግም !” የሚለውን ዜጋ ምክንያት ሊሰማበሊደመጥ ይገባልና ፣ ስሙት ! ” እንውጣ !”ሲል እንግልት የሚገጥመውን ዜጋ ታደጉት ! በአረብ አሰሪዎች ቤት ሆነው “ወደ ሃገራችን እንግባ ድረሱልን!” የሚሉ የኮንትራት ሰራተኞችን ያላባራ ጩኸት ይሰማል ። የሰማነውን ለሃላፊዎች ብናሰማም መፍትሔ የሚሰጥ ጠፍቷል ! ይሀወ አሁንመወ ያሳስባል ! “ድረሱልን! ” ሲሉ ደራሽ ያጡትን የኮንትራት ሰራተኞች ፈጥናችሁ ድረሱላቸው ! መውጣት ያለበት “ህገ ወጥ ” የተባለ ሁሉ ዜጋ ይውጣ ! አስከፊውን የስደት እንግልትና መከራን ማየቱ ይብቃን !

ሰው ተጨንቆ ተጠቦ ፣ የመረጃዎችን እውነት እውሸት የሙግት ጅማሮ ቀልቤን ባይስበውና መነታረኩን ባልፈልገውም ለሚወረወረው አሳሳች መረጃ እውነቱ ለማስጨበጥ ስድቡን ባልገባበትም ትክክለኛውን መረጃ ከምንጩ ለማቅረብ ወደ ኋላ የምል አይደለሁም! ይህም በመሆኑ ይህንና ያንን በሰፊው እስክመለስበት ሰላም !

አስኪ ቸር ያሰማን !

ነቢዩ ሲራክ

ከአምባገነን ባሻገር-የተወሳሰቡ ነገሮችን የመረዳት አስፈላጊነትና የነፃነት ጥያቄ ! ከፈቃዱ በቀለ

“እኛና አብዮቱ”የመጽሃፍ ግምገማ ሰሎሞን ገ/ስ

አቡጊዳ –የፌዴራል ፖሊሲ አጽቢን ቶቆጣጥሯታል ፣ ሕወሃቶች በሕዝቡ ተናደዋል ፣ ህዝቡም ጥያቄዉን አላቆመም

$
0
0

አቡጊዳ – የፌዴራል ፖሊሲ አጽቢን ቶቆጣጥሯታል ፣ ሕወሃቶች በሕዝቡ ተናደዋል ፣ ህዝቡም ጥያቄዉን አላቆመም

ከመቀሌ በስተሰምኔ 70 ኪሎሜተር ርቃ በምትገኘው የአጽቢ ከተማ በሕዝቡና በሕወሃቶች መካከል ትላንት የተፈጠረው ዉዝግብ ዛሬም ቀጥሎ ዉሏል። የአካባቢዉ ፖሊስ አቅም በማጣቱ በብዙ መኪና በተለያዩ አቅጣጫዎች፣ ኬሎች አካባቢዎች፣ ተጭነው የመጡ ፌዴራል ፖሊሶች ከተማዋን እንደ ጦር ካምፕ ወረዋታል። ወደ አካባቢዉ የደረሱ የሕወሃት አመራሮች በሕዝቡ ላይ ዛቻን ስድብ እያወረዱበት ነዉ። በሕዝቡ መናደዳቸውን እየገለጹ ነዉ። ሕዝቡ የታሰሩ እንዲፈቱ እየጠቀ ነዉ። ከታስሩት ዉስጥም የ16 አመት ወጣት ይገኝበታል። ወደ ከተማዋ መግባትና መዉጣ አይቻልም። የከተማዋ ነዋሪዎች፣ በየትኛዉም መንግስት እንዲህ አይነት ግፍ አይተን አናውቅም እያሉ ነዉ።

ሰሞኑን የሕወሃት/ኢሕአዴጉ አቶ በረከት ስምኦን፣ ገበሬዉን የፈለገ ነገር ብናደርገዉ የም አይሄዱም በማለት በገዳ ቴሌቭዥኝ (ትንሿ ኢቲቪ) መናገራቸው ብዙዎች እያነጋገረ እንደሆነ ይታወቃል። ነገር ግን በአጸቢ፣ ትግራይ በገበሬዎች ላይ እየተደረገ ያለው አሳዛኝ ግፍ ፣ ገበሬዉ በስፋት በስፋራዉ ተገኝቶ ችግሩን የሚነግርለት ባለመኖር እንጂ ፣ ገበሬዉ ከሃያ አመታት በላይ ግፍ እየተፈጸመበት እንደሆነ በግልጽ ያሳየ ነው።

ከአንድነት ፓርቲ ጋር የቅርብ ግንኙነት ያለዉና ለዉህደትም ጥያቄ ያቀረበዉ፣ የአረና አመራር አባል፣ አብርሃ ደሳት ከመቀሌ ዛሬ አርብ ጥር 9 ቀን በፌስቡክ ያስተላለፈዉን እንደሚከትለው አቅርበናል፡

የአፅቢ ዓመፅ (ክፍል ሰባት)
——————————–

ግጭቱ ቆሟል። መከላከያ ሰራዊት የሃይል እርምጃ ከመውሰድ ታቅቦ ህዝቡ እንዲበተን ተማፅኗል። በፖሊስ የታሰሩትን ነገ (ዛሬ ዓርብ 09/05/06 ዓም) እንደሚፈቱ ቃል ገብቷል። ድርማው ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት (7:00) ላይ ተፈፅሟል። ድርድሩ ዛሬ ዓርብ ይቀጥላል።

የዓመፁ ምክንያት

Basic Cause: የፍትሕ እጦት

የአፅቢ ወንበርታ ወረዳ አስተዳዳሪዎችና ፖሊስ በህዝቡ ጥሩ ስም የላቸውም። አስተዳዳሪዎች የህዝብን የፍትሕ ጥያቄ በአግባቡ ከመመለስ ይልቅ ህዝቡን ማስፈራራት ይቀላቸዋል። ህዝቡ ደግሞ የሚፈራ አይደለም። የወረዳው አስተዳዳሪ ጥያቄ ለሚያነሱ ዜጎች ተቃዋሚዎች እንደሆኑ ይሰብካል፤ ተቃዋሚዎች እንደሚያጠፋም ይዝታል (ህዝብ ሰብስቦ)። ወጣቶች መንግስትን እንዳይቃወሙ ወላጆቻቸውን ያስፈራራል። የፍትሕ ጥያቄ የሚያነሳ ሰው የመንግስት አገልግሎት አያገኝም፤ የፍርድቤት አገልግሎት አያገኝም፣ ፍትሕ ተከልክሏል። የህወሓት አገልጋይ ካልሆነ መሬት አይሰጠውም፣ መስኖ እንዲጠቀምም አይፈቀድለትም። ማዳበርያ እንዲወስድ ይገደዳል፣ ለመውሰድ ፍቃደኛ ያልሆነ ይታሰራል፣ ይሰቃያል። በአፅቢ ወንበርታ የፍትሕ ጥያቄ ማንሳት ክልክል ነው።

ፖሊስም እንደፈለገ ሰው ያስራል፤ ይገድላል። በፖሊስ የተገደሉ የአከባቢው ኗሪዎች አሉ። ፖሊስ ሰዎች አስሮ ይገርፋል። የወረዳው ፖሊስ በህዝቡ በጣም ይጠላል። ባጠቃላይ የአፅቢ ወንበርታ ህዝብ በመንግስት እምነት የለውም። ህወሓትን አይደግፍም። አስተዳዳሪዎቹ ህዝቡን በአሸባሪነት ፈርጀውታል። ህዝቡና አስተዳዳሪዎቹ በፍትሕ እጦት ምክንያት ሆድና ጀርባ ከሆኑ ቆይተዋል።

Immediate Cause: የካሳ ጥያቄ

በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ “ሕኔቶ” ተብሎ በሚጠራ መንደር በመንግስት ባጀት የተገነባ ግድብ አለ። ግድቡ የተቆፈረ ትልቅ የውኃ ጉድጓድ ነው። የውኃ ጉድጓዱ የተቆፈረበት ቦታ ሰፊ የእርሻና የግጦሽ መሬት ነበር። ቁፈራው ሲጀመር ለባለ መሬቶቹ ተገቢ ካሳና ተለዋጭ መሬት እንደሚሰጣቸው በመንግስት ቃል ተገብቶላቸው ነበር። ባለመሬቶቹም በጉዳዩ ተስማምተው ጉድጓዱ ተቆፈረ (ግድቡ ተገነባ)። ለገበሬዎቹ የተገባ የካሳ ቃል ግን አልተተገበረም። መንግስት ቃሉ አጠፈ። ገበሬዎቹ በተደጋጋሚ ጠየቁ። መልስ አላገኙም። የወረዳው አስተዳዳሪዎች ህዝቡን ሰብስበው ምንም ዓይነት የካሳ ጥያቄ እንዳያነሳ አስጠነቀቁት።

ባለ መሬቶቹ መሬት አልባ ሆኑ (በፍትሕ እጦት ምክንያት)። ካሳም አልተከፈላቸውም። ተለዋጭ መሬት ስላልተሰጣቸው የመስኖ ተጠቃሚም መሆን አልቻሉም። በመስኖው እንዲጠቀሙ መሬት የተሰጣቸው የተወሰኑ የስርዓቱ አገልጋዮችና ሌሎች ከግድቡ በመስኖ መጠቀም የሚችሉ (በቶፖግራፊ ምክንያት) የሌላ ቁሸት (ቀበሌ) ናቸው።

በግድቡ ምክንያት መሬታቸው ያጡ ገበሬዎች (ካሳ ያልተከፈላቸው) ልጆቻቸውን ወደ ስዑዲ በመላክ ይተዳደሩ ነበር። አሁን ይጠውሯቸው የነበሩ ልጆቻቸው አብዛኞቹ ከስዑዲ ተመልሰዋል። መሬት ወይ ካሳ ይፈልጋሉ። እንደገና ጥያቄው ተነሳ። አስተዳዳሪዎችም “አርፋቹ ተቀመጡ፤ አለበለዝያ ከዚህ እናጠፋችኋለን። ለተቃዋሚዎች (ጥያቄ ለሚያነሱ ማለት ነው) ቦታ የለንም። ጥያቄም አናስተናግድም” የሚል የማስፈራርያ መልስ ተሰጣቸው።

ጥያቄ የሚያነሱ ገበሬዎች ከግድቡ መስኖ ከሚጠቀሙ ገበሬዎች ጋር በጉዳዩ ተወያዩ። “መንግስት ካሳ ይክፈለን፤ እናንተም ከኛ ጋር ጠይቁ። አግዙን ወይም ደግሞ እናንተ ካሳ ክፈሉን” የሚል ሐሳብ አነሱ። ምክንያቱም ግድቡ ያለው በሰዎች መሬት ላይ ነው። ባለመሬቶቹ ተመልካቾች ሌሎች ተጠቃሚዎች የሚሆኑበት ሁኔታ ፍትሐዊ አይደለም የሚል የክርክር ሐሳብ ተነሳ። ባለ መስኖዎቹም በካሳ ጥያቄው ተስማምተው መንግስት ለገበሬዎቹ ካሳ መክፈል እንዳለበት ሐሳብ ቀረበ።

አስተዳዳሪዎችም ካሳ እንደማይከፍሉ አረጋገጡ። ህዝብ ካመፀ የሃይል እርምጃ እንደሚወስዱ አስጠነቀቁ። ባከባቢው የነበሩ አስራ አምስት ምልሻዎች ትጥቃቸው በሃይል እንዲፈቱ ተደረገ። ግጭት እንደሚነሳ ታወቀ።

የ ሐሙስ ዓመፅ

ካሳና ተለዋጭ መሬት የተከለከሉ ገበሬዎች ዓመፅ ጀመሩ። ዓመፁ የተጀመረው “ግድቡ በመቆጣጠር” ነበር። መፍትሔ እስኪገኝ ድረስ በግድቡ የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ (የመስኖ ስራ ጨምሮ) እንዲቆም አደረጉ። “ግድቡ መሬታችን ነው፤ ተገቢውን ካሳ ካልተሰጠን ዉኃችን አንሰጥም” አሉ። ግድቡን ለማስለቀቅ የፖሊስ ሃይል ተላከ። ዓመፁና ግርግሩ ተጀመረ። ፖሊስ መቆጣጠር ስላልቻለ መከላከያ ሰራዊት ገባ።

ስለዚህ የዓመፁ መነሻ የፍትሕ እጦት ነው። መንግስት የገባውን ቃል ባለማክበሩ የተፈጠረ ዓመፅ ነው።

አሁን ከወረዳ አስተዳደሩ የደረሰኝ መረጃ እንደሚያመለክተው የወረዳው አስተዳዳሪዎች የህዝብ ዓመፅ ከሽብርተኝነትና ተቃዋሚ ፓርቲዎች (ዓረና) ጋር በማገናኘት ዜጎችን ለማስወንጀል ተዘጋጅተዋል። ሌላኛው ዕቅድ ደግሞ ህዝቡን ለመከፋፈል ያለመ ስትራተጂ እየቀረፁ ነው (መስኖው የሚጠቀምና የማይጠቀም በማለት ለሁለት ሊከፍሉት ነው)። በአንድ በኩል ለዓመፁ ተቃዋሚ ፓርቲን ተጠያቀ ማድረግ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በመስኖው የሚገለገሉ ገበሬዎች ከአስተዳዳሪዎቹ ጎን እንዲሰለፉና ህዝቡ እንዲከፋፈል ለማድረግ እያሴሩ ነው። ከተሳካላቸው ህዝብ ከህዝብ ጋር በማጣላት እነሱ ከሐላፊነት ለማምለጥ መመኮራቸው አይቀርም። ህዝብ ይህን የህወሓት ከፋፋይ ስትራተጂ ነቅቶ መጠበቅ አለበት። (እኛን ያልደገፈ መስኖ አይጠቀምም በማለት መስኖ ተጠቃሚዎቹ በ አስተዳዳሪዎች ጎን ለማሰለፍ ጥረት ሊያደርጉ ይችላሉ)።

ዓርብ 09/05.06 ዓም ከጠዋቱ 3:05 ተፃፈ

የአፅቢ ዓመፅ (ክፍል ስምንት)
—————————–

ህዝቡ እየተሰባሰበ ነው፣ የፌደራል ፖሊስ እየገባ ነው

አከባቢው በመከላከያ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ይገኛል። የአፅቢ ወንበርታ ህዝብ (ሕነይቶ) በፖሊስ የታሰሩትን ወገኖቹ ለመቀበል ባከባቢው እየተሰባሰበ ነው። የተያዙትን ሰዎች ግን እስካሁን ድረስ ባከባቢው የሉም። በነሱ ምትክ ብዙ የፌደራል ፖሊሶች አከባቢውን (ከመከላከያዎች ጋር በመሆን) እየተቆጣጠሩት ይገኛሉ።

ትናንት በፖሊስ ተይዘው ወዳልታወቀ ስፍራ የተወሰዱ ያከባቢው ኗሪዎች ብዛታቸው በዉል አይታወቅም። ህዝብ እያየ ፖሊስ እየደበደበ የወሰዳቸው አራት ሰዎች ግን የሚከተሉ ናቸው።

(1) ታደሰ ሃይሉ
(2) አሰፋ ካሕሳይ
(3) ገብረእግዚአብሄር ገብረሚካኤል
(4) የአቶ ግርማይ ግብረየሱስ ልጅ (የ16 ዓመት ወጣት) ናቸው።

የአፅቢ ወንበርታ ህዝብ በታሪክ ይህን ያህል ግፍ ያደረሰበት መንግስት እንዳልነበረ አስተያየት ሰጪዎች እየተናገሩ ነው። አስተያየት ሰጪዎቹ ለመብት ጥያቄ ይህን ያህል ግፍ መፈፀም አግባብነት የለውም ይላሉ።

የተፈጠረ አዲስ ነገር ካለ አቀርባለሁ።

(ዓርብ ጠዋት ከረፋዱ አምስት ሰዓት ነው የተፃፈው)።

የአፅቢ ዓመፅ (ክፍል ዘጠኝ)

ህዝቡ እንዳይንቀሳቀስ በፌደራል ፖሊስ ተከቧል
———————————————

አሁን ዓርብ ከጠዋቱ አምስት ሰዓት ተኩል ነው። ዓመፁ ወደ ሌላ አከባቢ እንዳይሰፋ በመፍራት የፌደራል ፖሊሶች አከባቢው ከበውታል፤ ህዝቡም በፖሊስ ተከቧል። የፖሊስ አዛዦች ህዝቡን እያስፈራሩ ይገኛሉ። ህዝቡም መብቱ እንዲከበርለትና ታፍነው የተወሰዱ ወገኖቹ (ትናንት ማታ በተገባላቸው ቃል መሰረት) እንዲፈቱ እየጠየቀ ነው። አከባቢው ግን ተከቧል። ካከባቢው መውጣትና ወደ አከባቢው መግባት ተከልክሏል። አንድ ባህረ ገብሩ የተባለ ያከባቢው ኗሪ ካከባቢው ወደ አፅቢ ከተማ ሲጓዝ በፖሊስ ታፍኖ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስዷል።

ህዝቡ ታፍነው የተወሰዱ ያከባቢው ኗሪዎች ፖሊስ ይደበድባቸዋል፣ ይገድላቸዋል በሚል ስጋት ተጨናንቀዋል። ሳይፈቱም ህዝቡ እንደማይበተን አስታውቀዋል። የፖሊስ ማስፈራርያው ግን አይሏል። ባከባቢው በዜጎች ላይ ግፍ ሲደርስ የተለመደ በመሆኑ የተያዙት ሰዎች ድብደባና ግድያ እንደሚጠብቃቸው ይገመታል።

ባከባቢው (አፅቢ ወንበርታ) እስካሁን ድረስ (ከዚህ ቀደም ማለት ነው) ታደሰ ጊደይ አባዲ የተባለ የሩባ ፈለግ ኗሪ በመንግስት አካላት በጥይት ተገድላል። የአቶ ገብረሂወት (ስሙ ለግዜው አልያዝኩትም) ልጅም በመንግስት አካላት በጥይት ተመቶ ህይወቱ አልፏል። አቶ ገብረሚካኤል ተስፋይ (ጣብያ ፈለገወይኒ)፣ አቶ ታደሰ መዝገቦ (ጣብያ ሩባ ፈለግ)፣ አቶ ህይወት አባይ (ጣብያ ሩባ ፈለግ) ወዘተ በፖሊስ ድብድባ (ቶርቸር) እንደደረሰባቸው ታውቋል: ከፍተኛ የስነ ልቦና ጉዳት ደርሶባቸዋል።።

ከዚህ በመነሳት ታፈነው በተወሰዱ ዜጎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የህዝብ ቅሬታ አለ። ፖሊስ ግን ህዝቡን ከቦ አላንቀሳቅስ ብሏል።

(በ 5:55 ተለጥፏል)።

የአፅቢ ወንበርታ ህዝባዊ ዓመፅ (ክፍል አስር)

የህወሓት አመራር አባላት ባከባቢው ይገኛሉ
————————————

አከባቢው በብዙ የወረዳና የክልል ፖሊሶች፣ የፌደራል ፖሊሶችና መከላከያ ሰራዊት ተከቦ ህዝቡም እንዳይንቀሳቀስ ታግቶ በመከላከያ ሰራዊት የታጀቡ የዞንና ክልል አስተዳዳሪዎች (የህወሓት ባለስልጣናት) ህዝቡን እያነጋገሩ ነው። ባለስልጣናቱ ህዝቡ ዓመፁ የቀሰቀሰው ማን እንደሆነ፣ ለምን የሃይል መንገድ መጠቀም እንደመረጠ ወዘተ በማስፈራራት እየጠየቁ ነው። ህዝቡም የመሬቱ ካሳ ወይ ተለዋጭ መሬት የማግኘት መብቱ እንዲከበርለት፣ ታፍነው የተወሰዱ እንዲፈቱ ይጠይቃል። መግባባት የለም። የህዝቡ ጥያቄ ያናደዳቸው አስተዳዳሪዎች ህዝቡ ትናንት የቀሰቀሰው ዓመፅ “ስህተት” መኖሩ ካላመነ ወደ ቤቱ እንዲሄድ እንደማይፈቅዱለት እያስፈራሩት ነው። ህዝቡ በሃይል ዓፍነው ይዘውታል (በፀጥታ ሃይል ብዛት)። የኢህአዴግ የደህንነት ሰዎች እዛው ይገኛሉ። ካከባቢው ለመውጣትና ወደ አከባቢው ለመግባት የሞከሩ የአከባቢው ኗሪዎች እየታሰሩ ነው። እስካሁን ሰባት ሰዎች ታስረዋል (አንድ ሃፍቱ ገብረመድህን የተባለ የቀድሞ የመከላከያ ሰራዊት አባል ጨምሮ)።

ዓርብ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ተኩል ተፃፈ።

የአፅቢ ወንበርታ ህዝባዊ ዓመፅ (ክፍል አስራ አንድ)
————————————
-
ትልቁ ኪሳራ

የትናንትው የአፅቢ ወንበርታ ህዝባዊ ዓመፅና የፖሊሶች ተኩስ (የነበረውን አጠቃላይ ግጭት) በካሜራና በሞባይል ሲቀርፁ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ። የግጭቱ ሙሉ ሂደት ቀርፀው ለህዝብ ለመበተን ዉቅሮ ከተማ ሊገቡ ሲሉ በልዩ የህወሓት የደህንነት ሃይሎች ተይዘዋል። ታፍነው ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደዋል። ሞባይላቸውና ካሜራቸው ተነጥቀዋል። ህወሓቶች የአፅቢ ወንበርታ ህዝብ በደልና ዓመፅ ሌሎች ህዝቦች እንዳይሰሙት ለማፈን በማቀድ ቪድዮውን ይዘውታል። መረጃው መበተኑ ግን አይቀርም። ለኔ ግን ትልቅ ኪሳራ ነው።

ይህን የተደረገው ዓርብ 09/05/06 ዓም ከቀኑ ስምንት ከአርባ (8:40) ነው።

“የአንድነት ፓርቲ የመጪው ጊዜ ፈተና” – የመልስ መልስ ለአቶ ግርማ ካሳ እና ለመሰሎቻቸው – ከፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)

$
0
0

January16/2014
“የአንድነት ፓርቲ የመጪው ጊዜ ፈተና” በሚል ርዕስ ለጻፍኩት ጽሁፍ ስለሰጡት ምላሽ ከልብ አመሰግናለሁ። ሀሳቦችን በጨዋ መንገድ ማንሸራሸር ለእድገት ይጠቅማልና ሁላችንም ይልመድብን እላለሁ። ስለአንድነት ፓርቲ ተቆርቋሪ ሆነው የሰጡት መልስ ብዙም እንዳላረካኝ ስገልጽልዎ በከፍተኛ አክብሮት ነው። ማንም ጤናኛ ሰው በአገር ውስጥ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ዴሞክራሲያዊ ለውጥ እንዲመጣ ይፈልጋል። አንድነት ፓርቲ በዚህ እምነት የሚያደርገውን ትግልም አደንቃለሁ። ይሁን እንጅ የትግል ፍሬ መለኪያው ሂደት ሳይሆን ውጤት ነውና አንድነት ፓርቲ፣ ኢ/ር ግዛቸው ሊሄዱበት ባሰቡት መንገድ ከተጓዘ፣ ውጤታማ ይሆናል የሚል እምነት የለኝም። እርስዎ በዚህ አስተያየት አልተስማሙም። አለመስማማትዎን ሁለት ቁምነገሮችን በማንሳት ለማሳየት ሞክረዋል፤ እኔም በእነዚህ ነጥቦች ላይ ተመስርቼ የመልስ መልስ አቀርባለሁ።

አንደኛ፤ አንድነት ፓርቲ፣ የአገሪቱ የህግ አካል የሆነውን ፣ የምርጫ ስነምግባር መመሪያው እስካሁን አለመፈረሙ ስህተት ነበር፣ አሁንም ፈርሞ ከኢህአዴግ ጋር መነጋገር አለበት የሚል መከራከሪያ አቅርበዋል። የስነምግባር መመሪያውን ፈርመው ለድርድር ተቀምጠው የነበሩት የቀድሞው የመኢአድ ሊቀመንበር ኢ/ር ሃይሉ ሻውል በመጽሀፋቸው የተናገሩት ሰነዱን መፈረም ያዋጣል አያዋጣም የሚለውን ለማየት ይረዳናልና ልጥቀስ፤-

” ከኢህአዴግ ጋር ያደረግነውን ድርድር በተመለከተ አንዳንዱ ‘ ወደሰለጠነ ፖለቲካ ልንገባ ይሆን?’ ብሎ በደህና ሁኔታ ያየው ወገን ነበር። ሌላው ወገን ግን ‘እንዴት ያሰረውን ሰው ሄዶ እጅ ይጨብጣል’ የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አሰምቷል። የ2002ቱን የምርጫ ስነምግባር ሰነዱን ስንፈርም ተቃውሞ እንደሚኖር ሳናውቅ ቀርተን አይደለም። ፊርማው ብቻውን ለእኛ ደስታን የሚሰጠንም ሆኖ አልነበረም።ሌላኛው አማራጭና አስተሳሰብ ግን ግብዝነትናን የሚያጠናክርና የሰላም ሂደትን የሚገታ ይሆናል የሚል ግምት መያዛችን አንዱ ምክንያታችን ነው። በወቅቱ እኛ ሰነድ መፈረማችን ለህዝብ ምን ፋይዳ አለው የሚለውንም በአግባቡ አይተነዋል። እኛ ያሰብነው ወረቀት ቢሮ ውስጥ ይፈረማል፣ ያልቃል የሚል ነበር። እነሱ ግን አምባሳደሮች ጋብዘው፣ ሚዲያዎችን ጠርተው የተለየ ዝግጅት አደረጉ። ነገሩን ለዓለም ለማሳወቅ መፈለጋቸው ለሁሉም ግልጽ ሆነ። በዚያን ወቅት እኛ የማናውቀው ውጥረት ነበረባቸው የሚል የዘገየ ግምት ተከሰተልኝ ። እኔ እንደሚመስለኝ የአውሮፓ ህብረት ታዛቢዎች የመታዘብ ይሁንታ የሰጡት ያ ስምምነት ስለተፈረመ ይመስላል። መኢአድ ሰነዱን የፈረምንበት ዋናው ምክንያት ግን የ500 ስቃይ ላይ የነበሩ እስረኞችና የቤተሰቦቻቸው ሰቆቃ አሰቃይቶን ነው። እኔን በተመለከተ ኢህአዴግ ወደ እኛ አስገባነው ብሎ ቢያስወራም አልሰመረለትም።”

(ህይወቴና የፖለቲካ እርምጃየ፣ ሃይሉ ሻውል፣ ገጽ139)።

አቶ ግርማ እዚህ ላይ አራት ነጥቦችን ላንሳ። አንደኛው፣ አቶ ሃይሉ እንዳሉት የስነምግባር መመሪያው ለኢህአዴግ አለማቀፍ ተቀባይነትን ለማሰጠት ጠቅሟል። ቢያንስ የምርጫ ታዛቢ እንዲላክ አድርጓል። የታዛቢው የመጨረሻ ሪፖርት ባያምርም። ሁለተኛ አቶ ሃይሉ 500 ሰዎችን ከእስር ለማስፈታት ብለው እንጅ ሙሉ በሙሉ አምነውበት ሰነዱን አለመፈረማቸውን ገልጸዋል። ልብ ይበሉ አቶ ግርማ! ከ80 ሚሊዮን እስረኞች የተፈቱት 500 ዎቹ ብቻ ናቸው። 80 ሚሊዮኑ ህዝብ ከእስር እንዲፈታ ስንት የምርጫ ስነምግባር ፊርማዎችን መፈረም ይኖርብን ይሆን? ሶስተኛ ፣ መኢአድ ፊርማውን መፈረሙ ህዝቡ እንዲከፋፈል አድርጎታል። አንድነትስ ተመሳሳይ ነገር አይሰራም ብለው ያስባሉ? የሚከፋፈለውን ህዝብ አንድ ለማድረግ እርስዎ የህዝብ ግንኙነት ስራ ለመስራት ተዘጋጅተዋል? አይርሱ ፖለቲካ 50 በመቶው ገጽታ ( image) ነው። አራተኛ፣ ኢህአዴግ የፊርማውን ስነስርአት ለራሱ የፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ተጠቅሞበታል። በድብቅ ይፈረማል የተባለውን ፊርማ ለአደባባይ አብቅቶታል። በአንድነት ላይስ እንዲህ እንደማይደረግ ምን ዋስትና አለ? በህዝቡ ላይ የሚፈጥረውን አሉታዊ ስሜትስ እንዴት ነው መቋቋም የሚቻለው?

ኢ/ር ሃይሉ ሻውል አያበቁም፣ ይቀጥላሉ ” በሌላ በኩል ከህዝቡ ወገን ደግሞ ” ሃይሉ ከዳን” የሚልም ነበር። ውጪ አገር ያሉትማ በኢንተርኔት ላይ ፎቶግራፌን እያገላበጡ እኔ ለቀድሞው ጠ/ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊ እጅ እንደምነሳ አስመስለው ሲዘልፉኝ ከርመዋል።… የሰነዱ መፈረም ለ2002 ምርጫ ዝግጅት ለእኛ አባላት ትንሽ ፋታ ሰጥቷል። ገጠር ሲታገሉ የሰነበቱት እሳት ውስጥ ነበሩ፤ ከፊርማው በሁዋላ ለአጭር ቀናት ቢሆንም በመጠኑ ማስፈራራት ጋብ አለ።” ይሄ ፊርማውን በመፈረም የተገኘ ጥሩ ዜና ነው አቶ ግርማ። ግን ይቀጥል ይሆን ? እንመልከተው፦ ” ምርጫው እየተቃረበ ሲመጣ ግን ሁሉም ነገር ተረሳና ኢህአዴግ የተለመደ ጭቆናውን ማስፋፋት ተያያዘው… መኢአድ ከ2002 ምርጫ ጋር ተያይዞ ከኢህአዴግ ጋር የስነምግባር ደንቡን ከፈረመ በሁዋላ በኢህአዴግ በኩል የተገቡ ቃሎች ባለመተግበራቸው ከጋራ መድረኩ ራሱን አግልሏል። ኢህአዴግ ሁሉም ነገር በቁጥጥር ስር እንዲሆን ፈለገ። በመድረኩም እንነጋገር ብለን የምንጠይቀውን አጀንዳ አይቀበሉትም። የሄ ከሆነ የጋራ ስምምነት የምክክር አይደለም ብለን ተውነው። ስንመለከተው ኢህአዴግ ትእዛዝ የሚያስተላልፍበት መድረክ ስለሆነ ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ግንባታ ጸር እንጂ ጠቃሚ አለመሆኑን በገሀድ ታየ። ገዢው ፓርቲ በዚህ በጋራ መድረክ አባልነት የቀጠሩትን ፓርቲዎች ደመወዝ መሰል ድጎማ እየከፈለ በቁጥጥር ይዟቸው ቀጥሎአል።በ2002 የስነምግባር ደንቡን ብንፈርምም የእኛ አባሎች ላይ የሚደርሰው ወከባና እንግልት ከዚያ በሁዋላ እየቀጠለ መጣ…” ይሉና አቶ ሀይሉ ይቀጥላሉ…

አቶ ግርማ ካሳ እንግዲህ አንድነትንም ወደዚህ የአራዊቶች ጉባኤ ( ፋቡላ) በመክተት ፓርቲውን በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር ሊያደርጉት እና ደሞዝ ሊያሰፍሩለት ያስባሉ ማለት ነው። ለአንድነት ፓርቲ ታጋዮች ካለኝ ከበሬታ አንጻር ፓርቲው በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር እንዲሆን አልመኝም። ወርሃዊ ደሞዝ እንዲሰፈርለትም አልሻም።ምክንያቱም እንዲህ አይነቱ አካሄድ ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል የሚገድል ነውና ።

መድረክም አንድነትም ፊርማውን እስከዛሬ ባለመፈረማቸው የረባ ውጤት አላገኙ ይሆናል፤ ነገር ግን ” No to cheating!” በማለታቸው ከመኢአድ የተሻለ ክብር እና ድጋፍ አግኝተው እንደነበር አንዘነጋውም።

ሁለተኛው መከራከሪያዎ አቶ አንዱዓለምንና ናትናኤልን በተመለከተ የሰጠሁትን አስተያየት ተንተርሶ የቀረበ ነው። እኔ አንድነቶችን ከመከፋፈል ማዳን እንጅ፣ እነሱን የመከፋፈል አላማ የለኝም፣ በፍጹም!። ይሄን ስጽፍም ፓርቲውን ከመከፋፈል ለማዳን እንጅ ለሌላ አላማ አይደለም። ወ/ት ብርቱካን እስር ቤት ከገባች በሁዋላ ፓርቲዋ ( አመራሩ) ረስቷት ነበር። እንዴያውም አንዳንዶች “እንኳን ታሰረች” ሳይሉ ሁሉ አልቀረም። ያን ጊዜ ማን ነበር ለብርቱካን አብዝቶ የጮኸው? ዲያስፖራው እና በተለይ ኢሳት አልነበሩምን? የካናዳው ልጅ ተክሌ ” ብርቱካኔ ብረሳሽ ቀኜ ይርሳሽ” ብሎ ዜማ ያወጣላት አምስተርዳም የኢሳት ስቱዲዮ ውስጥ ሆኖ ነው። በወቅቱ የነበሩ ባልደረቦቼ ብርቱካንን በተመለከተ ብዙ ዝግጅቶችን ይሰሩ ነበር። ምንም እንኳ ኢሳት እዚህ ውስጥ እንዲገባ ባልሻም፣ “የኢሳቱ ባልደረባ” እያሉ ስለጻፉና በተዘዋዋሪም እኔ የጻፍኩትን የኢሳት አቋም አድርገው ለማሳየት ስለሞከሩ ትንሽም ብትሆን እውነቱን ለመናገር ይጠቅማል ብየ ስላሰብኩ ነው ኢሳትን መጥቀሴ። ( በነገራችን ላይ ኢሳት የግል አስተያየቴን እንዳልጽፍ እያደረገኝ ነው፣ በግሌ የምጽፈውን አንባቢዎች ” የኢሳት አቋም አድርገው ይወስዱብኝ ይሆን” እያልኩ በመስጋት፣ መጻፍ እየፈለኩ አልጽፍም፤ ለሀሳብ ነጻነት በሚታገል ድርጅት ውስጥ የምሰራ ሰው፣ በዚሁ ድርጅት መልሼ መታፈኔ ይገርመኛል፤ ያፈነኝ ግን ድርጅቱ ሳይሆን፣ ሰዎች ከድርጅቱ ጋር ያያይዙብኝ ይሆን የሚለው ፍርሀት ነው።)

አንዱዓለምና ናትናኤል የብርቱካን እጣ እንዲገጥማቸው አልሻም። በፓርቲው ሸውራራ አካሄድ ስነልቦናቸው እንዲጎዳም አልፈልግም፤ የስነምግባር ደንቡን መፈረም አንዱዓለምን እና ናትናኤልን ከእስር እንደያማያስፈታ አስረግጬ መናገር እችላለሁ። እነሱን የማያስፈታ ሰነድ ደግሞ ጥንቅር ብሎ ይቅር። አንዱዓለምና ናትናኤል በመረሳታቸው እጅግ ያንገበግበኛል። የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጉና የገንዘብ መዋጮ የመሰብሰቡ ስራ እንኳ ቆሟል። ይሄ አልበቃ ብሎ በደንብ ባልተጠና የፖለቲካ አካሄድ ስነልቦናቸው ሲጎዳ አይቶ በሁዋላ ከመጸጸት አሁን የሚመስለንን መናገሩ ይጠቅማል እንጅ አይጎዳም።

እነ አንዱዓለም ያልመከሩበት ፖሊሲ በምንም ታዕምር ተግባራዊ መሆን የለበትም! አንዱዓለም የታሰረው ሮቢን አይላንድ አይደለም! ማማከር ይችላል። አንዱዓለም ” አይቃወምም ፣ ይስማማል” በሚል የሚቀርበው መከራከሪያ ብዙ መንገድ አይወስድም።

አንዱአያም አራጌ ” ያልተሄደበት መንገድ” በሚለው መጽሀፉ በገጽ 58 ላይ ስለ አምባገነኖች ባህሪ የጠቀሰው ትክክለኛ ነው እላለሁ ” የአለም ታሪክ እንደሚያሳየው አምባገነኖች በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣናቸው ለቀው አያውቁም። እንደውም እነርሱ ስልጣን ከለቀቁ ሀገር እንደሚበታተን፣ ህዝብ እንደሚጨራረሽ የማስፈራሪያ ፕሮፓጋንዳ ይነዛሉ። ፈርተው ያስፈራሉ። ይሄ ባህሪያቸው መሆኑን መረዳትና ያለመዘናጋት መታገል ያስፈልጋል… ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ አሁን ያለውን አገዛዝ ለህዝብ ፈቃድ እንዲገዛ የግድ ማለት ያስፍልጋል።”

እኔ ነገ ስለሚሆነው ነገር ነው የምጽፈው፣ ትክክል መሆንና አለመሆኔን ለማየት ትንሽ ጊዜ መጠበቁ የሚሻል ይመስለኛል። ተሳስቼም ከሆነ ያን ጊዜ ሂሳቤን አወራርዳለሁ። ( በነገራችን ላይ አንድ ጊዜም እንዲሁ ሰማያዊ ፓርቲ በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዱን በመቃወሜና ቀኑን እንዲቀይረው በመጠየቄ ብዙ ትችቶችን አስተናግጃለሁ፤ በሁዋላ ፓርቲው ( የእኔን ምክር ሰምቶ ይሁን አይሁን አላውቅም) ቀኑን ቀየረው፤ ለወረደብኝ ትችት ግን ሂሳቡን ያወራረደልኝ ሰው አልነበረም፤ ሲጽፉብኝ የነበሩ የማውቃቸው ሰዎች ሳይቀር ድምጻቸውን አጠፉ። እኔ ከተሳሳትኩ ሂሳቤን እንደማወራርድ ቃል እገባለሁ፣ ለመመጻደቅ ሳይሆን ለእድገት ይጠቅማል ብየ ስለማምን ነው።)

አቡጊዳ –ሰማያዊ ፓርቲ በጎንደር ከተማ በድንበሩ ጉዳይ ሰልፍ ሊጠራ ነው

$
0
0

በኢትዮጵያ ዉስጥ በምርጫ ቢርድ ተመዝግቦ እየተንቀሳቀስ ያለው የሰማያዊ ፓርቲ ፣ በጎንደር ከተማ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ለመጥራት እየተዘጋጀ እንደሆነ ፓርቲዉ በፌስ ቡኩ ገጽ ባወጣው መግለጫ ገለጸ።

«ሕወሓት ኢህአዴግ በህገ ወጥ መንገድ ሉዓላዊ መሬታችንን ለሱዳን መንግስት አሳልፎ አሳልፎ ለመስጠት እያደረገ ያለውን ህገወጥና ሀገር ቆርሶ የመስጠት ወንጀል በመቃወም ሰማያዊ ፓርቲ እሁድ ጥር 25 2006 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ ማዘጋጀቱን የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ብርሀኑ ተክለ ያሬድ ገለፁ፡፡የህዝብ ግንኙነት ሃላፊው አያይዘው እንደገለፁት ቅዳሜ ጥር 17 2006 ዓ.ም በፓርቲው ፅህፈት ቤት የፓናል ውይይት እንደሚደረግና በነዚህ ፐሮግራሞች ላይም የፖለቲካ ፓርቲዎች የሲቪክ ተቋማትና ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንዲሳተፍ ጥሪ አስተላልፈዋል»

ሲል በሰልፉ ሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶ፣ የሲቪክ ማህበራት እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርቧል። የሰማያዊ ፓርቲ ምን ያህል በጎንደር ሰልፍ ዙሪያ፣ ከሌልቾ ተቃዋሚዎች ጋር ምክክር እንዳደረገ እስካሁን ለማወቅ አልተቻለም። በሰኔ 2005 ዓ.ም ወቅት ሰማያዊ፣ በሕዝብ ዘንድ የበለጠ እንዲታወቅበት ያደረገውን የአዲስ አበባን ሰልፍ፣ መኢአድ እንዲጉሁም የአንድነት ፓርቲ ድጋፉቸዉን ሰጥተዉ እንደነበረ ይታወቃል።

ከዚያም በኋላ ከሰኔ 2005 ዓ.ም እስከ መስከረም 2006 ዓ.ም ፣ የአንድነት ፓርቲ በተለያዩ የአገሪቷ ግዛቶች የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል እንቅስቃሴ ሥር በጠራቸው ሰላማዊ ሰልፎች፣ የሰማያዊ ፓርቲ ለርሱ ድጋፍ እንደተደረገለት፣ የአጸፋዉን ድጋፍ አለመስጠቱ የሚረሳ አይደለም። በተለይም በመስከረም በአዲስ አበባ የተደረገዉን እና አንድነት ፓርቲ የጠራዉን ሰላማዊ ሰልፍ ፣ ሰላሳ ሶስቱ በሚባለዉ ስብስብ ዉስጥ ያሉ ድርጅቶች ሲቀላቀሉት፣ ሰማያዊ ፓርቲ ግን ፣ ከሌሎች ጋር አብሮ ከመስራት፣ በተናጥል የራሱን ሰልፍ በመጥራቱ ብዙዎችን አላስደሰተም።

የአንድነት ፓርቲ ለአማራዉ ክልል አስተዳዳሪና ለአቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በድበቅ፣ በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ዙሪያ እየተሰራ ያለዉን ጉዳይ በተመለከተ፣ በአስቸኳይሁሉም ነገር ለሕዝብ ይፋ እንዲሆን መጠየቃቸው፣ በዚህም ዙሪያ ፓርቲዉ በአዲስ አበባ ሕዝቡን ለማወያየት ዝግጅት እያደረገ እንደሆነም በቅርቡ ተዘግቧል።

በጎንደር ከተማ አንድነት ከአራት ወራት በፊት ባደረገዉ ሰላማዊ ሰልፍ ከ40 ሺሆች በላይ የሚሆን ሕዝብ መገኘቱ ይታወሳል።

የሰማያዊ ፓርቲ ከብቻ ጉዞ ተቆጥቦ፣ ይህ የኢትዮ-ሱዳን ቦርደር ፣ ሁሉንም ኢትዮጵያዉያን የሚመለከት አንገብጋቢ የአገር ጉዳይ መሆኑ ተረድቶ፣ በአስቸኳይ ፣ ከአንድነት፣ መኢአድና ከመሳሰሉ ፓርቲ አመራሮች ጋር በመነጋገር፣ ጥር 25 2006 ዓ.ም የሚደረገዉን ሰልፍ በጋራ ማቀናበር እንዳለበት የሚናገሩ አንድ የፖለቲካ ተንታኝ፣ «የድርጅት መሪዎች ከድርጅታዉ ጥቅምና ዝና ይልቅ ለአገር ማሰብ እንዳለባቸው ማወቅ አለባቸዉ። ከሰማያዊ ፓርቲ በፊት ኢትዮጵያ ትቀድማለች።ከአንድነት ፓርቲ በፊት ኢትዮጱያ ትቀድማለች። ከመኢአድ በፊት ኢትዮጵያ ትቀድማለች። ከአረና በፊት ኢትዮጵያ ትቀድማለች» ሲሉ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዉያን ሁሉ በዘር፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ ፓርቲ ልዩነት ፣ ሳይከፋፈሉ ለኢትዮጵያ እንዲቆሙ ጠይቀዋል።

ሁለተኛ መልስ ለኢሳቱ አቶ ፋሲል –ግርማ ካሳ

$
0
0

ሁለተኛ መልስ ለኢሳቱ አቶ ፋሲል – ግርማ ካሳ
=============================

ጤና ይስጥልኝ፣ ዉድ ወንድሜ አቶ ፋሲል። «የአንድነት ፓርቲ የመጪው ጊዜ ፈተና» በሚል ርእስ በጻፉት ላይ ለሰጠኹት አስተያየት፣ ለአንባቢያን ያቀረቡትን የመልስ መልስ አነበብኩ። ግሩም አቀራረብና ለዉይይት የሚረዱ ነጥቦች በማንሳትዎ ተደስቻለሁ። ዜጎች የተለያዩ ሃሳቦች ሊኗራቸው ይችላል። ብዙ ጊዜ፣ በተለይም በዳያስፖራ ፖለቲካ የተለመደው ፣ የሃሳብ ልዩነቶች በተፈጠሩ ጊዜ ያኛው ወገንን ማገድ፣ መሳደብ፣ ወያኔ ነው ሆዳም ነው እያሉ መጥራት ነዉ። ብዙ ጊዜ የሃሳብ ልዩነቶችን በሰለጠነ መልኩ የመወያየትና የመቻቻል ባህል አይታይም።

እርስዎም ላቀረብኳቸው ሃሳቦች አክብሮት በተላበሰ የኢትዮጵያዊ ጨዋነት ምላሽ ስለሰጡኝ ላመሰግንዎት እወዳለሁ። ሌሎች በራሳቸው አይን ላይ ያለውን ጉድፍ ማየት ተስኗቸው፣ እነርሱን አገር ወዳድ ሌላዉ ግን አገር አጥፊ አድርገዉ የሚወስዱ የዳያስፖራ ጸንፈኛ አክራሪዎች፣ ከርስዎ ትልቅ ትምህርት ይወስዳሉ ብዬ አስባለሁ።

ባለፈዉ ጽሁፉዎ አቶ ልደቱ አያሌው ነበሩ የተነሱት። በዚህኛው ደግሞ አቶ ኃይሉ ሻዉል እና ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ተነስተዋል። በቅድሚያ ስለ ወ/ት ብርቱካን ትንሽ ልበልዎት።

«ወ/ት ብርቱካን እስር ቤት ከገቡ በኋላ ፓርቲዋ ( አመራሩ) ረስቷት ነበር። እንዴያውም አንዳንዶች “እንኳን ታሰረች” ሳይሉ ሁሉ አልቀረም። ያን ጊዜ ማን ነበር ለብርቱካን አብዝቶ የጮኸው? ዲያስፖራው እና በተለይ ኢሳት አልነበሩምን? የካናዳው ልጅ ተክሌ ”ብርቱካኔ ብረሳሽ ቀኜ ይርሳሽ” ብሎ ዜማ ያወጣላት አምስተርዳም የኢሳት ስቱዲዮ ውስጥ ሆኖ ነው» ያሉት አባባል ትንሽ ቆረቆረኝ። እርግጥ ነዉ ወንድም ተክሌ ለወ/ት ብርቱካን መፈታት ብዙ ሲጽፍ እንደነበረ አውቃለሁ። ከብርቱካን ትፈታ ግብረ ኃይል ጋር ብዙ ሰርቷል። ነገር ግን ኢሳት፣ አሁን እርስዎ እንደሚሉት ለወ/ቷ መፈታት፣ ብዙ የአየር ሰዓት ሰጥቶ መታገሉን ግን አላስታወስም። የማላውቀዉን ስላሳወቁኝ አመሰግናለሁ።

«ወ/ት ብርቱካን ከታሰሩ በኋላ ፓርቲዋ ፣ አመራሯ ረስቷት ነበር» ያሉት አባባል ግን ከእዉነት የራቀ ይመስለኛል። በነገራችን ላይ እርስዎ በጽሁፍዎ እያሞካሹት ያለው፣ እኔም የማከብረዉና የምወደው ወንድሜ፣ አንዱዋለም አራጌ፣ የዚሁ «ብርቱካንን ረስቷል» ያሉት የአንድነት አመራር አባል እንደነበረም አይርሱት። የፓርቲዉ አመራር አባላት፣ ምን ያደርጉ እንደነበረ ብዙ መረጃ ያልዎት አልመሰለኝም። ምናልባት ያኔ ትኩርትዎት ከመረብ በስተሰሜን ስለነበረ ሊሆን ይችላል።፡«ተሳስቼ ከሆነ ሃሳቤን አወራርዳለሁ» እንዳሉ፣ ሃሳብዎትን ይመረምሩ ዘንድ፣ ከብዙዎች፣ ሶስት እዉነታዎችን ብቻ ልንገርዎት፡

1. በዳያስፖራ በቀዳሚነት ለብርቱካን መፈታት ሲታገል የነበረዉ፣ የብርቱካን ትፈታ ግብረ ኃይል ነበር። ይህ ግብረ ኃይል በየወሩ ለብርቱካን ቤተሰቦች የገንዘብ እርዳታ እንዲሰጥ ከማድረጉ በተጨማሪ፣ የተለያዩ ዘመቻዎችን በሁሉም አቅጣጫዎች ይሰራና ይመራ የነበረ ነዉ። ከሊቀመንበሩ አቶ ግርማ ግዛው (አሁን የአንድነት ሰሜን አሜሪካ አመራር አባል) በስተቀር፣ የግብረ ኃይሉ ሌሎች አባላት ብዙም አይታወቁም ነበር።

ይህ ግብረ ኃይል እንዴት እንደተቋቋመ ልንገርዎት። ያኔ በአቶ አክሎግ ልመንህ የሚመራዉ የሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ድርጅት፣ አዲስ አበባ ካለዉ የአንድነት ፓርቲ ጋር በመመካከር፣ «የብርቱካን ጉዳይ የፓርቲ ጉዳይ ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያዉያን ጉዳይ ነው» በሚል ነዉ፣ የብርቱካን ትፈታ ግብረ ኃይል እንዲቋቋም የተደረገዉ። ስለዚህ የብርቱካን ግብረ ኃይልን ሲያዩ፣ ለዚያ ምክንያት የሆነውን ፣ «ብርቱካንን ረስተዋት ነበር» ያሏቸዉን የፓርቲዉ አመራሮች ማየት አለብዎት።

2. ወ/ት ብርቱካን እሥር ቤት በነበሩበት ወቅት፣ ሳያቋርጡ፣ ተራ በተራ፣ ከሰኞ እስከ አርብ፣ እርስዎ «ብርቱካንን ረስተዋት ነበር» ያሏቸው የአንድነት አመራር አባላት፣ ቃሊቲ ድረስ ምግብ ሲያመላልሱ እንደነበረስ ያዉቁ ኖሯል ? ጨዋዎችና ትሁቶች በመሆናቸው «እንዲህ እያደረግን ነዉ» ብለው አልተናገሩም። በብርቱካን ስም ለመነገድ አልሞከሩም፡፡ ይሄን ያደርጉ እንደነበረ የታወቀዉም፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከቃሊት እሥር ቤት እንደወጡ፣ በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት በመሄድ ለአመራር አባላቱ ምስጋናቸውን እንዳቀረቡ በተዘገበበት ወቅት ነዉ። (ቅዳሜና እሁድ ወ/ሮ አልማዝ ነበሩ ምግብ ለልጃቸዉ ይዘዉ ይሄዱ የነበሩት) በወቅቱ፣ የአንድነት አመራር አባላት፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን ለመጎብኘት ብዙ ጊዜ ሞክረዉ፣ ገዢዉ ፓርቲ ፈቃድ ሊሰጣቸዉ ስላልቻለ ብዙም ለመጠየቅ አልቻሉምም ነበር።

3. ፓርቲዉ በሚሰጣቸው አመራሮች፣ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች፣ የብርቱካን ፎቶ ያለበት ኬኔቴራ እያደረጉ፣ ለወይዘሪቷ መፈታት ብዙ ዘመቻ በአገር ዉስጥ ተደርጓል። ብዙዎች የብርቱካንን ከኔቴራ ካላወለቃችሁ ተብለው የታሰሩም ነበሩ። በአንድነት ጽ/ቤት በየጊዜዉ የሻማ ማብራት ሥነ ስርዓትም ይደረግ ነበር።

እነዚህን ጥቂቶች እንደምሳሌ ሳቀርብ፣ የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላት ያኔ የበለጠ መስራት አልነበረባቸውም ነበር ማለቴ አይደለም። በወቅቱ በአንድነት ፓርቲ ስለነበሩት ችግሮችና ስህተቶች ንገረኝ የሚሉኝ ከሆነ፣ ብዙ ልነግርዎት እችላለሁ። የፓርቲዉ አመራሮች ብዙ ያጠፏቸው ጥፋቶች፣ የሰሯቸው ስህተቶች አሉ። ማን የማይሳሳት አለ ? ነገር ግን «ብርቱካንን ረስተው ነበር» ያሉት ክስ፣ በአክብሮት እዉነቱን ልንገርዎትና፣ ከመስመር ያለፈ፣ የአንድነት አመራር አባላትን ይቅርታ ሊጠይቁበት የሚገባ መሰለኝ።

አሁን ወደ አቶ ኃይሉ ሻዉልና የስነ ምግባር ኮዱ ልምጣ። በአሁኑ ጊዜ የአንድነት ፓርቲ ከመኢአድ ጋር ለመዋሃድ ንግግር ላይ ስላለ ወደ ኋላ ተመልሼ ስለአቶ ኃይሉ ሻውልም ሆነ ስለመኢአድ ማውራት አልፈልግም። መኢአድም ፣ አንድነትም ካለፈው ስህተቶቻቸው ተመረው አብሮ ለመስራት ትልቅ ፍላጎት አላቸው። በዚህም ረገድ በርቱ፣ ተበራቱ እያልኳቸው፣ አቶ ኃይሉ ሻወል የተናገሩት ትቼ ወደ ስነ ምግባር ኮዱ ልምጣ።

እርስዎ እንዳሉት፣ የስነ ምግባር ኮዱን መፈረም ለዉጥ አያመጣም። በዚስ ትክክል ኖት ። ሰነዱ እኮ ተራ ወረቀት ነው። በዚያኛዉ ወገን ደግሞ፣ የስነ ምግባር ኮዱን አለመፈረምም በራሱ ያመጣው ፋይዳም አልነበረም። መኢአድና ሌሎች መፈረማቸው ምንም አልጠቀማቸዉም እንዳሉት ሁሉ፣ መድረክና ሌሎችም አለመፈረማቸው ምን ያመጣላቸው ጥቅም የለም። አንድ ሰው «ሰነዱን ፈረሙ ወይም አልፈረሙም» ብሎ የሚደሰት ወይንም የሚቆጣ ከሆነ፣ ያ ሰው ብስለት የጎደለው ሰው ነዉ ማለት ነዉ።

የአንድነት ፓርቲ በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ የመጣዉ፣ ሰነዱን ስላልፈረመ ሳይሆን፣ ትልቅ ድርጅታዊ ሥራ እየሰራ ስላለ ነዉ። የሚሊየነሞች ድምጽ ለነጻነት የተስኘው እንቅስቅሴ አይነት እንቅስቅሴዎች በማድረጉ ነዉ። ይዞ የሚያራምዳቸው የሰለጠነ፣ የፍቅርና የኢትዮጵያዊነት ዴሞክራቲክ ፖለቲካዉና እሴቶቹ ናቸው።

በሴምፕቴበር 2012፣ አቶ በረከት ስምኦን በሰንደቅ ጋዜጣ ላይ በሰጡት አስተያየት «መድረኩ የስነ-ምግባር ኮዱን ካልፈረመ አንደራደርም» ማለታቸውን ተመርኩዤ፣ ሴምፕቴምበር 20 2012፣ ለአንባቢያን ባቀረብኩትና ፍኖት ባወጣው ጽሁፌ፣ ሰሞኑን ከማካፍላቸው ሃሳቦች ጋር ተመሳሳይነት ያላቸውን ነጥቦች፣ ያኔም አስፍሬ ነበር።

«የመድረክ አመራር አባላት፣ ያኔ የስነ ምግባር ሰነዱን አለመፈረማቸው በወቅቱ ከነበረው ሁኔታ አንጻር ስናየው፣ ሊያስኬድ ቢችልም፣ አሁን ባለንበት ወቅት ግን ፣ ይህን ሰነድ በመፈረም ኳሷን ወደ ኢሕአዴግ ሜዳ ቢልኳት ጥሩ ይሆናል ብዬ አስባለሁ፡ ቢያንስ ቢያንስ፣ አቶ በረከት «መድረኩ አመጸኛ ነው» ለሚሉት ክሳቸው እንደምክንያት የሚያቀርቡትን አንድ ነጥብ ያሳጣቸዋል» ብዬ በመጻፍ የመድረክ አለመፈረም ገዢዉ ፓርቲ የበለጠ መድረክን ለማግለል እንደመሳሪያ መጠቀሙን ለማሳየት ሞክሪያለሁ።

ሳክልም «የስነ ምግባር ኮዱ፣ ሕግ እንደመሆኑ፣ የመድረክ አለመፈረም ችግር ሊያመጣ እንደማይገባዉም፣ ለሰላም ሲባል መፈረሙም ችግር የለዉም። ይህ በጣም ትንሽ ጉዳይ ነዉ። ትንሹ ጉዳይ ደግሞ በትልቁ ነገር ላይ እንዳንወያይ ሊያድገን አይገባም። በመሆኑም ለሰላም ሲባል፣ መድረኩ በአስቸኳይ የስነ-ምግባር ኮዱን በራሱ አነሳሽነት በመፈረም ጉልህ እንቅስቃሴዎች እንዲያደርግ እመክራለሁ። ይሄንንም ያደርጋል የሚል ሙሉ ተስፋ አለኝ» ብዬ ነበር የጻፍኩት። ለርስዎ ጽሁፍ በመለስኩት የመጀመሪያው ጽሁፌ፣ ሰነዱ ያኔ መድረክ ያለፈረመው፣ በራሱ ሰነዱ ችግሮ ኖርቶ ሳይሆን ፣ ሌሎች ሰነዶች አብረዉ ካተፈረሙ በሚል ነበር። ሁሉም ወይም ባዶ የሚል አቋም ከመያዝ፣ ከባዶ አንድ ይሻላል፣ አንዱ ይዘን ወደ ሁለቱን እንሂድ የሚል ነበር አስተሳሰቤ።

በወቅቱ የመድረክ አመራር ፣ ሆነ የአንድነት፣ ሃሳቤን ለማስተናገድ ፈቃደኛ አልነበሩም። አሁን ያለውም አዲሱ አመራር ይቀበል አይቀበል አላውቅም። በሂደት የምናየው ይሆናል።

የአንድነት ፓርቲ ከኢሕአዴግ ጋር ቁጭ ብለን መነጋገር አለብን የሚል አቋሙን ጠንከር ባለ መልኩ አዲሱ አመራር ይፋ አድርጓል። የአለም አቀፍ ማህበረሰብም ፣ ሰላም ወዳድ ኢትዮጵያዉያ ሁሉ፣ ዉይይቶችና ንግግሮች እንዲደረጉ ይፈልጋል። ኢሕአዴግ ዉስጥ ያሉ፣ ጤነኛ አካላት፣ ድርጅታቸው ወደ ዉይይት እንዲመጣ ይፈልጋሉ። በአሁኑ ወቅት ስልጣኑን ጨብጠው ያሉ የሕወሃት/ኢሕአዴግ አክራሪዎች ግን በስልጣናቸው እንዲቆዩ ጠንካራ የሚሉትን ድርጅት ማዳከም እንጂ ለዚያ ድርጅት መድረክ መስጠት አይፈልጉም። በአለም አቀፍ ማህበረሰቡም ሆነ በኢሕአደግ ዉስጥ ባሉ ሞደሬቶች «ለምን ከአንድነት ጋር አትነጋገሩም ? » የሚል ግፊት ሲመጣባቸው ፣ ከማንም ተቃዋሚ ጋር መነጋገር የማይፈልጉት አክራሪዎቹ፣ የሚመልሱት መልስ «እኛ ለመነጋገር ዝግጁ ነን። እነርሱ ናቸው ፍቃደኛ ያልሆኑ። ፍቃደኛ ከሆኑ ለምን ሰነዱን አይፈርሙም ? » የሚል ነዉ።

እንግዲህ የኔ ትሁት አስተያየት፣ የአንድነት ፓርቲ የስነ ምግባር ኮዱን በመፈረም፣ ለሰላምና ለድርድር መሰናክል የሆነውን ጉዳይ ከመንገዱ እንዲወገድ ቢያደርግ ጥሩ ሊሆን ይችላል እላለሁ። ያን በማድረጉ አገዛዙ ለዉይይት ይዘጋጃል ማለት አይደለም።\ እዚህ ላይ ልብ ይበሉ። እርስዎም ስለአገዛዙ አምባገነንነት ቅልብጭ አርገው እንደሚያውቁትም እኛም በደንብ እናውቃለን። ነገር ግን አንድነት በኢሕአዴግ ዉስጥ ላሉ ሞደሬቶች፣ ለአለም አቀፍ ማህበረሰቡ፣ ትልቅ መልእክት ያስተላልፍበታል። የሕወሃት/ኢሕአዴግ አካራሪዎች አንድነት የአመጽ ኃይል ነው የሚሉበትን መከራከሪያ ያሳጣቸዋል።። በሰላም ወዳዱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድም፣ ለሰላም እስከ ጫፍ መሄዳቸውን፣ የሰለጠነ ፖለቲካ የሚያራምዱ መሆናቸውን በማሳየት፣ ዝም ብሎ የነበረዉን የአብዛኛው የኢትዮጵያን ህዝብ ድጋፍ ሊያገኙበት ይችላሉ። ይህን በማድረጋቸው ትልቅነታቸውን በገሃድ ያስመሰክራሉ። ሌላም ደግሞ ትልቁ ምክንያቴ ሰነዱ ኢሕአዴግ ኖረን አልኖረም ለወደፊት የሚጠቅም ሰነድ በመሆኑም ነዉ። ከምርጫ በኋላ ችግሮች፣ ደም መፋሰሶች እንዳይኖሩ የምርጫዉን ሂደት ሰላማዊ በሆነ መልክይ ጋይድ ሊያደርግ የሚችል ሰነድ ነው። እርስዎ እንደሚያስቡት ክፉ ሰነድ አይደለም።

አንድ ነገር ግን ግልጽ ላድርግ። በዉጭ ያለን፣ እኔም ፣ እርስዎም፣ ስለአንድነት ፓርቲ ብዙ ልናውቅ ብንችልም፣ ከኛ፣ በበለጠ ግን፣ አገር ቤት ያሉት፣ ስላለው ሁኔታ ያውቃሉ። እንግዲህ የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላት፣ እኔም፣ እርስዎም፣ እንዲሁም ሌሎች ከተለያዩ ማእዘናት የምናቀርባቸውን አስተያየቶችን አገናዝበው የሚወስኑትን ይወስናሉ የሚል እምነት አለኝ። ውይይቱ፣ ክርክሩ መልካም ነዉ። ይቀጥልበት እላለሁ።

በመጨረሻ ይችን አጭር ወንድማዊ ምክር ጣል ላድርግልዎትና ላብቃ። የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላት ተጠያቂ መሆን አለባቸው። ስድስት ወራት ይጠብቁና፣ በአንድነት ዉስጥ እየተሰራ ያለውን ገምግመው፣ አመዛዝነው፣ በኢንጂነር ግዛቸውም ሆነ ሌሎች የድርጅቱ አመራሮች ተግባራት ላይ ትችት እንዲጽፍ አበረታታቸዋለሁ። በጎም ይሆን መጥፎ። ጋዜጠኞች የፖለቲካ መሪዎችን ማፋጠጥ አለባችው። የድርጂቶች ፕሮፖጋንዲስቶ መሆን የለባቸዉ። ግን ሲተቹ፣ በመላምትና በስሜት ሳይሆን፣ መረጃና እዉነታን በመያዝ፣ የጋዜጠኝነትን ፕሮፌሽናሊዝምን በጠበቀ መልኩ።

ሌላዉ አቶ ፋሲል፣ ገለልተኝነትዎትን ማሳየት አለብዎት ባይ ነኝ። የሌሎች የፖለቲክ መሪዎች የሥራ እንቅስቃሴ ቢመረምሩና ጋዜጣዊ አስተያየታቸውን ቢያስነብቡንም መልካም ይሆናል። ለምሳሌ ዶር ብርሃኑ ነጋ፣ ይኸው ለስድስት አመታታ ግንቦት ሰባትን እየመሩ ናቸው፤ ብቸኛው መሪ ናቸው። (ዶር ብርሃኑ ላለፉት ስድስት አመታት ብችኛ የግንቦት ሊቀመንበር ሆነዉ ባለበት ሁኔታ፣ የአንድነት ፓርቲ ግን ሶስት ሊቀመናብርትን አፈራርቋል) በዚህ በስድስት አመታት ዉስጥ ምን ተደረገ ? ከሕዝቡ ብዙ ገንዘብ ተሰብስቦ ፣ አንድ ቀበሌ በጠመንጃ ነጻ ወጣ ወይ? ይኽዉ ዉጤቱ በሻእቢያ ቀሚስ ዉስጥ መተኛት አልሆነምን ? ይሄንን በሚገባ እያወቁ፣ በነዶር ብርሃኑ እንቅስቃሴ ላይ እንደ ጋዜጠኛ ትችት ማቅረብ አልነበረብዎትምን? የግንቦት ሰባት የስድስት አመታት ክስረትን እንዳላዩ ሆነዉስ ለምን ያልፋሉ ? ፈረንጆች እንደሚሉት Why the double standard ?

ትላንት ፓልቶክ ላይ «ፋሲል የዶር ብርሃኑ ፈረስ ነዉ …የግንቦት ሰባት አባልና ካድሬ ነዉ …በነ ዶር ብርሃኑ ታዞ ነዉ የሚጽፈው» እያሉ የሚናገሩ ነበሩ። ያንን አባባል አልጋራዉም። ለምን መረጃ የለኝምና። ግንቦት ሰባት ሚስጥራዊ በመሆኑ እርስዎ አባል ይሆኑ አይሆኑ ማወቅ አልችልም። ነገር ግን ግንቦት ሰባትን እንደ ጣኦት የማምለክ ያህል፣ አንዳች ትንፍሽ ሳይሉ፣ አንድነት ፓርቲ ላይ ይሄን ያህል መሰረት የሌለዉ ጠንካራ ትችት ማቅረብዎ፣ በብዙዎች አይምሮ ዉስጥ ጥያቄን የሚጭር ነዉ። እንግዲህ በምን መልኩ ይሄንን ጥያቄ እንደሚያስተናግዱት አላውቅም። ጉዳዩን ለርስዎና ለሕሊናዎ ትቼዋለሁ።

በድጋሜ ለጊዜዎት ምስጋና አያቀረብኩ እሰናበትዎታለሁ። ቸር ይግጠምዎት !


አቡጊዳ –ርዮት አለሙ ጡቷ ላይ ቱመር አለ፣ ግን ክትትል አላገኝችም !

$
0
0

አቡጊዳ – ርዮት አለሙ ጡቷ ላይ ቱመር አለ፣ ግን ክትትል አላገኝችም !

ሴፍ ዎርልድ ፎር ዎማን ( safe world for women) የተሰኘው ለሴቶች መብት የሚሟገተዉ ድርጅት፣ ርዮት አለሙ እንድትፈታ የሚጠይቅ ፔትሽኖች እያስፈረመ ነዉ። ድርጅቱ, የርዮት አለሙ አባት አቶ አለሙ ጎቤዶን በመጥቀስ እንዳስቀመጠዉ፣ ርዮት አለሙ፣ በአንድ ጡቷ ላይ ቱመር ያለ ሲሆን ፣ ከጡቷም ደም እንደሚፈስ ይገልጻል።

ያለችበት ሁኔታ ክትትል የሚያስፈለገዉ ቢሆንም፣ ክትትል እያደረገች እንዳልሆነ የገልጹት አቶ አለሙ፣ የልጃቸው ጤንነት ሁኔታ በጣም እንዳሳሰባቸው ይናገራሉ።

ርዮት አለሙ በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ እንግሊዘኛ አስተምራ እንደወጣች ሲሆን በአገዛዙ ደህንነቶች የተያዘችው፣ ከተያዘች ከሁለት አመት ከስደስት ወራት አልፏታል።

ሴፍ ዎርልድ ፎር አፍሪካ ወደ አዘጋጀዉ ፔትሽን ለመሄድ እዚህ ይጫኑ !

የማለዳ ወግ ኢትዮጵያን ለማየት ፣ ጥምቀት በጎንደር ማክበር … ! ነቢዩ ሲራክ

$
0
0

የከተራው በአል

ከተራ ምንድን ነው? ከሚለው ትርጓሜ እንነሳ … በየዓመቱ የጥምቀት በዓል በድመቀት ይከበራል፡፡ ከበዓሉ በፊት የከተራ በዓል የሚከበርበትን ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ገለጻ ከተራ ከበበ ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡ የጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላል፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥል ይውላል፡፡ የምንጮች ውኃ ደካማ በመሆኑ እንዲጠራቀም ይከተራል ፣ ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ ይገደባል፡፡

ከተራ በዓል በየዓመቱ በበዓለ ጥምቀት ዋዜማ ጥር 10 ቀን ይውላል ። የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታይ ምእመናን ሲወርድ ሲዋረድ ይዘው በመጡት ሃይማኔታዊና ባህላዊ እሴት መሰረት በጥምቀትን በዓል ዋዜማ ወንዝ ምንጭ ውሃው ይገደባል ፣ ይከተራል። ውኃው የሚከተረው በማግሥቱ ጥር 11 ቀን የጥምቀት በዓል ስለሚከበር ለሕዝቡ መጠመቂያ እንዲሆን ነው። ይህ በጥምቀት ዋዜማ የሚደረገው ውኃውን መከተርና መገደብ ስርአትም ” ከተራ ” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡

የከተራው በዓል ሲከበር

ታቦተ ሕጉን ተሸክመው ዮርዳኖስን እንደ ተሻገሩት ካህናተ ኦሪት፤ ካህናቱ የማይለወጠውን ታቦተ ሕጉን በራሳቸው ተሸክመው የብሉዩን ሥርዓት ከሐዲስ ኪዳን ጋር አንድ አድርገው የሐዲስ ኪዳን መሠረት ኢየሱስ ክርስቶስን እያሰቡ፤ ካህናተ ሐዲስም ወደ ከተራ (ዮርዳኖስ) ይጓዛሉ፡፡ ሊቃውንቱም እንዲሁ ለበዓሉ የሚስማማውን ቃለ እግዚአብሔር እያደረሱ እንደሚያድሩ የሃይማኖት ልሂቃን አባቶች ያስረዳሉ።

የከተራ ዕለት ጥር 10 ቀን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ የሄደበትን ለማዘከር ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን “ኃዳፌ ነፍስ ለጻድቃን” የሚለውን ዋዜማ ይቆማሉ፡፡ የዋዜማው ቀለም ከቀኑ በአራት ሰዓት በመላው አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ይጀመራል ። ከዚያም የዋዜማው ሥርዐት ቅዱስ ተብሎ እስከ ሰላም ያለው ቀለም ይደርሳል፡፡ በዕለቱም ቅዳሴ ይቀደሳል፡፡ ታቦተ ሕጉን የሚያነሡት ሰሞነኛ ካህን ከምግበ ሥጋ ተከልክለው ለዕለቱ የሚገባውን ጸሎት ያደርሳሉ፡፡በከተራው ዕለት ድንኳን ተተክሎ፣ ዳሱ ተጥሎና ውኃው ተከትሮ ሁሉም ነገር ከተስተካከለ በኋላ ታቦተ ሕጉ የሚንቀሳቀስበት ሰዓት ሲደርስ የየቤተ መቅደሱ ታቦታት በወርቅና በብር መጎናጸፊያ እየተሸፈኑ በተለያየ ኅብር በተሸለሙ የክህነት አልባሳት በደመቁ ካህናትና የመጾር መስቀል በያዙ ዲያቆናት ከብረው፣ ከቤተ መቅደስ ወደ አብሕርት /ምጥማቃት/ ለመሄድ ሲነሡ መላው አብያተ ክርስቲያናት የደወል ድምፅ ያሰማሉ፡፡ ምእመናን ከልጅ እስከ ዐዋቂ በዐጸደ ቤተ ክርስቲንና ታቦታቱ በሚያልፉባቸው ህዝበ ክርስትያኑ ያጅቧቸዋል። በአማሩ አልባሳት ተውበውም መንገዶች በእልልታ በሆታና በጭፈራ በማድመቅ ታቦቶችን በክብር ወደ ተዘጋጀው የበዓሉ ቦታ አጅበው ይደርሳሉ!

በዓለ ጥምቀት እና ኢትዮጵያ

ታላቁ የከተራ እና የጥምቀት በዓል ሲነሳ ኢትዮጵያውያን ሩቅ ዘመንን ተሻግረን ቅዱሳን ሰማዕት አባቶችን ሊቃውንት አባቶችን አስተምሮት እናዘክራለን። በቅዱስ ላልይበላ ዘመነ መንግሥት በኢትዮጵያ ምድር እየተመላለሱ በብሕትውና እና በስብከተ ወንጌል ያገለግሉ የነበሩት ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአክሱም፣ በመቐለና በመርጡለ ማርያም እየተዘዋወሩ ባሕረ ጥምቀቱን ባርከዋል፡፡ በዐፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት (1260-1275 ዓ.ም) በጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (1203-1204 ዓ.ም) አሳሳቢነት የተጀመረው ሥርዐተ በዓል ተጠናክሮ እንዲቀጥል በዐዋጅ ትእዛዝ አስተላልፈዋል፡፡ ታቦታቱም በሕዝብ ጥበቃና ክብካቤ ተደርጎላቸው በየጥምቀተ ባሕሩ እንዲያድሩ ወስነዋል፡፡ የበዓሉ አከባበር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋና አድማሱ ብሔራዊነትን እየያዘ መጣ፡፡

ከዐፄ ገብረ መስቀል ጀምሮ የአደባባይ በዓል የሆነው የጥምቀት በዓል በ15ኛው ክ/ዘመን በደገኛው ኢትዮጵያዊው ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ(1426-1460 ዓ.ም) አማካኝነት ታቦታቱ ወደ ወንዝ ወርደው ዕለቱን እንዳይመለሱ፣ በዚያ ፈንታ በጥምቀት ዋዜማ ጥር 10 ቀን ከሰዓት በኋላ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርደው እንዲያድሩ፣ አገሩን በኪደተ እግር ይባርኩም ዘንድ በሄዱበት መንገድ እንዳይመለሱ በዐዋጅ ወሰኑ፡፡ ይህን ታሪክ በመከተል ዐፄ ናዖድ (1486-1500) ዓ.ም) ማንኛውም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ምእመን ታቦተ ሕጉ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ በሚወርድበት እና ከባሕረ ጥምቀቱ ወደ ቤተ መቅደሱ በሚመለስበት ጊዜ አጅቦ አውርዶ፣ አጅቦ መመለስ እንዳለበት በዐዋጅ አስነግረው ነበር፡፡ ሕዝቡም ታቦታተ ሕጉን በሆታና በእልልታ ከቤተ መቅደስ አጅቦ ከአወጣ በኋላ በባሕረ ጥምቀት ከትሞ ማደር ጀመረ ። …

ኢትዮጵያ ዜና ጥምቀተ ክርስቶስን ከሰማችበት ከመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን አንሥቶ በተለይም ከአጤ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት (6ኛው መ/ክ/ዘ) ወዲህ የጥምቀትን በዓል ዛሬ በሚታየው አኳኋን ስታከበር እንደ ቆየች ይታመናል፡፡ በክብረ በዓሉ ከመንበረ ክብራቸው ወጥተው ወደ ባሕረ ጥምቀት የሚወርዱት ታቦታት በካህናቱ ሃሌታ፣ በምእመናኑ እልልታ እና በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያኑ በተቋቋሙ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች መዝሙሮች ታጅበው በተመሳሳይ አኳኋን እንደሚመለሱ ይታወቃል፡፡

ኢትዮጵያን ለማየት ፣ ጥምቀት በጎንደር ማክበር …

በአርባ አራቱ ታቦት መናህሪያ በጎንደር ከልጅነት እስከ እውቀት የማውቀው ታላቅ ህዝባዊ በአል ቢኖር የጥምቀት በአል ነው . . . የጎንደር አባቶችና እናቶች ባማረ የባህል ልብሶቻቸው ተውበው ደምቀው ጎንደርና ጥምቀትን ያደምቋታል። ጥምቀት ገና ከጥንት ከጠዋቱ የውጭ ሃገር ጎብኝዎችን ቀልብ ከሚስቡት በአላት ቀዳሚ መሆኑንም አውቃለሁ ። አባቶች ጥንግ ድርብ እና አልፎ አልፎም ቀደምቱን ያማራ በርኖስ የባህል ልብሳቸውን ለብሰው ጥምቀትን ደምቀው ሲያደምቁት ፣ የቀረው ነዋሪም “ለጥምቀት ያልሆነ ልብስ ይበጣጠስ” ሆነና አቅሙ የፈቀደ አዲስ ልብስ አስገቶ ይለብሳል። ያጡ የነጡት ደግሞ ያላቸውን መላብስ አጣጥበውና በወግ በወጉ ጠቅመው በአደባባይ የሚታዩት በጥምቀት ነው፡፡ በጥምቀት የጎንደር ስመ ጥሩ የአርባ አራቱ ታቦት ፣ ሊቃውንት፤ ስመጥር የደብር አለቆችና ካህናት በሚያምረው ልብሰ ተክህኖ አምረውና ደምቀው ይታያሉ . . . በነጭ የባህል ልብሳቸው ላይ ጣል ከሚያደርጉት ጥቁር ካባቸውንና በራሳቸው ጥምጣም የሚታወቁት በጎንደር የቅኔ ፤ የመወድስና የአቋቋም ዝማሬ ሊቃውንት ባማረው አንደበታቸው የውዳሴ መዝሙር ጣዕመ ዜማ፣ ወርብና ሽብሸባውን በአደባባይ የሚያሰሙበት ልዩ አጋጣሚ ቢኖር ይህ የጥምቀት በአል ነው . . . ዘመን በዘመን ሲተካ ጥምቀት በጎንደር እንዲህ እያደመቀ እዚህ ደርሰናል . . . !

ዛሬም ጎንደር በጥምቀት በቱሪስት መናህሪያ ሆና ዘመንን የኢትዮጵያ መገለጫ ሆና አይን እንደሳበች ትገኛለች ! ከዛሬ አራት ከፍለ ዘመን (400 አመት ) በፊት የተሰሩት የጎንደር ቤተ መንግስቶች አስገራሚ ጥበብ ዛሬ ድረስ ውበትና ግርማ ሞገስ ይታይባቸዋል፡፡ የዚያን ዘመን ሰማይ ጠቀስ ቤተ መንግስቶችን አስገንብተው የጎንደርን ከተማ በመቆርቆራቸው የሚታወቁት አጼ ፋሲል ሱስንዮስ ጥምቀት መዋኛ ገንዳንም ከቀሃ ወንዝ ዳረወቻ ገንብተዋል። አጼ ፋሲለደስ ሃገሬ በአሉን የሚያከብርበትን የመዋኛ ቅጽግ ግቢ ከልለው ያሰሩ ብልህ መሪ ነበሩ ! ይህም የያኔው ብልህ መሪ ለጥምቀት የሰጠውን ልዩ ክብር አመልካች ለመሆኑ ጥርጥር የለኝም ፡፡ አጼ ፋሲል በቀሃ ወንዝ ዳርቻ ያሰሩት የመዋኛ ገንዳ ዛሬ ድረስ ለጎንደር ጥምቀት መድመቅ ፈርጥ ሆኖ ዘመን ሲነጉድ የዚያ ዘመን የስልጣኔ አሻራችን ያስቃኘናል፡፡ ከመዋመኛው አንድ ጫፍ ታቦተ ጽላቱ በክብር የሚያርፍበት መቅደስ አሰርተዋል፡፡ በዚያ የጸሎት ቤት ስርአተ ቅዳሴ ፤ ማህሌት ሽብሸባው ጥምቀት በመጣ በሄደ ቁጥር ይከወንበታል፡፡ ግራማ የተላበሰውን ይህን መዋኛ ሶስት ፎቅ ህንጻ በአስገራሚ ጥበብን ይታይበታል።

ጥምቀት በጥንታዊዋ መዲና በጎንደር ሲከበር የጥበብና የስልጣኔ አሻራ ሲከበር ለበአል አክባሪዎቹ ብዙ መልዕክትን ማጫሩ አይቀርም ! የአጼ ፋሲል የቀደመ ስልጣኔ ቅሪት ውብ ህንጻዎች የጥንቱን ማንነታችን እያወሱ ካወቅንበት ከዛሬ የኢሊ ጉዞዋችን እንድንነቃም እያደመቀ እያዋዛ ያዘክሩናል …

ጥምቀትን ታኮ የተመረቀው የመይሳው ካሳ ሃውልት ፣ የማይረሳኝ የመኪና አደጋ … ትዝታ

ዛሬ ዛሬ የጥምቀት በአል በአብዛኛው በወጣቱ ሙሉ ተነሳሽነት በልዩ ስሜትና ዝግጂት በልዩ ስሜት እንደሚከበር በስልክ ያጫወተችኝ እድሜዋ ከ80 የዘለለው የእድሜ ባለጸጋ እመሆይ እናቴ ነበረች ። ዛሬን አያድርገውና ድሮ በልጅነት ካህን አባቴንና እናቴን ተከትየ በፋሲል ውቅር ከተማ በጎንደር በአሉ አከባበር ደምቄ አድጌበታለሁና የጥምቀትና ጎንደር ትዝታ አብረውኝ ይኖራሉ …፡

ከሁለት አመት በፊት ጥምቀትን በጎንደር ለማክበር ባደግኩበት ቀየ ተገኝቸ ነበር ። በከተራው በአል በጥምቀት ዋዜማም በጉጉት ይጠበቅ የነበረው የአጼ ቴዎድሮስ ሃውልት ምረቃ ላይ ተገኝቸም ኢትዮጵያን በጎንደር አይቻታለሁ ፡፡ በተወለዱ ባደጉበት ምድር ለአንድ ክፍለ ዘመን ጥርኝ አፈር ለመታሰቢያቸው የተነፈጋቸው የኢትዮጵያ አንድነት ተምሳሌት የአጼ ቴዎድሮስ ሃውልት በጎንደር ከተማ እምብርት በፒያሳ መሃል አደባባይ ተሰርቶ የምረቃውን ስነ ስርአት ሲካሔድም ተመልክቻለሁ ። ካች አምና በተከበረው ጥምቀት በጎንደር ደመና አሳዛኝ ትዕይንት ሲስተናገድም እማኝ ነበርኩ ! የአባይ በርሃው የመኪና አደጋ : (

የጎንደር ጥምቀት ክብረ በአል ጋር የቴዎድሮስ ሃውልት ምረቃ ሊከበር በዝግጅት ላይ እያለ ከወደ አባይ በርሃ የተሰማው መርዶ የከፋ ነበር። መርዶው በመይሳው ካሳ ሃውልት ምረቃና በጥምቀቱ የደመቀ ዋዜማ ስሜታቸው በደስታ ላይ የነበርነውን በአል አክባሪ ሁሉ ቅስም የሰበረ ነበር። በአሉን ለማክበር አስበው ወደ ጎንደር ሲገሰግሱ በአባይ በርሃ በተከሰተው የመኪና አደጋ ህይዎታቸው ያጡበት ወገኖች ቁጥርም ከፍ ያለ ነበር ። በርሃው ወገኖቹን በልቶታልና ጎንደሬውን አንገቱን በሃዘን ደፍቶ ማቅ ያለበሰው ቀን ቢኖር ይህ ቀን ነበር :( ደስታቸውን ለመግለጽ ሳግ እየተናነቃቸው ለቴዎድሮስና ለሚናፍቋት አንድነቷ የተጠበቀች ኢትዮጵያ ያላቸውን ፍቅር በመግለጽ ላይ የነበረው ኢትዮየጵያዊ ከትንሽ እስከ ትልቅ በርሃው በበላቸው ወገኖቹ በሃዘን ቅስሙ መሰበሩና ስሜቱ መጎዳቱን በእያንዳንዱን ፊት ይነበብ እንደነበር አይረሳኝም …

በአባይ በርሃ ገደል ገብቶ ሰው የጨረሰው አውቶቡስ እኔ ልጆቸና እህቴ በአንድ ሆነን በተሳፈርንበት አውቶቡስ እኩል ከአዲስ አበባ ነበር የተነሳው። ከአዲስ አበባ እስከ አባይ በርሃ ድረስ ከበስተኋላችን ይጓዝ ነበር ። በአባይ በርሃ ደልደል ባለ መንገድ ዳር በአንድነት ለደቂቃዎች እረፍት አድርገንም ነበር ። እኛ ቀድመን አቀበቱን ወጠን ደጅን እንደደረስን የማይታመነውን አደጋ መርዶ ሰማን… ይከተለን የነበረው አውቶቡስ ከሃምሳ በላይ አብዛኛው እንደኛ ጥምቀትን በጎንደር ሊያከብር የተሳፈረው ወገን ገደል ገብቶ ሰው አንዳለቀ በቀትሩ የራዲዮ ዜና እወጃ ሰማን! ያ ቀን. ለእኔ የሚረሳ እና የሚዘነጋ አይደለም ! በአባይ አፋፍ አንድ ጫፍ እረፍት ባደረግንባት ደቂቃ ሰላምታ የተለዋወጥኳቸውን ወገኖች በሰአታት ልዩነት የማለቃቸውን አሰቃቂ ዜና የሰማሁባት እለት ሆዴን ያላወሰኝና ያስደነገጠኝ ስሜት ትዝታው አሁን ድረስ ያውከኛል …ነፍሳቸውን ይማር !

ኢትዮጵያ የምትከብርበት የጎንደር ጥምቀት …

ከአካባቢ የወረዳ የዞንና የገጠር ከተሞች የመጣው ኮበሌ ባለጀንፎ ሽመል ከዘራውን ወልውሎ ለሆታና ጭፈራው ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል፡፡ ከሁሉም ቀልብን የሚስቡት የከተማ ጎረምሶች በህብረት ተሰባስበው በዘመነኛና በባህላዊው ዘፈን ጥምቀቱን ሲያደምቁት ፣ ወጣት አርሶ አደሮች በበኩላችው የሚያምር አረንጓዴና ሰማያዊ በቁልፍ የተንቆጠቆጠ ቂምጣና ጨሸሞዞቻቸው በተጨማሪ የሚያምር ገናባሌ አድርገው በአልባሳት ደምቀዋል፡፡ ኮበሌዎች ጠባብቡን ቁምጣ ፣ ሸሚዝና ገንባሌ ለብሰውና ከጎፈሬያቸው ላይ ሚዷቸውን ሻጥ በማድረግ በአሉን ለማድመቅ የበኩላቸው በማድረግ ላይ ናቸው ፡፡ አልፎ አልፎም ቢሆን ኮረዳ ሴቶች ጭምር በቅባት የጠገበ ጸጉራቸውን ቁንዳላ ተሰርተው አረንጓዴ ቀሚስ አሰፍተውና በነጩ ቁልፍ አሽቆጥቁጠው ከመቸውም ጊዜ በላይ ለጎንደር ጥምቀት ህብረ ባህላዊ ድምቀትን ሰጥተው አድማቂዎች ናቸው። ወጣቶች ፣ ሃገር ቤት ከመጣው ቢጤያቸው ጋር ሲላቸው ሰይ ሰይ ተብሎ የሚታወቀውን ባህላዊ የዱላ ጫወታ እየተጫወቱ ባአሉን ያደምቁታል። እንዲያው በአጠቃላይ ከህጻናት ጀምሮ ኮበሌው፣ ኮረዳው ፣ እና እድሜ ጠገብ አባቶችና እናቶች የጎንደር ጥምቀትን በአል ልዩ ውበት ናቸው . . .

አንተ የት መጣህ አይባልም …ማን የማንን ይጫወት አይባልም! ኦሮሞው ፤ከንባታው ፤ ጉራጌው፤ ሃረሪው ፤ትግሬው ፤ አማራው ፤ ሱማሌው ይዘፈናል ፣ የደለቃል ፣ ጃሎ ይባላል! ኢትዮጵያዊ በጎንደር የጥምቀት በአል አንድ ሆኖ ባንድ ክብረ በአሉን ይታደማል ! አገር ጎብኝው ፈርንጅና ጥቁሩ ከሃገረ አሜሪካ ፤ ከአውሮፓን ከሩቅ ምስራቅና ከአውስትራልያና ከተለያዩ አለማት የመጡት ሀገር ጎብኝዎች በካሜራቸው እያጠመዱ ጥምቀትን በጎንደር ሲያከብሩ የኢትዮጵያን በጎንደር እያዩ ነው! የእረፍት ጊዜያችውን በዓለ ጥምቀትን ተጠግተው ጎንደርን ሲጎበኙ በጨዋታው ደምቀው ተውበው፣ የዚያን ዘመን የእነ አጼ ፋሲልን ቤተ መንግስቶች ፣ የቅድመ አያቶቻችን ድንቅና ውብ ባህልና ያለፈ መልካም ስራ እየተደነቁ የሚያልፉበት ትዕይንት በመሆኑ ኢትዮጵያን ለማየት ጎንደርን በጥምቀት ማየት ያሰኝዎታል! በሀገሬው ሆታ ጭፈራ ተደምመው የደስታ የፌስታ ቀንወትን እያሳመሩ ኢትዮጵያን በጎንደር እያዩ ጥምቀትን ያከብራሉ ! . . . የካች አምናው ትዝታ ራሴን ቢያነሆልለው በከተራው በአል በትዝታ ተጉዠ በማለዳ ወጋዎጌ ይህችን ያህል ላስቃኛችሁ ወደድኩ . . .

መልካም የከተራና የጥምቀት በአል !

የግርጌ ማስታዎሻ : ስለከተራና ጥምቀት ብዙን መረጃ ያገኘሁት ከሐመር መጽሔት ሲሆን ለወዳጆች እንዲስማማ አድርጌ ማቅረቤን ሳልጠቁም አላልፍም።

ሞረሽ!የጐንቻው !

አቡጊዳ –አቶ ሌንጮ ለታ በርግጥ አዲስ አበባ ገብተው ይሆን ?

$
0
0

«የቀድሞ የኦነግ አመራር ሌንጮ ለታ፣ አዲስ ፓርቲ ይዘው አዲስ አበባ ገቡ» ሲል አዲስ አድማስ በቅዳሜ ጥር 10 እትሙ ላይ ዘገበ። አቶ ሌንጮን ለማነጋገር ያደረግነዉ ሙከራ እንዳልተሳካለት የዘገበው አዲስ አድማስ ፣ መረጃዎን ያገኘነው ከምንጮቹ እንደሆነም ገልጿል።

አቶ ሌንጮ በጀርመን ድምጽ ራዲዮ በቅርቡ ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ኢትዮያጵያ ዉስጥ ገብቶ በሰላም ለመታገል ፍልጎቱ እንዳላቸው ገልጸው፣ ከኢሕአዴግ ጋር ምንም አይነት ድርድር እንዳላደረጉ መናገራቸው ይታወቃል። የአዲስ አድማሱ ዘገባ፣ በቀጥታ አቶ ሌንጮ ለጀርመን ድምጽ ራዲዮ ከሰጡት ጋር የሚቃረን ሲሆን፣ ጉዳዩን በትክክል ለማጣራት ያደረግነዉ ሙከራ አልተሳካም። የአቶ ሌንጮ የጀርመኑ ቃለ ምልልስ ወይንም የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘገባ ትክክል መሆኑ የሚያመላከት መረጃ እንዳገኘን ለአንባቢያ ግልጽ እናደርጋለን።

«ከአንድ አመት በፊት አቶ መለስ ሞተው በነበረ ጊዜ የተለያዩ እርስ በርስ የሚቃረኑ ዘገባዎች አገር ቤት በሚታተሙ ጋዜጦችና በድህረ ገጾች ይወጡ እንደነበረ የሚታወቅ ነዉ። አዲስ አድማስ የተጨበጡ ማስረጃዎች እስካላቀረበ ድረስ፣ አቶ ሌንጮ እራሳቸው በጀርመን ድምጽ የተናገሩትን ለጊዜዉ መቀበሉ ነው የሚያስኬደው» ያሉት አንድ የፖለቲካ ተንታኝ፣ አቶ ሌንጮ በርግጥ አዲስ አበባ ገብተዉ ከሆነ፣ በቅርብ ጊዜ ዉስጥ በቀላሉ እንደሚታወቅ ይናገራሉ። «የኢትዮጵያ ሕዝብ በስፋት በሚያዳምጠዉ የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ‘ከኢሕአዴግ ጋር ድርድር አላደረግንም ብለው አቶ ሌንጮ መዋሸታቸውም፣ በድርጅታቸው ላይ ከወዲሁ ጥላሸት እንደቀቡት ነዉ የሚቆጠረዉ» ሲሉ ያከሉት እኝሁ ተንታኝ፣ በአንጻሩም አቶ ሌንጮ ኖርዌይ ሆነው ከሆነ አዲስ አበባ ገቡ የሚባለው፣ የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ተአማኒነት ክፉኛ እንደሚጎዳም አስረድተዋል።

አቶ ሌንጮ ለታ የሚመሩት የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ግንባር ፣ እንደ ዶር በያን አሴቦ፣ አቶ ሌንጮ ባቲ፣ ዶር ዲማ ነግዎ የመሳሰሉ የኦነግ መስራችን አንጋፋ አመራር አባላት የተመሰረተ እንደሆነ ይታወቃል። ላለፉት ሰላሳ አመታት ኦነግ ወደ ፊት እንዳይሄድና ከተቀረዉ ኢትዮጵያዊ ጋር በቀጥታ እንዲላተም ያደረገዉን፣ የመገንጠል ፖለቲካ ወደ ጎን በመጣል.፣ የኢትዮጵያን አንድነት በመቀበል፣ የኦሮሞ ጥያቄ በዴሞክራሲ መከበር ይፈታል የሚል አቋም በመያዝ ነዉ ኦዴፍ የተመሰረተዉ።

እነ አቶ ሌንጮ ለታ፣ በኢሳያስ አፈወርቂ ከሚመራዉ የኤርትራ መንግስት ጋር በመወዳጀት፣ የትጥቅ ትግል ያደርግ የነበረዉን ኦነግን ትተዉ ፣ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመታገል መወሰናቸው፣ የኦነግ ዉጤት አልባና ኤርትራ ጥገኛ፣ የሃያ አመታት የትጥቅ ትግል፣ ኦሮሞዉን በስመ ኦነግ ስም ከማስጨረስ ዉጭ ምንም ጠቀሜታ እንዳላመጣለት ከመረዳት ሊሆን እንደሚችል ብዙዎች ይናገራሉ።

የአቶ ሌንጮ የቀድሞ ኦነግ፣ ለአራት የተከፋፈለ ድርጅት መሆኑም ይነግራል። እነርሱም አዲስ አበባ ገባ የሚባለዉ የአቶ ሌንጮ ለታ ኦዴፍ፣ በጄነራል ከማል ገልቹ የሚመራዉና በኢትዮጵያ አንድነት የሚያምነው አስመራ የሚገኘዉ የኦነግ ቡድን፣ በአቶ ዳዎድ ኢብሳ የሚመራዉ ሌላዉ አስመራ የሚገኝ፣ ኦሮሞዉ ሕዝብ ዉሳኔ ያደርግና ይወስን የሚለው ቡድን እና እነ ዶር ነጋሳ ዲልቦ ያሉበት ኦሮሞያ የሚሉትን ለመገንጠል የሚፈልገዉ የአክራሪዉ ኦነግ ቡድን)

አቶ ሌንጮ ከኢሕአዴግ ጋር ድርድር አላደረግንም ያሉበት የጀርመን ድምጽ ራዲዮን ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ !

አዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ “አቶ ሌንጮ ደርጅታቸውን ይዘው ገቡ” የሚለውን ዘገባ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ !

አቡጊዳ –ሌንጮ ለታ ኖርዌይ እንጂ አዲስ አበባ አይደሉም አሉ –አቶ ሌንጮ ባቲ

$
0
0

አዲስ አድማስ አቶ ሌንጮ ለታ አዲስ አበባ ገቡ ብሊ በዘገበዉ «አንጻር የአዲስ አድማሱ ዘገባ፣ በቀጥታ አቶ ሌንጮ ለጀርመን ድምጽ ራዲዮ ከሰጡት ጋር የሚቃረን ሲሆን፣ ጉዳዩን በትክክል ለማጣራት ያደረግነዉ ሙከራ አልተሳካም።የአቶ ሌንጮ የጀርመኑ ቃለ ምልልስ ወይንም የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘገባ ትክክል መሆኑ የሚያመላከት መረጃ እንዳገኘን ለአንባቢያ ግልጽ እናደርጋለን”” ብለን ነበር።

አቶ ሌንጮ ለታ በሊቀመንበርነት የሚመሩት የኦዴፍ ሌላዉ የአመራር አባል፣ አቶ ሌንጮ ባቲ፣ ከሚኒሶታ ለዘበሃሻ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ አቶ ሌንጮ ለታ ደዉለው እንዳነጋጋሯቸውና፣ አዲስ አበባ ናቸው የተባለው ወሬ ፍጹም ዉሸት መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ሌንጮ ለታ በጀርመን ድምጽ ራዲዮ እንደተናገሩት፣ ከጅምሩ ድርጅቱን ስቋቁም በሰላም አገር ዉስጥ ገብቶ ለመታገል ፍላጎት እንደነበራቸው ይሄን ያኔም ይፋ እንዳደርጉ የገለጹት፣ አቶ ሌንጮ ባቲ፣ «አገር ቤት ስንገባ በግልጽ እንጂ በድብቅ አይደለም» ሲሉ ነበር ለዘሃበሻ የገለጹት።

ዘሃበሻ ከአቶ ሌንጮ ባቲ ጋር ያደረገዉን አጭር ቃለ ምልልስ ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ !

በሚኒሊክ ዘመን የደነቆረ…በታሪኩ አባዳማ

“ወደው አይስቁ”ክንፉ አሰፋ

$
0
0

የጥምቀት በዓልን ተሰባስበን በምናከብርበት አንድ ቤት ውስጥ ካለወትሮው ፓልቶክ ተከፍቷል። በዚያ የበዓል ድባብ፤ የፓልቶክ ንትርክ መከፈቱ ሳይገርመን፣ ርእሱ የሁላችንንም ቀልብ መሳቡ። በእርግጥ አንድም ቁም ነገር በንግግሩ አልሰማንም። አዲሱን ቋንቋ ልዋስና የፓልቶኩ ተናጋሪዎች ሙድ የሚያስይዙ ነበሩ። ሰዎቹ በዚህ ከቀጠሉ የእነ ክበበው ገዳን ገበያ መዝጋት እንደሚችሉ አያጠራጥርም።

የድምጽ መነጋገርያውን የያዘው ሰው ጉሮሮውን ጠራርጎ ንግግሩን እንዲህ ሲል ጀመረ። “የምኒሊክ ወንጀል በጡት መቁረጥ ብቻ አያበቃም። … የወንዶች ብልትም ተቆርጧል።…”
በአኖሌ ሃውልት የምትገረሙ ነፍጠኞች ካላችሁ። በዚህ ብዙም አትደነቁ። ገና የወንድ ልጅ ሃፍረተ-ስጋ በሃውልት መልክ በአደባባይ ይቆምላችኋል። “የባሰ አታምጣ!” ነው ነገሩ። ሜንጫዎቹ ሰክረዋል። አእምሮዋቸውም ስቷል። የሚናገሩትን አያውቁትም። የማየውቁትን ነገር ሁሉ ይናገራሉ። እነሱ የሚናገሩትን ደግሞ በምኒሊክ ቤተ-መንግስት ያሉ ሰዎቻቸው በተeግባር ይፈጽሙላቸዋል።

ተናጋሪው የእለቱ የክብር እንግዳ መሆኑ ነው። በጉዳዩ ላይ ብዙ ጥናት እንዳደረገም አስቀድሞ ገለጻ ተደርጓል። ሰዎቹ የወንዶች ብልት መቆረጥን የፈጠራ ታሪክ ያነሱት ያለምክንያት እንዳልሆነ ግልጽ ነው። ጡትን በአደባባይ ያቆሙ እብዶች፣ የወንድ ብልትን አያቆሙም ማለት አንችልም። “ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም!” ይላል የሃገሬ ሰው። ስለ አኖሌ የፈጠራ ውጤት በያዝነው አዲስ አመት አውርተን ሳንጨርስ፤ ይኸው የባሰ ነገር እየመጣ ነው። ምኒሊክ የወንድ ብልትምም ቆርጠዋል ነው እያሉን ያሉት – ጨዋታቸውን ሲያራዝሙት። አጼ ሚኒሊክ ለካ የጉጂ ኦሮሞ ኖረዋል። ትንሽ ቆይተው ጉጂዎች የወንድ ብልት መቁረጥ የተማሩት ከምኒሊክ ነው ይሉናል። እዚህ ላይ ሰዎቹ እየቀለዱ ብቻ አይደለም። እየቀለዱብንም ነው። ወዳጆቼ ግን አሁንም ሙድ ይዘዋል።…

በነዚህ ቀልደኞች ዘና እንል ይሆናል። አንድ የዘነጋነው ነገር አለ። የሴት ልጅ ጡት በአደባባይ ሃውልት የተሰራለት በእኛ ምድር ላይ ብቻ ነው። ይኸውም በእኛ ዘመን። ሴት ልጅ በሃገራችን ትከበራለች። የውስጥ አካልዋ እንዲህ በአደባባይ ላይ ሲውል ክብርዋን ይቀንሰዋል። የሴትን ልጅ ጡት በአደባባይ ላይ አውለው፤ ህጻናትና አዋቂው እንዲመለከተው ማድረግ በባህላችንም እጅግ ነውር ነገር ነው።

“ምሁሩ” የታሪክ ተንታኝ ንግግሩን በዚህ አላበቃም። ማብራራቱን እንደቀጠለ ነው። “…ይህንን ታሪክ ለማወቅ የታሪክ መጽሃፍ ማንበብ አይጠበቅባችሁም። በኢንሳይክሎፔዲያ ላይም ግዜያችሁን አታባክኑ። በቀላሉ ጉግል አደርጉና ታገኙታላችሁ… ” አለ። ጉግል ስናደርግ ይህንኑ መረጃ በራሱ ድረ-ገጽ ላይ ልናገኘው እንችል ይሆናል።

አጼ ምኒሊክ አምስት ሚሊዮን ጡት ቆርጠዋል ሲሉን ግን፤ ስሌቱ ላይ የቤት ስራቸውን በደንብ የሰሩት አይመስልም። በአጼ ምኒሊክ ዘመን አጠቃላይ የህዝብ ብዛት ቁጥሩ ስምንት ሚሊዮን ነበር። የአምስቱ ሚሊየን ህዝብ ጡት ከተቆረጠ፣ በዘመኑ ወንዶቹም ጡት እንደነበራቸው ያመላክታል። ግን ያንን ሁሉ ጡት እንዴት ሊቆርጡት እንደቻሉ ተናጋሪው አላብራሩም። ስልጣኔን ወደ ኢትዮጵያ ያስገቡት አጼ ምኒሊክ በመጀመሪያ ያደረጉት የጡት መቁረጫ ማሽን ማስገባት መሆኑን ከጉግል ላይ በቅርቡ ሊገኝ ይችላል።
ጉግል፣ ጉግል፣ጉግል፣ጉግል፣…… እያለ መነጋገርያውን ለቆ ወረደ – የምኒሊክን አዲስ ታሪክ የሚያስተምረው።

“ሉሲ ኦሮሞ ናት። ጎንደርም ከኦሮሞ ላይ የተቀማች ሃገር እንደሆነች ጥናት አድርገን ጨርሰናል።… ይህንንም በቅርቡ ይፋ በሚሆነው ጥናት ታገኙታላችሁ… ።” የሚል ሌላ ተናጋሪ መድረኩን ይዞ ሲናገር ከማርስ የመጣ ፍጡር ነበር የመሰለን።
ጨርቁን ጥሎ እርቃኑን መንገድ ለመንገድ የሚሄድ፤ ወይንም ደግሞ እጅና እግሩ በሰንሰለት የታሰሩ ሰው ስናይ፤ በተለምዶ ይህ ሰው አብዷል እንላለን – ውጭውን ብቻ አይተን። ጥሩ ልብስ ለብሰው በስነልቦና እና በአእምሮ መታወክ የሚሰቃዩ እጅግ ብዙ እብዶች እንዳሉ ብዙውን ግዜ እንዘነጋለን። እንደዚህ አይነቶቹ ሰዎች በቀን ቅዠት የሚሰቃዩ፣ የስነምግባርና የሞራል እስረኞች በመሆናቸው አእምሯቸው ይታወካል። በእውናቸው ይሁን በህልማቸው የአጼ ምኒሊክ ጣእረ ሞት እየመጣ እንቅልፍ እንደነሳቸው ግልጽ ነው።

ፓልቶክን ከሰባት አመታት በኋላ መስማቴ ነው። ይህን ትልቅ መድረክ፣ አንዳንዶች ታሪክ ሰርተውበታል። ሌሎች ታሪክ ሲያወሩበት ሰንብተዋል። እነሆ ዛሬ ደግሞ ታሪክ የሚያጎድፉ ጉዶች ይዘውታል። ከሰባት አመታት በኋላ የኛ ፓልቶክ ሽቅብ ሳይሆን ቁልቁል አድጎ እዚህ ደረጃ ላይ መድረሱ ቢገርመኝም፤ በአንጻሩ ግን እንደ አዝናኝም እየሆነ መምጣቱን አልጠላሁትም።

እንደሰማነው የፓልቶክ ርእሱ ላለፉት ሶስት ሳምንታት አልተቀየረም። የዛሬውም መነጋገርያ ርእስ ዳግማዊ ምኒሊክ ናቸው። እኚህ መሪ ካለፉ እነሆ መቶ አመት ሆናቸው። “የሞኝ ለቅሶ፣ መልሶ መላልሶ!” እንዲሉ አንዳንዶቹ ቀኑን ሙሉ ስለ አጼ ምኒሊክ አውርተው ሌሊቱንም ይመለሱበታል። ዛሬ ግን ወሬውም፣ ስድቡም ያለቀባቸው ይመስላል። ዛሬ ስለጀኖሳይድ እያወሩ አይደለም። ይልቁንም ጀኖሳይድ እያወሩ ነበር። ወንጀሉን ራሳቸው በቃል እየፈጸሙት…።

ሌላኛው ተናጋሪ ተራውን ጠብቆ መነጋገርያውን ያዘ። የተለመደውን የአጼ ምኒሊክን አጽም ከመቃብር እየጠራ ካወገዘ በኋላ፤ እንዲህ ሲል ተናገረ። “…አበበ ቢቂላን በባዶ እግሩ እንዲሮጥ አድርገው ታላቅ በደል ፈጽመውበታል።”
መቼም ወደው አይስቁ። እንዲህ አይነቶቹ ሰዎች እንኳ አይፈረድባቸውም። ገና ሃገር ሲለቅቁ የለቀቁ ስለሆኑ ለክርክርም አይመቹም። “አበበ ቢቂላ በሮም እና በቶክዮ ላይ የሮጠው በአጼ ምኒሊክ ዘመን ነው።” ብሎ ከሚከራከር ሰው ጋር ሙግት መግጠም እብደት ይሆናል።
“የቁቤ ትውልድ ነን።” የሚል ሌላ ታናጋሪ ደግሞ መጣ። ይሄኛው ደግሞ የቆሪጥ መንፈስ የሰፈረበት ሳይሆን አይቀርም። የሚያወራው ሁሉ ስለ መቁረጥ ብቻ ነው። ሚኒሊክ ጡት፣ እጅ፣ ቆለጥ፣ እግር፣ ጥፍር… ቆርጠዋል አለን። እንደታናጋሪው ከሆነ እኚህ መሪ ያልቆረጡት ብልት የለም። ሃገር ማስተዳደሩን ትተው አስራ ሁለቱንም የሰውነት አካል ሲበልቱ ኖሯል!
አርፍደው የሚገቡት ተሳዳቢዎች ከአፋቸው የሚወጣውን ጸያፍ ስድብ ለመድገም ይዘገንናል። በ”ምሁሮቻቸው” ገለጻ መሃል እንደ አዝማች ጣልቃ እየገቡ በአማራው ህዝብ ላይ ይወርዱበታል። በዚህ ሁሉ መሃል ትንሽ የገረመኝ አንድ ክስተት ነበር። የክፍሉ መሪ በስድድቡ መሃል ገብቶ በኦሮምኛ እንዲህ ሲል ተናገረ።

“ጀሪን ወል አኛተኑ። ማይኪ ኢቲ ኬኒ። ኑ ሂንደጌኛ”።
ወደ አማርኛው በግርድፉ ሲመለስ፣ “ማይኩን ስጣቸው። እነሱ እርስበርስ ይባሉ። እኛ እንሰማለን።” እንደማለት ነው። ዋናው ጨዋታ እዚህ ላይ ኖሯል። ምክንያቱም ይህንን ውግዘት እና ውርጅብኝ ሜንጫዎቹ ያለምክንያት በዚህ ሰዓት አላነሱትም። ነብሳቸውን ይማርና አፄ ምኒሊክ ካረፉ 100 አመት አለፈ። የሙት አመታቸው መከበር ከጀመረ ደግሞ 70 አመት ሆነው። ይህንን ወቅት ጠብቆ በአማራ እና በክርስትና እምነት ላይ ለመዝመት የሚደረገው ሙከራ፣ ግብታዊ ሳይሆን በጥናት የተደረገ ስለመሆኑ ያመላክተናል። ግርግር በመፍጠር እና ዜጎችን እርስበርስ በማባላት፣ ትንሽ የፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት የሚፈጸም የፖለቲካ ዝሙት መሆኑ ነው።

ልብ በሉ! የዚህ የሜንጫ ዘመቻ መሪዎች ኦሮሞዎች አይደሉም። አብዛኞቹ በግማሽ ከሌላ ዘር የሚወለዱ ናቸው። በእምነታቸውም ሆነ በዘራቸው የተቀላቀሉ ሰዎች ብዙውን ግዜ የማንነት ቀውስ ውስጥ ይገባሉ።
ስድስት ሚሊየን አይሁዶችን የፈጀው አዶልፍ ሂትለር ግማሽ አይሁድ እንደነበር አንዘንጋ።


አቡጊዳ –ግብጾች አንድ ሲሆኑ ኢትዮጵያዉያን በአባይ አንድ መሆን እንዳለባቸው አቶ ግርማ ሰይፉ ገለጹ

$
0
0

በሱዳን፣ ግብጽና ኢትዮጵያ መካከል ሲደረግ የነበረዉ የሶስትዮች ንግግር መበተኑን አስመልክቶ ፣ የአንድነት ብሄራዊ ምክር ቤት እንዲሁም የፓርላማ አባል፣ የግብጽን አቋም «የኢትዮጵያን ሕዝብ መናቅ» እንደሆነ በመግልጽ፣ መንግስት የወሰደዉን አቋም ደገፉ።

በአባይ ግድብ ዙሪያ እንኳን የተቀረዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የፓርላማ አባል የሆኑት እርሳቸዉም በቂ መረጃ እንደሌላቸዉ የገለጹት አቶ ግርማ፣ «የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ከዚህ አንፃር በጭፍን የአባይን ግድብ እንዲደግፉ እንጂ መረጃን መሰረት አድርገው ትንተና እንዲሰሩ እና የራሳቸውን ምክረ ሃሳብ እንዲሰጡ እድል የላቸውም፡፡ ለዚህ ጉዳይ የሚፈለጉት ልማታዊ የሚባሉት ጋዜጠኞች ብቻ ናቸው እነርሱም መንግሰት የሚለውን እንደ በቀቀን መድገም ነው የሚጠበቅባቸው፡» ሲሉ በመንግስት ሜዲያዎች የሚነዙ ፕሮፖጋንዳዎችን አማረዋል።

የሰባአዊ መብት ከተከበረ፣ በአባይ ፕሮጀክት ዙሪያ የተሸፋፈነዉን የተደባበቀ ገሃድ ወጥቶ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራር ከተዘረጋ፣ ግብጾችን ከመለማመጥ በዉጭ ያሉ ኢትዮጵያዉያን ብቻ ግድቡን ሊገነቡት እንደሚችሉ የገለጹት አቶ ግርማ አገዛዙ በዉጭ ያሉት ለማቀፍ እምሰረታዊ ለዎጦች እንዲያደርግ አሳሰበዉል።

«በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ይህን ግድብ በሚያስደንቅ ሁኔታ ሊገነቡት የሚችሉበት አቅም እንዳለ ተገንዝቦ ግብፅን አንገት የሚያስደፋ መንገድ ከመቀየስ ይልቅ አሁንም በውጭ የሚገኙትን ዜጎች መከፋፈል ተገቢ አይደለም የሚል እምነት አለኝ» ሲሉ ነበር አቶ ግርማ የጻፉት።

«የመንግሰት ሹማምንት የአባይ ግድብን ያህል ትልቅ ፕሮጀክት ይዘው ተቃዋሚና ገዢ ፓርቲ የሚል ክፍተት መፍጠር እንደሌለባቸው ሲነገራቸው፣ በተግባር የሚሰሩትን ሀቅ ወደ ጎን ትተው ጉዳዩን በሙሉ ፕሮፓጋንዳ ያደርጉታል» ያሉት አቶ ግርማ፣ የኢሕአዴግን አግላይ ተቃዋሚዎችን የመግፋት ኃላ ቀር ባህሪን ለማሳየት ሞክረዋል።

«ግብፆች የአባይ ጉዳይ ሲነሳ የፖለቲካ ልዩነታቸውን ትተው እንደ ግብፅ ሲያስቡ እኛን መለያየት ለምን ያስፈልጋል? የአባይ ግድብ ፕሮጀክት በተግባር የኢትዮጵያ ህዝብ ፕሮጅክት አንዲሆን የፖለቲካ ድባቡ ላይ ያጠላው የፕሮፓጋንዳ አዚም ሊገፈፍ ይገባል፡፡ አንድነት ፓርቲ ኢትዮጵያ የአባይ ወንዝን መጠቀም ተፍጥሯዊ መብቷ ነው ይላል፡፡ ይህ የማይገሰስ መብት ላይ ምን ፕሮፓጋንዳ ያስፈልጋል ? የዛሬው መልዕክቴ ዋና ማጠንጠኛ በሀገር ጉዳይ እንዳንግባባ አዚም ያደረገብን ማን ነው? የዚህ አዚም መፍቻ ቁልፍ መተማመን እና ሀገራዊ ዕርቅ ይመስለኛል» ሲሉም በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የፖለቲክ ልዩነቶች ሳይኖሩ ኢትዮጵያዉያን በአንድ ላይ መቆም እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የአቶ ግርማ ሰይፉ የጻፉትን ዝርዝር ለማንበብ እዚህ ይጫኑ !

የጥምቀት በዓል ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

ድሃን የምትወድና የምትረዳ ሴት፣ ርዮት፣ ሽብርተኛ ስትባል ! ግርማ ካሳ

$
0
0

ጃኑዋሩ 22 ቀን 33ኛ አመቷን ታከብራለች። በሃይ ስኩል የእንግሊዘኛ አስተማሪ ነበረች። በሕገ መንግስቱ ላይ የተደነገገዉን መብት በመጠቀም፣ በተለያዩ አገር ውስጥ በሚታተሙ ሜዲያዎች ትጽፋለች። «እነርሱ እንዲጻፍ ከሚፈልጉት ዉጭ እንዲጻፍ የማይፈልጉት ባለስልጣናት፣ የሃሰት ክስ መሰርተዉ፣ ዳኛ ለተብዬዎች መመሪያ ሰጠዉ፣ መሰረተ ልማቶችን ለማፍረስ አሴራለች፣ ሽብርተኛ ናት» ብለዉ ፈረዱባት።
1185860_10200561003368447_1105290103_n
ይች ሴት ርዮት አለሙ ትባላለች። ጡቷ አካባቢ ችግር ስላለበት ክትትል እንደሚያሰልጋት እየታወቅም ክትትል ለማግኘት አልቻለችም። ከሁለት አመት ተኩል በላይ፣ ባላጠፋችዉ ጥፋት፣ ኢሕአዴግን ስለተቃወመች ብቻ፣ እየማቀቀች ነዉ። የርዮት ወንጀል አገሯ፣ ሕዝቧን መዉደዷ ነዉ።

ርይቶ አለሙ፣ ከጋዜጣኛ ነብዩ ሃይሉ ጋር በአዲስ ፕሬስ፣ ከጋዜጣኛ ስለሺ ሃጎስ ጋር በ ቼንጅ መጽሄት ላይ ሰርታለች። ነብዩና ስለሺ፣ በአንድነት ራዲዮ ስለርዮት አለሙ፣ ከሚያወቁት ያጋሩንን ጥቂቱን ላካፍላችሁ።

ያዉ በአገራችን ባለዉ የዘር ፖለቲካ ምክንያት «የትግራይ ልማት ማህበር»፣ «የአማራ ልማት ማህበር» የሚባሉ አሉ። እነዚህ ማህበራት በየቦታዉ ለልማት ሥራ በሚል ገንዘብ ያሰባስባሉ። የአማራዉ ልማት አማራ የሚላቸዉን ነዉ የሚያነጋግረዉ፣ የትግሬዉ ደግሞ ትግሬዎችን።

አንድ ጊዜ የትግራይ ልማት ማሕበር ርዮት በምታስትምረበት ትምህርት ቤት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ትኬቶች ይሸጣል። አንዱ ትኬት 30 ብር ነበር። በትግራይ፣ መቀመጫ አጥተዉ በመሬት ላይ ተቀምጠዉ የሚማሩ ተማሪዎች የሚያሳይ ቪዲዮ አሳዩ። ርዮት «ይሄማ መሆን የለበትም» ብላ በቪዴዎ የታዩ ተማሪዎችን ለመርዳት ወሰነች። እርሷ ብቻ 300 ብር አወጥታ አሥር ትኬቶች ገዛች። ሌሎች ጓደኞቿም እንዲገዙ ግፊት አደረገች። ምንም እንኳን ትግሬ ባትሆንም፣ የትግራይ ልማት ማህበሩ ያነጣጠረው ትግሬዎች ላይ የነበረም ቢሆን፣ እርሷ ግን ያየቸው የተማሪዎችን ዘር ሳይሆን፣ ስብእናቸዉን እና ኢትዮጵያዊነታቸውን ነበር።

ርዮትን ያሰሩ ሰዎች፣ «መሰረተ ልማትን ለማፍረስ ፣ በሰዎች ላዩ ጉዳት ለማድረግ የምትፈልግ ፣ አሸባሪ ናት» ነዉ የሚሉን። እንግዲህ በትግራይ ያሉ ተማሪዎች ይመስክሩ።

በአገራችን ትልቅ የኢኮኖሚ ችግር እንዳለ የሚታወቅ ነዉ። ጥቂቶች እላይ ሲመጠቁ፣ አብዛኛዉ ኑሮ ከብዶት፣ በቀን አንዴ እየተመገበ ነዉ የሚኖረዉ። ርዮት አስተማሪ እንደመሆኗ በተማሪዎቿ አካባቢ ያለዉን ችግር ታዉቃለች። ብዙ ጊዜ በጠኔ ሲወድቁ አይታለች። ብዙዎች እንደ ታላቅ እህት ችግራቸውን ያጫዉቷታል። አቅሟ በፈቀደ መጠን ከማስተማር በተጨማሪ ተማሪዎቿን የምትረዳ ፣ የተከበረችና የተወደደች ምህሩ ነበረች። በጣም ችግረኛ ለሆኑ፣ አሥራ ሁለት ተማሪዎች፣ የሚለብሱት ዩኒፎርም በየአመቱ የምታሰፋ ነበረች።

ርዮትን ያሰሩ ሰዎች፣ «መሰረተ ልማትን ለማፍረስ ፣ በሰዎች ላዩ ጉዳት ለማድረግ የምትፈልግ አሸባሪ ናት » ነዉ የሚሉን። እንግዲህ በአዲስ አበባ ያሉ፣ ርዮት እንደ ታልቅ እህት የረዳቸቸዉን የደገፈቻቸው ተማሪዎች ይመስክሩ።

አንድ ጊዜ ደግሞ እንዲህ ሆነ። አንድ በጣም ጎበዝ የሆነ፣ ተማሪዎ፣ የማትሪክ ዉጤት እንደጠበቀዉ አልመጣለትም። የመንግስት ተቋማት መመደብ አልቻለም። በዚህም ምክንያት በጣም ተስፋ ቆርጦ እራሱን ወደ ማጥፋት ደረጃ ደረሰ። ይሄንን ስትሰማ ቤተሰቦቹን አነጋገረች። ያለዉን ነገር አስረዷት። በጣም ድሃዎች እንደመሆናቸው፣ ልጃቸውን የግል ትምህርት ቤት ከፍለው ሊያስተምሩት እንደማይችሉ ነገሯት። ይህን ወጣት፣ ወጭዉን በሙሉ ሸፍና፣ ዩኒቲ ኮሌጅ ገብቶ እንዲማር አደረግቸው።

እንግዲህ አስቡት ወገኖቼ፣ እንደ ርዮት አለሙ አይነት የተከበሩ፣ አገር ወዳድ፣ ለሰው የሚያዝኑ ኢትዮጵያዉያንን ነዉ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ሽብርተኞች እያለ ወደ ቃሊቲ የሚወረወረው። ዜጎች መልካም በሰሩ፣ የአገርንና የወገንን ጥቅም ባስቀደሙ፣ ለሕዝብ ክብርና ነጻነት በቆሙ፣ ፍትህን በሰበኩ፣ የአገሪቷ ባለስልጣናት የሚሰሩትን ስህተቶችን በደሎች ባጋለጡ ለምንድን ነዉ የሚታሰሩት ? ኢትዮጵያስ እስከምቼ ለልጆቿ ሲኦል ትሆናለች ?

አንዳንድ ሰዎች በጣም ክፉ ከመሆናቸው የተነሳ ሌሎች ሲሰቃዩ የሚደስቱ አለ። እነዚህ በዉስጣቸው ያለው የሕሊና ድምጽ የማይቃጭልባቸዉ ፣ ርህራሄና ሃዘኔታ የሚባል ነገር የሌላቸው፣ ለስብእና ክብር የማይሰጡ ናቸው። ኢሕአዴግ እየተመራ ያለ በእንደነዚህ አይነት ሰዎች ነዉ። እነዚህ ሰዎች የራሳቸዉን የጠላቻ እርካታ ለማጥገብ ሲሉ በሚሰሩት ግፍ፣ ኢሕአዴግን ወደ ገደል እየወሰዱኢት ነዉ።

የርዮት አለሙ መታሰር እንደ ፓርቲ ኢሕአዴግ ለሚያደርጋቸው የልማት እንቅስቃሴዎች ምንም አይጠቅምም። በፖለቲካም የበለጠ እንዲጠላ ነዉ እያደረገው ያለዉ። የኢሕአዴግ አባላትና ደጋፊዎች የሚመሯቸውን አክራሪዎች ገፍተዉ እንዲያስወጡ እመክራቸዋለሁ። በአስቸኳይ ርዮት አለሙ እንዲሁም ሌሎች የሕሊና እስረኞች መፈታት አለባቸው። ቀናት እየጨመሩ በሄዱ ቁጥር ነገሮች እየተወሳሰቡ ነዉ የሚመጡት። ኢሕአዴግ እየመነመነ፣ እነርዮት አለሙ ደግሞ ተወዳችነታቸው እየጨመረ ነዉ የሚመታዉ።
ርዮት አለሙ፣ አሁን ብትታሰርም፣ ሚሊዮኖች የርዮት አፍ ሆነዉ ድምጻቸዉን ያስተጋባሉ። የሚሊዮኖች የፍትህ ድምጽ የአራት ኪሎ ቤተ መንግስት ግድግዳን እያለፈ፣ ባለስልጣናቱ በተኙበት ይሰሙታል። ያለ ምንም ጥርጥር ርዮት አለሙ፣ እንደ ደራርቱ ቱሉ የኢትዮጵያን አረንጓዴ፣ ቢጫ ቀይ ሰንድቅ አላማ በላይዋ ላይ ለብሳ በክብር ከቃሊቲ ትወጣለች።

በርዮት ዙሪያ በአንድነት ራዲዮ የቀረበዉን ለማዳመጥ የሚከተለዉን ይጫኑ !

አቡጊዳ –ጡት የሚያሳይ፣ በሕዝብ ገንዘብ የተሰራ ሃዉልት !

$
0
0

የኦሮሚያ ክልል የቱሪዝምና ባህል ቢሮ ሃላፊ የሆኑት አቶ ሞሃመድ ጂሊ፣ የአኖሌ ሃዉልት እንደተሰራና በመሰራቱም ትልቅ ኩራት እንደሚሰማቸው፣ ገዛ ተጋሩ በተባለ የፕላቶክ ክፍል ቀርበው ገለጹ።

የአጼ ሚኒሊክ ወታደሮች በአርሲ የሴቶችን ጡት ቆርጠዋል የሚባለዉ ወሬ፣ የቀድሞ የሕወሃት ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩት አቶ ተስፋዬ ገብረ አብ በጻፉት መጽሃፍ ከመጻፉና በአንዳድን አክራሪ የኦሮሞ ድህረ ገጾች ላይ ከመዉጣቱ መቀር፣ በታሪክ ባለሞያዎች የተደገፈ፣ ተፈጸመ የተባለውን መፈጸሙን የሚይሳይ መረጃ እስከአሁን አልቀረበብም።

ሆኖም የኦሮሚያ ክልል መንግስት፣ ዉሸት ሊሆን የሚችል ወሬን ተመርኩዞ ፣ በትክክል በተረጋገጠዉ በበደኖ እና አርባ ጉጉ፣ በተፈጸመ ግፍና ጭካኔ ዙሪያ ማስታወሻ ሃዉልቶች ሳይሰሩ፣ በሕዝብና በሕዝብ መካከል ጥላቻ ሊያሰፍን የሚችል፣ የሴት ልጅን ጡቱ የሚያሳይ ሃዉልት በአርሲ መሰራቱ ፣ ብዙዎችን እያነጋገረ ነዉ። በበደኖ በኦነግ ታጣቂቶች ነፍሰ ጦር ሴቶች ሁሉ ሳይቀሩ፣ በሕይወት አይኖቻቸውን ተሸፍነዉ የጠልቀ ገድል ዉስጥ እንዲወረወሩ መደረጉ የሚታወቅ ነዉ። በተመሳሳይ ሁኔታ በኦህዴድ.ኢሕአዴግ ታጣቂዎች አቀነባባሪነት፣ በአርባ ጉጉ አርሲ በርካታ ዜጎች በተኙበት ቤታቸው እንዲቃጠል ተደርጎ አልቀዋል።

አንዳንድ የኢሕአዴግ ደግፊዎች፣ «የኦሮሚያ ክልል ራሱን በራሱ የሚያስተዳደር ነዉ። ፌደራል መንግስት እዚህ ዉስጥ ጣልቃ አይገባም። ነበገሩም የለበትም። ክልሉ እንጂ» በማላት ሃላፊነት ላለመዉሰድ እየሞከሩ ነዉ።

«በተለይም የአርሲን ሕዝብ ጨምሮ፣ መላዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከድህነት ጋር እየታገለ ባለበት ወቅት፣ በሚሊዮን ዶላሮች የሚቆጠር ገንዘብ፣ ከሕዝብ ካዝና ተሰብስቦ፣ ይህ ሃዉልት መሰራቱ፣ ኢሕአዴግ/ኦሕደድ ምን ያህል ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የማይፈነቅለው ድንጋይ እንደሌለ፣ ወደፊት ከመሄድ ይልቅ ዜጎችንም ወደኋላ እየጎተተ እንደሆነ የሚይሳይ ነዉ» ሲሉ የገለጹት አንድ የፖለቲካ ተንታኝ፣ ኢትዮጵያዉያን በተለይም ኦሮሞ ነን የሚሉ ከበስተጀርባ ያለዉን ተንኮል እንዲያስተዉሉ መክረዋል።

ኦሕደድ እና በዉጭ እየጮሑ ያሉ አክራሪዎች፣ ኦሮሞዉ በተቀረዉ ሕዝብ እንዲጠላ እያደረጉት ነዉ » ያሉት እኝህ ተንታኝ፣ የኦሮሞዉ ማህበረሰብ በአካባቢዉና አብረዉት ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ጋር እድሉ የተሳሰረ እንደመሆኑ፣ የሚያፋቅርና የሚያሰባስብን አጀንዳ የሚያራምዱትን እንጂ፣ አካራሪዎች ማስተናጋድ እንደሌለበት ይናገራሉ።
በአርሲ፣ በሕዝብ ገንዘብ የተሰራዉን ጡት የሚያሳይ ሃዉልት ለማየት እዚህ ይጫኑ !

የ 2014 የዓለም የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት፡- ኢትዮጵያ (HRW)

$
0
0

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ በነሀሴ ወር 2012 ዓ.ም. መሞታቸውን ተከትሎ በኢትዮጵያ የተተካው አዲሱ አመራር ሰብዓዊ መብቶችን የሚመለከቱ ማሻሻያዎች እንደሚያደርግ ተጥሎ የነበረው ተስፋ ተዳፍኗል፤ በ2013 ዓ.ም ተጨባጭ የሆነ የፖሊሲ ለውጥ አልታየም፡፡ ይልቁንም የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ሃሳብን የመግለጽ፣ የመደራጀት እና በሰላም የመሰብሰብ ነጻነት ላይ የጣሉትን ጥብቅ ገደብ ማስፈጸማቸውን የቀጠሉበት ሲሆን የሲቪል ማህበራትን እና ነጻ መገናኛ ብዙሃንን እንቅስቃሴ ለማዳከም አፋኝ ሕጎችን ይጠቀማሉ፤ግለሰቦችንም ፖለቲካዊ መነሾ ያላቸውን ክሶች በመመስረት የጥቃት ዒላማ ያደርጋሉ።

መንግስት በሃይማኖታዊ ጉዳዮቻቸው ላይ ጣልቃ መግባቱን የተቃወሙ ሙስሊሞች ዓመቱን ሙሉ በጸጥታ ሃይሎች የዘፈቀደ እስር፣ እገታ፣ ድብደባ እና ሌሎች ተገቢ ያልሆኑ አያያዞች ተፈፅሞባቸዋል፡፡ በሐምሌ ወር 2012 ዓ.ም. የታሰሩት 29ኙ የተቃውሞው መሪዎች የፍርድ ሂደት ከጥር ወር 2013 ጀምሮ ለህዝብ፣ ለመገናኛ ብዙሃን፣ እና ለቤተሰብ አባላት ዝግ ተደርጓል፡፡ እጅግ አወዛጋቢና መሠረታዊ ግድፈት ያለባቸውን ድንጋጌዎች በያዘው የሃገሪቱ የጸረ ሽብርተኝነት ህግ መሰረት ጥፋተኛ የተባሉ የተቃዋሚ መሪዎች እንዲሁም አራት ጋዜጠኞች አሁንም በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡

ከሃገር ውስጥ በሚገኝ ገቢ እና ከውጭ በሚመጣ እርዳታ በሚደገፉ ስፋት ያላቸው የልማት ፕሮግራሞች አፈጻጸም ምክንያት የአንዳንድ ማህበረሰብ ተወላጅ ነዋሪዎች ያለበቂ ምክክር ወይም ምንም አይነት ካሳ ሳይከፈላቸው ከመኖርያቸው እንዲፈናቀሉ ይደረጋል፡፡ የጸጥታ ሃይሎች ነዋሪዎችን ከመኖሪያ ቀያቸው አንስተው ወደ ሌላ ቦታ ለማስፈር ሃይል፣ ማስፈራሪያ እና ዛቻ ይፈጸማሉ፤ ለምሳሌ በታችኛው የኦሞ ሸለቆ የሚገኙ ተወላጅ ነዋሪዎች ለዘመናት የኖሩበት መሬት መንግስት ለሚያካሂደው የስኳር መስኖ ልማት ይፈለጋል በሚል መፈናቀላቸው እንደቀጠለ ነው።

በሰላም የመሰብሰብ ነጻነት

ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ ከሀገሪቱ አጠቃላይ ህዝብ ቢያንስ 30 በመቶ የሚሆነውን ቁጥር የሚይዙት የኢትዮጵያ ሙስሊም ማህበረሰብ አባላት ተከታታይ ህዝባዊ ተቃውሞ አድርገዋል፡፡ የተቃውሞው መነሻ ምክንያት መንግስት በእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ውስጥ እና በአዲስ አበባ በሚገኘው የአወሊያ መስጊድ ላይ ይፈጽማል የተባለውን ጣልቃ ገብነት በመቃወም ነው፡፡

የተቃውሞ እንቅስቃሴዎቹን ለመግታት መንግስት ሃይል ተጠቅሟል፤ የዘፈቀደ እስር እና ድብደባ በተቃዋሚዎቹ ላይ ፈጽሟል፤ እነዚህ ሕገ ወጥ ተግባራት በሀምሌ 2012 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ውለው በጥቅምት 2012 ዓ.ም በጸረ ሽብርተኝነት አዋጁ መሰረት ክስ በተመሰረተባቸው 29 ታዋቂ የተቃውሞ እንቅስቃሴው መሪዎች ላይም ተፈጽመዋል፡፡ ከፍተኛው ፍርድ ቤት የፍርድ ሂደቱን መገናኛ ብዙሃንን፣ ዲፕሎማቶችን እና የቤተሰብ አባላትን ጨምሮ ህዝብ እንዳይከታተለው ከጥር ወር ጀምሮ ዝግ አድርጎታል፡፡ አንዳንዶቹ ተከሳሾች በእስር ላይ እያሉ ተገቢ ያልሆነ አያያዝ እንደተፈጸመባቸው ተገልጿል። እንዲሁም እንዳንዶቹ ተከሳሾች ለሁለት ወራት ያህል የሕግ አማካሪ ወይም ጠበቃ ያላገኙበት ሁኔታና ከቤተዘመድ ጋር ለመገናኘት የነበረውን ችግር ጨምሮ የፍርድ ሂደቱ በሕግ በተቀመጡ ስርዓቶች አግባብ መካሄዱን ጥያቄ ውስጥ የሚከቱ በርካታ ግድፈቶች ተፈጽመዋል።

በተከሳሾቹ ላይ በመንግስት ቴሌቪዥን ውንጀላ እና ክስ ያለበት መረጃ በማስተላለፍ መንግስት ተከሳሾቹ ከፍርድ ውሳኔ በፊት ነጻ ሆነው የመገመት መብታቸውን የሚጋፋ ድርጊት ፈጽሟል። መንግስታዊ በሆነው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) ጃሃዳዊ ሃረካት የሚል ርዕስ ያለው ፕሮግራም በጥር ውስጥ የተላለፈ ሲሆን ፊልሙ ከተከሳሾቹ ውስጥ አምስቱ የፍርድ ሂደቱ ከመጀመሩ በፊት በቁጥጥር ስር እያሉ የተቀረጸ ክፍል አካቷል። ፕሮግራሙ የተቃውሞው መሪዎችን እንደ አሸባሪዎች በመቁጠር የሙስሊሞቹን የተቃውሞ እንቅስቃሴ ከአክራሪ የእስልምና ሃይሎች ጋር አነጻጽሯል፡፡

እስሩ እንዳለ ቢሆንም በ2013ም ተቃውሞው ቀጥሏል፡፡ በነሃሴ ወር መጀመሪያ ላይ በአዲስ አበባ እና በሌሎች ከተሞች የረመዳን ወር መጨረሻ የሆነው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሚከበርበት ዕለት የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡ የአይን እማኞች በአዲስ አበባ በርካታ ቁጥር ያላቸው ፖሊሶች ተሰማርተው እንደነበረ የገለጹ ሲሆን ታማኝ ምንጮች ደግሞ ሰልፈኞቹን ለመበተን ፖሊስ ከተገቢው በላይ ሃይል እንደተጠቀመ እና ለጊዜውም ቢሆንም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞችን በቁጥጥር ስር አውሎ እንደነበር ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ተሳትፎ አዲስ መጭ የሆነው ሰማያዊ ፓርቲ በሰኔ ወር ሰላማዊ ሰልፍ አካሂዷል፤ ሰልፉ በስምንት ዓመት ጊዜ ውስጥ በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ የተዘጋጀ የመጀመሪያው ሰልፍ ነው፡፡ የጸጥታ ሃይሎች የሰማያዊ ፓርቲን ጽህፈት ቤት ጥሰው በመግባት በርካታ ሰዎችን በማሰራቸውና የፓርቲውን ንብረቶች በመውረሳቸው ምክንያት ፓርቲው በነሀሴ ወር ሊያካሂድ አቅዶ የነበረው ሰልፍ ተሰርዟል። ሰማያዊ ፓርቲ ቀደም ብሎ ሰላማዊ ሰልፉን ለማካሄድ ለመንግስት አቅርቦ የነበረው ጥያቄ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቶ ነበር።

የዘፈቀደ እስር እና ጎጂ አያያዝ

የዘፈቀደ እስር እና በእስር ቤቶች የሚደረግ ጎጂ አያያዝ ከፍተኛ ችግር መሆኑን ቀጥሏል፡፡ ተማሪዎች፣ የተቃዋሚ ጎራ አባላት፣ ጋዜጠኞች፣ የሰላማዊ ሰልፍ ተሳታፊዎች እና ሌሎችም የመሰብሰብ፣ ሃሳብን የመግለጽ እና የመደራጀት መብታቸውን መግለጽ የሚፈልጉ ሰዎች በየጊዜው በዘፈቀደ ይታሰራሉ፡፡

አብዛኛውን ጊዜ በፖለቲካ ምክንያት የሚያዙ ሰዎች ላይ በተለይም እነዚህ ሰዎች ከክስ ወይም ከፍርድ ሂደት በፊት በሚታሰሩበት እና ማዕከላዊ በመባል በሚታወቀው አዲስ አበባ በሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ማዕከል ጎጂ አያያዝ ይፈጸማል፡፡ በሃይል በማስገደድ ከእስረኞች መረጃ፣ የእምነት ቃል እና ሃሳብ ለማውጣጣት እስከ ማሰቃየት የሚደርስ ጥቃት እና ሌሎች ጎጂ አያያዞች የሚፈጸሙባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ናቸው።

የተያዙ ሰዎች በተለይ ክስ ከመመስረቱ በፊት ብዙ ጊዜ የህግ አማካሪ እንዳያገኙ ይደረጋል፡፡ ያልተገባ አያያዝ የተፈጸመባቸው እስረኞች ፍርድ ቤት ሲቀርቡ ከፍርድ ቤቶች የሚያገኙት መፍትሄ እጅጉን ውሱን ነው፤ አንዲሁም እስር ቤቶች እና ሌሎች የማቆያ ቦታዎች በገለልተኛ መርማሪዎች በመደበኛነት እንዲጎበኙ አይፈቀድም፡፡ ከመንግስት ጋር ቀረቤታ ያለው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የተወሰኑ እስረኞችን እና እስር ቤቶችን የጎበኘ ቢሆንም በማንኛውም ገለልተኛ የሰብዓዊ መብቶች ወይም ሌላ ድርጅት መደበኛነት ያለው የክትትልና የምርምራ ስራ አይሰራም።

በሃምሌ ወር ወደ ኢትዮጵያ ተጉዞ የነበረው የአውሮፓ ፓርላማ የልዑካን ቡድን አባላት አስቀድሞ ፈቃድ ተሰጥቶአቸው የነበረ ቢሆንም አዲስ አበባ የሚገኘውን የቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንዳይጎበኙ በባለስልጣናት ተከልክለዋል።

ሃሳብን የመግለጽ እና የመደራጀት ነጻነት

በ2009 ዓ.ም የጸረ ሽብርተኝነት አዋጅ እና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና ማህበራት አዋጅ ከወጡ በኋላ በኢትዮጵያ ሃሳብን የመግለጽ እና የመደራጀት ነጻነት በከፍተኛ ደረጃ ተገድቧል፡፡ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና ማህበራት አዋጁ በዓለም ላይ ካሉ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ለመቆጣጠር ከወጡ በጣም አፋኝ ህጎች አንዱ ነው፡፡ በሰብዓዊ መብቶች፣ መልካም አስተዳደር፣ ግጭት አፈታት፣ እና የሴቶች፣ የህጻናት እና አካል ጉዳተኛ ሰዎች መብቶች ዙሪያ አድቮኬሲ የሚሰሩ ድርጅቶች ከጠቅላላ ገቢያቸው 10 በመቶ በላይ እርዳታ ከውጭ ምንጮች መቀበል እንደማይችሉ ይደነግጋል፡፡

በዚህ ሕግ ሳቢያ እጅግ መልካም ስም የነበራቸው የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ይሰሩ የነበረውን ስራ በከፍተኛ ደረጃ የቀነሱ ሲሆን ሌሎቹም ሰብዓዊ መብቶችን የሚመለከቱ ስራዎችን መስራት ጭራሹኑ አቁመዋል። በርካታ ታዋቂ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች በተፈጠረባቸው ስጋት ምክንያት ሃገሪቱን ለቀው ተሰደዋል፡፡

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን በከፍተኛ የመንግስት ቁጥጥር ስር ይገኛሉ፤ እንዲሁም በርካታ ጋዜጠኞች ራሳቸው ላይ ቅድመ ምርመራ ያካሂዳሉ፡፡ መንግስትን በፅኑ የሚተቹ ድረ ገጾች እና ጦማሮች በመደበኛነት ይዘጋሉ እንዲሁም የውጭ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ስርጭቶች በተደጋጋሚ ይታፈናሉ። ለነጻ የሃገር ውስጥ ጋዜጦች የሚሰሩ ጋዜጠኞች የሚደርስባቸው ተከታታይ ጥቃት እና ማስፈራራያ እንደቀጠለ ነው።

የጸረ-ሽብርተኝነት አዋጁ የፖለቲካ ተፎካካሪዎችን ለማጥቃት፣ ነጻ ሃሳብን ለማፈን፣ እንዲሁም ጋዜጠኞችን ዝም ለማሰኘት ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ በሐምሌ ወር 2012 ዓ.ም የሽብር ጥቃት ለመፈጸም በማሴር እና አሸባሪ ድርጅት ውስጥ በመሳተፍ በሚል በተከሰሰው ጋዜጠኛ እና ብሎገር እስክንድር ነጋ ፈንታ ላይ የተሰጠውን የ 18 ዓመት የእስር ቅጣት ጠቅላይ ፍርድ ቤት በግንቦት ወር 2013 እንዲጸና ወስኗል። እስክንድር ‘የፔን’ የመጻፍ ነጻነት ሽልማትን በ2012 ተሸልሟል፡፡

የፍትህ ጋዜጣ ጋዜጠኛ የሆነችው ርዕዮት ዓለሙ ገቤቦ በጻፈችው ጽሁፍ ምክንያት በጸረ ሽብር ህጉ በተጠቀሱ ሶስት ክሶች ተከሳ የጥፋተኝነት ውሳኔ ተሰጥቶባታል፡፡ በመጀመርያ ተፈርዶባት የነበረው 14 ዓመት በይግባኝ ወደ 5 ዓመት የተቀነሰላት ቢሆንም የቀረው የአምስት ዓመት ፍርድ ላይ ያቀረበችው ይግባኝ በጥር ወር ውድቅ ተደርጎባታል፡፡ ርዕዮት ከፍተኛ ዝና ያለውን የ2013 የዩኔስኮ ጉሌርሞ ካኖ የዓለም ፕሬስ ነጻነት ሽልማት ተሸልማለች፡፡

የሙስሊሙ ህብረተሰብ የሚያካሂዳቸውን የተቃውሞ ሰልፎችን ሲዘግቡ የነበሩ ጋዜጠኞች ማስፈራሪያ ደርሶባቸዋል እንዲሁም በዘፈቀደ ታስረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ከህትመት ውጭ የሆነው የሙስሊሞች ጉዳይ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ሰለሞን ከበደ በጥር ወር የታሰረ ሲሆን የጸረ-ሽብር ህጉን አዋጅ በመጣስ ክስ ተመስርቶበታል፡፡ የጋዜጣው የቀድሞ ዋና አዘጋጅ ዩሱፍ ጌታቸው በ2012 በተመሳሳይ ህግ ተከሷል፡፡ ሌሎች በርካታ ጋዜጠኞች በ2013 ከኢትዮጵያ ተሰደዋል፤ ይህም ሃገሪቱን በስደት ላይ ባሉ ጋዜጠኞች ብዛት ከዓለም ሶስተኛ ሃገር አድርጓታል፡፡

ከልማት ፕሮግራሞች ትግበራ ጋር በተያያዘ የሚፈጸም በሃይል ማፈናቀል

የኢትዮጵያ መንግስት ከሚያካሂደው የሰፈራ መርሃ ግብር ጋር በተያያዘ አንደሚፈፀሙ የሚገለጸውን በደሎች መንግስትም ሆነ የለጋሽ ማህበረሰብ አባላት በበቂ ሁኔታ መመርመር አልቻሉም፡፡ የመሰረታዊ አገልግሎቶችን አቅርቦት ለማሟላት በሚል ምክንያት በዚህ መርሃ-ግብር 1.5 ሚሊዮን የገጠር አካባቢ ነዋሪዎች ከመኖርያ አካባቢያቸው ተነስተው በሌሎች ቦታዎች እንዲሰፍሩ ተደርጓል፡፡ ይሁንና መርሃ ግብሩ ተግባራዊ በተደረገበት በመጀመሪያው ዓመት በጋምቤላ ክልል አንዳንድ ቦታዎች የተካሄደው ሰፈራ በሃይል የተደረገ ሲሆን ድብደባ እና የዘፈቀደ እስር የተፈጸሙባቸው አጋጣሚዎችም ነበሩ። ከዚህም ሌላ የማስፈሩ ስራ የተካሄደው ከተነሺዎቹ ጋር በቂ ምክክር ሳይደረግ እና በቂ የካሳ ክፍያ ሳይፈጸም ነው።

የዓለም ባንክን የአሰራር ተጠያቂነት የሚከታተለውና ከባንኩ ነፃ የሆነው የቁጥጥር ቡድን በስደት ላይ የሚገኙ የአኙዋክ ብሔረሰብ አባላት ባንኩ ጋምቤላ ውስጥ የራሱን የአሰራር ሁኔታዎች ጥሷል በማለት ያቀረቡት አቤቱታ ላይ ሙሉ ምርመራ እንዲደረግ በማለት ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ የዓለም ባንክ ስራ አስፈጻሚ ዳይሬክተሮች ቦርድ በሐምሌ 2013 ተቀብሎታል። ይህ ሪፖርት በሚዘጋጅበት ወቅት ምርመራው በመካሄድ ላይ ነበር፡፡

ኢትዮጵያ በታችኛው የኦሞ ሸለቆ የሚኖሩ 200 ሺህ ተወላጅ ነዋሪዎችን ከመሬታቸው ላይ በማስለቀቅ በ245 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የስኳር ልማት ስራ ማከናወኗን ቀጥላለች። እነዚህ በጥምር ግብርና እና ከብት እርባታ የሚተዳደሩ ተወላጅ ነዋሪዎች ለዘመናት ከኖሩበት መሬት ተፈናቅለው በሰፈራ መርሃ ግብር አማካኝነት በቋሚ መንደሮች እንዲሰፍሩ ተደርጓል።

ዋና ዋና ዓለምአቀፍ አካላት

ኢትዮጵያ ከውጭ ለጋሾች እና ከአብዛኞቹ የቀጠናው ጎረቤቶቿ ጋር መልካም ግንኙነት አላት፡፡ ይህ ጠንካራ ግንኙነት የተመሰረተው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በመሆኗ፣ ለተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ በምታደርገው አስተዋጽኦ፣ ከምዕራብ ሃገራት ጋር በጸጥታ ጉዳይ ላይ ባላት ትብብር እና የተወሰኑ የሚሊኒየም የልማት ግቦችን በማሳከት ረገድ ባስመዘገበችው እድገት ምክንያት ነው፡፡ ሃገሪቷ ያላት ይህ ጠንካራ ግንኙነት የዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ላይ ያለችበትን አሳሳቢ ሁኔታ በዝምታ እንዲያልፍ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡

በ2013ም ኢትዮጵያ በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን መካከል ያላትን የአደራረዳሪነት ሚና የቀጠለች ሲሆን ወታደሮቿም በአወዛጋቢው አቢዬ ግዛት የሰፈነውን አስተማማኝ ያልሆነ ጸጥታ በማስጠበቅ ተግባር ላይ ተሰማርተዋል። የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደሶማልያ ዘልቀው መግባታቸውን የቀጠሉ ቢሆንም ወታደሮቹ በዚያ የተሰማራው የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ሃይል አካል አይደሉም።

ኢትዮጵያ ከፍተኛ መጠን ያለው ድጋፍ ከለጋሾች ማግኘቷን የቀጠለች ሲሆን በ2013 ያገኘችው ድጋፍ 4 ቢሊዮን ዶላር ይጠጋል፡፡ የኢትዮጵያ የልማት አጋሮች አንደመሆናቸው መጠን ለጋሽ ሃገራት እጅግ አስከፊ ሆነውን የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ሁኔታ አስመልክቶ ግን ዝምታን መርጠዋል። ከልማት መርሃ ግብሮች አፈጻጸም ጋር በተያያዘ ተፈጽመዋል የተባሉ በደሎችን አስመልከቶ የሚቀርቡ ክሶችን ለመመርመር የሚወስዱት እርምጃም እጅግ ውሱን ነው።

ግብጻዊያን ኢትዮጵያ በምትገነባው ታላቁ የህዳሴ ግድብ ምክንያት ከናይል ወንዝ ከፍተኛ መጠን ያለው ውሃ ወደ ግድቡ ይቀየሳል የሚል ስጋት ስለገባቸው በ2013 ዓ.ም. የኢትዮጵያ እና የግብጽ ግንኙነት የበለጠ ሻክሯል። 85 በመቶ የሚገመተው የናይል ወንዝ ውሃ ምንጭ ኢትዮጵያ ስትሆን ግብጽ ደግሞ ለሚያስፈልጋት ማንኛውም የውሃ ፍላጎት ሙሉ በሙሉ በናይል ወንዝ ላይ ጥገኛ ነች፡፡ ግድቡ 6 ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል በማመንጨት ከአፍሪካ ትልቁ የሃይድሮኤሌክትሪክ ፕሮጀክት ይሆናል፡፡ የግድቡ ግንባታ የተጀመረው በ2012 ሲሆን በ2018 ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ከምዕራባዊያን ለጋሽ ሀገራት በተጨማሪ ቻይና፣ ህንድ እና ብራዚል የተለያዩ ከፍተኛ መጠን ላላቸው የልማት ስራዎች የሚያደርጉት የገንዘብ ድጋፍ በየጊዜው እየጨመረ መጥቷል። ወደ ኢትዮጵያ የሚገባው የውጭ የግል ኢንቨስትመንት እየጨመረ የሚገኝ ሲሆን በ2013 የግብርና ንግድ፣ ሃይድሮኤሌክትሪክ፣ ማዕድን ማውጣት እና ነዳጅ ፍለጋ ኢንቨስትመንት ስራዎች በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመሩ ነው።የግብርና ንግድ ኢንቨስትመንት በዋናነት ከህንድ፣ ከመካካለኛው ምስራቅ እና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሚመጡ ሲሆን የመሬት ዋጋው ዝቅተኛ መሆን እና ለጉልበት የሚከፈለው ዋጋ አነስተኛነት ባለሃብቶቹን የሚስብ ሆኗል። እንደ ሌሎቹ በርካታ ትልልቅ የኢትዮጵያ የልማት ፕሮጀክቶች ሁሉ እነዚህ መርሃ ግብሮች ሲተገበሩ ሰዎችን ከመሬታቸው በሃይል የማፈናቀል ተግባር ሊፈጸም ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አለ።

Viewing all 1809 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>