አቡጊዳ –የመኢአድ መሪ አቶ አበባዉ ዉህደቱን ላለመፈረም ያቀረቡት ምክንያት በቂ አይደለም ተባለ
የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ አበባዉ መሃሪ በደብተራው ፓልቶክ ክፍል ቀርበዉ ባደረጉት ሰፊ ዉይይት፣ በመኢአድ እና በአንድነት መካከል ስላለዉ የዉህደት እንቅስቃሴ ማብራሪያ ሰጥተዋል። «አንድነቶች እኮ ልጆቻችን ናቸው። መኢአድ የነበሩ ናቸው» ያሉት አቶ አበባዉ በመኢአድ እና በአንድነት መካከል የፖለቲካ ፕሮግራም ልዩነቶች...
View Articleሲቪል ድርጅቶች –ግርማ ሞገስ
ዴሞክራሲ ስርዓት በመገምባት ላይ በሚገኙ ወይንም የዴሞክራሲ በዳበረባቸው አገሮች ውስጥ እጅግ ብዙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና ተቋሞች ከመንግስት ነጻ ሆነው ይመሰረታሉ። በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የጋዜጠኞች ማህበሮች፣ የጋዜጠኞች መድረኮች፣ የሰራተኛ ማህበሮች፣ የተማሪ ማህበሮች፣ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች፣ የስነጽሑፍ...
View Articleየአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን ምክር ቤት ስብሰባ በመንግስት ካድሬዎች በሀይል ተደናቀፈ –አንድነት
የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ እና ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ደህንነታቸው አደጋ ላይ ነው፡፡ የሟቹን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር የአቶ መለስ ዜናዊ ምስል ያለበት ቲሸርት የለበሱ ከ 10 የሚልቁ የመንግስት ካድሬዎች በወላይታ ሶዶ እየተደረገ የነበረውን አንድነት ፓርቲ የወላይታ...
View Articleየአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ልሳን የሆነው ፍኖተ-ነጻነት ጋዜጣ በግማሽ ሚሊዮን ብር የራሱን ማተሚያ...
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ልሳን የሆነው ፍኖተ-ነጻነት ጋዜጣ በግማሽ ሚሊዮን ብር የራሱን ማተሚያ ማሽን በመግዛት እና በመትከል በቅርብ ቀን ሕትመቱ ለሕዝብ በገበያ ላይ እንድሚውል ተገልጸ፡፡ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ሐላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ተፈራ እንደገለጹት፤ የአንድነት ፓርቲ እና የፍኖተ...
View Articleእነ ዳንኤል ተፈራ ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ተለቀቁ!! ወላይታ ሶዶ ነፃነት አልባዋ የማፊያ ካድሬዎች ከተማ!!
ከወላይታ ዞን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች የእስርና እንግልት ማብራሪያ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራና ድርጅት ጉዳይ ም/ሃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ በደቡብ ቀጠና በወላይታ ዞንና በሲዳማ ዞን አዋሳ ከተማ ያሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር የፓርቲውን የትግል ስትራቴጅክ ዕቅዶች ላይ...
View Articleአቡጊዳ –የአንድነት እና መኢአድ ዉህድ ፓርቲ የመድረክ አባል አይሆንም ተባለ
መኢአድ እና አንድነት መጋቢት 11 ቀን የቅድመ ዉህደት ፊርማ ይፈረማሉ ተብሎ ሲጠበቅ ፣ ከመኢአድ ፕሬዘዳንት አቶ አበባው መሃሪ በተጻፈ ደብዳቤ፣ ላልተወሰነ ጊዜ ፊርማው እንዲዘገይ መደረጉ በስፋት ተዘግቧል። አቶ አበባዉ የቅደመ ዉህደቱን ፊርማ ላለመፈረም ሶስት ያልተፈቱ ነጥቦች የሚሏቸውን ያቀርባሉ። ነጥቦቹም የዉህድ...
View Articleአቡጊዳ –ሕወሃቶች አሰብን እናስመልሳልን እያሉ ነው !
በሕዝብ ብዛት ቁጥር ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሁለተኛ ከአለም ደግሞ አሥራ አምስተኛ ናት። ወደ ሰማኒያ ሚሊዮን ሕዝብ ሲኖራት፣ ያን ያህል ሕዝብ ኖሯት የባህር በር የሌላት ብቸኛ አገር ናት። ከኢትዮጵያ ቀጥሎ ብዙ ሕዝብ ኖርቷት የባህር በር የሌላት አገር፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድ ሶስተኛ የሚሆን ሕዝብ ያላት ዩጋንዳ ናት።...
View Articleየአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት በተፈናቃዩች ተጥለቀለቀ:: –አንድነት
ተፈናቃዩቹ ከጎንደር አካባቢ ተነስተው ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ወደ ምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ዳኖ ወረዳ በመውረድ በእርሻ ስራ የተሰማሩ ገበሬዎች ናቸው፡፡ከ1996ዓ.ም ጀምሮ በተለያየ ደረጃ ‹‹ክልላችንን ለቅቃችሁ ውጡ››ሲባሉ ቆይተዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማስፈራሪያው ወደ ግድያ፣ድብደባና ወከባ በማደጉ ለአቤቱታ...
View Articleበወላይታ የተፈፀመው መንግስታዊ ውንብድና የስርአቱን ዝቅጠት የሚያሳይ ነው!! ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ...
በአገራችን ኢትዮጵያ ሁሉም መብቶች ያለምንም ገደብ የሚከበሩበትን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ላለፉት ዓመታት በርካታ መስዋዕትነቶች ተከፍለዋል፡፡ ዜጎች የመደራጀትና ሀሳባቸውን የመግለጽ ህገ-መንግሥታዊ መብት እንዳላቸው ጧት ማታ በመንግሥት ብዙሀን መገናኛዎች ቢለፈፍም፤ ሁሉም ነገር የይምሰልና የስልጣን እድሜ...
View Articleየእሳት ፖለቲካ በኢትዮጵያ (Fire Politics in Ethiopia) –ይሄይስ አእምሮ
በሃይማኖት መሪዎችና አገልጋዮች ዙሪያ ሰሞኑን አንዲት መጣጥፍ ጽፌ ለድረ ገፆች ልኬ ነበር፡፡ ለኅሊናቸው ተገዢ የሆኑ አወጡት – አስነበቡን፤ እግዚአብሔር ይስጣቸው፡፡ ለባህልና ለይሉኝታ ያደሩት እንዲሁም እነሱ በሚፈልጉት ሙዚቃ ብቻ ታንጎና ማሪንጌ መደነስ የሚፈልጉት ወደቅርጫታቸው ከተቱት – ይክተቱት፡፡ ሁሉም...
View Articleየአዲስ አበባው የእሪታ ቀን ተቆረጠ –የአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቅ ክፍል የፓርቲውን ደብዳቤ ተቀብሏል፤ –ፍኖተ ነጻነት
የአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቅ ክፍል የፓርቲውን ደብዳቤ ተቀብሏል የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የከተማይቱ መሰረታዊ ችግሮች እየተባባሱ ከመምጣት ውጪ ለውጥ ማሳየት ባለመቻላቸው ለዚህ ተጠያቂ መሆን ያለበትን የከተማይቱን አስተዳደርና ገዢውን ፓርቲ የሚቃወም ‹‹የእሪታ ቀን››በሚል...
View Articleአቡጊዳ –የሕገ መንግስቱ መሰረት የሆነው ቻርተር በኤርትራዊዉ በረከተ ሃብተ ስላሴ በሚመራ ኮሚሽን እንደዘጋጀ ተገለጸ
ኢሕአዴግ አዲስ አበባ ሲገባ፣ በጎሳ የተደራጁ ድርጅቶችን በማሰባሰብ ፣ በ1991 በተደረገው የአዲስ አበባ ኮንፈራንስ ፣ የሽግግር መንግስት ቻርተር ተብሎ የሚታወቀዉን ሰነድ እንዲጸድቅ ማስደረጉ ይታወቃል። ቻርተሩ አሁን ያለውን በጎሳ ላይ የተመሰረተ ዘረኛ ፌዴራል አወቃቀር ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲገበር ያደረገ ከመሆኑም...
View Articleየውህደቱ ቁማርተኞች –አስራት አብርሃ
የሀገራችን የተቃውሞ ፖለቲካ ወደ አንድ ጠንካራ የለውጥ አማራጭነት እንዲሰባሰብ እና ገዥውን ፓርቲ የሚገዳደር ወሳኝ ኃይል ሆኖ እንዲወጣ ማስቻል የብዙ ቀናት አሳቢ ኢትዮጵያውያን ፍላጎት እንደሆነ ይሰማኛል። እኔም ራሴን ይህ ዓላማ ከፍፃሜ እንዲደርስ ከሚፈልጉ ወገኖች ውስጥ እንደ አንዱ በማድረግ እቆጥረዋለሁ። ውህደት...
View Articleየሰማያዊ ፓርቲ ቁጥር 5 ነገረ- ኢትዮጵያ ጋዜጣ ርእስ አንቀጽ –ለለውጡ ዝግጅት ያስፈልጋል!
ለለውጡ ዝግጅት ያስፈልጋል! እንዲህም ተብሏል ለውጥን ማዘግየት ይቻል እንደሆን እንጂ ገድቦ ማስቀረት እንደማይቻል ከትርክት አልፎ በተግባር የታየ ሀቅ ነው፡፡ በተለይ ህዝባዊ የለውጥ እንቅስቃሴን አፍኖ መዝለቅ የማያዛልቅ ሙከራ እንደሆነ በተለያየ ጊዜ በተለያዩ ሀገራት ታይቷል፡፡ በዓለም ላይ የማይለወጥ ነገር አለ...
View Articleአቡጊዳ –አትላንታ እና ዴንቨር የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በአዋሳና በደሴ የሚደረጉትን የሚሊየም እንቅስቅሴ ስፖንሰር...
በአትላንታ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በአዋሳ፣ በደንቬር የሚኖሩ ደግሞ በደሴ ለሚደረጉት የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነትና ለፍትህ እንቅስቃሴዎች የሚያስፈልግትን ወጭዎች ሙሉ ለሙሉ እንደሚሸፍኑ ማረጋገጣቸውን ፣ የሰሜን አሜሪካ የአንድነት ድጋፍ ማህበራት፣ ሸንጎን እና የሽግግር ምክር ቤቱን ያሳተፈው የሚሊዮኖች ድምጽ...
View Articleወያኔ ኢህአዲግ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅም የቆመ መንግስት አይደለም :: (ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ)
ወያኔ ኢህአዲግ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅም የቆመ መንግስት አይደለም :: ሀገር ማለት የተለያዩ ብሄሮች ፣ የተለያዪ ጓሳዎች እና የተለያዩ ሃይማኖቶች ያሎቸው ሰዎች መኖሪያ ናት :: እኛም ሀገራችን ብለን የምንጠራት ሀገራችን ኢትዮጵያ አኩሪ ታሪክ ያላት የተለያዩ ህዝቦች መኖሪያ ሀገር ስትሆን ሕዝቦቾም...
View Articleያልታሰረው ማን ነው?? ከአንተነህ መርዕድ
ሰሞኑን አንድ ኢትዮጵያዊ በቶሮንቶ የህሊና እስረኞችን ለመዘከር በግሉ አዳራሽ ተከራይቶ የአንዱዓለም አራጌን “ያልተሄደበት መንገድ” የሚለውን መጽሃፍ ለሽያጭ በአቀረበበት ቦታ ተገኝቼ ነበር። በዚህ አዳራሽ አንዱዓለምን፣ እስክንድርን፣ ርዕዮትን …ወዘተ ለመዘክር ብለው የተሰባሰቡ ሰዎች ብዛት ስመለከት “በእውነቱ...
View Articleየነጻነት ደዉል በአዲስ አበባ፣ በአዋሳ እና በደሴ ተደዉሏል! –የሚሊዮኖች ድምጽ
የአንድነት ፓርቲ ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነው። በኢትዮጵያ የፌዴራልም ሆነ የክልል ባለስልጣናት የተለያዩ ሕጎችን ደንቦች ሊያወጡ ይችላሉ። ነገር ግን ሕገ መንግስቱ የሕጎች ሁሉ የበላይ ነው። በሕገ መንግስቱ የተቀመጡ መሰረታዊ የሕግ አንቀጾችን ማንኛዉም አካል ሊሽረው ወይንም ሊቀለብሰው...
View Articleየክህደት ኣቀበት አብረሃ ደስታ
እውነቱን ለመናገር በኢትዮጵያ ፖለቲካ ምክንያት እንደሰሞኑን በግኜ የማውቅ ኣይመስለኝም። ኣቤት ክህደታችን! እንዴት ተክነንበታልሳ ወገኖች! ረጋ ብላችሁ በጥሞና ኣንድታነቡኝ ብርታቱን ይስጣችሁ፥ 1• በዛሬይቱ ኢትዮጵያችን ነባራዊ ሁኔታ ብሄር ማለት ምን ማለት እንደሆነ በትክክል የሚነግራችሁ ሰው ኣታገኙም። የብሄር...
View Articleጎሠኛነትና ሽብርተኛነት (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)
March 29, 2014 የጎሠኛነት አጭር ትርጉም ዓለምን በራሱ ጠባብ ኢምንትነት የሚለካ ሰው ነው፤ ለኪው መለኪያው ነው፤ መለኪያውም ለኪው ነው፤ ጎሠኛነት የዘረኛነት የባሕርይ ልጅ ነው፤ ዘረኛነትም ሆነ ጎሠኛነት መሠረታቸው ድንቁርና ነው፤ የድንቁርናው ዓይነተኛ መገለጫ ‹‹ንጹሕ›› የሚለው ቃል ነው፤ ለዚህ ዋና ምስክር...
View Article