Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all articles
Browse latest Browse all 1809

አቡጊዳ –አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የታፈኑት ጠቅላይ ሚኒስተሩ ሳይነገራቸው ነው ተባለ

$
0
0

ኢትዮጵያ ሪቪው ምንጮቹን ጠቅሶ ፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን የታፈኑት፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ የሆኑት አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ሳያወቁት ፣ በአቶ ጌታቸው አሰፋ የሚመራው የሕወሃት ደህንነት ጽ/ቤት እና በአቶ ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል ዉሳኔ እንደሆነ ዘገበ። ሁለቱ የሕወሃት ባለስልጣናት፣ የሆነውን ነገር ለጠቅላይ ሚኒስተሩ ለመንገር እንኳን ደንታ እንደልነበራቸው ኢትዮጵያ ሪቪው፣ እነ አቶ ጌታቸው አሰፋ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝን እንደ አለቃቸው ሳይሆን እንደ «አህያቸው» እንደሚመለከቷቸው በዘገባው አስፍሯል።

«ያለ እንግሊዞች ትብብር፣ የየመን ደህንነቶች የእንግሊዝ ፓስፖርት ያለው ሰው፣ ያለ እንግሊዞች አዎንታ የመያዙ እድል በጣም ትንሽ ነው» ሲልም የእንግሊዝ ደህንነት በጉዳዩ ላይ እጁ ሊኖርበት እንደሚችል ኢትዮጵያ ሪቪዉ አክሎ ገልጿል።

የእንግሊዞች እጅ እንዳለበት በኢትዮጵያ ሪቪዉ የቀረበው ግምት እንደተጠበቀ፣ በተለያዩ መድረኮች ሌሎች ግምቶችም እየተሰጡ ነው። የኤርትራ መንግስት ባለስልጣናት ወይንም አስመራ ባለው የግንቦት ሰባት መዋቅር ዉስጥ ያሉ አመራሮች፣ የአቶ አንዳርጋቸውን የጉዞ መረጃ አስቀድመው ለሕወሃት ደህንነቶች በመስጠታቸው፣ አቶ አንዳርጋቸው ሊያዙ እንደቻሉም የሚናገሩ ጥቂቶች አይደሉም።

«አቶ አንዳርጋቸውን ማን አስያዛቸው ? » ለሚለው ጥያቄ ግልጽነትና ተጠያቂነት ባለበት መልኩ የግንቦት ሰባት ድርጅት፣ ምላሽ መስጠት እንዳለበትም ብዙዎች ይናገራሉ።

የኢትዮጵያ ሪቪዉን ዘገባ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ !


Viewing all articles
Browse latest Browse all 1809

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>