Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all articles
Browse latest Browse all 1809

ኢህአዴግና የመልካም አስተዳደር እጦት ብሩህ ቦጋለ ከስዊዘርላንድ

$
0
0

ኢትዮጵያ ለብዙ ዘመናት የምትታወቅበት ነገር ህዘቦቸ አብሮ የመኖር የመተሳሰብ፣ የመከባበር እና የሠላም ተምሳሌት መግለጫ መሆናን ነው፡፡ እኛ የተለያየ ጎሳ ያለን የአትዮጵያ ልጆች ባለፈው ታሪካችን ብዙ አንድ የሚያደርጉን ነገሮች አሉን የዛሬ ማንነታችን ላይ አሻራ ያላቸው ማንም በቀላሉ ሊለያያቸው የማይፈቅዱለት የጋራ የሆነ ታሪክ ያለን የብዙ እምነቶችና ባህሎች ባለቤቶች ነን አንዱም ጎሳ የሌነውን ጎሳ ባህል ቋንቋውን ማንነቱን አክብሮ በሠላምና በፍቅር የኖረ ህዘብ ነው ማለት ይቻላል፡፡

ይሁን እንጂ ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢህአዴግ /ህውሃት ስልጣኑን ከተቆናጠጠበት ከ1983 ማግስት በአጠቃላይ የአፊድሪ መንግስት ከተቋቋመበት ጀምሮ ባሉት አመታት ውስጥ ኢህኢዴግ እራሱ በመለመለቸው የህዝብ ተወካዮች አማካይነት በህግ መንግስቱ ጉባኤ ኅዳር 29 ቀን 1987 በስራ ላይ እንዲውል ብሎ ካፀደቃቸው ህጎች ውስጥ አንዱ አጨቃጫቂና አከራካሪ የነበረው አንቀፅ 39 ላይ የተቀመጠው የብሔሮች ብሔረሰቦች ሕዝቦች መብት በሚለው ስር ማንኛውም የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሠብ ሕዝብ የራስን ዕድል በራሱ የመወሠን እስከመገንጠል ያለው መብቱ በማናቸውም መልኩ ያለ ገደብ የተጠበቀ ነው የሚለው አዋጅ ነበር፡፡

ይህን አዋጅ ተከትሎ በተለያዩ የኢትዮጵያ የታሪክ ምሁራን እና ስለወደፊቷ አንዲት ኢትዮጵያ በሚጨነቁ የአትዮጵያዊነት ስሜት በሚሠማቸው የፖለቲካ አዋቂዎች በወቅቱ ህጉ ከህዝባችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር በአንፃሩ ሲታይ ከአትዮጵያ የባህልና አኗኗር ጋር ይጋጫል በማለት ተቃወሙ ይሁን እንጂ ኢህዴግ/ህወሃት ጆሮ ዳባ ልበስ ከማለቱም ሌላ ይባስ ብሎ በተቆጣጠረው የመገናኛ ብዘሁን አዋጁ ለግለሠብ እና የብሔር ብሔርሰቦችን መሠረታዊ መብቶች ለማስከበር ባህሎችና ሀይማኖቶች ካላንዳች ልዮነት እንደራመድ፣ጥቅሙን፣ መብቱን ነፃነቱን በጋራ እና በተደጋጋፊነት ለማሳደግ እንደሁም ልማትን የሚያሳልጡ ናቸው እያለ ይዘምር ነበር፡፡ዛሬም ድረስ ይህን ፕሮፓጋንዳ () ለህዝቡ በሠፊው መለፈፋን አላቆመም፡፡ ወደ እውነታው ስንመጣ ግን የተባለው፤ አሁን ዕየተባለ ያለውና ዕየሆነ ያለው ነገር ግን ፍፁም ለየቅልናቸው፡፡

ዕስኪ ስለ ዕውነት የማንናችን የብሄረሰብ ክፍል ተወላጆች ነን እንደፈለግን ከክልል ክልል ተዘዋውረን ወደ ትግራይ ወይ ወደ ሌላው ክልል ሄደን ስንቶቻችን ነን በቋቋችን ስራ ተቀጥረን መኖርስ የምንችለው?ለዚህም ነው ወትሮም የፀደቀበት አላማ የኢትዮጵያን ኅዝብ ለመከፋፈል ነው የተባለበት ምክንያት፡፡ለምሳሌም መጥቀስ በያስፈልግ ትግራይን የመገንጠል አላማ ይዞ ይንቀሳቀስ የነበረው ህወሀት ዛሬም መንግስት ከሆነ በኃላም የቀድም የጎሳ ስሙን ከለመቀየሩም በላይ ለስልጣን ያበቃቸው አጋር ድርጅቶቹም ባብዛኛው በአንድም ሆነ በሌላ ኢትዮጵያን ለመከፋፈል ከሚሹ ኃይላት በተገኘ ድጋፍ የተመሠረቱ ናቸው፡፡ለዚህም ነው ዛሬ አህአዴግ/ህወሃት ኤትዮጵያ ከነበረችበት የአንድነትና የአብሮነት ስሜት ውስጥ ለማስወጣት ህዝቡን ወደ ማይፈልገው ጎሳዊ አስተሳሰብ ግጭት ውስጥ ለመስገባት የሚሞክረው፡፡ ይህ ጎሳዊ አስተሳስብና ግጭት ዛሬ ከአሮሚያ ከአማራው ክልል አልፎ ወደጋምቤላ ቤንሻንጉል ጉመዝ ክልል ተዛምቷል፡፡

እነኚህ ጎሳዊ ፅንፈኛ ፀብ አጫሪ ሀይሎች የሚላቸውም ከእራሱ ከአህዴግ/ህዋሀት ጋር የተለያዩ ይምሠሉ እንጂ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው እንጂ ህዝብ እንዳይደለ እንዳልሆነም ሠፊው ህዝብ በገሀድ ያውቃቸዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በአሁኑ ወቅት ህዝባችን በከፍተኛ በሆነ የኑሮ ውድነት ውስጥ ተዘፍቆ ይገኛል፡፡ ይኸውም ገዢው ፓርቲ በሀገር ውስጥ በመንግስት ቁጥጥር ስር ባሉት የምርት ውጤቶች ላይ ዋጋቸውን ከውጭ አገር የጉምሩክ ቀረጥ ተከፍሎባቸው ለታችኛው ተጠቃሚ በሚሸጥበት ዋጋ ላይ ተንተርሶ የሀገር ውስጥም ምርት ዋጋ ጣራ ላይ እንዲወጣ መሰረት በመጣል፤ ከሀገር ውስጥ ምርትን ገዝተው ወደ ውጭ ሀገር ኤክስፖርት ለሚያደርጉ ግለሰቦች ገደብ የለሽ ፍቃድ በመስጠት እነዚህ ገደብ የለሽ ላኪ ነጋዴዎች በሀገር ውስጥ የሚገኘውን የሰብል ምርት በየገጠሩ በደላላ እየገቡ በውድ ዋጋ ተሸምተው እየገዙ ወደ ውጭ በሚልኩበት ጊዜ ለከተሜው ሸምቶ አደር ሕዝብ ላይ አቅርቦቱ ዝቅተኛ እየሆነ ይበልጥ ዋጋው ከእለት ወደ እለት እየናረ ይገኛል፡፡

በዚህ አካሄድ መንግስት ከላኪው ነጋዴ ከፍተኛ የሆነ ቀረጥ ሲሰበስብ ነጋዴው በተመሳሳይ ከፍተኛ ተጠቃሚ ነው፡፡ በዚህ መሀል አሁንም ተጎጂው አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ሸምቶ አደሩ ሆኖ ይገኛል፡፡ ለኔ የሚገርመኝ ሌላው ነገር ደግሞ ይህ መንግስት በሀገር ውስጥ የሚመረቱትን የምርት ውጤቶች ለአከፋፋዮች በኮታ በተመጣጠነ ዋጋ ሽጦ ለታችኝ ህዝብ ክፍል እንዲደርስ በማድረግ ፈንታ እራሱ መንግስት እንደ አንድ የግል ነጋዴ በሞኖፓል የያዘውን ምርት ለሌላኛ አከፋፋይ በጨረታ ይሸጣል፡፡ እንደኔ እንደኔ ይህ መንግስት ይሄን የሚያደርግበት ምክንያት ብዙ ተጫራቾች በሚቀርቡበት ጊዜ ሁሉ ተጫራቾች አንዱ ካንዱ ዋጋ አብልጦ ካልተጫረተ የማሸነፍ እድል ስለማይኖረው የግድ ለምርቱ ዋጋ መናር አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ ይሁን እንጂ ነጋዴው በፈለገው የዋጋ እርከን አሸንፎ ቢገዛ ኪሳራ የለበትም፡፡ ለምን በገዛው ዋጋ ላይ ተተርሶ ትርፉን አክሎበት ለታችኛው ሸማች አቅርቦ አትራፊ መሆኑ አይቀሬ ነውና፡፡ በዚህ አካሄድ መንግስት የሚፈልገውን ገቢ ይሰበስባል፡፡ነጋዴውም ትርፉን ያገኛል ለዛም ነው አሁንም ተጎጂው ሰፊው ሸምቶ አደሩ ህዝብ ነው ለማለት የተገደድኩት፡፡
ከዚህም የበለጠ ልናሰምርበት የሚገባው ጉዳይ ቢኖር የማናቸውም ምርት ዋጋ እንዲንር ያደረገው አከፋፋዩ ወይም የታችኛው ነጋዴ ሳይሆን አሁን ስልጣን ላይ ያለው መንግስት ብቻ ነው፡፡ ይህ የማይዋጥላቸው ካሉም አንድም ወኪሎቻቸው ወይም አድር ባዮች ወይም ዝቅተኛ የንቃተ ህሊና ያላቸው ብቻ ናቸው፡፡ ለዚህም ነው የሀገራችን የእድገት ደረጃ ከጊዜ ወደ ጊዜ ማዕከላዊ ባልሆነ የመልካም አስተዳደር እጦት መዛባት ነው ሀገራችን ኢትዮጵያ ለውጥ የማይታይባትና የህዝቡንም የፖለቲካ አመለካከት እንዳይዳብር በማድረግ ለገዥ ወደቡ ብቻ ተንበርካኪ ሆና መብትና አንድነት ጥቅሙን ማስከበር ተስኖት እንዲኖር ያደረገው፡፡

በተጨማሪም ከመንግስት ፖለቲካ ጭ በሰፊው ህዝብ ተቆርቋሪ የሆኑ ከስልጣን ፈላጊነት ባሻገር በግል የሚንቀሳቀሱ የበሰሉ ኤክስፐርቶች ብሎም ኢኮኖሚስት አስተያየት ሰጪ ምሁራን ሀሳብ እና አመለካከታቸውን የመግለፅ መብት ያለመከበሩም ጉዳይ ሌላኛው ችግር ነው፡፡ ለዚህም ነው ገዢው ፓርቲ እንደፈለገ ከተቀሩት የታችኛው ህብረተሰብ ክፍል ተጨማሪ ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ በነጻ ገበያ በሚል ሽፋን በህብረተሰቡ ላይ ከፍተኛ ታክቲክና ስውር ደባ ተጠቅሞ በግብር መልክ ያላአግባብ በቢሊዮን የሚቆጠር ህጋዊ ልሆነ ገቢ እየሰበሰበ ህዝቡን ባለ ዕዳ እና አሁን ኢትዮጵያ ላለችበት ከፍተኛ የሆነ የኑሮ ውድነት ውስጥ ተዘፍቃ እንድትቆይ ያደረጋት፡፡


Viewing all articles
Browse latest Browse all 1809

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>