የ24 አመታት ሂደቶች .. ዜጎች በሃገራቸው ሰርተው እንዳይኖሩ የሆነበት…ለአንድ ወገን ያደላ እና በፓርቲ አባልነት ላይ የተመሰረተ አድልኦ የተንሰራፋበት … ጥቂት የፖለቲካ ቱጃሮች ብዙሃን ደሆች የፈሉባት … አምባገነንነት የነገሰባት ….ሃገራችን ኢትዮጵያ ልጆቿን አቅፋ እንዳታኖር የተደረገበት እና ወደ ስደት የተበተኑበት … ይህንን ሁሉ ተሸክመን ከትከሻችን ለማውረድ የምንታገልበት ወቅት … ከትግሉ ፍሬዎች አንዱ ሰማያዊ ፓርቲ ነው::ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊነቱን ይዞ በሚቀሳቀስበት ቦታ ላይ እንደ አሸባሪ አድርጎ መፈረጅ የማያዛልቅ ጸሎት ለቅጽበት መሆኑን ማወቅ ግድ ይላል::ስርአቱ የገፋቸው በሃገራቸው ሰርተው እንዳይኖሩ ያደረጋቸው ወጣት ወገኖቻችን በስደት በረሃ መሰዋታቸው ለለውጥ የሚደረገው አብዮታዊ ትግል አንዱ አካል መሆኑን ይመሰክራል::
አለም እየመሰከረ ወያኔ በሊብያ የሟቾችን ዜግነት አጣራለሁ ማለቱ ሲገርምን ሳማያዊ ፓርቲ መወንጀል የፖለቲካ ኪሳራን በግልጽ ያሳያል::በሊቢያ የታረዱትን ወገኖቻችንን ሃዘን ተከትሎ የወያኔው ስርአት መወንጀል የሚገባውን አሸባሪው አይሲስ እያለ ሰማያዊ ፓርቲን መወንጀል እና ሃዘኑን ለመግለጽ የወጣውን ሕዝብ ደም ያፋሰሰው ሰማያዊ ፓርቲ ነው በማለት መፈክር አሲይዞ አደባባይ ላይ ማሰማራት የስርአቱን ዋልጌነት እና በዜጎች ደም መቀለድ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል::ከዜጎች መታረድ ጀርባም ሌላ ምስጢር ያዘለ ነገር እንዳለ ጠቋሚ ነገሮች እንዲታሰቡ እድሉን አስፍቷል::ሰማያዊ ፓርቲን እንደ ደም አፋአሳሽ እና አፍሳሽ አድርጎ ፕሮፓጋንዳ ማቀነባበር በአሸባሪው አይሲስ የታረዱ ዜጎችን ሃዘን የሚገልጸው ሕዝብ ላይ እንደማሾፍ ይቆጠራል::ያለው ስርአት ምን ያህል እንደወረደ በተደጋጋሚ ከማመልከቱም ባላይ ያሁኑ ግን ብሶ እና አግጥጦ መውጣቱ ለሕዝብ ያለውን ንቀት በተግባር እያሳየ ነው::
የህዝቡ አንድነት ያስደነገጠው ወያኔ ከፋፈለነዋል ብለው እፎይ ብለው ፕሮፓጋንዳ ሲረጩ ድንገት ተቆጥቶ የተመመው ህዝብ አንድነቱን ከማሳየቱም በላይ ኢትዮጵያዊነት የማይበረዝ የማይከለስ መሆኑን ሲያሳይ የቀድሞው ወታደራዊ መሪን ማረን እስከማለት መድረሱ ሕዝቡ ለአንድነቱ እና ለኢትዮጵያዊነቱ ምን ያህል ቀናኢ እንደሆነ አሳይቷል:: የወያኔ የጎሳ ፖለቲካ እንዳልሰመረ በተግባር የታየበት የህዝብ ድምጽ የተሰማበት ሕዝብ ብሶቱን የተነፈሰበት ትእይንት ግርምትን ከመፍጠሩም በላይ የወያኔ ሴራዎች ምንም እንዳልሰሩ እና የ24 አመታት የስርአቱን ክሽፈት በተግባር አሳይተዋል::ከሕዝብ ያልወጣ አስተዳደር እና መንግስት ለዜጎቹ እንደማይበጅ መንግስት የለም የሚል ድምጽ በማሰማት አሳይቷል::ከፋፈልነው ያሉትን ሕዝብ አንድነቱን አዩት::ይህንን እኩይ ስርአት ለማስወገድ በጋራ ልንቀሳቀስ ይገባል::