እማማ ኢትዮጵያ የሐዘን ማቅ ለብሳ በዋይታና በልቅሶ ተጨንቃ ልጆቿን የድረሱልኝ ጥሪ እያሰማች ትገኛለች!!
አንገታችንን የሚያስደፋና በሐፍረት የሚያሸማቅቅ፣ ጆሮን ጭው የሚደርግ፣ የወላድ እናቶችን አንጀት የሚያላውስና በእንባ ጎርፍ
እንዲታጠቡ የሚያደርግ ሌላ የሞት፣ ሌላ የውርደት፣ ማብቂያ የሌለው የሚመስል መሪር የሆነ የመርዶ፣ ሰቅጣጭና ክፉ ዜና ለእናት
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ምድር፣ ከሊቢያ፣ ከደቡብ አፍሪካ፣ ከሀገረ የመን ተሰምቷል፡፡
ስለሆነም በቦስተን እና አካባቢዋ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ለወገን ደራሽ ወገን ነው፤ ሰለሆነም ይህንን የወገኖቻችንን እና
የእማማ ኢትዮጵያን የድረሱልኝን ጥሪ ምላሽ ለመስጠት፤ ቁጭታችንን ለመግለጽ እና የወገን አጋርነታችንን ለማሳየት በመጪው ቅዳሜ
ሁላችንንም ኢትዮጵያውያኖች በዘር፤ በሃይማኖት፤ በፖለቲካ ያለንን ልዩነት ወደጎን በመተው በጋራ የምንሰባሰብበት መድረክ
ተዘጋጅቷል።
ቀን፤……………………………… ቅዳሜ ኤፕሪል 25 2015
ሰዓት፤…………………………… ከቀኑ 2፡00 PM ሰአት ጀምሮ
የስብስባ አድራሻ፤ ………… 85 Bishop Allen Dr, Cambridge, MA 02139
Central square behined former Harvest supermarket.
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
ለወገን ደራሽ ወገን ነው!!
ይህንን መልዕክት ለቤተስብዎ፤ ለጓደኝዎት በስልክ፤ በኢሜይል እንዲደርስ በማድረግ የድርሻዎን ይወጡ!!
በቦስተን ኢትዮጵያውያን የወገን ጥሪ ምላሽ አስተባባሪ ኮሚቴ- ቦስተን
ለበለጠ መረጃ 617 669 1542