ትናንት በ19/04/07 ዓ.ም የአንድነት ፓርቲ የኮምቦልቻ ጽ/ቤት መከፈቱን ተከትሎ የማስተዋወቅ ስራ ሲሰሩ ከነበሩት የአንድነት አመራሮች መካከል አቶ ተማም መሀመድ በከተማ አስተዳደሩ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች ተጠርተው ተጠይቀዋል፡፡ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎቹ ‹‹እናንተ ያለጊዜው የምርጫ ቅስቀሳ እያደረጋችሁ ነው፤ የፀጥታ ችግር ለመፍጠር እያሰባችሁ ነው፤ሳታሳውቁ ነው የምትሰሩት›› የሚሉ ጥያቄዎች ያቀረቡባቸው ሲሆን፤ አቶ ተማም እኛ ቢሯችንን ስንከፍት ተገቢውን የማሳወቂያ ደብዳቤ ለሚመለከታቸው የአስተዳደርና የፖሊስ ሀላፊዎች ያስገባን ሲሆን ከቢሮው መከፈት ጋር ተያይዞም የማስተዋወቅ ስራ እየሰራን እንገኛለን፤ነገርግን እናንተ እንዳላችሁት የምርጫ ቅስቀሳ አላከናወንም እኛ የአንድነት ፓርቲ አባላት መብትና ግዴታችን እስከምን እንደሆነ ስለምናውቅ ስህተቶችን አንሰራም ህጋዊና ለህግ ተገዥም ነን፤ ይልቁን በማንአለብኝነት የምርጫ ቅስቀሳ እያደረገ ያለው የኢህአዲግ ፓርቲ ነው በማለት መልስ የሰጡ ሲሆን፤ በቢሮው ለጥቂት ሰአታት ካቆዩአቸው በኋላ ‹‹በደረሰን መረጃ መሰረት መስሎን ነው፤መሄድ ትችላለህ›› ተብሎ ተመልሷል፡፡
↧
የትናንትናውን የቢሮ ማስተዋወቅ ቅስቀሳ ተከትሎ የኮምቦልቻ አንድነት የድርጅት ጉዳዮች ሀላፊ በደህንነትና ጸጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች ተይዘው ተጠየቁ፡፡
↧