የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ጥር 3 በባህርዳር ለሚያደርገው ህዝባዊ ሰልፍ የቅድመ ዝግጅት ስራ የሚያከናውኑ ከፍተኛ የፓርቲው ልዑካን ወደ ስፍራው አምርቷል፤ ቀደም ሲል የሰሜን ቀጠና ሀላፊ አቶ አእምሮ አወቀ የሄዱ ሲሆን አሁን ደግሞ አቶ አስራት ጣሴና አቶ ብሩ በርመጅ ወደ ስፍራው አቅንተዋል።
የከተማው አስተዳደር ሰልፉን ላለመፍቀድ አሁንም እያንገላገረ ቢሆንም፤ ህጉ በሚፈቅደው መሰረት የሰልፉን ቦታና ጊዜ አንድነት አሳውቀዋል፤ ስለዚህ በተያዘበት ዕለት ሰልፉ የሚካሄድ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን።