ጥቅምት 22 ቀን 2007ዓ.ም ለተሰዉ ሰማዕታትና የህሊና እስረኞች በማሰብ የሻማ ማብራት ሥነ ስርዓት አደረገ
በዛሬዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ የተሰበሰበው የአዲስ አበባ አንድነት ክር ቤት ስብሰባውን የከፈተው ጥቅምት 22 ቀን 1998 ዓ.ም ለተሰዉት ሰማዕታትና የህሊና እስረኞችን በማሰብ የሻማ ማብራት ሥነ ስርዓት በማድረግ ነበር፣ የሻማ ማብራቱ ሥነ ስርዓት እንደተጠናቀቀ በፓርቲው ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተሄደ፡፡ በውይይቱ ላይ የተገኙት የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ የፓርቲው ም/ፕሬዚዳንትን ጨምሮ 4 የፓርቲው ስራ አስፈፃሚዎች በወቅታዊ የፓርቲው ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም ምክር ቤቱ በሚቀጥለው ሳምንት ቅዳሜ የአ/አ ስራ አስፈፃሚ ዕቅድን ለማጽደቅ ቀጠሮ በመያዝ መጠናቀቁን ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል የደረሰው ዜና አመልክቷል፡፡
↧
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የአ/አ ም/ቤት ተሰበሰበ
↧