Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all articles
Browse latest Browse all 1809

የኢትዮጵያን አዲስ ዓመት በዓል ታዋቂው ድምጻዊ በሃይሉ አጎናፍር ከዝነኛዋ ቤተልሄም መላኩ ጋር በመሆን ሊያስደስቱዋችሁ ተዘጋጅተዋል!! በቦስተን የኢትዮጵያ አዲስ አመት በዓል ዝግጅት ኮሚቴ

$
0
0

በቅድሚያ የማክበር ሰላምታችንን እያቀረብን፤

እንኳን ለመጪው የ2007 አዲስ ዓመት በዓል በሰላም አደረስዎ!!“

እያልን ይህንንው የኢትዮጵያን አዲስ ዓመት በዓል አስመልከቶ በቦስተን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያኖች በጋራ፤ በዓሉን በጨዋና በኢትዮጵያዊነት መንፈስ በደመቀ ሁኔታ በየአመቱ እንደሚያከበሩ ይታወቃል። በዚሁ መሰረት የዘንድሮውን የ2007 ዓ. ም. የአዲስ ዓመት በዓልን በደመቀ ሁኔታ ሁሉም ኢትዮጵያውያኖች፤ በዘር፤ በሃይማኖት፤ በፖለቲካ፤ በጾታ ሳይከፋፈሉ በሕብረት ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን እያስታዋሱ በጋራ እንዲያክበሩ ለማድረግ የዝግጅት ኮሚቴው ስራውን በማጠናቀቅ ላይ መሆኑን ሲገልጽ በደስታ ነው። ይኸው በዓል
ሴፕቴምበር 6 ቀን 2014 ዓ. ም ከምሽቱ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ (September 6, 2014 – starting from 6:00PM)
በ St James Armenian Apostolic Church, 465 Mt Auburn St, Watertown, MA 02472
በድምቀት ይከበራል።

 በእለቱ ታዋቂው ድምጻዊ በሃይሉ አጎናፍር ከዝነኛዋ ቤተልሄም መላኩ ጋር በመሆን ሊያስደስቱዋችሁ ተዘግጅተዋል፤ በተጨማሪም በእለቱ ሕጻናት አበባየሆሽ በማለት የበዓሉን ታላቅነት ሲያበስሩ ፤ ወጣቶችም የተለየ ዝግጅት ይዘው ይቀርባሉ።

 በእለቱ በሰዓቱ በቦታው ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን በዝግጅት ኮሚቴው የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ባንዲራ ፒን ለመጀመሪያ 300 አዋቂዎች በነጻ ይታደላል።

 በእለቱ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሐበሻ ልብስ አድርጎ እንዲመጣም እንጠይቃለን!

 እራት በነጻ ይስተናግዳል፤ መጠጥ በተመጣጣን ዋጋ ይቀርባል፤ ሕጻናት በነጻ!!

የመግቢያ ዋጋ $30.00 ብቻ ነው

መልካም አዲስ ዓመት!!

በቦስተን የኢትዮጵያ አዲስ አመት በዓል ዝግጅት ኮሚቴ
ቦስተንEnqutatsh2 (2)Enqutatsh2

በቦስተን የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት በዓል ዝግጅት ኮሚቴ – ከፖለቲካ፤ ከሐይማኖት፤ እና ዘር፤ ነጻ የሆነ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በጋራ አዲስ ዓመትን በደስታ እና በደስታ እንዲቀበለው፤
የወደፊት ተተኪ ሕጻናትም ባህላቸውን እንዲያውቁ፤ ኮሚቴውም በሕዝብ በአዲስ ዓመት በዓል ላይ በሕዝብ የተመረጠ ነው።
አዲሱ ዓመት የሰላም፤ የፍቅር እና የብልጽግና፤ ይሁንላችሁ!! መልካም አዲስ አመት!!Enqutatsh2 (2)


Viewing all articles
Browse latest Browse all 1809

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>