Quantcast
Channel: Abugida Ethiopian American Amharic Web Page
Viewing all 1809 articles
Browse latest View live

የአዳማው አንድነት ፓርቲ ቢሮ በፋይናንስ እጥረት ምክንያት ለሁለት ወራት መዘጋቱ ታወቀ፤ ቶኩማ አንድነትን ሊከስ ነው! –ተስፋዬ ዋቅቶላ

$
0
0

ለሰሚም ግራ ሆነ አማርኛ ይመስላል-አይደል…ነገሩ ግን ወዲህ ነው፡፡ አንድነት ፓርቲ በ2006 ሚያዚያ 5 በቶኩማ ሆቴል ከአዳማ ዩኒቨርሲቴ ተማሪዎችና ከከተማው ደጋፊዎቹ ጋር ውይይትና በእለቱም አዲሳባ ዩኒቨርሲቲ መምህሩ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋን በመጋበዝ በፖለተካዊ ፍልስፍና ላይ በጥያቄና መልስየዳበረ ፓናል ተካሂዶ ነበር፡፡በፕሮግራሙ ላይ ከዋናው ቢሮ የአንድነት ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እናተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት እንዲሁም አሁን በእስር ላይ የሚገኘው ያፓርቲው ሕ/ግ ሃላፊ ተገኝተዋል፡፡

በተጨማሪም ፓርቲው የአዳማ አስተባባሪዎች በየወሩ የሚያደርጉትን “የስነጥበብ ለለውጥ”-art for change- ዝግጅት ለጋዜጠኛዋና መምህሯ ርዕዮት አለሙ መታሰቢያ በማድረግ ልዩ የስነ ፅሁፍ ዝግጅት አቅርበዋል፡፡ የርእዮት ቤተሰቦችም በቦታው በመገኘት ስለርዕዮት የናዝሬት ልጅ መሆን በመግለፃቸው ዕለቱ ያልታሰበ ደስታን ፈጥሮ ውሏል፡፡ይህ ሁሉ ሲሆን በቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ ሙሉ ወጪ ለመሸፈን የታቀደው ፕሮግራም ወጪው ከአቅም በላይ በመሆኑ ቀሪ ክፍያ ሳፈጸም የቀረ ቢሆንም ወጪውን ለመሸፈን ለዋናው ቢሮ በቃልና በቃለ-ጉባዔ በማሳወቅ ስድስት ወራት ጊዜ አለፈ፡፡ሆቴሉ ካደረገው ትብብር አኳያ የሚያሰመሰግነው ሆኖ ሳለ ፤ክፍያው ሊፈፀምለት ይችል ዘንድ ማረጋገጫ እንኳን በማጣቱ ፤ ፓርቲውንና ከፓርቲው ጋር በመተባበር የስነ ጥበብ ፕሮግራሙን ያከናወነውን ሊያ የተሰኘ ማሰልጠኛ ለመክሰስ እንደሚገደድ አሳውቋል፡፡

ይህን ዘገባ እስክንሰራ ድረስ የአዳማው ቢሮ በፋይናንስ እጥረት ምክንያት ለሁለት ወራት ተዘግቶ ዕቃዎቹም እንደተዘጋባቸው የታወቀ ነው፡፡በተደጋጋሚ ወደዋናው ቢሮ ያደረግነው መመላለስም ሆነ የተላላክናቸው ደብዳቤዎች ምንም ውጤት አላመጡም፡፡ በመሆኑም የአዳማው የፓርቲው ሐላፊዎች ይከሰሱ ዘንድ ፤ መልካም በሰሩና የፓርቲውን እንቅስቃሴ ባቀላጠፉ በሽልማትና ምስጋና ፋንታ ቢሮአቸው ተዘግቶ ሳለ ለተጨማሪ ተጠያቂነት ተገፍተዋል፡፡ሁላችንም ይህንን በጸጋ የምንቀበለው የትግሉ አንድ አካል አድርገን መሆኑን፤ ሁሉም የአንድነት ደጋፊ እንዲያውቅልን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

ተስፋዬ ዋቅቶላ
የአዳማ አንድነት ሕ/ግ ተጠሪ


“ፍፁም ነው እምነቴ”መጽሃፍ ላይ የተሰጠ አስተያየት

ዘራአይ ደረስ በዋሽንግተን ዲሲ በታሪኩ አባዳማ

የሕዝብ ተስፋ የሆነው አንድነት ፓርቲ ትልቅ አደጋ ላይ ነው –አማኑኤል ዘሰላም

$
0
0

ያለፈው የ2006 ዓ.ም የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ፣ ከዘጠና ሰባት አመት ጊዜ ጀምሮ ታይቶ የማይታወቅ፣ ለሕዝቡ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ፣ ከፍተኛ አገር አቀፍና ሕዝባዊ ንቅናቄዎችን ሲያደርግ እንደነበረ ይታወቃል። በባህር ዳር፣ በአዳማ፣ በጊዶሌ፣ በጂንካ, በአርባ ምንጭ ፣ በደሴ፣ በጎንደር፣ በወላይታ ፣ በደብረ ማርቆስ፣ በፍቼ በመሳስሉ ከተሞች የሚሊዮኖች ድምጽ በሚል ንቅናቄ ፣ ብዙዎችን ለትግሉ ለማነሳሳት የቻለ ሲሆን፣ የፓርቲው ተቀባይነት እጅግ በጣም ከፍተኛ እንዲሆንም አድርጎት ነበር።
ጠንካራ ፓርቲ እንዲኖር የማይፈልገው ሕወሃት/ኢሕአዴግ በፓርቲው ጠንካራ አመራር የሆኑትን በማሰር የአንድነት ፓርቲን እንቅስቃሴ ለመግታት መሞከሩ አልቀረም። እንደ ሃብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሺ ያሉ ወጣት የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ ክስ ሳይመሰርትባቸው በማእከላዊ እየተሰቃዩ ይገኛሉ፡

የአገዛዙ እኩይ ተግባር እንደተጠበቀ የአንድንት ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፍፈራው፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አባላትን እና ደጋፊዎች አሰባስበው ትግሉን ከማስቀጠል ይልቅ፣ በአባላት ዘንድ መከፋፈሎች እንዲመጡ፣ ሊሰሩ የሚችሉ አባላትና ደጋፊዎች እንዲሸሹ በማድረግ፣ አንድነት ፓርቲን ትልቅ አደጋ ላይ እየጣሉት እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።

የሚሊዮኖች ንቅናቄ ሐሳብ አመንጪና በአባላትና ደጋፍፊዎች ዘንድ ትልቅ ተቀባይነት ያለውን ፣ አቶ በላይ ፍቃዱን ጨምሮ፣ በርካታ የሥራ አስፈጻሚ አባላት፣ ከኢንጂንር ግዛቸው ጋር ልንሰራ አንችልም በሚል ከሥራ አስፈጻሚ ሃላፊነታቸው የለቀቁ ሲሆን፣ በምክር ቤት አባልነት ብቻ ለፓርቲው የድርሻቸውን ለማበርከት ተወስነዋል።

ያለፈው ሰኔ 8 ቀን 2006 በአዳማ እና በደብረ ማርቆስ ፣ ተጠሪነቱ ለምክርር ቤቱ በሆነውና ሃብታሙ አያለው በሚሰበስበው የሚሊዮኖች ንቅናቄ ግብረ ኃይል አመራርነት ፣ ከተደረገው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ዉጭ ፣ ላለፉት ሶስት ወራት ከአሥራ አምስት ቀናት ምንም አይነት እንቅስቃሴ የአንድነት ፓርቲ ከማድረግ ተቆጥቧል። ፓርቲው እንደነ ዶር በየነ ፓርቲ በቢሮ ዉስጥ መገልጫዎችን በማወጣት ላይ ብቻ የተወሰነ ፓርቲ ሆኗል።

በቅርቡ የፓርቲዉን መፍዘዝ ያዩ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ወጣቶች፣ ከሌሎች ድርጅቶች ወጣቶች ጋር በመመካከር ፣ የታሰሩ ወገኖችን ለማሰብ የሻማ ማብራት እና ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንቅስቃሴዎች ቢጀምሩም፣ ኢንጂነር ግዛቸው ከኢሕአዴግ ጋር መጋጨት አያስፈልግም በሚል፣ መግለጫ በመስጠት ብቻ በመወሰናቸው፣ በርካታ ወጣቶችን ከማሳዘን አልፈው ተስፋ እያስቆረጡ ነው።

በአንድነት ፓርቲ ዉስጥ ያሉ በርካታ አባላት፣ ደጋፊዎች ብቻ ሳይሆኑ በፓርቲው ዉስጥ ትልቅ አስተዋጾ አድርገው አሁን ከጀርባ ሆነው የሚያገለግሉ ወገኖች፣ ምሁራን፣ የተከበሩ ኢትዮጵያዉያን ፣ የኢንጂነር ግዛቸው አመራር ስላሳሰባቸው ፣ ሕዝቡ ተስፋ የጣለበትን ፓርቲ ለማዳን ሲባል፣ ኢንጂነሩ እንዲለቁ መጠየቃቸውንም፣ አንዳንድ ዜናዎች ይጠቁማሉ። ከነዚህ የተከበሩ ኢትዮጵያዉያን መካከል ፣ ከኢንጂነር ግዛቸው ጋር አንድነት የመሰረቱትና ከኢንጂነሩ ጋር የብዙ አመታት የትግል አጋር የሆኑት ዶር ያእቆብ ወልደማሪያም፣ የተከበሩ አቶ ይልማ ይፍሩ፣ ዶር ዳኛቸው ይገኙበታል።

በዉጭ አገር የሚገኙም፣ አንድነት ከተመሰረተ ጊዜ ጀምሮ ፓርቲው ሲደገፉ የነበሩ፣ የአንድነት ድጋፍ ድርጅቶች፣ የፓርቲው አቅጣጫ እንዳሳሰባቸው በመገልጽ ፣ አንድነት ከቢሮ ፖለቲካ ወጥተው ሕዝቡን ወደ ማንቀሳቅቀስ እንዲመለስ በማሳሰብ ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ በኢንጂነሩ አመራር ትግሉ ዉጤት ያመጣል ብለው እንደማያምኑም እየገለጹ ነው።
በቅርቡ የሰሜን አሜሪካ የአንድነት ድጋፍ ማህበር ሰብሳቢ አቶ ግርማይ ግዛው፣ ለኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው በላኩትና ለደጋፊዎች ግልባጭ ባደረጉት ደብዳቤያችው፣ ኢንጂነር ግዛቸው ለትግሉ ሲሉ ሃላፊነታቸው እንዲለቁና ፣ ሊሰሩ ለሚችሉ አዳዲስ አመራሮች እንዲያስረክቡ ተማጽነዋል።

“I plead with you for the sake of your legacy and honor as well as for UDJP, step down now and with dignity, honor and the love of the country, please transfer your leadership for a new bread of leaders. You have many unchartered opportunities such as to be a member of the council of elders and advice and mentor many young leaders for years to come like Dr. Hailu Araya”

ሲሉ ነበር አቶ ግርማይ ትልቅ ተማጽኖ ያቀረቡት።

ኢንጂነር ግዛችው በአስቸኳይ ከሃላፊነታቸው ተነስተው ፣ የፓርቲዉን አባላትና ደጋፊዎች በቶሎ በማሰባሰብ፣ ፓርቲው ሕዝቡን ወደ ማደራጀት ሥራ በቶሎ ካልተመለሰ፣ የአንድነት ፓርቲ ትልቅ አደጋ ላይ ሊወድቅ እንደሚችልም ይገመታል። በመሆኑም አባላትና ደጋፊዎች የጉዳዩን አሳሳቢነት በመግለጽ፣ አቶ ግርማዬ ግዛዉ እንዳደረጉት፣ መልእክታችንን ለኢንጂነር ግዛቸው እናስተላልፍ። “ የወያኔ ተጠቃሚ እንደሆነው፣ በሕዝብ እንደቀለለው ፣ እንደ አየለ ጫሚሶ አይሁኑ። የዶር ኃይሉ አርአያ ፈልግ ተከትለ፣ ስምዎትን በክብር ቦታ ያስፍሩ እንበላቸው” ። አንድነት እንደ ዶር በየነ ፓርቲ፣ ሕዝባዊ ሳይሆን የግለሰቦች ፓርቲ ሆኖ እንዲቀር፣ እንዲሞት የማንፈልግ ከሆነ፣ አሁን ድምፃችንን እናሰማ። አንድነትን እናድን !!!

የኢንጂነር ግዛቸው ኢሜል የሚከተለው ነው ፡ Gizachew Shiferaw (president)

ስማቹህ የለም በዳንኤል ክብረት

ዶ/ር ጳውሎስ ገብረ ስላሴ አረፈ፤ የቀብር ስነ ስርዓቱ የፊታችን ቅዳሜ በቦስተን የሚፈጸም መሆኑ ታውቋል!! –ከአርአያ ተስፋማርያም

$
0
0

ዶ/ር ጳውሎስ ገብረ ስላሴ አረፈ፤ የቀብር ስነ ስርዓቱ የፊታችን ቅዳሜ በቦስተን የሚፈጸም መሆኑ ታውቋል!! የቀብሩን ዝርዝር መረጃ እናዳገኘን እናስታውቃለን።
ደግነትን፣ ለአገርና ወገን ተቆርቋሪነትን፣ በሙያው ለሚሳቃዩ ወገኖች ነፃ የህክምና እርዳታ መስጠትን፣ አክብሮት የተሞላበት ትህትናና የሰዎችን ሃሳብ በዝምታና ትእግስት የማዳመጥን፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮችን በበሳል ሁኔታ የማስረዳትና የመተንተንን፣ ለኢትዮጵያና ለዜጐቿ ዘወትር በማሰብ ከተገፉና በጭቆና ስር ለሚማቅቁ ወገኖች በገንዘብና በሙያው ፍፁም ተቆርቋሪነትን በተግባር ጭምር ማረጋገጥን…. ወዘተ የተለየ ድንቅና ውድ ስብዕና የነበረውን ዶ/ር ጳውሎስ ከእንግዲህ ላናገኘው ተለይቶን ሄደ። የዶ/ር ጳውሎስ ህልፈት ብዙዎችን ጥልቅ ሃዘንና ድንጋጤ ውስጥ ከቷቸዋል። በህይወት ዘመኔ ከተዋወቅኳቸውና ልዩ ስብእና ከተላበሱ እጅግ መልካም ሰዎች የተለየ የክብር ስፍራ የምሰጠው ዶ/ር ጳውሎስ ምን እንደምል ቸገረኝ! ..የ30 አመት የጳውሎስ ወዳጅና የትግል አጋር የሆነው አቶ ኢሳይያስ አሁን ከመሸ ሳገኘው በሃዘን ኩርምት ብሎ ነበር።

ኢሳይያስ በሃዘን ስሜት « ጳውሎስ ለራሱ ሳይኖር ስለሌሎች ኖሮ ያለፈ የጥንካሬና የመልካምነት ተምሳሌት ነው! የአገሩና የወገኑ ነገር እረፍት የሚነሳው የእውነት ሰው ነበር!..» አንገቱን እንዳቀረቀ ዝም አለ። ከዛ በላይ መናገር አልቻለም።.. በዲሲ የተለያዩ ሃበሾች ተመሳሳይ የሃዘን ድባብ ውስጥ ናቸው። በትላንትናው እለት ከዚህ አለም በሞት የተለየው ዶ/ር ጳውሎስ የቀብር ስነስርዓት የፊታችን ቅዳሜ በቦስተን የሚፈፀም ሲሆን በእለቱ ለመገኘት በርካቶች ከዲሲ ለመሄድ ተዘጋጅተዋል።

ዶ/ር ጳውሎስ ከዲሲ ወደ ቦስተን ያቀናው በቁም እስር ለሚገኘው ለልጁ ወጣት ሮቤል ሲል ነበር። ..ግን..ግን ለምንድነው መልካም ሰዎች በዚህ ምድር የማይበረክቱት!?.. ጳውሎስን የመሰለና ገና ረጅም የህይወት እቅድ (ለአገሩና ወገኑ) የነበረው ታላቅ ሰው ማጣት ያንገበግባል!! ..ፈጣሪ ሆይ ለምን!?

የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህብረት አንድነት ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ አባል አቶ አየለ ሥዩም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

$
0
0

የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህብረት አንድነት ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ እና ጽፈት ቤት ኃላፊ እንዲሁም በመድረክ የስ/አስፈጻሚና የፋይናንስ ተግባር ኮሚቴ አባል የነበሩት አቶ አየለ ሥዩም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ከመድረክ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመለከተ፡፡
አቶ አየለ ስዩም ከ 1986 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ፍትህ፣ ነጻነትና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ከደቡብ ህብረት እየታገሉ የነበሩና በ1997 ዓ.ም በተወለዱበት አካባቢ ሃዲያ ለፓርላማ ተወዳድረው በማሸንፍ ለ 5 ዓመታት 2002 ዓ.ም ህብረትን በመወከል የተወካዮች ም/ቤት አባል የፓርላማ አባል ሆነው አገልግለዋል።
ዓርብ መስከረም 23 ቀን 2007 ዓ.ም እስከ 10፡00 ሰዓት በስራ ላይ የነበሩ ሲሆን ወደቤታቸው ከገቡ በኋላ ማታ በድንገት በመታመማቸው ጎተራ አካባቢ የሚገኘው ኢንተርናሽናል የልብ ህሙማን ሆስፒታል ተወስደው ከለሊቱ 6፡00 ሰዓት ህይወታቸው አልፏል፡፡ እሁድ መስከረም 25 ቀን 2007 ዓ.ም ከቀኑ በ6፡00 ሰዓት አስኮ በሚገኘው ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ዘመድ ወዳጆቻቸው እና የትግል አጋሮቻቸው በተገኙበት የቀብራቸው ስነ-ስርዓት ተፈጽሟል፡፡1902727_794905317234886_7844775702703238665_n

“ዲሲና ደደቢት ኤንባሲ ፊት ለፊት”የጎንቻው


“ትግሬ ትጠላለህ” በጌታቸው አበራ

በዋሽንግተን ዲሲ ጥቂት የወያኔ ኢምባሲ ሠራተኞች እና ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በየፊናቸው ሰልፍ ወጡ!! – (ዘ-ሐበሻ)

$
0
0

ጥቂት የሕወሓት የዋሽንግተን ዲሲ ኢምባሲ ሠራተኞች እና አንዳንድ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጉሮሮ ተነጥቆ በሚሰጣቸው የስኮላርሺፕ ገንዘብ የደለቡ የስርዓቱ ደጋፊዎች በሰለሞን ተካልኝ መሪነት በስቴት ዲፓርትመንት ደጃፍ ዛሬ ሰልፍ ወጡ። በተመሳሳይም የአሜሪካ መንግስት በዋሽንግተን ዲሲ የሕወሓት ኢምባሲ ውስጥ በኢትዮጵያውያን ላይ ጥይት የተኮሰውን የስርዓቱን ተላላኪ ከሃገሩ በማባረሩ ለዚህም ምስጋና ለማቅረብ ኢትዮጵያውያን በስቴት ዲፓርትመንት ተመሳሳይ ሰልፍ አድርገዋል።

ሃገር ወዳዱ ኢትዮጵያውያን ልሙጡን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ በመያዝ እንዲሁም የሕወሃት ደጋፊዎች በመሃሉ ላይ ሰማያዊ ኮከብ ያለብትን እና ብዙዎች አይወክለኝም የሚሉትን ባንዲራ ይዘው ሰልፍ የወጡ ሲሆን በስቴት ዲፓርትመንት ደጃፍ በየፊናቸው ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ አርፍደዋል። የሕወሓት ደጋፊዎች “ኢምባሲያችን ተደፈረ፣ ባንዲራችን ተዋረደ” በሚል ሰልፍ የጠሩ ሲሆን ኢትዮጵያውያኑ በበኩላቸው ሃገራችንን ከነክብሯና ባንዲራዋ ያዋረደው ገዢው የሕወሓት መንግስት ነው በማለት የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያውያኑ ላይ ጥይት የተኮሰውን ግለሰብ ወደሃገሩ በማባረሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ቀድሞ ከተቃዋሚዎች ጋር የነበረውና ተገልብጦ የሕወሓት ደጋፊ ሆኖ ቁጭ ያለው ሰለሞን ተካልኝ የሕወሓት ደጋፊዎችን ሰልፍ የመራ ሲሆን፤ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያኑም ሰለሞን የሕወሓትን መንግስት ይቃወምበት የነበረውን “ሁሉም ዜሮ ዜሮ” የሚለውን ዘፈኑን ከፍተው ለምስጋናው ሰልፍ ማድመቂያ አድርገውታል። ሰለሞን ጥቂት የኢምባሲ ሠራተኞችን ሰብስቦ ራሱን በራሱ በማይክራፎን “ሰለሞን እንዲህ የሚሆነው ለሃገሩ ለባንዲራው ነው፤” ያስባለ ሲሆን የሕወሃት ሰልፍ አላማውን ስቶ እንደተባለው የአሜሪካ መንግስትን መቃወሚያ ሳይሆን የሰለሞን ተካልኝ ሞራል መገንቢያና ማወደሻ ሆኖ አልፏል ሲሉ በአካባቢው የነበሩ ኢትዮጵያውያን ለዘ-ሐበሻ ዘጋቢ ተናግረዋል።

በዋሽንግተን ዲሲ መንግስትን የሚደግፍም ሆነ የሚቃወመው በአንድ ቦታ ቆሞ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጉ ለራሳቸው ለወያኔ ደጋፊዎች ሊያሳፍራቸው ይገባል የሚሉት አንድ አስተያየት ሰጪ “እኛ እንዲህ ያለው ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ነው ትግላችን። ሕወሓትን የሚደግፍም የሚቃወምም በእኩል እንዲታይ። ሆኖም በሃገራችን መንግስትን መቃወም የማንችል መሆኑን የወያኔ ደጋፊዎች እያወቁት ሰሜን አሜሪካ ላይ ከእኛ እኩል ሰልፍ መውጣታቸውና የአሜሪካ መንግስት የመናገር መብትን መፍቀዱ የሚደግፉት መንግስት የሚሰራው ስህተት እንደሆነና እንዲማሩበት ትልቁን ሚና ይጫወታል: ሆኖም ግን ደጋፊዎቹ በአሜሪካ ሃገር ያገኙትን ነጻነት እኛ ሃገራችን ላይ እንድናገኝ ስለማይፈልጉ ከኛ እኲል ዲሞክራሲያዊ መንግስት እየደገፍን ነው ብለው መውጣታቸው ሊያሳፍራቸው ይገባል። ልክ እንደአሜሪካ መንግስት ሁሉ የሚደግፉት የሕወሓት መንግስት ተቃራኒ ሃሳብ ያላቸውን ወገኖች እኩል የመናገር መብት ሊሰጥ እንደሚገባ ከዚህ ሰልፍ ሊማሩ ይገባል” ብለውናል።1911893_956357471058429_6951365719872808750_n

ወያኔ ሲያስር አሜን….ሲገድልም አሜን በኤፍሬም ማዴቦ

$
0
0

ብዕር የያዘ ማንም ሰዉ በዘመናችን ደግሞ የኮምፒተር መክተቢያ ፊቱ ላይ የደቀነ ሁሉ ከሱ ዉጭ ያለዉን ማንንም ሰዉ “ሌባ”፤ “ባንዳ” ወይም “ከሃዲ” እያለ እንዳሰኘዉ መጻፍ ይችላል። በተለይ በእንደኛ አይነቱ ሀላፊነትም ተጠያቂነትም በሌለበት ህብረተሰብ ዉስጥ ደግሞ የጓደኛዉ ሀሳብ ያልተስማማዉ ሁሉ እየተነሳ የገዛ ጓደኛዉን ባንዳና ከሃዲ አድርጎ ስለሚስለዉ የላይ የላዩን ብቻ ለሚመለከት ሰዉ አገራችን በባንዳና በአገር ወዳድ መሳ ለመሳ ለሁለት የተከፈለች ትመስላለች። እግዝአብሄር ይመሰገን እዉነቱ ግን ከዚህ እጅግ በጣም የተለየ ነዉ። ርዕሴን የጀመርኩት አሜን ብዬ ነዉና እስኪ አንባቢዉ አንተም አሜን በል። ባንዳነትና ከሃዲነት ኃብታምና በእድገት ወደፊት የገፉ አገሮችን እየዘለለ ደሃና ኋላ ቀር አገሮችን ብቻ የሚጠናወት ተራ በሽታ አይደለም። ብዙዎቻችን አምባገነን መሪዎቻችንን ሸሽተን የተጠለልንባት አገር አሜሪካ እነ ሄንሪ ቤስትንና ጆን ብራዉንን የመሳሰሉ ከሃዲዎችን እንዳበቀለች ሁሉ ኢትዮጵያችንም ትናንት እነ ኃ/ሥላሤ ጉግሳን ዛሬ ደግሞ የኃ/ሥላሤ ጉግሳ የልጅ ልጆች የሆኑትን እነ መለስ ዜናዊን፤ አባይ ፀሐዬንና ሰብሃት ነጋን የመሳሰሉ የለየላቸዉ ከሀዲዎችን አፍርታለች። በነገራችን ላይ ሙስሊሙ በዱአዉ፤ ክርስቲያኑ በፀሎት፤ ጠቢብ በጥበቡ ፤ፀሐፊ በምናቡ የባንዳዉንና የከሃዲዉን ብዛት ለመቀነስ ካልተባበሩ በቀር “ወላድ በድባብ ትሂድ” ብለን ባንመርቃቸዉም የባንዳ አባትና አናት አስካሉ ድረስ ባንዳም መወለዱ አይቀርም።

ደጅአዝማች ኃ/ሥላሤ ጉግሳ ማንም ሳያስገድደዉ ወድዶና ፈቅዶ ለወራሪዉ የጣሊያን ጦር ካደረ በኋላ ከጄኔራል ደቦኖ ጋር ሆኖ እናት አገሩን ኢትዮጵያን ወግቷል። ጣሊያኖች ኃ/ሥላሤ ጉግሳ ከነተከታዮቹ ከጎናቸዉ ተሰልፎ አገሩን ሲወጋ ያደረጉት የመጀመሪያዉ ነገር ይህ ከሃዲ ሰዉ ከጎናቸዉ መሰለፉን የሚያሳዩ ፎቶግራፎች ለዓለም ህዝብ ማሰራጨት ነበር። ታሪክ እራሱን ይደግማል ሲባል አይኑ አላይ እያለዉ በጆሮዉ ብቻ ለሰማ ሰዉ ዛሬ ማረጋገጫዉ እነሆ በግልጽ ቀርቦለታል። ትናንት ማክሰኞ መሰከረም 27 ቀን የወያኔ ቴሌቭዥንና ሬድዮ ኢትዮጵያ ዉስጥ በጋዜጠኞች ላይ የሚፈፀመዉን እስርና ስደት፤ ወያኔ በወገኖቻቸን ላይ የሚፈጽመዉን የዕለት ከዕለት ሰቆቃና እንዲሁም በቅርቡ አምቦና ኦጋዴን ዉስጥ የተካሄዱትን የጅምላ ግድያዎች የሚደግፉ የዚህ ዘመን ኃ/ሥላሤ ጉግሳዎች ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ያካሄዱትን የክህደት ሰለማዊ ሠልፍ በተደጋጋሚ ለህዝብ አቅርበዋል። እነዚህ ትናንት ክቡር ባንዲራችን በአለባሌ ሰዉ አንደበት “ጨርቅ” ተብላ ስትሰደብ ከተሳዳቢዉ ሰዉ ጎን ቆመዉ የሳቁና የተሳለቁ ከሃዲ ሆድ አምላኪዎች ዛሬ “ባንዲራችን ተደፈረ” ብለዉ የአዞ እምባ ያነቡብናል። የትኛዉ ባንዲራ? ለመሆኑ እነዚህ “እናቴን ያገባ ሁሉ አባቴ ነዉ” ባዮች ጀግናዉ ዘርዐይ ደረስ ጣሊያኖችን በራሳቸዉ አደባባዮች አንገታቸዉን በጎራዴ የቀላዉ ለዬትኛዉ ባንዲራ እንደሆነ ያዉቃሉ? እነ አብዲሳ አጋ፤ በላይ ዘለቀ፤ ባልቻ አባ ነብሶና እልፍ አዕላፋት የኢትዮጵያ ልጆች ምትክ የሌላትን ህይወታቸዉን የሰጡት ለዬትኛዉ ባንዲራ አንደሆነ ያዉቃሉ?

እነዚህ ወያኔ አዲስ አበባ ዉስጥ የገዛ ወገኖቻዉን ሲያስርና ሲገድል አሜን ብለዉ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ሠላማዊ ሠልፍ የሚወጡ የለየላቸዉ ከሃዲዎች ባንዲራ አዲስ መንግስት በመጣ ቁጥር እንደ ፖሊሲና እንደ ካቢኔ ሚኒስቴር የማይቀያየር ቋሚ የአገር ማንነትና የትዉልድ ትስስር መታወቂያ መሆኑን ሊገነዙ ይገባል። ባንዲራ ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ሊቀየር ይችላል ብለን ብናስብ እንኳን ምን አይነት ሰዎች ብንሆን ነዉ ባንዲራን የመሰለ ህዝብና አገር ማስተሳሰሪያ ማተብ ኢትዮጵያንና ታሪኳን ከልቡ ለሚጠላዉ መለስ ዜናዊና የትግራይ ሪፓብሊክ ካላቋቋምኩ ብሎ ይታገል ለነበረዉ ለከሃዲዉ ስብሀት ነጋ የምንተዉላቸዉ? ደግሞም እነዚህ ምናምንቴዎች አንደሚሉት ባንዲራችን ላይ ባዕድ አካል ሆኖ የተለጠፈዉና የኢትዮጵያ ህዝብ በተለምዶ “ባላ አምባሻዉ” እያለ የሚጠራዉ የወያኔ ጨርቅ እዉነትም ኢትዮጵያ ዉስጥ የብሄር ብሄረሰቦችን እኩልነት አረጋግጦ ቢሆን ኖሮ ዛሬ አገራችን በየቀኑ ብሄር ብሄረሰቦች ዉጣልኝ አልወጣም እየተባባሉ የሚተላለቁባት አገር አትሆንም ነበር። አባቶቻችን የሞቱት ለአረንጓዴ፤ ብጫና ቀይ ባንዲራ ነዉ፤ እኛም ዛሬ በየተሰደድንበት አገር አገሬን እያሰኘ የሚያስጮኸን ይሄዉ አረንጓዴ፤ ብጫ ቀይ ባንዲራችን ነዉ። አገር ቤት ያለዉ ኢትዮጵያዊም አንዱን “ባላአምባሻዉ” ሌላዉን ደግሞ ባንድራዬ እያለ የሚጠራዉ ይህንኑ አረንጓዴ፤ ብጫና ቀይ ባንዲራዉን ነዉ። በአንዲት አገራችን ኢትዮጵያ ዉስጥ እነሱም እኛም ለየቅላችን የኛ የምንለዉ ባንዲራ ሊኖር በፍጹም አይችልም። ይልቅ ወያኔዎች ሲጠፉ እነሱ ይዘዉብን የመጡት ኮተቶ ሁሉ አብሯቸዉ መጥፋቱ አይቀርምና ዛሬ “ባንዲራችን ተደፈረ” ብላችሁ የምታቅራሩ እዉሮች ነገ ከወያኔ በጸዳችዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ጭራሽ ባንዲራ ላይኖራችሁ ይችላልና መጀመሪያ ከራሳችሁ ጋር ቀጥሎም ከአገራችሁ ከኢትዮጵያ ጋር እንድትታረቁ አጥብቄ እማጸናችኋለሁ።

የወያኔን ቂልነትና ባዶነት በሰብኩ ቁጥር ትዝ የምትለኝ አንዲት ቀልድ ብጤ አለችና እስኪ ለፈገግታ ትሆናለችና አዳምጡኝ። ሁለት አመት የፈጀዉ የኤርትራና የኢትዮጵያ አላስፈላጊ ጦርነት እንዳለቀ በጦርነቱ ወቅት ስንቅና ትጥቅ በማመላለስ ትልቅ ዉለታ የዋለች ኣንዲት አህያ ጦርነቱ አብቅቶ የድል በዐል ሲከበር መስቀል አደባባይ ተጋብዛ መለስ ዜናዊ ፊት ትቀርባለች፤ በቋንቋ ይግባቡ ነበርና መለስ ጎንበስ ብሎ በጆሮዋ አንድ ነገር ሹክ ሲላት አህይት በደስታ እየፈነጠዘች አደባባዩን መዞር ጀመረች። በልማታዊ አህይት ዝላይና ፍንጠዛ ግራ የተጋቡት የወያኔ ጋዜጠኞች ዜና ያገኙ መስሏቸዉ “ታላቁ መሪ” ምን አለሽ ብለዉ አህይትን ጠየቋት። የዕድሜ ልክ የህወሓት አባል ሆነሻል ተብያለሁ ብላ አህይት ዝላይዋንና ፍንጠዛዋን ቀጠለች።

ትናንት እዚህ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ የወያኔን ጭፍጨፋ፤ እስርና በዘር መድሎ የተጨማለቀ ስርዐት አበጀህ ቀጥልበት ብለዉ አደባባይ የወጡ ጥቂት ህሊና ቢሶችና እነሱን አመስግኖ የነጻነት አርበኞችን “ዱሪዬዎች” ብሎ የዘለፈዉ የአድር ባዮች ሁሉ አድርባይ የሆነዉ ግርማ ብሩ ከዚያች ባድመ ላይ ብዙ ስንቅና ትጥቅ ካመላለሰችዉ ጎበዝ አህያ የሚለዩበት መንገድ ቢኖር አህያዋ ማሰብ ስለማትችል አለማሰቧ እነሱ ግን ማሰብ እየቻሉ አለማሰባቸዉ ብቻ ነዉ። በተረፈ እነሱም አህያዋም የወያኔ አባልነታቸዉ ያስደስታቸዋል፤ ምክንያቱም ሁለቱም አያስቡም። መቼም የገዛ ወንድሙና እህቱ ሲታሰሩ፤ ሲደበደቡና ሲገደሉ አሜን ብሎ ተቀብሎ ነብሰ ገዳዮችን ደግፎ ሰላማዊ ሠልፍ የሚሰለፍ የሰዉ ዘር ያለዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ብቻ መሆን አለበት። ለዚያዉም በወያኔ ዘመን ብቻ!

እነዚህን ሆዳሞች ደግሜ ደጋግሜ እዉሮች እያልኩ የምጠራቸዉ አለምክንያት አይደለም። በእርግጥም ስለማያዩ ነዉ። ባለፈዉ ወር አዚህ አሜሪካ ሚዙሪ ግዛት ፈርግሰን የሚባል ከተማ ዉስጥ ከባድ መሳሪያ የታጠቁ ፖሊሶች መሳሪያቸዉን ሰላማዊ ሰልፈኛዉ ላይ ስላዞሩ (ልብ በሉ ስላዞሩ ነዉ ያልኩት እንጂ ስለተኮሱ አላለኩም እነሱም አላደረጉትም) የአሜሪካ ህዝብ፤ መሪዎችና የህዝብ ተወካዮች ምን ያህል እንደተንጫጩ ሁላችንም ተመልክተናል። እነዚያ እዉሮች ያልኳቸዉ ወንድሞቻችንም እኛ የተመለከትነዉን ተመልክተዉት ይሆናል፤ ግን እነሱ የአዕምሮ እዉራን ናቸዉና ስዕሉን ብቻ ነዉ እንጂ ቁም ነገሩን አላዩትም። ስለዚህም ነዉ የነሱ ድፕሎማት ተብዬዉ ድንጋይ ራስ (ርዕስ እምኒ) አዲስ አበባ ዉስጥ ያለ መስሎት ሠላማዊ ሠልፈኛ ለመግደል ደጋግሞ ሲተኩስ አበጀህ ብለዉ ሠላማዊ ሠልፍ የወጡለት። እግዚአብሄር ከዚህ አይነቱ የአዕምሮ እዉርነት ያድነን! እባካችሁ አሁንም አሜን በሉ። እኔ እያረረ የሚስቅ ማሽላ ብቻ ይመስለኝ ነበር . . . . ለካስ የገዛ ወገኖቹ ሲገደሉ ደስ ብሎት የሚስቅ ሰዉም አለ። አቤት እግዚኦ!!!!

ሌላዉ የገረመኝ ነገር ቢኖር እነዚህ የአዕምሮ እዉራን ትናንት ረፋዱ ላይ ለአሜሪካዉ ዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጆን ኬሪ በጻፉት ደብዳቤ ግንቦት 7 ያ እንቅልፋም ፓርላማቸዉ “ሽብርተኛ” ብሎ የፈረጀዉ ድርጀት ነዉና ምነዉ ዝም ብላችሁ ታያላችሁ ብለዉ ኬሪን መወትወታቸዉ ነዉ። ኬሪ እንደነሱ ጨካኝና አምባገነን መሪዎች የማይወደዉንና የሚጠላዉን ሁሉ አይንህ አላማረኝም እያለ ማሰር የሚችል መስሏቸዋል። እነዚህ ሆዳቸዉ ልባቸዉን የሸፈነ ከሃዲዎች አይገባቸዉም አንጂ የነሱን “ግንቦት ሰባቶችን” እሰሩልን ብሎ ጥያቄ እንኳን ኬሪ የአለማችን ሀይለኛዉ መሪ አባማም ማስተናገድ አይችልም። እኛስ ብንሆን የምንታገላቸዉ ለዚሁ ነዉኮ – ኢትዮጵያን የሚመራ ሁሉ ሀሳባችን ከሀሳቡ በተጋጨ ቁጥር አንዳያስረንና እንዳይደገድለን። እኔኮ ምን ይሻለኛል . . . . በአንድ በኩል ኢትዮጵያዉያን የወገኖቻቸዉን መገደል ተቃዉመዉ ሠላማዊ ሠልፍ ሲወጡ የወያኔዉ ተላላኪ ግርማ ብሩ የኤርትራን መንግስት ይከስሳል፤ የአይጥ ምስክር ድንቢጥ እንዲሉ የግርማ ብሩ ተላላኪዎች ደግሞ (የተላላኪ ተላላኪ ማለት ነዉ) ግንቦት ሰባት የሚረዳዉ በኤርትራ መንግስት ነዉና ስጋታችንን እዩልን እያሉ ኬሪን ይለማመጡታል። መቼም አዉቆ የተኛን ቢቀሰቅሱት አይነቃም ነዉና የወያኔ ደጋፊዎች አይገባቸዉም አንጂ ለሻዕቢያ ጎንበስ ቀና እያሉና የሻዕቢያን መሪዎች እንደ ታቦት እየተሳለሙ ለዚህ ዛሬ ላሉበት ደረጃ የበቁት የወያኔ መሪዎች ናቸዉኮ። ዛሬ በባነኑ ቁጥር አንዴ ግንቦት ሰባት አንዴ ሻዕቢያ እያሉ ዛር እንደያዘዉ ሰዉ የሚያጓሩትም ተደምስሰዉ ከታሪክ ምዕራፍ የሚፋቁት በዚሁ እንደ ህጻን ልጅ እጃቸዉን ይዞ ለታሪክ ባበቃቸዉ በሻዕቢያ በኩል መሆኑን በሚገባ ስለሚያዉቁት ብቻ ነዉ። ምድረ የወያኔ አጎብጋቢዎች ዛሬ እቅጩን ልንገራችሁ፤ ወደዳችሁም ጠላችሁ ይህ “ልማታዊ” ብላችሁ የምትጠሩት ነብሰ ገዳይ አገዛዝ ይደመሰሳል- ስጋታችሁ ትክክለኛ ስጋት ነዉ። ግን ከዚህ ስጋት የሚያድናችሁ ኬሪ ሳይሆን የራሳችሁ ሂሊና ብቻ ነዉና ሳይዉል ሳያድር ዛሬዉኑ ኑና ከህዝብ ጎን ተሰለፉ፤ አለዚያ ዕድላችሁ ከኑግ የተገኘህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ ይሆናል። መቼም እንደኔዉ የዚያች ምስኪን አገር ልጆች ናችሁና በተረት ብነግራችሁ ይገባችኋል ብዬ ነዉ እንጂ በእናንተና መወቀጥ በሚገባዉ ኑግ መካከል ምንም ልዩነት የለም።

የዘረኞቹ የወያኔ መሪዎችና እንደ ችግኝ ኮትኩተዉ ያሳደጓቸዉ ቡችሎቻቸዉ አስቂኝ ታሪክ በዚህ ብቻ አያበቃም፤ እነዚህ ጣምራ ጉደኞች ብዙ ተነግሮ የማያልቅ ጉድ አላቸዉ። ወያኔዎች ጋዜጠኛ እያሰሩና ከአገር እንዲሰደድ እያደረጉ ተዉ ያላቸዉን ፀረ አገርና ፀረ ልማት ይሉታል፤ በየሰላማዊ ሠልፉ ላይ ንጹህ ዜጎችን በጅምላ ሲጨፈጭፉ ምነዉ ያላቸዉን ደግሞ ሽብርተኛ ብለዉ ያስሩታል። እነዚህ አረመኔዎች ይህንን የመሰለ ለጆሮ የሚቀፍ ወንጀል በህዝብና በአገር ላይ ፈጽመዉ ሰዎች በነጻነት ወደሚኖሩበት አገር ሰዉ መስለዉ ሲመጡና ስንቃወማቸዉ ደግሞ እዚህ ዉጭ አገር ያስቀመጧቸዉ ተናካሽ ዉሾቻቸዉ “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የጎደላቸዉ ብለዉ ይዘልፉናል። ለመሆኑ ለእነዚህ እንደ ዉሻ ቁራሽ ስጋ በተወረወረላቸዉ ቁጥር ለሚያላዝኑ ምናምንቴዎች ማነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንደነሱ ነዉርን አሜን ብሎ መቀበል ብሎ የነገራቸዉ? ዜጎችን አንደ እንስሳ አየጎተቱ ገድለዉ አስከሬኑን በሟቹ ወንድም እያስጎቱና ይህንን ነዉር በቪድዮ እየቀረጹ መሳቅና መሳለቅ ነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ወይስ ይህንን ኔሮና ሂትለር ምን አደረጉ የሚያሰኝ ጭካኔና አረመኔነት መቃወም ነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት? አዲስ አበባ ዉስጥና እዚህ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ተቃዋሚ ኃይሎችን “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የጎደላቸዉ ብለዉ የዘለፉት ሬድዋን ሁሴንና ግርማ ብሩ የዉኃ ጠብታን ያክል ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በደማቸዉ ዉስጥ ቢኖር ኖሮ “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የኢትዮጵያዉያንን ህይወት በየአደባባዩ መቀማት አይደለምና እናከብራቸዉ ነበር እንጂ በወጡና በገቡ ቁጥር ስማቸዉን እየጠራን ሌባና ከሃዲ እያልን አናሸማቅቃቸዉም ነበር። ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ስንታሰርና ስንዋረድ እልል፤ ስንገደል ደግሞ አሜን ብለን እንደ በሬ አንገታችንን ለቢለዋ መስጠት ማለት አይደለም። ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ለወገን ማዘን ነዉ፤ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ወገን ሲጎዳና ሲጠቃ ከለላ መሆን ነዉ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ዜጎች ሰቆቃ ሲፈጸምባቸዉና ሲገደሉ ቆሞ ከመመልከት ይልቅ ወይም የገዳዮች ጠበቃ ከመሆን ባጭር ታጥቆ ነብሰ ገዳዮችንና የጭካኔ ምልክቶችን ከአገር አናትና ከህዝብ ጀርባ ላይ ማስወገድ ነዉ – ወላድ በድባብ ትሂድ – ይህንን የሚያደርጉ የቁርጥ ቀን ልጆች እናት ኢትዮጵያ ትናንንት ነበሯት፤ ዛሬ አሏት ነገም ይኖሯታል።
ebini23@yahoo.com

‘አሸባሪ ብዕሮች’ክንፉ አሰፋ

$
0
0

ይህች አጭር ጽሁፍ የተወሰደችው በአውስትራሊያ ከምትታተም “አሻራ” ከተሰኘች መጽሄት ልዩ እትም ላይ ነው።

የፈረንሳዩ አንባገነን ገዥ የነበረው ናፖሊዮን ቦናፓርት በአንድ ወቅት ስለ ነጻ ፕሬስ ሲናገር “ከአንድ ሺህ ሻምላዎች ይልቅ አራት ጋዜጦች የበለጠ መፈራት አለባቸው።” ነበር ያለው።

አንባገነኖች ፕሬስን ይፈራሉ። ይጠላሉም። የህዝብ መሰረት የሌላቸው፤ በራሳቸው የማይተማመኑ ሁሉ ነጻ ሃሳብን ይጠላሉ። ነፍጥን ብቻ ተማምነው በሕዝብ ጫንቃ ላይ የሚቀመጡ፤ እንደምን ነጻ አመለካከትን ሊቀበሉ ይችላሉ? ፍጹም አንባገነናዊነት በሰፈነባቸው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገሮች፤ ህግ አውጭው ህግ አስፈጻሚውን፣ ህግ አስፈጻሚው ደግሞ ህግ ተርጓሚውን እርስ-በርስ የሚቆጣጠሩበት እና የሚያስተከክሉበት አካሄድ የለም። ይህንን ቁጥጥር በጥቂቱም ቢሆን ተክቶ ይሰራ የነበረው ነጻው ፕሬስ ነው። ከዚህም አልፎ ሕዝቡ መብቱን እንዲያውቅና መብቱንም እንዲያስከብር ብዙ ሰርቷል-ፕሬሱ። ሙስናን አጋልጧል፣ እንደ እንባ ጠባቂም እየሆነ የህዝብን በደልም ይፋ አድርጓል። ይህን የተቀደሰ ተግባር ማከናወን እንደወንጀል፤ ጠንከር ሲል ደግሞ እንደ ሽብርተኝነት የሚቆጠርበት ሃገር ሆናለች የዛሬይቱ ኢትዮጵያ።

መብትን ማወቅ እና ማሳወቅ፤ ‘ህዝብ ለጦርነት እንዲነሳ ማድረግ፤ ወይንም በስራዓቱ ላይ ጥርጣሬ መፍጠር ነው’ ተብሎ ከተተረጎመ ደግሞ ጋዜጠኛን በአሸባሪነት መፈረጁ ብዙ ሊደንቀን አይገባም።
ኢትዮጵያ ላለፉት አስርት-አመታት ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ በቁጥር አንደኛ ደረጃ ላይ የነበረች ሃገር ናት። አሁን ይህንን ደረጃዋን ለቃለች። እድገትና ትራንስፎርሜሽኑን ተከትሎ ከመጡት ለውጦች አንደኛው መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ የአንደኝነት ደረጃዋን ያጣችው ታዲያ ትራንስፎርሜሽኑ ይዞት በመጣው መሻሻል አይደለም። ነጻ ፕሬሱ ከሃገሪቱ እንዲጠፋ በተደረገ ሁለገብ ጦርነት እንጂ። አብዛኛው ጋዜጠኛ ተሰድዷል፣ ጥቂቶቹ ታስረዋል፣ አንዳንዶቹም አቅማቸው ተሟጦ አልቆ፤ ዝም ብለው እንዲቀመጡ ተደርገዋል። ለነጋሪ የተረፉትንም እስከዛሬዋ እለት ድረስ እያሳደዷቸው ይገኛሉ።

ከጅምሩ በፕሬሱ ላይ የተከፈተው የገዥው ፓርቲ ውግያ ቀላል አልነበረም። ፕሬሱ ግን እለት ተዕለት የሚያርፍበትን የአንባገነኖች ጡጫ ሁሉ ችሎ ብዙ ተጉዟል። እየተንገዳገደ፤ እየወደቀና እየተነሳ የህዝቡን የህሊና ንቃት እንዲሰፋ ከማድረጉም ባሻገር በኢትዮጵያ የማንበብ ባህል እንዲዳብር ነጻው ፕሬስ ተግቶ ሰርቷል። የህትመት ዋጋ እስከ 500% እንዲጨምር ቢደረግም ፕሬሱ አልቆመም ነበር። ጋዜጠኞች እንደጥጃ እየታሰሩ፣ እየተደበደቡ፣ እየተሰቃዩም ስራቸውን ላለማቋረጥ መትጋታቸውን አላቆሙም። በካድሬ ዳኞች ፍርደ-ገምድል ፍትህ ሲሰጣቸው፤ ያለ አግባብ በእስርና በገንዘብ ሲቀጡም ሰራቸውን አላቋረጡም…
የአሜሪካው ፍሪደም ሃውስ በተከታታይ ባወጣቸው ዘገባዎች ኢትዮጵያን ፕሬስ (Status: NOT FREE) “ነጻ ያልሆነች” ሃገር ሲል ፈርጇል። የፕሬስ አዋጁንም ፍጹም አፋኝ ሲል ይከሳል። የፈረንሳዩ ሪፖርተርስ ዊዝ አውት ቦርደርስ፣ የኒውዮርኩ ሲ.ፒ.ጄ. እና የብራስልሱ አይ.ኤፍ.ጄ. በሽብር ክስ የተያዙ የጋዜጠኖችን ሰነድ እያከታተሉ አሳፋሪነቱን ቢገልጹም አፍ እንጂ ጆሮ ከሌለው ስርዓት ያገኙት የስድብ ምላሽ ብቻ ነው። አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና ሂዩማን ራይትስ ዋችም አፈናውን ይፋ ማድረጉን ተያይዘውታል። ከገዥው ፓርቲ የሚያገኙት ምላሽ “የኒዮ ሊበራል” አቀንቃኞች የሚል ስድብ እና ዛቻ ብቻ ነው።
ከምርጫ 97 ነኋላ ግን የህወሃት እድገት እና ትራንስፎርሜሽን፤ ጫን ያለ ነገር ይዞ ብቅ አለ።

ሽብርተኝነት!
ከዚህ በኋላ ጋዜጠኛ በህገ-መንግስት ሳይሆን፤ ህጉን በሚጻረረው አዋጅ መዳኘት እንዳለበት ተነገረ። ስርዓቱም በባሩድ ሳይሆን ይልቁንም በብእር ጫፍ እንደሚሸበር አረጋገጠ።
ይህ የሽብርተኝነት አዋጅ ቃል በቃል የተቀዳው ከአሜሪካ እና ከእንግሊዝ መንግስታት ሰነድ መሆኑን ሃይለማርያም ደሳለኝ ለቢቢሲ ሲናገሩ ተደምጠዋል። ድንቅ ነው። ሰውየው ግን ምን እየተናገሩ እንደሆን የሚያውቁት አይመስልም። በዚህች በሙት መንፈስ የምትመራ ሃገር ሌላም ብዙ እንግዳ ነገር እንሰማለን። የቡሽ አስተዳደር ከቶኒ ብሌየር ጋር አልቃይዳ የተባለውን አደገኛ ሽብርተኛ ለማጥፋት የነደፉት ይህ ሰነድ ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ጋዜጠኞችን ለማጥፋት እየተጠቀሙበት እንደሆነ ነው የሚነግሩን። የፈረንጆቹ ሽብርተኝነት (terrorism) ሲተረጎም፤ “በሃይማኖት ወይንም በርዕዮተአለም ጥላ ስር ተደራጅቶ አመጽን የማድረግ ተግባር” እንደሆነ ይነግረገናል።
በሽብርተኝነት ተወንጅለው በየእስር ቤቱ የተጣሉት የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች፤ የትኛውን ርዕዮተ-አለም ወይንም ሃይማኖት ተንተርሰው አመጽ እንደፈጠሩ፣ የትኛውን አውሮፕላን እንዳስጠለፉ፣ የትኛውን ህንጻ እንዳፈረሱ፣ የትኛውን ንጹህ ዜጋ እንደገደሉ አልተነገረንም።

እርግጥ ነው። የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች እየተቹ ይጽፋሉ። ትችቱ ታድያ ለውጡ ላይ አይደለም። የለውጡ አቅጣጫ ላይ እንጂ። አቅጣጫው ትክክለኛ መስመር መያዝ እና አለመያዙን መተቸት “ወንጀል ነው” ሲባል ለቀረው አለም አዲስ ነገር ሊሆን ይችላል። ከዚያ የባሰም አለ። ገዢውን ፓርቲ መተቸት እና ስለ ለውጥ አስፈላጊነት መጻፍ በሽብርተኛነት ያስከሰሰ ወንጀል ሆኖ ሰማን። አስቂኙ ነገር፤ አዋጁ ለኦሳማ ቢን ላደን ሽብር በምእራባውያን ሀገሮች የረቀቀ የጸረ-ሽብር ህግ መሆኑ ነው።

ጋዜጠኞች በሽብርተኝነት ሲፈረጁ ነው ነጻው ፕሬስ በኢትዮጵያ አፈር የለበሰው። ይህ የመጨረሻ ጥይታቸው መሆኑ ነው። አለማቀፍ የጋዜጠኞች ተሟጋች ተቋማት ሳይቀሩ ተስፋ የቆረጡ እስኪመስል ድረድ በዘንድሮ አመታዊ ዘገባቸው የኢትዮጵያን ጉዳይ ችላ ብለውታል። እነዚህ ተቋማት በየአመቱ ስለኢትዮጵያ ፕሬስ ሁኔታ የሚያወጧቸው ዘገባዎች የሚዘገንኑ ነበሩ። ወያኔን የማይማር፣ የደነዘዘ እና የማይለወጥ ስርዓት አድረገው ስላዩት ችላ ያሉት ይመስላል። ሃያ አመት የማይሰማ፣ ያሃ አመት የማይሻሻል፣ ሃያ አመት የማይማር ስርዓት… ውሃ ቢወቅጡት እንቦጭ ሆነባቸው።

በምርጫ 97 ሰሞን በርካታ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች ቃሊቲ ተወርውረው ነበር። በጉዳዩ ላይ የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ዲያሬክተር ከነበሩት ዶ/ር ማርቲን ሂል ጋር ስናወራ አንድ ጥያቄ አነሱልኝ።
“ለመሆኑ ሰርካለም ፋሲል ላይ ለምን እንዲህ ጨከኑባት? ” የሚል ነበር የማርቲን ጥያቄ። እኝህ ታላቅ ሰው ይህን ጥያቄ ለምን እንዳነሱልኝ አሁን ነው የተገለጠልኝ።
የሰርካለም ፋሲልን ጉዳይ ማንሳቱ የኢትዮጵያን ፕሬስ የሰቆቃ ጉዞ በከፊልም ቢሆን ይገልጸዋል።

ሰርካለምን ከባለቤትዋ እስክንድር ነጋ ጋር አፍነው ወደ ቃሊቲ ሲወስዷት ነብሰ-ጡር ነበረች። የመውለጃዋ ቀን ሲደርስም ከእስር አልለቀቅዋትም። በምጥ ስቃይ፣ ነብስ ውጭ፤ነብስ ግቢ ሁኔታ ውስጥ ሆና እንኳን አሳሪዎችዋ ርህራሄ አላሳዩዋትም ነበር። በመጨረሻ እዚያው ቃሊቲ እስር ቤጥ ናፍቆትን ተገላገለች። በዚያ የጭንቅ ወቅት የሚይዘውን እና የሚጨብጠውን ያጣ ስርዓት ምን እያደረገ እንደነበር እንኳን በውል አየውቀውም። “የመንግስት ጠላት” የሚል ታፔላ ተለጥፎለት የሚንቀሳቀስ ጋዜጠኛ፤ ሊወድቅ ከሚንገዳገድ ስርዓት ከዚህም በላይ ሊደረግበት እንደሚችል ለማስረዳት ሞከርኩ።

ነብሰ-ጡርዋ ሰርካለም የተከሰሰችው ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በሃይል ለመናድ እና ለማፍረስ፣ ጥላቻን የምታስፋፋ፣ ጥርጣሬን የምትነዛ… ተብላ ነበር። በ “ምህረት” ከእስር እንደተፈታች ወደ ኬንያ ተሰደደች። በኋላም ሀገር ሰላም የሆነ ሲመስላት ከስደት ተመለሰች። ይህች ወጣት እትብትዋ ወደተቀበረባት ሃገርዋ ብትመለስም እንደዜጋ የመኖር ዋስትናዋ ግን በአንባገነኖች መዳፍ ስር ሆነ። በኑሮዋ እና በትዳርዋ ዙርያ ካለፈው የባሰ ችግር መጣባት። ባለቤትዋ እስክንድር ነጋ በሽብርተኝነት ተከሶ በፍርደ-ገምድል ዳኛ ለአመታት ተፈረደበት። ቤት ንብረታቸውም በግፍ ተቀማ። ከዚህ በኋላ በመኖር እና ባለመኖር የሚደረግ ምርጫ ውስጥ መግባት ግድ ሆነባት። እናም ባለቤትዋን ወህኒ ቤት ጥላ ዳግም ተሰደደች። እስዋም ሆነች በሰቆቃ የተወለደ ልጅዋ በመንገድ ከመወርወራቸው በፊት ያላቸው አማራጭ ይህ ብቻ ነበር። የሚወዷት ሃገራቸውን ጥለው ከሁለት መቶ በላይ የሚሆኑ ስደተኛ ጋዜጠኞችን ተቀላቀሉ። እንደቀልድ የሚነገር ሌላም እውነታ አለ። ከ”ሽብርተኛ” ጋር በስልክም ሆነ በአካል ያወራ፣ አብሮ የታየ፣ አብሮ ሻይ የጠጣ፣ የተነካካ ሰው ሁሉ ሽብርተኛ እንደሆነ አዋጁ ይደነግጋል። ሰርካለም እና ናፍቆት በእስር ያለው እስክንድር ጋር በሚያደርጉት ግንኙነት ሽብርተኛ ተብለው ሊወነጀሉም ይችሉ ነበር።

በስልጣን ላይ ያሉት ሰዎች ፍርሃት ውስጥ እንዳሉ ግልጽ ነው። በጋዜጠኛ የሚናድ ሀገ-መንግስት ይዘው ስንት አመት ሊዘልቁ እንደሚችሉ ባናውቅም፤ አሁንም ጋዜጠኞችን ሲያስሩ ይህንንኑ ዘፈን ይደጋግሙታል። 99.7 በመቶ በህዝብ የተመረጠ መንግስት መራጩን ሕዝብ ከቶውንም መፍራት አልነበረበትም። ነገሩ ስላቅ ነው። ይህ ቀልዳቸው ግን የህዝቡን ንቃተ-ህሊና ዝቅ አድርጎ ከመመልከት የሚመጣ ይሁን እንጂ ጉዳዪ ሌላ ነው። አንባገነኑ ናፖሊዮን ቦናፓርት ብሎታል። ከሺ ሳንጃ አንድ ጋዜጠኛ ያስፈራል። የጭቆና እና የአፈና ስርዓት ገንብቶ ለረጅም አመት የቆየ አንባገነን በታሪክ አልታየም።
የፈቀደውን መምረጥ የሚችልን ህዝብ አዲስ ዘመንን ብቻ እንዲያነብ መምከራቸው ብቻ አይደለም በሕዝብ ላይ ያላቸው ንቀት፤ የፍትህ ስርዓቱን ለበቀል የሚዘረጋ እጃቸው አድርገው ነጻውን ፕሬስ ለማጥፋት ሲጠቀሙበትም እጅግ ያንገበግባል። የህግ የበላይነትን እንዲህ እያደረጉ ናዱት።

ኢሕአዴግ የፕሬስ ነጻነትን ለህዝቡ እንዳጎናጸፈ ይመጻደቃል። ይህ ስህተት ነው። መናገር፣ ሃሳብን በነጻነት መግለጽ፣ መጻፍ፣ … ወዘተ መብት የሰው ልጅ የተፈጥሮ ጸጋ እንጂ አንድ ስርዓት የሚያጎናጽፈን ጉዳይ አይደለም። በሌላ በኩል ደግሞ ይሀው ስርዓት እነዚሁኑ መብቶች እየጨፈለቀ እነሆ ሃያ ሶስት አመታትን ዘልቋል።
ነጻ ፕሬሱን ለምእራባውያን የዲሞክራሲ ማሳያ አድርጎ እንደተጠቀመበት እርግጥ ነው። የአለም ባንክ እና ለጋሽ ሃገሮች በኢትዮጵያ የሳንሱር አዋጅ እንደጠፋ ነው የሚነገራቸው። የእርዳታና ብድር እጃቸውን የሚዘረጉልንም ከቀድሞው የተሻለ የመጻፍና የመናገር ነጻነት አለ ብለው ስለሚያምኑ ይመስላል። ግና ይህ የሳንሱር አዋጅ በአእምሮ ሳንሱር መተካቱን የምናውቀው እኛ ብቻ ነን። ሳንሱር ቢኖር ይህ ሁሉ ጋዜጠኛ ባልታሰረ፣ ባልተንከራተተ እና ባልተሰደደ ነበር።

ምርጫ መጣ! ጋዜጠኛ ይውጣ! እንዲሉ… በቅርቡ በስድስት ነጻ ፕሬስ ህትመቶች ላይ ከተመሰረተው ክስ ጋር በተያያዘ አስራ ሁለት ጋዜጠኞች ለስደት መብቃታቸው ተዘግቧል። በጭላንጭል የነጻነት ድባብ ይንቀሳቀሱ የነበሩት፤ አዲስ ጉዳይ፣ ሎሚ፣ ጃኖ፣ አፍሮ ታይምስ እና እንቁ ጋዜጦች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ጋዜጠኞቹም በአሸባሪነት ሽፋን ተከስሰው እስከ አስራ ስድስት አመት የሚደርስ ጽኑ እስራት ተበይኖባቸው የነእስክንድር ነጋ፣ ውብሸት ታዬ እና ርእዮት አለሙ እጣ ይደርሳቸዋል። እነዚህ ጋዜጠኞች የነበራቸው አማራጭ የሽብር አዋጁ ሰለባ መሆን አልያም አገር ለቀው መሰደድ ነው። ተሰደዱ። የስደተኛ ጋዜጠኛውን ቁጥር ወደ 210 አሳደጉት።
ውንጀላው ግን በተያዘለት መርሃ-ግብር ቀጥሏል። ሰሞኑን “ያልተገሩ ብዕሮች” በሚል ርእስ በኢቲቪ የቀረበውን “ዘጋቢ ፊልም” ያስተውሏል? በአንድ በኩል የጋዜጠኖቹ ጉዳይ በህግ የተያዘ እንደሆነ ይነግሩናል። በሌላ በኩል ደግሞ “ልማታዊ” ተዋንያን እና የስርዓቱ አጎብዳጆችን በመገናኛ ብዙሃን አቅርበው ፍርድ እንዲሰጡ ያደርጓቸዋል። በእርግጥ በመገናኛ ብዙሃን እየቀረቡ አንድ ተጠርጣሪን በወንጀለኝነት መፈረጅ አዲስ ነገር አይደለም። የፍትህ አካሉ ውሳኔ ከመስጠቱ በፊት ተጠርጣሪው በኢቲቪ የፖለቲካ ፍርድ ይበየንበታል። ከዚያም እንደ “ዳኛ” ልዑል አይነት የሲቪል ሰርቪስ ምርቶች ውሳኔውን ያጸኑታል።

በዚያ የኢቲቪ ቅንብር ሃይሌ ገብረስላሴም ተዋንያን ነበር። የሚናገረውም የትዬለሌ። “ትልቁ የጦር መሳርያቸው ፕሬስ ነው።… ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው ይባላል… ” ይለናል ሃይሌ ገብረስላሴ። “ዘጋቢ” ፊልሙም የእነ እስክንድር ነጋን ፎቶ፣ የእነ ተመስገን ጽሁፎች ያሳየናል። የዚህ ድራማ ሌሎቹ ተዋንያን ከሙያው ጋር የተያያዝን ነን የሚሉ አድርባዮች ናቸው። ሃይሌ ግን ምን ቤት እንደሆነ ግልጽ አይደለም። በየትኛውስ እውቀቱ ነው ፍርድ ሊሰጥ የደፈረው? “አንድ ጋዜጣ የውሃ አምራች ድርጅትን እንዲዘጋ አድርጓል።” ሲል ሃይሌ በዚያ “ዘጋቢ ፊልም” ይወነጅላል። አንድ ጋዜጠኛ እውነትን ጽፎ የንግድ ድርጅትን ወይንም የመንግስት ተቋምን ማፍረስ ወይንም በተቋማቱ ላይ ጥርጣሬ መፍጠር ከቻለ እንዲያውም ጀግና ነው የሚባለው። ጋዜጠናው የሚጽፈው ውሸት ከሆነ ደግሞ ፍርዱን ለህዝቡ ለምን አይተውለትም?
አብራሃ ደስታ ሌላው በአሸባሪነት ሽፋን የተከሰሰ ጋዜጠኛ ነው። አብርሃ አሸባሪ መሆኑ የተረጋገጠው ፍርድ ቤት ሲገባ እና ሲወጣ ነው። ሲገባ በጭብጨባ ሲወጣ በጭብጨባ ተሸኝቷል። ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ኣብርሃ ጀግና! የነፃነት ታጋይ! እንወዳሃለን፤እናከብርሃለን ሲለው እነ ሃይሌ ገ/ስላሴ የት ነበሩ?

ያልተገራ አንደበታቸውን በመገናኛ ብዙሃን ሲከፍቱ የነበሩት እነዚህ ተዋንያን የሚነግሩን እጅግ አሳፋሪ ነገር ነው። አጠቃላይ ይዘቱ በመንግስት ላይ ምንም አይነት ትችት መቅረብ የለበትም የሚል እንድምታ አለው። የህወሃትን አንባገነናዊነት መተቸት፣ የስርዓቱ ፖሊሲዎች መንካትና በባለስልጣናቱ ላይ ጥርጣሪ እንዲኖር ማድረግ… ስርዓቱን ያፈርሰዋል ነው እያሉን ያለው። ህግ አውጭው ከህግ አስፈጻሚውን፣ ህግ አስፈጻሚው ደግሞ ህግ ተርጓሚውን እርስ-በርስ የሚቆጣጠሩበት እና የሚያስተከክሉበት አካሄድ በሌለበት ሃገር ነጻው ፕሬስ ከዚህ ውጭ ምን ይስራ ነው የሚሉት? ፕሮፓጋንዳ?

ለፕሮፓጋንዳውማ በርካታ አማራጮሽ አሉ። አዲስ ዘመን ጋዜጣም አለልን። ለ90 ሚሊዮን ህዝብ የቀረው ጋዜጣ። አዲስ ዘመን በቁጥር ስንት ሺ እንደሚታተም ባናናውቅም በኪሎ እየተሸጠ የሸቀጥ እቃ መጠቅለያ ሆነ እንጂ። ‘የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተመረቁ፣ ሃይለማርያም ደሳለኝ ወደ ሱዳን ሄዱ፣ ሃይለማርያም ደሳለኝ ከሱዳን ተመለሱ። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ 11 እጅ እንደሚያድግ ሃይለማርያም ደሳለኝ ተናገሩ።’ …. የሚሉ ዘገባዎችን እየያዘ ከሸቀጥ እቃ መጠቅለያነት ውጭ ለሚመጻደቁለት እድገት ምንም እንዳልፈየደ እንኳ አያውቁትም።

የመገናኛ ብዙሃን አፈናው በነጻ ፕሬሱ ላይ ብቻ አልተገደበም። በኢትዮጵያ የመረጃ መረቦችም ታፍነዋል። ከሰብ ሰሃራ አፍሪካ በኢንተርኔት ይዞታ እና አገልግሎት የመጨረሻዋ ሃገር ናት። ኢንተርኔቱን የሚቆጣጠረው መንግስታዊው ቴሌኮም ስርዓቱን የሚተቹ ድረ-ገጾችን በቻይና ቴክኖሎጂ እንዲዘጉ አድርጓል። የዜጎችን ስልክ በህገወጥ ማንገድ መጥለፍ የተለመደ ተግባር ነው። እንዲሁም ስካይፕ እና ቫይበር ያሉ የቮይስ ኦቨር ስልኮች ደግሞ ፊን ፊሸር በተባለ የኮምፒዩተር ቫይረስ አማካኝነት ይጠለፋሉ። እንዲህ እያሉ በዜጎች የግል ህይወት ሳይቀር እየገቡ ቴሌን ሙሉ በሙሉ የስለላ ተቋም እንዳደረጉት የአሜሪካው ሂዩማን ራይትስ ዋች ይፋ አድርጓል።
ኢትዮጵያን ወደ ጨለማ ዘመን እየወሰዳት ያለው ይህ የህወሃት ስርዓት የኢንተርኔት ተጠቃሚው እንዲያሽቆለቁል እየጣረ እንደሆነ ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት። በተለይ የፌስቡክ አብዮትን ለመግታት ስለሚሻ የኢንተርኔት አገልግሎትን ማዳከሙ ላይ ጥብቅ አቋም ይዟል። መንግስት አልባዋ ሶማልያ እንኳን፣ ስድስት የቴሌፎንና ስልክ አቅራቢ ኩባንያዎች አሏት። በዚህ ቀላል ቴክኖሎጂ እንኳን ከሶማልያ በታች ሆኖ ስለ እድገት መመጻደቃቸው ሊያፍሩበት ይገባል።

እጅግ የሚያሳዝነው ይህ ስርዓት ለፈጸመው ለዚህ ሁሉ በደል ለሽልማት መብቃቱ ነው። ልማታዊው አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ በአርቲስቶች ስም ለሟቹ ጠቅላይ ሚ/ር የወርቅ ብዕር ነበር ያበረከተላቸው። ብዕር ትልቅ ትርጉም አለው። ብእር የሚሸለም ሰው ለፕሬስ ክብር ያለው፤ ፕሬስን የሚያከብር ሰው ነው። ሰራዊት የወርቅ ብዕር እንዲሸልም አርቲስቶች አልወከሉትም ነበር። ይህንን ሲያደርግ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች እስር ቤት ውስጥ ይንገላቱ ነበር። ሰራዊት ይህንን ሲያደርግ የአለም አቀፍ ህብረተሰብ ጠ/ሚኒስትሩን የፕሬስ አፈና በእጅጉ ያወግዝ ነበር። እንደ ሰራዊት ያሉ ሃላፊነት የጎደላቸው ሰዎች ብዙ አይደሉም። ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው ሲሉ እንዲህ አይነት ስራ እየሰሩ በሰው በቁስል ላይ እንጨት ይሰድዳሉ። ታዲያ እንደነዚህ አይነቶቹ አድርባዮችም ለፕሬሱ መጥፋት ሚናቸው ቀላል አይደለም። የማያልፍ የለም። ሁሉም ያልፋል። መንግስትም እንደ አንሶላ ተጠቅልሎ ይሄዳል። ይህ ቀን አልፎም ለትዝብት ያበቃናል።

ማን ነበር “ፕሬስ የሌለው መንግስት ከሚኖረን መንግስት የሌለው ፕሬስ ቢኖረን እንመርጣለን።” ያለው? እርግጥ ነው። ያለ ፕሬስ የሚኖር ህዝብ በጨለማ ነው የሚጓዘው። ያለ ነጻ አስተሳሰብ እና ያለ ነጻ ፕሬስ፣ እድገት ይመጣል ማለት አይታሰብም። እንዲያው የህዝብን ንቃተ-ህሊና ዝቅ አድርጎ መመልከት ይሆናል እንጂ።

አቡጊዳ –አቶ በላይ ፍቃዱ አዲሱ የአንድነት ፓርቲ ፕሬዘዳንት ሆኑ፤ ኢንጂንር ግዛቸው በፍቃዳቸው ለቀቁ

$
0
0

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት አቶ በላይ ፍቃደን የድርጅቱ ፕሬዘዳንት አድርጎ መርጧል። belay

ከሰባት ወራት በፊት ድርጅቱን እንዲመሩ የተመረጡት ኢንጂነር ግዛቸው ፣ “ወጣቶችን ወደ አመራር አመጣለሁ፣ ወጣቶችን ባካችሁ አቅማችሁን አጎልብቱና ተኩኝ” በማለት ለወጣት አመራሮች ሃላፊነታቸውን ለማስረክብ ፍላጎት እንደነበራቸው መግለጻቸው ይታወቃል። ቃላቸውን በመጠበቅ አዳዲስ አመራሮች ወደ ፊት መምጣታቸው ትግሉን ይረዳል የሚል እምነት ስላደረባቸው ኢንጂነር ግዛቸው፣ በፍቃዳቸው ሃላፊነታቸውን በመልቀቃቸው ነው፣ በድርጅቱ ሕገ ደንብ መሰረት፣ ብሄራዊ ምክር ቤቱ አዲስ አመራር የመርጠው።

አቶ በላይ ፍቃደ የአንድነት ምክትል ሊቀመንበር ሆነው የሰሩ፣ በድርጅቱና አባልትና አገር ዉስጥም ሆነ ከውጭ ባሉ ደጋፊዎች ዘንድ፣ ከመኢአድ፣ ከሰማያዊ ፓርቲ ፣ ከትብብር …እንዲሁም ሌሎች የተቃዋሚ ድርጅት አመራሮች ዘንድ ትልቅ ተቀባይነት እንዳላቸው ይነገርላቸውል።

ሰቆቃወ ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም- ኢትዮጵያዊ በዲ/ን ተረፈ ወርቁ

$
0
0

የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራን እስራኤላዊውን ነቢዩ ኤርምያስን ‹‹አልቃሻው ነቢይ›› በሚል ሰቆቃና ምሬት፣ ዕንባና ኀዘን ዕጣ ፈንታው የሆነበት የመከራ ሰው ሲሉ በዚህ ቅፅል ስም ይጠሩታል፡፡ ለነገሩ ራሱ ነቢዩም ቢሆን ስለ እስራኤል፣ ስለ እናት ምድሩ የታሪክ ስብራት አሊያም ፕሮፍ እንደሚሉት ‹‹የታሪክ መክሸፍ››፣ ስለ ሕዝቦቹ ስደት፣ መከራና ውርደት አነባ ዘንድ ምናለ ዓይኖቼ ሳያቋርጥ እንደሚፈልቅ የምንጭ ውኃ በሆኑልኝ ሲል የለመነና የተመኘ፣ የአገሩ ውርደት፣ የሕዝቡ መጎሳቆልና መዋረድ በእጅጉ እረፍት የነሳው ጻድቅና እውነተኛ ነቢይ ነበር፡፡ ነቢዩ በዚህ ተማጽኖውና ሰቆቃውም፡-

ስለ እስራኤል የታሪክ ስብራት/መክሸፍ፣ ስለ ሕዝቦቿ፣ ነገሥታቶቿ፣ ካህናቶቿና ሐሰተኛ ነቢያቶቿ ኃጢአትና ዓመፃ፣ በደልና ግፍ፣ የትውልዱ ውርደትና ጉስቁልና እንዲህ ሲል አንብቷል፣ ‹‹… ስለ ወገኔ እስራኤል ሴት ልጅ ቅጥቃጤና መከራ ዓይኔ በእንባ ደከመች፣ አንጀቴም ታወከ፣ ጉበቴም በምድር ላይ ተዘረገፈ፡፡›› በማለት ስለ ወገኑ፣ ሕዝቡና ምድሩ ነቢዩ ኀዘኑ ምን ያህል የከፋና የአገሩ ዕጣ ፈንታም ልቡን ምንኛ ክፉኛ ሰብሮት እንደነበር ‹‹የሰቆቃወ ኤርምያስ›› መጽሐፍ ይተርክልናል፡፡

ፍርድን በሚያዛቡ፣ ድሀን በሚበድሉና በሚያጎሳቅሉ፣ መበለቲቱንና ድሀ አደጉን በሚገፉ፣ ፍትሕን በሚያዛቡ አድር ባይ ሙሰኞቿ፣ የሕዝባቸውን ደም በከንቱ በሚያፈሱ ጨካኝ ነገሥታቶቿ፣ ኃጢአትን እንደ ውኃ በሚጨልጡ ካህናቶቿ፣ ሐሰተኛና ለባጭ በሆኑ ነቢያቶቿ፣ እውነትን በአደባባይ በሚረግጡ ገዢዎቿና ፈራጆቿ ምክንያት የአምላኳ ቁጣና መዓት በፈሰሰባት በእስራኤል፣ በአይሁዳውያኑ ሕዝቦች ‹‹የታሪክ መክሸፍ›› ታላቅ የትውልድ ኪሳራና ውርደት የተነሣ ነቢዩ ኤርምያስ የዕንባ፣ የሰቆቃ ሰው ‹‹አልቃሻው ነቢይ›› የሚል ስያሜ እንደተሰጠው የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡

በዚህ አጭር መጣጥፌ ፕ/ር መስፍንን እንደ እስራኤላዊው ነቢዩ ኤርምያስ የዕንባና የሰቆቃ ሰው ስላልኩበት ጉዳይ ወይም የታሪክ ተመሳስሎ አንዳንድ እውነታዎችን ላነሣ ወደድኹ፡፡ ለዚህ አጭር ጽሑፌ መነሻ የሆነኝ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም ከሸገር 102.1 ሬዲዮ የቅዳሜ ጨዋታ ዝግጅት ላይ ከመዓዛ ብሩ ጋር ያደረጉት ለሰባት ሳምንታት የዘለቀ ቆይታቸው ነው፡፡

በሸገር 102.1 ሬዲዮ በቅዳሜ የጨዋታ እንግዳ ዝግጅት ላይ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ ከእውቁ ምሁር፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች፣ ታሪክ ተመራማሪ፣ ፖለቲከኛ፣ ጸሐፊና ገጣሚ ከሆኑት ከአዛውንቱ ከፕ/ር መስፍን ጋር ያደረገችውን ቃለ መጠይቅ በታላቅ ጉጉትና ስሜት ውስጥ ሆኜ ነበር የተከታተልኩት፡፡ ፕ/ር መስፍን ለተከታታይ ሰባት ሳምንታት ከሸገር ሬዲዮ ጋር ያደረጉት ቆይታ አስደሳች፣ አስተማሪ፣ መካሪ፣ አዝናኝ፣ በአንጻሩ ደግሞ አሳዛኝ፣ የሚያስቆጭ፣ የሚያናደድ፣ በኀዘን፣ በቁጭትና በጸጸት ብግን የሚያደርግ፣ ቀቢጸ ተስፋ የተጫነው ባለ ብዙ ኅብር፣ ባለ ቡዙ መልክ ነበር ማለት ይቻላል፡፡

ፕሮፌሰሩ ከመዓዛ ጋር በነበራቸው ቆይታ ከልጅነት እስከ አሁን ዕድሜያቸው ድረስ ያሳለፉትንና የሚያስታውሱትን ትዝታቸውን ለዛ ባለው አንደበት ከገጠመኛቸው ጋር አዋዝተው ሊያጋሩን ሞክረዋል፡፡ ፕሮፌሰር እምነታቸውን፣ የሕይወት ፍልስፍናቸውን፣ ጽናታቸውን፣ ትዕግሥታቸውን፣ ወኔያቸውን፣ ውስጣዊ ስሜታቸውን፣ ኀዘናቸውን፣ ጸጸታቸውን፣ ብሶታቸውንና… እንዲሁም በማይጠፋና ሕያው በሆነ የፍቅር ማኅተም በውስጣቸው ለታተመችው ለውድ አገራቸው ኢትዮጵያና ለሕዝባቸው እንዲሆን የሚመኙለትን ሕልማቸውንና ምኞታቸውን ኀዘንና ብሶት እያበስለሰላቸው ቁጭትና ጸጸት በተቀላቀለበት ስሜት የልባቸውን አውግተውናልና እናመሰግናቸዋለን!!
ፕ/ር መስፍን ከሸገር ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታቸው ለዕንባ፣ ለለቅሶ ቅርብ የሆኑ፣ አሁንም ድረስ የሰቆቃና የትካዜ ሰው መሆናቸውን በሚገባ እንድገነዘብ አድርጎኛል፡፡ ፕ/ር በዚህ የጨዋታ እንግዳ ቆይታቸው እንደ አይሁዳዊው የእግዚአብሔር ነቢይ ኤርምያስ በተለያዩ ጊዜያት በጸጸትና በቁጭት ዕንባቸው እንዲፈስና ነፍሳቸው ትካዜ ውስጥ እንዲገባ ያደረጋቸው ግላዊና አገራዊ የሆኑ ትዝታዎቻቸው፣ አገራችን በረጅም ዘመን ታሪኳ ያለፈችበትና አሁንም ገና በቅጡ ያልተላቀቅናቸው ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ቀውሶቻችን ለዚህች አጭር መጣጥፌ ዐቢይ ምክንያት ኾኖኛል፡፡

እኚህ ኢትዮጵያዊ ምሁር ሦስት መንግሥታትን ባፈራረቁባት እናት ምድራቸው ያሳለፉት፣ አሁንም በዘመናቸው እያዩትና እየሰሙት ያለው ማለቂያ የሌለው የሚመስለውና መፍትሔውን አገኘነው ስንለው እየራቀን ያስቸገረን የኢትዮጵያችን ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ፣ በየቤተ እምነቶች የነገሠው የሞራል ውድቀትና ዝቅጠት፣ የመንፈሳዊነት ድርቅ፣ ዘርኝነቱ፣ በሥልጣን መባለጉ፣ ሙሰኝነቱ፣ የፍትሕ እጦቱ፣ ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ የቀጠለውና ድኃውን ኅብረተሰብ ግራ ያጋባው የኑሮ ውድነቱ… ወዘተ ለፕሮፌሰሩ የሰቆቃና የእንጉርጉሮ፣ የብሶትና የትካዜያቸው ምክንያት የኾናቸው ይመስላል፡፡

ፕ/ር መስፍንን ባሳለፉት የሕይወት ዘመናቸው ክፉኛ ውስጣቸውን በኀዘን ጦር የወጋውና ዛሬም ድረስ ሲያስታውሱት ውስጣቸውን የሚረብሻቸውና ብርቱ ኀዘን ካጫረባቸው አገራዊ፣ ታሪካዊ ክስተት መካከልም የትውልድ እልቂት፣ የአገር ውርድት ወይም የፕሮፍን አገላለጽ ልዋስና የኢትዮጵያችን ‹‹የታሪክ መክሸፍ›› አንዱና ዋንኛ መለያ ተብሎ ሊጠራ የሚችለው እራሳቸው ፕሮፌሰር በዓይናቸው ዐይተው ምስክር የሆኑበትና የታዘቡት በአገራችን በተለይም በሰሜኑ ኢትዮጵያ ግዛት እንደ እርሳቸው አገላለጽ ‹‹ችጋር›› ያስከተለው ዘግናኝ እልቂትና ዓለምን ሁሉ እንባ ያራጨው የ፲፱፻፷፮ቱ ራብ ነው፡፡

ፕ/ር በዚህ አገራችን ኢትዮጵያ በዓለም ሁሉ ፊት ስሟን የቀየረውና የራብ፣ የእልቂት ምድር፣ አኬል ዳማ- የደም ምድር ተብላ እንድትጠራ፣ ሕዝቦቿም በኼዱበት ዓለም ሁሉ አንገታቸውን እንዲደፉ ምክንያት ስለሆነው የችጋር ርእሰ ጉዳይ ላይ በአገር ውስጥና በውጭ አገር በሚገኙ ስመ ጥር በሆኑ እንደ ሀርቫርድ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ሳይቀር ሰፊና ጥልቅ የሆነ ምርምርና ጥናት እንዳደረጉ አጫውተውናል፡፡
ይህ ክፉ ዘመን፣ ይህ ክፉ ራብ የሠራልኝ ሥራ፣
አባቴን ለስደት እናቴን ለአሞራ፡፡

የወንድ ልጅ እናት ታጠቂ በገመድ
ልጅሽን አሞራ እንጂ አይቀብረውም ዘመድ፡፡

ተብሎ አገሬው በታላቅ ኀዘንና ብሶት የተቀኘለት የራብና የእርስ በርስ ጦርነት የደም ታሪካችን ዛሬም ድረስ በጸጸትና በቁጭት የምናስታውሰው ነው፡፡ ይህ አሳፋሪ፣ ዘግናኝና አሳዛኝ የታሪክ ስብራትና የትውልድ እልቂት ፕ/ሩን አገሪቱን ‹‹የከሸፈ ታሪክ ባለቤት›› እስከ ማለት አደርሷቸዋል፡፡ እናም ዛሬም ድረስ በአዛውንቱ በፕ/ር መስፍን ልብ ውስጥ እማማ ኢትዮጵያ በውስጣቸው በምሬትና በብሶት የሚያነቡላት፣ ሙሾ የሚደረድሩላት የነፍሳቸው ስብራት፣ ሕመምና ስቃይ ሆና እንደዘለቀች ነው፡፡ ዛሬም በእኚህ አዛውንት ስለ እናት ምድራቸው ኢትዮጵያ ያላቸው ተስፋ ያለቀ፣ የተቆረጠ ነው የሚመስለው፡፡

ሌላኛው ፕሮፌሰር ከመዓዛ ጋር ባደረጉት የመጀመሪያው ሳምንት ቆይታቸው እስካሁንም ድረስ ውስጣቸውን በቁጭትና በጸጸት የሚያንገበግባቸው የዘጠኝ ወር ቤታቸው ለሆኑት፣ በመልካም ሥነ- ምግባር ተቀርጸው እንዲያድጉ ትልቅ መሠረት ለጣሉላቸው ለወላጅ ለእናታቸው የሚገባቸውን ውለታ ሳያደርጉላቸው በሞት የመለየታቸው ጉዳይ እንደሆነ እንባና ሳግ በተቀላቀለ ስሜት አጫውተውናል፡፡

እኚህ ዕድሜ ባለጠጋ በሆኑ አዛውንትና አንጋፋ ምሁር ስለ እናታቸው ባሰቡ ቁጥር ዓይናቸውን በሚሞላው እንባቸውና ውስጣቸውን በሚያብሰለስላቸው ጸጸትና ኀዘን ውስጥ በፕሮፌሰሩ የልባቸው ዙፋን ላይ የነገሠችውና የትካዜያቸውና የሰቆቃቸው ምክንያት የኾነችው የትልቋና የሁላችንም እናት የሆነችው የምድራችን፣ የእማማ ኢትዮጵያ ኀዘንና ትካዜ፣ ብሶትና ሰቆቃ የሞላበት የተዥጎረጎረ የታሪኳ ገጽ ተራ በተራ፣ ምዕራፍ በምዕራፍ እየተገለጸ ከፊታችን ድቅን እንደሚልብን አስባለሁ፡፡

እናም ፕሮፍ ለሰባት ሳምንት በዘለቀ የቅዳሜ ጨዋታቸው ይኸውን የተዥጎረጎረ፣ በደም የቀላ የኢትዮጵያን ታሪክ እያነሡ፣ እየፈተሹና እንያንገዋለሉ ‹‹የታሪካችንን መክሸፍ››፣ የሕዝባችንን ውርደትና ጉስቁልና እንደ አይሁዳዊው ነቢዩ ኤርምያስ በእንባ፣ በኀዘንና በሰቆቃ ተውጠው ተረኩልን፡፡

ፕሮፌሰር መስፍን አክለውም የራብና የእርስ በርስ ጦርነት፣ የእልቂት ምድር-አኬል ዳማ በሚል ስያሜ የጠለሸውን የትናንትና መልካም ታሪኳን፣ ስሟንና ክብሯን ለመመለስና ለተሻለ ነገ ጉልበቴ በርታ በርታ እያለች ያለችውን እናት ኢትዮጵያን የእግር እሳት ሆኖ እየለበለባትና አላንቀሳቅሳት ያለ ሌላ የዘረኝነት/የጎሰኝነት ክፉ አደጋ እንደተጋረጠባት በስጋት ስሜት ሆነው ነገሩን፣ ውስጣቸውን ክፉኛ ፍርሃት፣ ቁጭትና ሥጋት እያረሰው፡፡ እናም ከዚህ ዙሪያችንን ከከበበን ክፉ አደጋ አገሪቱን ይታደጉ ዘንድ በሥልጣን ላይ ላሉት ሰዎች አስተዋይና ይቅር ባይ ልቦናን ፈጣሪ ይቸራቸው ዘንድም ፕሮፌሰር በሸገር የቅዳሜ እንግዳ ቆይታቸው ከልብ ለምነዋል፣ ተማጽነዋል፡፡

ለፕሮፌሰሩ ከወዲሁ ስለ ነገይቱ ኢትዮጵያ የታያቸው ምስል ዝብርቅርቅ ያለ፣ ጥፋትን ያዘለ፣ የማይስብ፣ አንዳች ውብና አዲስ ተስፋ የማይንጸባረቅበት፣ አሳሳቢና ድንግዝግዝ ይመስላል፡፡ እናም በፕሮፌሰር ልብ ውስጥ ብዙ ሐዘን፣ የማያቋርጥ ጭንቀት፣ በቃላት ሊገለጽ የማይችል ቁጭትና እልህ የሚንጠው ብርቱ የነፍሳቸው ጩኸት ስለ እናት ምድራችን ኢትዮጵያ በቃለ ምልልሳቸው ውስጥ በለሆሳስ ተሰማኝ፣ አሊያም ቁጭታቸውንና ሐዘናቸውን ለምንጋራ ሁሉ እንዲያ እንደሚሰማን ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እኔም የኸው የፕሮፌሰሩ ሰቆቃና ብርቱ ኀዘን ነው ብዕሬን እንዳነሳ የገፋፋኝም፡፡

በእርግጥም እኚህ የዕድሜ ባለጠጋ፣ ምሁር አዛውንት የዕድሜያቸውን ግማሽ ማለት ይቻላል ስለ እናት ምድራቸው፣ ኢትዮጵያ ልባቸው በኀዘን ጦር እንደተወጋ፣ ዓይናቸው ዘወትር እንዳነባ፣ እንደ አይሁዳዊው የእግዚአብሔር ነቢይ ኤርምያስ የምሬትና የብሶት፣ የትካዜና የሰቆቃ ሰው ሆነው አብዛኛው ሕይወታቸውን ዘመን እንደፈጁ ነው በቃለ ምልልሳቸው የነገሩን፣ ያጫወቱን፡፡

እናም ፕሮፌሰር ታሪኳ ሁሉ የከሸፈ ነው፣ የልማት፣ የዕድገትና የብልጽግና ጎዳናዎቿ ሁሉ በእሾህ የታጠሩባት ናት፤ እንዲያም ሲል ደግሞ ‹‹በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ›› እንዲሉ ሌላ ውስጥ ለውስጥ እየነደደ ያለ ሞትን፣ ጥፋትንና እልቂትን የደገሰልን የዘረኝነት፣ የመለያየት አደጋ ተጋርጦባታል ለሚሏት አገራቸው ኢትዮጵያ ሥጋታቸውና ጭንቀታቸው እጅጉን የበረታ፣ ያየለ ነው የሚመስለው፡፡

ይህች በፕሮፌሰሩ ሕሊና ውስጥ የዘመናት ታሪክ ልቃቂት ውሏ ሲተረተር፣ ሲገለጽ ከከሸፈ ታሪክና ገድል በቀር ሌላ ታሪክ የሌላት፣ እድገትና ብልጽግናን ያዝኳቸው ስትላቸው የሚያመልጧት ነጻነትና ሰላም፣ ፍትሕና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ብሎ ነገር ሕልም የሆነባት፣ በእርስ በርስ እልቂት፣ በፍጅትና በራብ የምትታወቅ፣ በአብራኳ ክፋዮች፣ በገዛ የማኅፀኗ ልጆቿ ደም የምትዋኝ፣ በደም ሸማ፣ በደም ሰንደቅ የደመቀች፣ በደም ታሪክ የተንቆጠቆጠች የተባለች ኢትዮጵያ- ምስሏም፣ ገጽታዋም ይኽው ነው በፕሮፌሰር መስፍን ልብ፣ እይታና የረጅም ዓመታት ትዝታቸው ትርክት ውሰጥ፡፡

በማብቂያዬም ይህን ሰቆቃወ ፕ/ር መስፍን-ኢትዮጵያ ብዬ የሰየምኩትን አጭር መጣጥፌን በእንዲህ ቀቢጸ ተስፋ ባየለበት የጨለምተኝነት መንፈስ ልደምድመው አልወደድኩም፡፡ በፕሮፌሰር መስፍን እይታ የረጅም ዘመን ታሪክ መዝገቧ ሲከፈት በአብዛኛው ‹‹የከሸፈ ታሪክ›› ባለቤት ናት ብለው ስለሚጠሯት ኢትዮጵያ ታሪክ አንድ የሚግረን ትልቅ ሐቅ እንዳለ ለማንሣት እወዳለኹ፡፡

ይኸውም ይህች አብዛኛው ታሪኳ የከሸፈ ነው፣ ሞተች በቃ፣ ከአሁንስ ወዲያ ተስፋም የላት የተባለች ኢትዮጵያ፣ በተለያዩ ዘመናት ከመውደቅ፣ ከውርደት፣ ከሽንፈት ታሪኳ እንደገና የተቀበረችበትን አፈር አራግፋ ዳግም በአዲስ የዘመን ብስራት ትንሣኤ ብድግ ያለችበት ወርቃማ የታሪክ ዘመንም እንደነበራት ማሰብ፣ ማስታወስ ያለብን ይመስለኛል፡፡

ይህን አሳቤን የሚያጠናክርልኝ አንድ የጥናት ወረቀት እዚህ ላይ ማነሣቱ ተገቢ ይመስለኛል፡፡ ራሳቸው ፕ/ር መስፍን ተሳታፊ በነበሩበት በ1997 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማኅበር ባዘጋጀው ‹‹Vision 2020›› በ2020 ልናያት የምንፈልጋት ወይም የምንመኛት ኢትዮጵያ በሚል የውይይት መድረክ ላይ የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ፡- ‹‹ምን አለምን? የት ደረስን? ወዴትስ እያመራን ይሆን?›› በሚል ርዕስ ባቀረቡት የጥናት ወረቀታቸው እንዲህ ብለው ነበር፡-

… ከኢትዮጵያ ታሪክ የምንገነዘበው አንድ ሐቅ ቢኖር፣ ካንዴም ሁለቴ አለቀላት፣ ፈረሰች ተብሎ ከተደመደመ በኋላ እንደገና እንዴት እንዳሰራራችና አዲስ ሕይወት እንደዘራች ነው፡፡ በአክሱም ዘመን ፍፃሜ፣ በ፲፮ኛው መቶ ዓመት፣ በዘመነ መሳፍንትና በዘመናችንም በአብዮቱ ወቅትና በደርግ ውድቀት ጊዜ የታየው ሁኔታ ይኸው ነው፡፡ ይህ የኢትዮጵያ እንደገና የማንሰራራት ችሎታ ሀገሪቱ በዘመናት የታሪክ ሂደት ያካበተችው ሰብዓዊና ባሕላዊ እሴቶች ውጤት ይመስለኛል፡፡

ፕሮፌሰር ባሕሩ ተስፋዋ የተቆረጠ፣ የጨለመ ነው የተባለችው ኢትዮችጵያችን ከአሁን ወዲያ አበቃላት፣ በቃ፣ ሞተች፣ ተረሳች ስትባል ዳግም ያንሰራራችበት የትንሣኤ/የሕዳሴ ታሪክ ዘመናት እንደነበሯትም ማስታወስ አለብን፡፡ ፕ/ር ባሕሩ መጪው ዘመን ለኢትዮጵያችን የተሻለና ብሩህ ዘመን እንዲሆን የምንመኝ ሁሉ ብሩህ ተስፋን ሰንቀን በአንድነት እጅ ለእጅ በመያያዝ መነሳት እንደሚገባን የሚያሳስበን ምሁራዊ አስተውሎት የታከለበት ትንታኔ ነው በዚህ ጥናታዊ ጽሑፋቸው ያስቀመጡት፡፡

ስለሆነም በዚህች አጭር መጣጥፌ መደምደሚያዬም ይህችን የሁላችንም የሆነች ኢትዮጵያችንን ለመጪው ትውልድ እንደተከበረች፣ እንደታፈረችና እንደተፈራች በክብር ማስተላለፍ አገራችንን እንወዳለን፣ ለወገን እንቆረቆራለን የምንል ኢትዮጵያን ሁሉ ግዴታና ሓላፊነት እንደሆነ ነው የማስበው፡፡

ስለዚህም እንደ አገርም፣ እንደ ሕዝብም ለረጅም ዘመናት በአንድነት አስተሳስሮ ያቆየንን ታሪካዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እሴቶቻችንና ቅርሶቻችንን ጠብቀን፣ ያለፈውን የታሪክ ጠባሳችንን/ቁርሾአችንን በይቅርታ ልብ ሽረን፣ እያመረቀዘ ያስቸገረንን የትናንትና ስብራታችንን፣ ቁስላችንን በፍቅር ዘይት አለስልሰንና አክመን እጅ ለእጅ በመያያዝ- የሰላምና የአንድነት፣ የልማትና የዕድገት ጮራዋ፣ ጸዳሏ የሚደምቅባትን ታላቋን ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በአንድነት ሆነን በፍቅርና በይቅርታ ልብ ቃል ኪዳናችንን ማደስ እንደሚኖርብን ማስታወስ፣ ማሳሰብ እወዳለኹ፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!!

ወገኖቻችን ዋጋ ለመከፈል ሲዘጋጁ እኛ ከጎን መቆም አለብን (የትግል ጥሪ)

$
0
0

አንድነት አዲስ ወጣት አመራር ይዞ ብቅ ብሏል። አቶ በላይ ፍቃዱ። ከዚህ በፊት በተከበሩ ዶር ነጋሶ ጊዳዳና እና የተከበሩ ኢንጂነር ግዛቸው አመራር ወቅት የተጀመሩ መልካም ስራዎችን በማጠናከር፣ በአዲስ አሰራና በአዲስ የትግል ግለት አዲስ ጉዞ ተጀምሯል።

የአንድነት ፓርቲ በአገሪቷ አራቱም ማእዘናት መረቡን የዘረጋ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ከተደረገ ኢሕአዴግን ማሸነፍ የሚችል፣ ብዙ አመራር አባላቱ እየታሰሩበትና ከፍተኛ ጫና እየደረሰበትም፣ የአምባገነኖችን ዱላ ተቋቁሞ የሕዝብን ጥያቄ ለማስከበር የሚተጋ ድርጅት ነው። ሕወሃት/ኢሕአዴግ፣ የአንድነት ፓርቲ፣ በፓርቲዎች ምክር ቤት እንደኮለኮላቸው፣ መድበለ ፓርቲ አለ ብሎ ለማስመሰል ለዲፕሎማሲ ፍጆታ እንደሚጠቀምባቸው፣ ፓርቲ ነን ባዮች ጀሌዎቹ፣ እንዲሆን ነው የሚፈልገው። ነገር ግን አንድነቶች፣ ትልቅ ዋጋ እየከፈሉም፣ ለአገዛዙ ራስ ምታት በመሆን፣ ትግሉን እየመሩት ነው።
ከሐምሌ 2005 እስከ ሰኔ 2006 ባሉት ጊዜያት፣ አንድነት የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነትና የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት በሚል መርህ በሃያ ከተሞች ተንቀሳቅሷል። በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ በደሴና በባህር ዳር ሁለት ጊዜ ፣ በአርባ ምንጭ፣ በጂንካ፣ በፍቼ፣ በደብረ ማርቆስ፣ በጎንደር፣ በጊዶሌ፣ በወላይታ ሶዶ አንድ ጊዜ ሰላማዊ ሰልፎችን ጠርቶ ሕዝቡን ያንቀሳቀሰ ሲሆን፣ በአዋሳ፣ በቁጫ፣ በመቀሌና በባሌ/ሮቢ ለቅስቀሳና ለመጓጓዣ ከፍተኛ ወጭ ከተደረገ በኋላ፣ በአገዛዙ አፈና ሰልፎቹ ቢስተጓጎሉም ፣ ቢያንስ በነዚህ ከተሞች ሕዝቡ የነጻነትን ድምጽ በቅስቀሳ ወቅት ለመስማት በቋቷል።

ኢሕአዴግ ከምእራቡ አለም የሚያገኘው እርዳታ፣ በግብር የሚሰበስበው በእጁ ነው። የአገሪቷ አበይት የመገናኛ ተቋማትን ይቆጣጠራል። ኢቲቪ፣ ፋና ፣ አዲስ ዘመን ….በመለስተኛነት ሪፖርተር የመሳሰሉ ሜዲያዎቹ ጠዋትና ማታ የአገዛዙን ፕሮፖጋንዳ ነው የሚረጩት።

አንድነት የሚተማመነው በሕዝቡ ድጋፍ ነው። የአንድነት ብቸኛ የኃይል ምንጭ እኛ ነን። እኛ ከመሪዎች ለዉጥ መጠበቅ የለብንም። እኛ መሪዎችን እየደገፍን የለውጡ አካል ነው መሆን ያለብን።
አንድነት የምርጫው ሜዳ እንዲሰፋና የፖለቲክ ምህዳሩ እንዲከፈት ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎችን፣ ሰልፎችን ማካሄድ አለበት። በአገሪቷ ሁሉ ያሉ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ለማደራጀት፣ አክቲቪስቶችን አስተባባሪዎችን፣ አደራጆችን በየክልሉ በብዛት ማሰማራት የግድ ነው። እንደ አቶ አንዱዋለም አራጌ፣ ሃብታሙ አያሌው አሁን ያሉትም አመራሮች፣ ነገ ሊታሰሩ እንደሚችሉ እያወቁ ትግሉን ለመምራት የቆረጡ፣ የፓርቲው አመራሮች፣ በራሳቸው ይሄን ትልቅ ሃላፊነት ሊወጡ አይችሉም። እንግዲህ እነርሱ ለመታሰር፣ ለመደብደብ፣ ለመገደል ሲዘጋጁ እኛ ትንሿን የድርሻችንን መወጣት ሊያቅተን አይገባም። አንድነትን ባለን አቅምና ጉልበት ሁሉ ለመደገፍ መዘጋጀት ይኖርብናል።

በአገር ቤት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በስፋት ለመከታተል የሚከተለውን የፌስ ቡክ ገጽ ላይክ ያደርጉ

https://www.facebook.com/MillionsOfVoicesForFreedomUdj

በዉጭ አገር ያላችሁ፣ ፓርቲዉን በጽሁፍ፣ ጠቃሚና ፕሮፌሽናል አስተያየቶች በመስጠት ሆነ በማንኛዉም ገንዝበ ነክ ባልሆኑ ጉዳዮች ለመርዳት ፣ የሚሊዮኖች ንቅናቄ ግብረ ኃይል ወይንም የአንድነት ድጋፍ ድርጅት አካል ሆናችሁ መስራት ለምትፈልጉ በሚከተለው አድራሻ ኢሜል ይላኩልን።

millionsforethiopia@gmail.com

በገንዘብ ለመርዳት http://www.andinet.org/ በመሄድ በስተቀኝ በኩል ከላይ «Donate» የሚለውን ይጫኑ !

ነጻነትን ስለተመኘናት አናገኛትም። ነጻነት ርካሽ አይደለችም። ዋጋ ታስከፍላለች። እያንዳንዳችን የነጻነትን ጉዞ፣ የነጻነትን ትግል እንቀላቀል። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን:: እስካሁን ብዙ የአገዛዙን ግፍ አውርተናል። እስከአሁን ነጻነታችንን ሌሎች እንዲሰጡን ጠብቀናል። እስካሁን ሌሎችን ተችተናል። አሁን ጣታችንን ወደኛ የምናዞርበትና፣ እያንዳንዳችን የምንነሳበት ጊዜ ነው። አሁን ካልተነሳን ፣ አሁን ትግሉን ካልተቀላቀልን መቼ ? እኛ ካልተነሳን ማን ?


ለሕገ መንግስቱ መቆም ሽብርተኝነት ሲባል (ዞን ዘጠኞችን በተመለከተ) ግርማ ካሳ

$
0
0

የተማሩ ናቸው። አገራቸውን የሚወዱ። በሕዝባቸውና በአገራቸው ዉስጥ የሚደረገዉ ግፍ እንዲቆም በጽሁፋቸው የሚመክሩ። ማንም ላይ ጥላቻ የሌላቸው። ኢፍትሃዊነትን የሚጠሉ ። አምባገነንነትን እንጂ ማንንም የማይጸየፉ።
1794785_473494906123906_4102774297410041449_n
በጽሁፋቸው ፍቅርን ሰብከዋል። ነጻነትን አውጀዋል። «ዜጎች እንደ እንስሳ ታስረዉና ታፍነው መኖር የለባቸውም። ነጻነታቸውና ስብእናቸው ሊጠበቅላቸው ይገባል» እያሉ ተከራክረዋል። ለሰብአዊነት ተሟግተዋል። ሰው ሲከብር እንጂ ሲዋረድ፣ ሲነሳ እንጂ ሲወድቅ፣ ሲድን እንጂ ሲሞት፣ ሲበለጸግ እንጂ ሲደኸይ ማየት አልፈለጉም።

በቢሯቸው፣ በቤታቸው፣ ሴቶቹ በቦርሳቸው፣ ወንዶቹ ደግሞ በኪሳቸው ቦምብ ወይም ፈንጂ አልተገኘባቸው። በድብቅ የዶለቱት ወይንም የሰሩት ነገር የለም። የተወሰኑቱ ካምፓላ ኡጋንዳ ሄዱ እንጂ በድብቅ አስመራ የሄደ ከነርሱ መካከል የለም። የጻፉትና የተናገሩት ሁሉም በግልጽና በአደባባይ ነው። የተወሰኑቱ አርቲክል ዘጠኝ ከሚባል ድርጅት ጋር ግንኙነት አላቸው።

አርቲል ዘጠኝ እንደ አይሰስ፣ ወይም አልካይዳ ያለ ደርጅት አይደለም። የአርቲክል 19 ድርጅት አመጣጥ እንደዚህ ነው፡

የተባበሩት መንግስታት የሰባአዊ መብት ድንጋጌ (THE UNIVERSAL DECLARATION OF HUMAN RIGHTS የሚባል አለ። የዚህ ድንጋጌ አንቀጽ 19 ( አርቲክል 19) እንዲህ ይላል ፡

«Everyone has the right to freedom of opinion and expression; this right includes freedom to hold opinions without interference and to seek, receive and impart information and ideas through any media and regardless of frontiers.»

በዚህ አንቀጽ ላይ የተጻፈው ነጻነት በአለም ዙሪያ ሁሉ እንዲከበር ለመርዳት (አድቮኬት ለማድረግ) የተቋቋመ የሲቪክ ማህበር ነው፣ አርቲክል ዘጠኝ። ይህ ማህበር አርቲክል 19 የሚል ስያሜ ይዞ፣ በአሜሪካ፣ በአዉሮፓ ባሉ በርካታ አገሮች፣ በኬንያ፣ በቱኒዚያ ፣ በባንግላዲሽ ሳይቀር እውቅና አግኝቶ የሚንቀሳቀስ ነው። በአገራችን ዉስጥ በኢሕአዴግ መንግስት ተጋብዞ በምርጫ ዙሪያ ስልጠናዎች የሰጠ ድርጅት ነው።

ይህ የተባበሩት መንግስታት አንቀጽ 19 ድንጋጌ በኢትዮጵያ ፌዴራል ሕገ መንግስት አንቀጽ 29፣ ን ኡስ አንቀጽ 1 እና 2 ላይ በግልጽ ተቀምቷል። «Everyone shall have the right to hold opinions without any interference.Everyone shall have the right to freedom of expression without interference. This right shall include freedom to seek, receive and impart information and ideas of all kinds, regardless of frontiers, either orally, in writing or in print, in the form of art, or through other media of his choice.» ይላል የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 29።

በተባበሩት መንግስታት የሰባአዊ መብት ድንጋጌ አንቀጽ ( አርቲክል 19) ወይንም የኢትዮጵያ መንግስት አንቀጽ 29፣ በኢትዮጵያ ተግባራዊ እንዲሆን የሚጽፉ፣ የተደራጁ ሰላማዊ ዜጎች ናቸው። ለሕገ መንግስቱ ፣ ለሕግ ከበሬታ ያላቸው ናቸው።

ነገር ግን ከዘመናዊት ፍጹም የራቁ፣ በሚድል ኤጅ ይኖሩ ከነበሩ በአስተሳሰብ የማይተናነሱ፣ አዲስ አበባ ያሉ ገዢዎች ግን፣ ራሳቸው ያወጡትን ሕገ መንግስት ረጋግጠው ፣ ሽብርተኞች ናቸው በሚል ክስ ከሰዋቸው ከፍተኛ መከራና እንግልት እየፈጸሙባቸው ነው። ይኸው ነገ ለዘጠነኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፣ የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን !!!

እንግዲህ አገራችን የምንላት ኢትዮጵያ እንዲህ አይነት አሳዛኛ አሳፋሪ ግፎች የሚፈጸምባት አገር ናት። ኢትዮጵያ ለጥቂቶች ገነት፣ በአሥር ሚሊዮን ለሚቆጠሩ ልጆቿ ግን ሲኦል የሆነች አገር ናት። ይሄ መለወጥ አለበት። ይሄ መቆም አለበት። ይህን አይነት ግፍ አይቶ ዝም የማለት ሕሊና ሊኖረን አይገባም። ሁላችንም የድርሻችንን በመወጣት፣ የሚሊዮኖች ንቅናቄ አካል በመሆን፣ ለነጻነት፣ ለፍትህ ለእኩልነት መቆም ይኖርብናል። ዞን ዘጠኞችን በማሰሩ አገዛዙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዞን ዘጠኞች መፈጠራቸውን ልናሳየው ይገባል።

ድንጋይን ዳቦ ብሎ መጥራት ይብቃን በበላይነህ አባተ

የሃገር ፍቅር የስነ ጥበብ መድረክ በፍራንክ ፈርት

በስማችንና በተግባራችን እንጠራዘንድ ከኦቦ አራዳ አባ ሻውል

በኢሕአፓ አመራር አባላት ላይ የተፈጸመውን ግድያ ሽንጎው በጥብቅ ያወግዛል

Viewing all 1809 articles
Browse latest View live